uk
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Відкрити в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 381 підписників, посідаючи 5 582 місце в категорії Релігія і духовність та 2 194 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 381 підписників.

За останніми даними від 09 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 38, а за останні 24 години на -1, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 21.91%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 9.42% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 370 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 449 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 25.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 10 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

15 381
Підписники
-124 години
-67 днів
+3830 день
Архів дописів
የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት #ታኅሣሥ_፲፱ #በዓለ_ቅዱስ_ገብርኤል፤ #ወሥርዐተ_ማኅሌት፡፡ ቅዱስ ገብርኤል፤ #ሊቀ_መላእክት_በመላእክት_ሁሉ_ላይ_የተሾመ_ነው_ሄኖክ_10፥14 #የአርባብ_የ10ሩ_ነገደ_መላእክት_አለቃ_ነው #ከከበሩ_መላእክት_አንዱ_ነው_ሄኖክ_6፥7፤ #አካሉ እንደ ቢረሌ የሚመስል (ጽሩይ የሆነ) ፥ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ የሆነ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነው፡፡/ዳን.10፥5-9/ #መልአከ_ራማ_ዘራማ_ልዑል_ነው፤ (የራማ ልዑል ነው) #አብሣሬ_ትስብእት_ነው፤ #መጋቤ_ሐዲስ_ነው፤ #በእግዚአብሔር_ፊት_የሚቆም_መልአክ_ነው_ሉቃ_1፥19፤ #ለቅዱሳን_እውቀትን_የሚገልጽላቸውና_ከአላውያን_የሚታደጋቸው_ነው_ /ድርሳነ_ገብርኤል/ #መልአከ_ሰላሞሙ_ወመልአከ_ኪዳኖሙ_መልአከ_አድኅኖ_መልአከ_ኀይል_መልአከ_ፍስሐ (የሰላም መልአክ ፥ የኪዳን መልአክ፥ አዳኝ መልአክ፥ ኀያል መልአክ ፥ የደስታ መልአክ ነው) #ከሣቴ ጥበብ (ጥበብን የሚገልጽ ነው) /ት.ዳን./ #ናዛዜ_ኅዙናን_ (ያዘኑትን_የሚያጽናና_) መልአክ_ነው፨ ✤ ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔር ልጅ ማለት ነው፤ የወልደ እግዚአብሔርን መወለድ አብሥሯልና፨ አንድም የሁለት ቃለት ጥምር ነው እነዚህም ገብር እና ኤል ሲሆኑ ትርጕማቸውም ገብር አገልጋይ ማለት ሲሆን ኤል ማለት ደግሞ አምላክ ማለት ነው፤ በተገናኘ ገብርኤል ማለት የአምላክ አገልጋይ /የእግዚአብሔርን ልጅ የሚመስል የአምላክ አገልጋይ/ ማለት ነው፡፡ ✼ ነቢዩ ዳንኤል “ዐይኖቼንም አነሣሁ” አለና