uk
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Відкрити в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 377 підписників, посідаючи 5 568 місце в категорії Релігія і духовність та 2 195 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 377 підписників.

За останніми даними від 04 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 23, а за останні 24 години на -1, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 22.11%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 9.42% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 401 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 449 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 20.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 05 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

15 377
Підписники
-124 години
-107 днів
+2330 день
Архів дописів
ቅዱስ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አድርጎ ሾመ !!! የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እንደማንኛውም ሀገረ ስብከት ራሱን ች
+1
ቅዱስ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አድርጎ ሾመ !!! የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እንደማንኛውም ሀገረ ስብከት ራሱን ችሎ በሊቀ ጳጳስ እንዲመራ ባስቀመጠው በድንጋጌው ማሻሻያ መሠረት፣ ሦስት ብፁዓን አባቶች ማለትም ብፁዕ አቡነ እንጦንስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል እና ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ፣ በምልአተ ጉባኤው ተጠቁመው በዕጩነት ቀርበዋል፡፡ በተሰጠው ድምፅም፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል እና ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ እኩል 17፣ 17 ድምፅ በማግኘታቸው፣ ተመራጩን ለመለየት የተጣለው ዕጣ ለብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ወጥቷል፡፡ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ የጉራጌ እና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ማገልገላቸው ይታወሳል። ብፁዕ አባታችን ከሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት አባ ኃይለ ገብርኤል ነጋሽ ጋር ተናቦ በመሥራት ሀገረ ስብከቱን ያሻሽሉታል ብለን እናምናለን... ለብፁዕነታቸው መልካም የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንላቸው ተመኝተናል!!! ጥቅምት 17

ሀገር አቀፍ #የሰንበት_ትምህርት_ቤቶች አንድነት በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ እንዲታዩ ያቀረባቸው ጥያቄዎች ምላሽ እያገኙ ነው። ፨፨፨፨፨ በዘንድሮው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ እንዲሰጥባቸው ፣ በጥልቀት እንዲታዩ እና ሥራ ላይ እንዲውሉ በርካታ ጥያቄዎች በሀገር አቀፍ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በኩል የቀረቡ ሲሆን ፤ ከዚህ ቀደም ለቤተክርስቲያን ዘርፈ ብዙ ጥቅም ሊያመጡ ይችሉ የነበሩ የቅዱስ ሲኖዶስ ወሳኔዎች ተፈጻሚ አለመሆንን አስመልክቶ ከወትሮው በተለየ አቋም ለተግባራዊነቱ እንደሚሠራ እና እንደሚከታተላቸው እንዲሁም ከሚስተዋሉት የውስጥ እና የውጪ ችግሮች ቤተክርስቲያንን ለመታደግ በባለቤትነት መንፈስ ግዴታውን ለመወጣት መዘጋጀቱን ለቅዱስ ሲኖዶስ በደብዳቤ አሳውቋል። #የቀረቡ ጥያቄዎች፦ ፩.