አስከትሎ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡… ይህንንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኃይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኃይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡(ዳን.10፥5-9) ነቢዩ ዳንኤል እንዲህ ብሎ የተናገረው የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ ነበር፡፡ ፠ “እነሆ ከዋነኞቹ አለቆች” አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ”(ዳን.10፥13) ብሎ በተናገረው ንግግሩ በመላእክት ላይ የተሾሙ ሌሎች አለቆች እንዳሉ ማስተዋል እንችላለን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በቅዱሳን መላእክት ዘንድ ስላሉት ነገዶች ሲገልጽ “… በሰማይ ያለውን በምደር ያለውን የሚታየውንና የማይታየውን መናብርትም ቢሆኑ አጋእዝትም ቢሆኑ መኳንንትም ቢሆኑ ቀደምትም ቢሆኑ ሁሉም በእጁ ሆነ፤ ሁሉም በእርሱ ለእርሱ ተፈጠረ” (ቈላ.1፥16) በማለት ይዘረዝራቸዋል፡፡ ከዚህ ተነሥተን መላእክት በተለያዩ ዐበይት ነገዶች የተከፈሉና ለእያንዳንዱም ነገድ የራሱ የሆነ አለቃ እንዳለው ማስተዋል እንችላለን፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ከእነዚህ ዐበይት የመላእክት ነገዶች መካከል አንዱ በሆነው አርባብ በሚባለው ዐቢይ ነገድ ላይ የተሾመ ሲሆን ከ100ው ነገደ መላእክት መካከል ከበታቹ የሚመራቸው ዐሥር ነገደ መላእክት አሉት፤ ከተማቸውም በሰማየ ራማ ነው፡፡ ✼ ቅዱሳን መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ፊት አውራሪነት የሰው ልጆች ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ተዋግተው ድል ከመንሳታቸው አስቀድሞ፤ እንደ አምላክ ሊመለክ የወደደውን ሳጥናኤልን ቅዱስ ገብርኤል በመቃወም ‹‹ንቁም በበህላዌነ እስከ ንረክቦ (ነአምሮ) ለአምላክነ “አይዟችሁ ፈጣሪያችን እስክናገኘው፣ እስክናውቀው ድረስ በያለንበት ጸንተን እንቁም፡፡” (አክሲማሮስ ገጽ.35) በማለት መላእክትን ያረጋጋ መልአክ ነው፡፡ ✼ ቅዱስ ገብርኤል በተወዳጁ መልአክ በቅዱስ ሚካኤል መሪነት የሰው ልጆች ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ተዋግተው ድል እንዲያደርጉ ወደ ጥልቁ እንዲጣል አድርጓል ራእ12፥7፤ ነቢዩ ኢሳይያስ በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፤… በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምድር ጥልቅም ትወርዳለህ” (ኢሳ.14፥16) በማለት ገለጠልን፤ ወደ ምድር የጣሉት በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል መሪነት እነ ቅዱስ ገብርኤል ናቸው፡፡ ✼ ቅዱስ ገብርኤል ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ከሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው ብሏል (ሉቃ 1፥19)፤ ✼ ታላቁ ነቢይ ሄኖክም ስለ ነገረ መላእክት በተናገረበት አንቀጽ እንዲህ ሲል መስክሯል ‹‹በአበቦች ላይ በገነትም በጻድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾሙ ከከበሩ መላእክት አንዱ ገብርኤል ነው፡፡›› ሄኖክ 6፥7፤ ‹‹በሦስተኛውም በመላእክት ሁሉ ላይ የተሾመ ቅዱስ ገብርኤል ነው›› ሄኖክ 10፥14 እያለ የመልአኩን ክብር ተናግሯል፡፡ ** ቅዱስ ገብርኤል መንፈሳዊ እውቀቱን የሚያካፍላቸው መልአክ ብቻ አይደለም፤ ለእግዚአብሔር በመገዛታቸው ምክንያት ከአላውያን ገዢዎች ከሚደርስባቸው መከራም የሚታደጋቸው መልአክም ነው፡፡ ነገር ግን ያደረጋቸው ተዓምራቶች በመጽሐፍ ቅዱስ፣ በመልክኡ፣ በድርሳኑ፣ በተአምሩ፣ …. የተጻፉ ቢሆንም፤ ✤✼ #ታኅሣሥ_19 #ካደረጋቸው_ተራዳኢነት_ዋናውን_እንደከሚተለው_እናያለን_፤ ፠ አናንያና(ሚሳቅ)፣ አዛርያ(ሲድራቅ) እና ሚሳኤል(አብደናጎ) ያዳናቸው ያዳነበት ቀን ነው፡፡ አናንያና(ሚሳቅ)፣ አዛርያ(ሲድራቅ) እና ሚሳኤል(አብደናጎ) የፋርስ ባቢሎን ንጉሥ የነበረው ናብከደነፆር በዱራ(አዱራን) በሚባል ስፍራ ላይ ላቆመው ጣየዖት ምስል ስገዱ ሲላቸው …. የምናምነው አምላክ ያድነናል፤ ባያድነን እንኳን (አምላካችን በእሳት ሰማዕት እንድንሆን ፈቃዱ ቢሆነረ አንኳን) አንተ ላቆምከው ምስል አንሰግድም ብለውታል፡፡ ንጉሡም ወደ እቶን እሳት እንዲጣሉ አድርጓቸዋል፤ በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት ግን ከእቶን እሳቱ የልብሳቸው ዘርፍ እንኳን እሳት ሳይነካው ከእሳቱ ድነዋል፡፡ እንዲሁም ዛሬ፤ #ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘሀገረ_ቡርልስ_በዓለ_ዕረፍቱ_ እንዲሁም #ኢትዮጵያዊው_አቡነ_ስነ_ኢየሱስ_ (#ገዳማቸው_በሰሜን_ጎንደር_ትክል_ድንጋይ_አካባቢ_የሚገኘው_) #በዓለ_ዕረፍታቸው_ነው_፡፡ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል፫_ #ሰይጣን_ሰዎችን_እንዴት_እንደሚፈትንና_ኃይል_እንዴት_እንደሚያገኝ_የሐሰት_አባት_ሁኖ_ሳለ_ሰዎች_እንዴት_እንደሚያምኑትና_ባይፈልጉም_አምላካቸውን_እንደሚያመሰግኑና_እንደሚታዘዙ፡፡ በሳምር ሃገር ሰሉቅያ (አስቀሎና) በምትባል ቦታ ከሄሮድስ ወገን የሚሆኑ ጣዖት የሚያመልኩ ክፉዎችና ኀጢአተኞች ነበሩ፤ ሴቶችም ወንዶችም ከሚስቶቻቸውና ከባሎቻቸው ከልጆቻቸው ጭምር ተሰብስበው በየወሩ ወደ ጭፈራ ቤት የመግባት ክፉ ልማድ ነበራቸው፡፡ ቅዱስና ንጹሕ፥ ጻድቅና መስተጋድል፥ መነኰስና ካህን አባ ጳውሊ ከዚህች አገር ደርሶ፤ የዚያችን ሃገር ሰዎች ወደ ጭፈራ ቤት ሲሄዱ ባደረበት ጸጋ እግዚአብሔር የሰዎቹን የኀጢአት ሥራ አውቆ ፈጽሞ አዘነ፤ ወደ ዳንስ ቤቱ ተጠግቶም ከበር ቆመ ሰዎቹም መብራት አጥፍተው፥ ራቁታቸውን ሆነው በዱር እንዳሉና እንደጠገቡ ፈረሶች ሲጮሁ ሰማቸው፡፡ አባ ጳውሊም ወደ እግዚአብሔር እነዚህ ሰዎች ለሌሎች የኀጢአት አብነት እንዳይሆኑ ቅጣቸው፤ አጥፊ የሆነውንም ሰይጣን በኀይልህ አጥፋው እያለ በፍጹም ልቡ ጸለየ፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰማውና አጥፊ የሆነው ሰይጣን የሚንቦገቦግና የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ እንዲገለጽለት