በኦርቶዶክሳዊነት ብቻ ስለሚደርስ ግድያ ፣ መፈናቀል ፣ ስደት እና የአብያተ ክርስቲያናት ውድመትን አስመልክቶ.... ቅዱስ ሲኖዶስ ጥቅምት 2011 ዓ.ም ምልዐተ ጉባኤው ቅድመ አደጋ ማስጠንቀቂያ እና የአደጋ መከላከል መምሪያ እንዲቋቋም ውሳኔ አሳልፎ ነበር። ይኸውም ዓላማ ያደረገው ግልጥ እና ተገማች አደጋዎችን እንዲሁም የስጋት አካባቢዎችን በመለየት አስቀድሞ የማስጠንቀቂያ እና የሰላም ግንባታ ሥራዎችን ለመስራት በተጨማሪም የግጭት ምክንያቶችን በመለየት የዝግጅት እና ሰላማዊ ምላሽ ስልተ ሥርዓት ለመገንባት የነበረ ቢሆንም እስከ አሁን ሥራ ላይ አልዋለም በመሆኑም ተግባራዊ እንዲሆን ፤ ፪. የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን ሥራ ላይ አለማዋል እና ክፍተኛ የአፈጻጸም ክፍተትን አስመልክቶ... ሀ. የ20 ዓመት የቤተክርስቲያኒቱ ተቋማዊ የለውጥ ሥራዎች መሪ ዕቅድ ጥቅምት 2008 ዓ.ም ጸድቆ 2.5 ሚሊዮን ብር የማስፈጸሚያ በጀት ተበጅቶለት ወደ ሥራ እንዲገባ ቢወሰንም አልተተገበረም በመሆኑም ቅዱስ ሲኖዶስ የመጨረሻ እልባት እንዲስጠው ፤ ለ. ጥቅምት 2008 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ፤ ንዋያተ ማኅሌት፣ ንዋያተ ቅድሳት ፣ የቀን አቆጣጠሯን ፣ አልባሰቶቿን ፣ መንፈሳዊ እና ቁሳዊ እንዲሁም የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ ቅርሶች እና ሐብቷን መንፈሳዊ የአእምሮ የሐብት ምዝገባ እንዲከናወን ቢወሰንም አልተተገበረም በመሆኑም በሚመለከተው መንግሥታዊ አካል በኩል እንዲከናወን ፤ ሐ. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ጥቅምት 2012 ዓ.ም ብዝኀ ቋንቋዎች አገልግሎት ማስተባበሪያን በመመሪያ ደረጃ ማዕከል እንዲቋቋም ወሳኔ አሳልፎ ነበር። የማዕከሉ ምስረታ ዓላማ በዋናነት በተለያዩ ቋንቋዎች ካህናት፣ መምህራን እና ሰባኪያን ስልጠና በመስጠት በማብቃት ትውልድ ማፍራት እና በልዩ ልዩ ቋንቋ የማስተማር ውስንነትን በመቀየር እየተስተዋለ ያለውን ቤተክርስቲያንን ሳይረዷት ከበረቱ የሚለዩ እና ሳያውቋት የራቁ እና ሳይገባቸው የሚተቿትን ለማስተማር እንዲሁም አስፈላጊ መጻሕፍትን ለማዘጋጀት እና ምላሽ ለሚሹ ሐሰተኛ ትርክቶችም ጭምር በቂ ምላሽ ለመስጠት እንዲይስችል ቢሆንም ወሳኔው አልተፈጸመም ተግባራዊ እንዲደረግ ፤ መ. የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመዋቅር ፣ አደረጃጀት እና አስራር ለውጥ ሰነድ 2006 ዓ.ም የጸደቀ ቢሆንም እስከ አሁን አልተተገበረም። በመሆኑም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዘመኑን በመዋጀት የተጠናውን የአስተዳደር እና የአፈጻጸም ስልት ተግባራዊ እንዲደረግ የአፈጻጸም ድክመቶች እና የአቅም ውስንነትን ከመሠረቱ እንዲታረሙ አቅጣጫ እንዲያስቀምጥ ሀገር አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አሳስቧል። ቅዱስ ሲኖዶስም በዛሬው ሁለተኛ ቀን የስብሰባ ውሎው በተራ ቁጥር አንድ ላይ የተጠየቀው ጥያቄ ላይ ተጨማሪ አቅጣጫ በማስቀመጥ እና ውሳኔውን በማጽናት እንዲተገበር ትዕዛዝ አስተላልፏል። አሁን እንደጀመረው ደረጃ በደረጃ ለጥያቄዎቹ ምላሽ ይሰጣል ብለን ተስፉ እናደርጋለን ። በመላው ሀገራችን የምትገኙ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በሙሉ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ሥራ ላይ ለማዋል በአንድነት እና በጥልቅ መንፈሳዊ ትጋት እንደትዘጋጁ በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፉለን። ፨፨፨፨፨ ሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት !!! ጥቅምት 2013 ዓ .ም!!!