አደረገ፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ሰይጣንን አንተ ማነህ? ማንንስ ትፈልጋለህ? ሰይፍህ በእጅህ የተመዘዘው ለምንድን ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ የምትሻውን ንገረኝ እንጂ አንተ ማነህ አትበለኝ፤ ከፈጣሪህ የለመንከውን አንተ ታውቃለህና አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ የአንተን ሥራ የሚሠሩትን ወዳጆችህን (ጭፈራ ቤት ያሉትን) እንዴት ታጠፋለህ አለው፡፡ ሰይጣን፤ እኔ ከፈጣሪ ታዝዣለሁ፤ የአዛዤን ትእዛዝ እተላለፍ ዘንድ አይቻለኝም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ብዙ ጥያቄ እጠይቅሃለሁና እንዳትዋሸኝ በሕያው በእግዚአብሔር ስም አምዬሐለሁ፥ አውግዤሃለሁ፥ በቅዱስ መስቀሉ አስሬያለሁ አለው፡፡ ሰይጣን፤ በሰዎች ላይ የማደርገውን ክፉ ሥራዬን ልትገልጽብኝ ነውን? የምትሻውን ጠይቀኝ፤ ትእዛዛህን አልተላለፈም ኀይሌ በጸሎህ ደክሟልና አለው፡፡ ++ አባ ጳውሊ፤ ከሰዎች በአንዱ አድረህ በኀጢአት ትጥለው ዘንድ አጋዥ የሚሆንህ ምንድን ነው? /ሔዋንን በእባብ አዳምን በሔዋን ማሳቱን ልብ ይሏል/ ሰይጣን፤ ሰው #በእግዚአብሔር_ሕግ_ጸንቶ ሳለ በማንም ላይ ማደር አይቻለንም፤ ከእግዚአብሔር ሕግ ትንሽ ፈቀቅ ቢል፤ እንዲሁም #በየጊዜው_ስሙን_ከልቡ_ባይጠራ (በፍጹም ሃይማኖት ሁኖ የማያማትብ፤ ሕፃን ቢሆንም ከመጠመቁ በፊትም እናቱ የማታማትብና የእግዚአብሔርን ስም የማትጠራ ከሆነ፤ ባለትዳሮችም ከመጋባታቸው በፊት በካህናት ጸሎት በሚጋቡ ጊዜ በሥጋ ወደሙ በመኝታቸው አንድ በሚሆኑ ጊዜም የአምላክን ስም የማይጠሩ ከሆነ) ያንጊዜ በሰው ላይ ለማደር ኀይል እናገኛለን፤ በእነርሱና በልጆቻቸውም ላይ እናድራባቸዋለን፤ እንሰለጥንባቸዋልን፤ ሰላምንና ፍቅርን እናሳጣቸዋለን፤ ኑሯቸው ጠብና ክርክር እንሞላበታለን፤ መጨረሻቸውም መለያየት ይሆናል አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ መላውን የዓለምን ሰዎች የምትፈትናቸው በምንድን ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ እንደምኞታቸው እንፈትናቸዋለን፤ ሥጋዊ ሐሳብን አሣምረን እናቀርብላቸዋለን፤ በከራት በትምክት እናቃጥላቸዋልን፤ እንቅልፍንና ዝሙት መመኘትን እናመጣባቸዋለን፤ ጾም እንዳይጾሙ፥ ጸሎት እንዳይጸልዩ እናደርጋቸዋለን፤ ከሥጋ ወደሙና ከመልካም ሥራ ሁሉ እናርቃቸዋለን፡፡ ዘወትር ይህን ዓለም በማሰብ (በስካር፥ በውሸት፥ በቂምና በቅናት፥ ሐሰት በመመስከር፥ ወርቅና ብርን በመውደድ፥ በስንፍና፥ ሰውን በመስደብ አእምሯቸው እንዲጠፋ እናደርጋለን፡፡ ቅዱሳንን ሳይቀር ልባቸው ከእግዚአብሔር ፍቅር እንዲርቅ፥ ቃልኪዳናቸውን እንዲተዉ በተለያዩ ምክንያት ባለን ኀይል እንዋጋቸዋለን አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ሰውን ታጠፋ ዘንድ ኀይልና ሥልጣን የምታገኘው እንዴት ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ #የእኛን ሐሳብ ተከትለው ኀጢአትን አዘውትረው በሚሠሩ ክፉዎችና አመንዝራዎች እንዲሁም ፈጽመው ንስሐ በማይገቡ ላይ ነው፡፡ የሚጠብቋቸው ቅዱሳን መላአክት ስለበደላቸውና ስለ ኀጢአታቸው ሲርቋቸው ያንጊዜ እኛ በእነርሱ ላይ እንበረታለን፡፡ #ክፉ ሥራንም ሁሉ ወደው እንዲሠሩ እናደርጋቸዋለን፡፡ መልካም በማስመሰል በሐሰተኛ ሕልም እናስታቸዋለን፡፡ እኛ እግዚአብሔርን መሳደብና መንቀፍ ባይቻለን ሰዎች ፈጣሪያቸውን ና ድንግል ማርያምን እንዲሁም ቅዱሳን መላእክትንና ቅዱሳን ሰዎችን ለመስደብና ለመንቀፍ እንዲነሳሡ እናደርጋቸዋለን፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ ሐሰተኛና የሐሰት አባቷ ሆነህ ሳለ /ዮሐ. ፰፥፵፬/ ሰዎች ቃልህን እንደት ያምኑሃል? አለው፡፡ ሰይጣን፤ አንተና እንዳንተ ያሉ ባታምኑኝም በኋላ ዘመን ብዙ ሰዎች በእኔ ቃል ያምናሉ፥ ምክሬን ይቀበላሉ፥ ጥበቤን ይፈልጋሉ፡፡ ያለ ጊዜዬ አኔን ማጥፋት የማይሻ ጌታ ክርስቶስን እንኳን ፈትኜዋለሁ አለው፡፡ እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት ሰዐት ደርሷልና የታዘዝኩትን ፈጥኜ አደርግዘንድ ልቀቀኝና ልሂድ አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ እግዚአብሔርን በምታመሰግኑበት ጊዜ ጥቅማችሁ ምንድን ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ በተፈጠርን ጊዜ ምስጋናው በአንደበታችን ተፈጥሯልና፤ ስሙ ኅቡዕ ለሚሆን ብርሃናትና ለፈጠረ ለእርሱ የምንሰግድበትና የምናመሰግንበት ሰዐት አለን እንጂ የምንጠቀመው ጥቅምና ክብር የለንም አለው፡፡ #ሰዐቱን ጠብቀን ካላመሰገንን መኖር አንችልም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ የምትሰግዱትና የምታመሰግኑት በፈቃዳችሁ ነውን? ወይስ ያለፈቃዳችሁ? አለው ሰይጣን፤ በግድ ነው እንጂ ደስ ብሎን አናመሰግንም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ደስ የማይላችሁ ለምንድነ ነው? አለው ሰይጣን፤ ከክብራችን ተዋርደን ጨለማ ከለበስን በኋላ ደስታ የለንም፤ ደስ ብሎንም አናመሰግንም፡፡ ስለዚህ እስከዛሬ ምስጋናውን አቋርጠን አናውቅም አለው፡፡ #ክፍል ፬.… ሰይጣን የቅዱሳን መላእክትን ቃል(ምሥጢር) እንደሚሰማና ከመደረጉ በፊት ለሰዎች በመናገር እንደሚያስት፤ ሰይጣን ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ በዘመን ብዛት ሰውን ያሚያስትበት ብዙ ጥበብ እንዳለው፤ የክርስቶስ ሰው መሆን ከሰይጣን የተሰወረ እንደነበር፤ ሰይጣናት አለቃና ታዛዥ እንዳላቸው፤ ገሃነነም ስለመኖሩና ዲያብሎስ ለምን ንስሐ እንደማይገባ፤ ክፍል ፬.… ይቀጥላል ይጠብቁን/ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

✤✤ #ፀሐይ_ማር_አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_(#ዘገዳመ_ዋሊ_) ✤✤ ፠ በሃገራችን በኢትዮጵያ በብቸኝነት በጌታችን የተመሠረተው ገዳመ ዋልድባ፤ ኋላ በአሕዛብ ጠፍቶ ነበርና በ13ኛው ክፍል ዘመን እንደ መሶብ ከፍ አድርገው በ4ቱም አቅጣጭ በ4 ወንዞች (በሰሜን ተከዜ፥ በምስራቅ እንስያ፥ በምዕራብ ዛሪማ ፥ በደቡብ እንዞና ወይቦ) ዙሪያውን ከልለውና አጥረው ያስባረኩ አባት ናቸው፡፡ ፠ አዲስ አበባና አካባቢውን ከ700ዓመታት በፊት በአንበሳ እየተጓጓዙ በስብከተ ወንጌል እርሻነት፥ በሥነ ምግባር ማለስለሻነት ያረሱ አባት