በመጨረሻም አዲሱ ዓመት ጠንካራ የዕርቅና የሰላም ሥራ ሠርተን ልጆቻችንን ከሥጋትና ከጥፋት የምንታደግበት ይሆን ዘንድ በርትተን እንድንሠራ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሁሉ ልባዊ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እያስተላለፍን፣ ዓመታዊውን የጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ባርከን በጸሎት የከፈትን መሆናችንን እናበሥራለን፤ ጉባኤያችንን ጉባኤ ሐዋርያት፣ ጉበኤ አበው ቅዱሳን ያድርግልን ። እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ፤ ይቀድስ፤ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!! #አባ_ማትያስ_ቀዳማዊ_ፓትርያርክ_ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም_ወዕጨጌ_ዘመንበረ_ተክለ_ሃይማኖት ጥቅምት 12 ,2013 ዓ.ም. አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ ጥቅምት 14 , ዘገብነው https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool

#በዓመት ሁለት ጌዜ የሚካሄደው የቅዱስ #ሲኖዶስ ስብሰባ (ጥቅምት 12 ኣና ትንሣኤ በዋለ በ25ኛው ቀን )፤ በጥቅምት 12 ቀን ተጀምራል ፡፡ ይህ ጉባኤ 22ኛ ዓመት 123ኛ መደበኛ ምልዕተ ጉበኤ ሲሆን ጥቅምት 12 በመንበረ ፓትርያሪክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በቅዱስ ፓትርያልኩ ተካሂዷል፡፡ በዕለቱም #ቅዱስ_ፓትርያርኩ ያስተላለፉት መልእክት #መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ!!! በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን #ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ #ብፁዕ አቡነ ያሬድ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ #ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ #ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በዚህ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት የተገኛችሁ ሁሉ፤ በማያልቅ ፍቅሩ እየጠበቀ አገልግሎታችንንም እየባረከ ሁሌ በቸርነቱ ከዘመን ወደ ዘመን የሚያሸጋግረን እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ለዓመታዊው የጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሁላችንንም በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ!!! “ ብፁዓን ገባርያነ ሰላም እስመ እሙንቱ ውሉደ እግዚአብሔር ይሰመዩ ”(“ የሚያስታርቁ ብፁዓን ናቸው፤ እነሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና ”) (ማቴ. 5፡9) ይህ ትምህርተ ብፅዕና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰላም፣ ስለ አስታራቂዎችና ዋጋቸውን አስመልክቶ ያስተማረው የሕይወት ቃል ነው፤ በሁሉም ዘንድ እንደሚታወቀው የሰላም ነገር በሰማይም ሆነ በምድር በፈጣሪም ሆነ በፍጡራን ዘንድ ያለው ዋጋ ተመጣጣኝም ሆነ ተወዳዳሪ አይገኝለትም፤ በሰማይና