ናቸው፡፡ ፠ ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን፣ ወላዴ መምህራን ወሊቃውንት የኾኑ ናቸው፤ ይህንንም ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በ40ቀን ዕረፍታቸው በመካነ መቃብራቸው ተገኝተው መልክዓቸውን ደርሰውላቸዋ፤ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰታቸው አውስተዋቸዋል፤ እንዲሁም በርካታ ቅዱሳን ደራስያን በየድርሰታቸው አንስተዋቸዋል፡፡ #ክቡር_መምህር፥ #የከበረ_መምህር፤ #መልአክ_ዘበምድር፥ #የምድር_መልአክ፤ #ካህን_ወድንግል፥ #ካህንና_ድንግል፤ #ፍጹም_ንጹሕ_ወልዑል፥ #ፍጹም_ንጹሕና_ልዑል፤ #ትጉህ_ወኅሩይ፥ #ትጉህና_ኅሩይ_የተመረጠ)፤ #ብእሴ_እግዚአብሔር፥ #የእግዚአብሔር_ሰው፤ #ለባሴ_ንጽሕና፥ #ንጽሕናን_የተላበሰ፤ #ወለብሰ_ብርሃናዌ፥ #ብርሃንን_የለበሰ፤ #ዘፈጸመ_ገድሎ_በሠናይ፨ #ገድሉን_በመልካም_ተጋድሎ የፈጸመ፨/ገድለ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ/ ፠ ከረድአቸው አባ ብንያሚና፤ ከጓደኞቻቸው ከአባ አንበስ ዘሐዘሎና ከአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ጋር በመኾን በወቅቱ ከነበሩት ርዕሰ አበው አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘንድ ለመባረክ ወደ ዝቋላና ምድረ ከብድ የመጡና በረከትን የተቀበሉ ከሰሜን እስከ ደቡብ ኢትዮጵያ ያስተማሩ ናቸው፡፡ ፠ አናታቸው በሥጋ ሞት በሕፃንንታቸው ቢለይዋቸውም፤ በሕፃንነታቸው ጌታችን አውራ ጣቱን አትብቷቸዋል፡፡ ‹‹እንዘ ይተግህ ለጸልዮ ወያስተበርክ ለስኢል፤ መንኰብያቲሁ አጠበዎ ወልደ ማርያም ድንግል፡፡ ሳሙኤል፥ ሳሙኤል፥ ሳሙኤል ዘዋልድባ መነኮስ ኀያል፡፡›› /እንዲል ነግሥ/ ፠ የተከዜ ወንዝ ሞልቶ የማያሻግራቸው ቢሆን ውሃውን በትዕምርተ መስቀል ባርከው በአንድ እጃቸው መጽሐፍ ፥ በአንድ እጃቸው መብራት እንደያዙ ወደ ወንዙ ገብተው መብራቱ ሳይጠፋ መጽሐፉም ሳይበላሽ ተሸግረዋል፡፡ ፠ ገባሬ ተዓምራት ወመንክራት የኾኑ፤ ⴲ ዝናብ በኾነ ጊዜ ዝሆኖች መጥተው እንደ ጥላ የሚያስጠልሉት፤ ‹‹ሳሙኤል አቡነ ሠረገላ ጸሎት፤ ጊዜ ርደቶሙ ለዝናማት፤ ዘከለሉከ ነጌያት፡፡›› እንዳለ መጽሐፈ ሰዐታት፤ ⴲ ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ (ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት) ጋር መንበረ ጸባዖትን ለ12 ዓመታት አጥነዋል፤ በዚህም በጎንደር ደባርቅ አካባቢ የመሠረቱት ገዳማቸው አብ ጠራ(ህ) በሚል ተሰይሟል፡፡ ‹‹ሳሙኤል አቡነ ትሩፈ ምግባር፤ ዐምድ ጽኑዕ ፀወነ ሃገር፤ ወመልአክ ዘበምድር፡፡›› እንዲል መጽሐፈ ሰዐታት፣ ⴲ በዋልድባ ምድር ላይ ቀድሞ ውኃ የለም ነበርና፤ ፸ የሚጠጉ ምንጮችን በተለያዩ ቦታዎች አፍልቀዋል፡፡ ⴲ ቅዳሴ ማርያምን ወደ መሃል ሃገር ያመጡ፤ ⴲ ቅዳሴ ወውዳሴ ማርያምን ሲደግሙ ከመሬት ክንድ ከስንዝር ያህል ከፍ የሚሉ፡፡ ⴲ በአናብስት ዘባን ላይ የሚጫኑ፤ መጻሕፍቶቻችውንም በአናብስት ላይ የሚጭኑ፡፡ ⴲ እመቤታችን ነጭ ዕጣን (ስለ ምዑዝ ክህነታቸው) እንዲሁም ዕንቊ (ስለ ንጽህናቸው፣ ቅድስናቸውና ድንግልናቸው) የሰጠቻቸው። ⴲ በሰኔ 