በምድር ሰላም በጠፋ ጊዜ ሰላምን ለማምጣት ሲባል አምላክ ሰው ሆኖአል፤ ዕርቅን ለማስፈን ሲባል አምላክ በሥጋ በመስቀል ተሰቅሏል፤ በዚህም ሰማይንና ምድርን ወደ ልጁ ኅብረት አምጥቶአል፤ ዕርቁንና ሰላሙንም አረጋግጦአል፡፡ እንግዲህ ይህ ከኅሊና በላይ የሆነውን የአምላክ ሥራ ስናስተውል ሰላምና ዕርቅ፣ ስምምነትና አንድነት በአምላክ ዘንድ ያላቸው ዋጋ ምን ያህል ትልቅ እንደሆነ እንገነዘባለን ፡፡ በሕዝብና በሕዝብ መካከል እንዲሁም በግለሰቦች መካከል የዕርቅ ተግባር እያከናወኑ ሰላምን የሚያወርዱ ሰዎችም ዋጋቸው የእግዚአብሔር ልጅ መሆንን እንደሆነ ተናግሮ የማይከዳው አምላክ ማረጋገጫ ቃሉ ሰጥቶአል ፡፡ #ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ # ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፤ ሰላምና ዕርቅ የእግዚአብሔር ተቀዳሚ ተግባራት ናቸው፤ እነዚህ ተግባራት በየቀኑ መፈጸምና መከናወን ያለባቸው የእርሱ ሉዓላዊት መንግሥት በሆነችው በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነው፤ የመንግሥቱ ተጠሪ ደግሞ ይህ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ነው፤ ይህ ጉባኤ በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ሆኖ ስለዕርቅና ሰላም አበክሮ እንዲሠራ “ጠብቅ፣ አሠማራ” ተብሎ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሥልጣን የተሰጠው አካል ነው፤ ምክንያቱም በሰዎች መካከል ሰላም ከሌለ ቤተ ክርስቲያንም ተጎጂ ናትና ነው፤ ቤተ ክርስቲያን ልጆቿ ጠባቂ እንደሌላቸው በጎች በሰላም እጦት ሕይታቸውንና ንብረታቸውን ሲያጡ ከማየት የበለጠ የቤተ ክርስቲያን ጥቃት የለምና ፡፡ በመሆኑም ቅዱስ ሲኖዶስ ከምንም ጊዜ በላይ በጎቹን ለመጠበቅ የሚተጋበት ጊዜ ላይ መሆኑን በውል መገንዘብ ይገባል፤ ቅዱስ ሲኖዶስ የሁሉም በጎች እኩል ጠባቂ ነውና፤የገለልተኝነትና የማእከላዊነት አቋሙን ጠብቆ የሁሉም ወገን አባትነቱን ሳያዛንፍ ለልጆቹ ዕርቅና ሰላም መረጋገጥ ሁሉንም በአባታዊ ፍቅር እያቀፈ ማስታረቅ በዚህ ዓመት የመጀመሪያ ተግባሩ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ # ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ #ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሁላችንም እንደምናየው በቃልም ይሁን በመሠረተ ሐሳብ ዕርቅንና ሰላምን የሚቃወም ወገን ፈጽሞ የለም፤ ነገር ግን በመጓጓዣ ሐዲዱ ላይ መግባባት እየጠፋ በሀገራችንም ሆነ በዓለማችን በአጠቃላይ ብዙ ጥፋት ተከሥቶአል፤ የሚያስገርመው ነገር ቢኖር ለውይይትና ለመቻቻል ሰፊ ዕድልና ጊዜ አለመስጠቱ ነው ፡፡ ጉዳዩ እጅግ ግዙፍ የሆነ የሀገር ኅልውና ጉዳይ ስለሆነ በጥልቀት፣ በስፋት፣ በሰከነ አእምሮና አስተሳሰብ በተረጋጋ መንፈስ ሊታይ የሚገባው ጉዳይ ነው ፡፡ አሁን እየተካሔዱ ያሉት የግጭቶች አቅጣጫዎች የሚመስሉ ትንኰሳዎች የኋላ ኋላ ምን ያህል ፀፀት እንደሚያስከትሉ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ድብቅ ምሥጢር አይደሉም ፡፡ ሳንግባባ ቀርተን ትናንትና ያጋጩን ነገሮች ብዙ አሳጥተውናል፤ ለማይመለስ ፀፀትም ዳርገውናል፤ አሁንም ተመሳሳይ ስሕተት ፈጽመን ፀፀት ላይ እንዳንወድቅ የፈለገውን ያህል ጊዜ ይውሰድ የፈለገውን ያህል ዋጋ ያስከፍል ያለአንዳች ግጭትና ደም መፍሰስ ሁሉም ነገር ወደዕርቅ፣ ወደሰላምና አንድነት ማምጣት አለብን፤ በነገሩ ላይ ሸማግሌ ከገባበት እግዚአብርሔርም ከተጋበዘበት የውይይት ጊዜና ትዕግሥትም ከታከለበት ሁሉም ነገር እየዋለ እያደረ የሰላም ጎህ እየፈነጠቀ መረጋጋት ሥር እየሰደደ፣ ጥላቻ እየተናደ እንደሚሄድ ጥርጥር የለውም፤ “ ዕለት ለዕለት ትጐሥዕ ነቢበ፤ ሌሊት ለሌሊት ታየድዕ ጥበበ፤ አንዷ ዕለት ለሌላኛዋ ዕለት መልካም ንግግርን፣ በጎ ሐሳብን ታመነጫለች፤ አንዷ ሌሊትም ለሌላኛዋ ሌሊት የበለጠ ጥበብና ማስተዋልን ትወልዳለች የሚለው የእግዚአብሔር ቃልም ይህንን ያረጋግጣልና ነው፡፡ በዚህ መንፈስ ጠንክረን ከሠራን ፍሬ እናጣለን ተብሎ አይገመትም፤ ስለሆነም ይህ ዓቢይ ጉባኤ እንደካሁን ቀደሙ ኮሚቴ አቋቁሞ መለያየት ሳይሆን የሀገር ሰላም ጉዳይ በቀጥታ ይመለከተናል በሚል ቅን መንፈስ፣ በተቃርኖ ያሉ ኃይሎችን በግንባር በማግኘትና በማነጋገር የአንድ ሰው ሕይወት እንኳ እንዳይጠፋ ሁሉም የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠንክሮ መማፀን አለበት፡፡ የሁሉም ምርጫ ውይይትና ውይይት ብቻ እንዲሆንም በርትቶ በመሥራት ሁሉንም ማሳመን አለበት፤ ከዓቅሙ በላይ ከሆነም ልምዱና ጥበቡ ያላቸው ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ገለልተኛ ወገኖችን በማሳተፍ የዕርቁና የሰላሙ ተልእኮ ግብ እንዲመታ ማድረግ አለበት፤ ይህ ተግባር ወቅቱ ኃላፊነት የጣለበት የቅዱስ ሲኖዶስ ተቀዳሚ ተግባር ነው ፡፡ #ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ! #ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት! በአሁኑ ጊዜ ቤተ ክርስቲያናችንን ለከፋ አደጋ የዳረጋት መሠረታዊ ምክንያት የአክራሪዎችና የተቃራኒዎች እንቅስቃሴ መሆኑ በውል ማወቅ አለብን፤ ይሁን እንጂ የእኛ አያያዝም በክፍተት የተሞላ በመሆኑ ከተቃራኒ አካላት ባልተናነሰ ሁኔታ እያስጠቃን ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን የሚታዩ ልዩ ልዩ የአሠራር ጉድለቶች ማለትም የአስተዳደር ስልታችን የፋይናንስና የንብረት አያያዛችን ምእመናንን እያበሳጩብን እንደሆነ አንዘንጋ፤ በመሆኑም እነዚህንና ሌሎች ችግሮቻችንን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስተካከል ዕውቀቱ፣ ልምዱና ችሎታው ባላቸው ባለሙያዎች በጊዜያዊም ቢሆን መድበን በጥናት ላይ የተመሠረተ መሪ ዕቅድ ዘመናዊ አሠራርን አዘጋጅተው እንዲያቀርቡልን ማድረግ አለብን ፡፡ በሠላሳ ዘጠነኛው የሰበካ ጉባኤ ስብሰባ ላይ እንደተጠቀሰው ቤተ ክርስቲያናችን በከባድ ፈተና ላይ መሆኗ ተገልፆአል፤ ስለሆነም ይህ የጥፋት ድርጊት እንዲቆም ሁነኛ መፍትሔ ማስቀመጥ ይኖርብናል ፡፡

#ጥቅምት_14 #ሐዋርያው_ቅዱስ_ፊልጶስ_ ** በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊልጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ✤ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ባለውለታችን (በእግዚአብሔር ፈቃድ ሰማያዊውም ሆነ ምድራዊውን ውለታ የዋለልን) የኾነውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሐዲስ ኪዳን የእግዚአብሔርን ቃል የተናገረን፤ የክርስትና ጥቀምት አባትና አጥማቂያችን ከ72ቱ አርድዕት አንዱ የኾነው ቅዱስ (ሐዋርያው) ፊልጶስ #በሀገራችን__ብቸኛ_በኾነውና በአ.