21 ቀን በቀደሱበት ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ አንድ ክንድ ከስንዝር ከምድር ለቆ እንደ ደመና በአየር ላይ ቆሞ የታየላቸው፡፡ ⴲ ውኃውን ወደ ኀብስት የቀየሩና ከነ ደቀመዛሙርቶቻቸው የተመገቡ፤ ‹‹ሶበ አተቦ ለማይ በቅዳሴኪ እንዘ ይጼሊ፤ ረሰዮ ኅብስተ ጽጌ ሃይማኖት ሳሙኤል ዘሐቅለ ዋሊ፡፡ ምሕረተ ወፍትሐ ለተአምርኪ እኅሊ፤ ሥረዪ ኀጢአትየ ወዕፀብየ አቅልሊ፤ አስመ ኵሎ ገቢረ ማርያም ትክሊ፡፡›› /ማኅሌተ ጽጌ/ ‹‹ …አርአዮሙ ለመምህራን ዐበይተ ኀይላተ፤ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በኀበ ተአኵተ፥ ወለማይኒ ረሰዮ ኅብስተ፡፡›› /ማኅሌተ ጽጌ/ የምንኵስና ተወረዱም፤ አባት አባትን ሲወልድ፤ መምህር መምህርን ሲተካ፥ ቅዱስ ቅዱስን ሲያፈራ፥ ገዳም ገዳምን ሲወልድ ነውና ቅሉ፤ የምንኵስና ተዋረዱም፤ ፠ ….. ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ መድኃኒነ እግዚእን፤ ፠ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ 7ቱን ከዋክብት /ፀሐይ አቡነ ሳሙኤልንና ሌሎች ቅዱሳንን/፤ ፠ ከ7ቱ ከዋክብት አንዱ ፀሐይ አቡነ ሳሙኤል ደግሞ ደቀ መዛሙርቶቻቸውን (አባ ተሥፋ ሐዋርያትን፥ አባ ዘሩፋኤልን፥ አባ ብንያሚን፥ አባ በኪሞስን፥ …… ሌሎች እልፍ አእላፋት መነኰሳትን አምንኵሰዋል፣ ሊቃውንትን አስተምረዋል፤ መምህራንና ደራስያንን ተክተዋል ….፤ በዚህም ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ፥ ወላዴ መምህራን ወሊቃውንት አባ ሳሙኤል በመባልም ይታወቃሉ፡፡ #አቡነ_ሳሙኤል_፤ በአኵስም ከተማ አካባቢ በ1295 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ አባታቸው እስጢፋኖስ እናታቸው ዓመተ ማርያም ይባላሉ፡፡ በአኵስም ጽዮን ከነበሩት መምህራን ከፊደል ጀምረው የቅዱስ ያሬድን ጸዋትወ ዜማና ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን ተምረዋል፡፡ ወላጆቻቸው በልጅነታቸው በሞት ተለይተዋቸዋል፡፡ ከወላጆቻቸው ሞት በኋላ ወደ ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘንድ ሔደው ደብረ በንኰል ገዳም ገቡ፡፡ በዚህም ገዳም እያገለገሉ በወቅቱ ከነበሩት ሊቃውንት የብሉያትና የሐዲሳትን ትርጓሜ እንዲሁም ሥርዐተ ምንኵስናን ተምረው ከገዳሙ አባት በአቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅ ከሌሎች 11ድ ወንድሞቻቸው ጋር አብረው መነኰሱ፤ ቆባቸውም እንደ አቡነ አረጋዊ የድንጋይ ቆብ ነበር፡፡ በዚህም ገዳም እህል ሳይበሉ ቅጠል ብቻ እየተመገቡ ይኖሩ ነበር፡፡ እግራቸው እስኪያብጥም ድረስ ይሰግዱ ነበር፡፡ **ኋላ ወደ ጣና ገብተው ከቆብ ወንድማቸው ከአቡነ ያሳይ ጋር ለ12 ዓመታት በሱባኤ ቆዩ፤ **በስተመጨረሻም ጌታችን ወደ መሠረተውና በመሃልም ጠፍ ሆኖ ወደ ነበረው ብዙ ቅዱንን፣ መምህራንን፣ ሊቃውንትንና መናንያንን ወደ ወለዱበት ዋልድባ ገዳም ገብተው ለ70 ዓመታት ያህል ከዚህ ዓለም በምናኔ ተለይተው፣ ግርማ ሌሊቱን፥ ፀብአ አጋንንቱን ፥ ድምፀ አራዊቱን፥ የሌሊቱን ቊር፥ የቀኑን ሐሩር ታግሠው፣ ረሃቡንና ጽሙን ችለው፣ መላ ዘመናቸውን በጽድቅ ጎዳና ተጕዘው በ1395ዓ.