አ ኮልፌ አጠና ተራ በሚገኘው ቤ.ክ. #ደብረ_ምጥማቅ-ቤ.ክ በዓለ ዕረፍቱ ይከበራል፡፡ " እነሆ በውሀ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድነው? " የሐዋርያት ሥራ ፰÷፴፮ **በኢትዮጵያ ብቸኛ የሆነውና በአዲስ አበባ የሚገኘው ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ.ክ የተመሠረተው በ3ኛው ፓትርያርክ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሲሆን፤ የቅዱስ ፊልጶስ ክብረ በዓል በዓመት 2ት ጊዜ ነው፤ #ጥቅምት 14 በዓለ ዕረፍቱ #የካቲት 20 ቅዳሴ ቤቱ ነው ‹‹የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።"ዕብ. 13፥7 ፠፠፠ ‹‹ደብሩሰ ለቅዱስ ፊልጶስ ትመስል ደብረ ሲና፤ ወሀደረ ላዕሌሃ እግዚአብሔር ሐፁር የዐውዳ ወጽጌረዳ በትምዕርተ መስቀል፡፡›› #አድራሻ_- ኮልፌ አጠና ተራ ወደ፡ሎሚ ሜዳ በሚወስደው መንገድ ኢንዱስትሪ መንደር ሳይደርሱ ፠1. ከመርካቶ በባስ ቁጥር 69 ጠሮ በሚወስደው መንገድ፣21 ልኳንዳ ወርደው ወደ ቀድሞ 04 ቀበሌ ፠2. ከአየር ጤና እና ዙሪያው በባስ ቁጥር 87 አጠና ተራ ወርደው የቀለበት መንገድ የእግረኛ መሻገሪያ ተሻግረው ባለው አስፋልት ቀጥታ በመሄድ ያገኙታል ፠3. ከቡራዩ አስኮ አካባቢ ለምትመጡ በባስ ቁጥር 28 አጠና ተራ ወርደው በቀኝ በኩል ባለው አስፋልት ቀጥታ በመሄድ ያገኙታል https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool

#ዳሕምሞ_ #ደብረ_ዳሞ መላእክትም ለአረጋዊ እንደባልንጀራ አንደ ጓደኛ ሆኑት፤ እሳቸውን ለመጐብኘትና በረከት ለማግኘት አባቶች ብቻ ሳይሆኑ ንጉሡ አጼ ገብረመስቀልም ወደእሳቸው ይመጣ ነበር፡፡ እሱም እሰከዛሬ ምስክር ሁኖ የሚገኘውንና በእመቤታችን ስም የተሰየመውን ድንቅ ገዳም ሲያንጽ ለእንሳሳቱ መመላለሻ እንዲሆን ተራራን አሠራ፤ ሕንጻው ቅዱስ ያሬድ በተገኘበት ተመረቀች፤ ኋላ ግን ንጉሡ ከአረጋዊ ተባርኮ ሲመለስ ‹‹ተራራውን ላፍርሰው፤ ወይስ ልተወው?›› አለ፤ አቡነ አረጋዊም በግዕዙ ‹‹#ዳሕምሞ_›› አሉት፡፡ በአማርኛ ቋንቋ ‹‹የሰራኸውን ደረጃ ናደው ፥ አፍርሰው እንጂ አትተወው›› ማለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት አካባቢው ዳሞ ገዳሙ ደግሞ ደብረዳሞ ተባለ፡፡ አቡነ አረጋዊም ንጉሡን ‹‹ስለዘንዶው ጅራት ፈንታ ሰዎች ይወጡበት ዘንድ ገመድ አብጅ፡፡ ለልጅ ልጅ መታሰቢያ እንዲሆንና ይህን ድንቅ ሥራ እያየ በፍጥረቱ ሁሉ አንደበት እግዚአብሔር ይመሰገን ዘንድ፡፡›› አሉት፤ ለመወጣጫ ይሆን ዘንድ ገመድ ተሰራለት፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ገመዱ የታሠረበት ግንድ እስካሁን ከ1500 ዓመታት በላይ አለ፤ ኋላ በ13ኛው ክፍለ ዘመን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለ12 ዓመታት በደብረ ዳሞ ቆይተው በዚሁ ገመድ ሲወርዱ ነው ሰይጣን ቀንቶ ገመዱን ቢበጥስባቸው እግዚአብሔር አምላክ ክንፍ የሰጣቸው፡፡ ደብረዳሞ ዙርያው ገደል ሆኖ የጠረጴዛ ቅርጽ ያለው ያለው አምባ ሲሆን 500*1000 ሜትር የሚሆን ስፋት አለው፡፡ ከባህር ወለልም በላይ 2216ሜ. ከፍ ይላል፡፡ ወደ ገዳሙ መውጣት አና መውረድ የሚቻለው 16ሜ. በሚረዝመው በአምሳለ ዘንዶ በተሰራው ገመድ ብቻ ነው፡፡ ንጉሡም ከተራራው እንደወረደ እንደታዘዘው አፈረሰ፡፡ አሁን የምናየው ዓይነት ገመድንም አዘጋጅቷል፤ የገመዱም ስመ ‹‹ዘንዶ›› ይባላል፡፡ በዚህ ገዳም ሴቶች በአፀደ ሥጋ እያሉ አይገቡም፤ ካረፉ በኋላ ግን እንደ አባ ጳኩሚስ ገዳምና ሥርዓት ከተከዜ ማዶ ከሚኖሩ የሴት መነኮሳት መካከል አንዲቱ የሞተች እንደሆነ ወደ ወንድሞች መነኰሳት አምጥተው በነሱ ዘንድ በሚገኘው የመቃብር ቦታ ይቀብሯቸው ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ የአቡነ አረጋዊ እናት የነበረችው ልጂ በሕፃንነቱ ሳለ መመንኰሱን አውቃ ከልጇ ሕይወቱን ተምራ ገና ከመጀመሪያ ወደ አባ ጳኵሚስ ገዳም ሄዳ መንኵሳ ነበርና በቅድስና በትሕትና ደናግሉ በፍቅር ስታስተዳድር ኖራ መንፈሳዊ ግዳጇን በጐ አገልግሎቷን ፈጽማ ጥር 4 ቀን ስታርፍ ለመቀበሪያዋ ይሆን ዘንድ አባታችን አቡነ አረጋዊ ባሰራላት አዲስ መቃብር ተቀብራለች፡፡ /ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ::/ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://t.me/medihanaelem

ሥርዓተ ማኀሌት ዘውርኀ ጽጌ ፫ኛ ዙር ዓመት፤ ፫ ኛ ሳምንት ጥቅምት ፲፭ በዓለ ቅዱሰ ቂርቆስ፡፡ ሥርዓተ ማኀሌት ዘውርኀ ጽጌ ፫ኛ ዙር ዓመት፤ ፫ ኛ ሳምንት ጥቅምት ፲፭ በዓለ ቅዱሰ ቂርቆስ፡፡ #sh
+4
ሥርዓተ ማኀሌት ዘውርኀ ጽጌ ፫ኛ ዙር ዓመት፤ ፫ ኛ ሳምንት ጥቅምት ፲፭ በዓለ ቅዱሰ ቂርቆስ፡፡ ሥርዓተ ማኀሌት ዘውርኀ ጽጌ ፫ኛ ዙር ዓመት፤ ፫ ኛ ሳምንት ጥቅምት ፲፭ በዓለ ቅዱሰ ቂርቆስ፡፡ #share

#የአቡነ_አረጋዊ_የበሶ_እምነት_፤ በዓመት አንድ ጊዜ ጥቅምት 14 በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል በሚከበረርባቸው አብያተ ክርስቲያንት ላይ በሶ ይሰጣል፤ ይኸውም የበሶ እምነት ለብዙ ችግሮች ፈውስ ነው፡፡ በሶ የአቡነ አረጋዊ እምነት የኾነበት ምክንያትም በታላቁ ገዳም በደብረ ዳሞ የመናንያኑ ምግብና ወደዚሁ ቦታ ለሚሄዱ ምዕመናንም እንደ እምነት ተደርጎ የሚሰጥ በመኾኑ ነው፡፡ *** +++ #የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል ከሚከበርባቸው ቦታዎች መካከል ዐበይቶቹ፤ ፠ በደብረ ዳሞ፣ ፠ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም፣ (የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት ይገኛል) (ደብራችን መጀመሪያ ሲመሠረት ይቀድሱና ያወድሱ የነበሩት የደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳት ናቸው፡፡ የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ክብረ በዓል በደብራችን ሲከበር 100 ዓመታት ሞልቶታል፤ እንኳን ክብረ በዓል የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ማኅበር እንኳን 100 አካባቢ አስቈጥሯል፡፡) ፠ በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ (አለርት ሆስፒታል አጠገብ፤ ወደ አለም ባንክ መስመር) ፠ በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በሽሮ ሜዳ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ.ክ. (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በጎንደር አቡነ አረጋዊ ቤ.ክ. (ብሉኮ አካባቢ) ፠ ፠ ፠ ፠