ም ታኅሣሥ 12 ቀን በዋልድባ አቴና ገዳም ዐርፈዋል፡፡ #ባርከኒ አባ እንሣእ ጸሎተከ፤ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን፤ አባ ሳሙኤል ባርከኒ እንሣእ በረከተከ፨ /ጸሎተ መሐረነ አብ/ #በታኅሣሥ ፲፪ በበዓለ ዕረፍታቸው ጊዜም፤ ሮም በጴጥሮስና በጳውሎስ ዕረፍት እንዳለቀሰች፤ ቅድስት ገዳማቸው ገዳመ ዋልድባ (ዋሊ) አልቅሳለች፨ ‹‹በከየት ወለሀወት ገዳምከ በሞትከ ዮም፤ ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ ሉያ፤ ምድረ ዋልድባ ቅድስት ሰሚዓ ዜና ሞትከ፤ እንዘ አንተ ሰብእ ምድራዊ ወመልአክ ተሠመይከ፤ ካህነ አርያም ሳሙኤል መንበረ ሥላሴ ዘአጠንከ፤ አንበሳ ወነምር ይሰግዱ ለከ፤ ወይልህሱ ጸበለ እግርከ፤ ዕንቈ ወዕጣነ ማርያም አምጽአት ለከ፤ በቅዳሴሃ ሶበ ጸለይከ፤ በከየት ወለሐወት ገዳምከ።>> እንዲል ዚቅ፨ (ሥርዐተ ማኅሌቱን ላልደረሰው ያድርሱ) በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ታኅሣሥ_12_የአቡነ_ሳሙኤል_በዓለ_ዕረፍት_ከሚከበርባቸው_ቦታዎች_ዋናዎቹ፤ ✤✤1. በሁሉም #የዋልድባ_ገዳም_ክፍልች_ (በውስጡ ባሉት 3ት ገዳማት፣ የተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት፣ ጸሎት/ስዕል/ ቤቶች፣ የአትክልት ቦታዎችና ሞፈር ቤቶች)፤ እነዚህም፤ 1.1. ዋልድባ አብረንታንት መድኀኔ ዓለም ገዳም **1.2. ዋልድባ ዳልሽህ ገዳም (ዋልድባ ዳልሽህ አባ ሳሙኤል ገዳም) **1.3. ዋልድባ ሰቋር ገዳም (የኪዳነምሕረት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስና የመድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን) **1.4. በዋልድባ አቴና (መቃብረ ሳሙኤል)፤ ሌሊቱንና ቀኑን ሙሉ ጧፍ እየበራ ገድላቸው እየተነበበ **1.5. በዋልድባ አባ ናፃ የአቡነ ተሥፋ ሐዋርያት ገዳም **1.6. በዋልድባ ደንደሮቃ ቅዱስ ሚካኤል ገዳም **1.7. በዋልድባ ማይ ለበጣ ቤተ እግዚአብሔር **1.8. በዋልድባ ማይጋባ ቅዱስ ሚካኤል ገዳም **1.9. በዋልድባ ደለሳ ቆቋ አቡነ አረጋዊ ገዳም **1.10.በዋልድባ ማይ ሃርገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም **1.11. በዋልድባ ዕጣኖ ማርያም ገዳም **1.12. በዋልድባ ዋልቅስ ኪዳነ ምሕረት **1.13. በዋልድባ አምብላ አቦ **1.14. በዋልድባ ስር ባሉ የስዕል ቤቶችና የአትክልት ቦታዎች (…..) ✤2. በተወለዱበት በርዕሰ አድባራት ወገዳማት አኵሱም ጽዮን ማርያም፤ ✤3. ምንኵስናን በተቀበሉበት በደብረ በንኰል አቡነ መድኀኒነ አግዚእ ገዳም፤ (ሽሬ አጠገብ) ✤4. በቆብ ወንድማቸው በአባ ያሳይ መንዳባ መድኀኔ ዓለም ገዳም፤ (ጎርጎራ ፥ ጣና) ✤ 5. በቆብ አያታቸው በአቡነ ተክለሃይማኖት ደብረ ሊባኖስ ገዳም በውዳሴና በቅዳሴ (በደብረ ሊባኖስ ቅዳሴ በየቀኑ በማይቀደስበት፤ በዓመት ውስጥ ጥቂት ቀናት ብቻ በሚቀደሱበት ከጥንት ጊዜ ጀምሮ የቅዳሴ ቀናቸው ከማይታጎሉ አንደኛውና ዋነኛው የአቡነ ሳሙኤል በዓለ ዕረፍት ነው) ፠፠ 5. አቡነ ሳሙኤል በመሠረቷቸውና ባስፋፏቸው ገዳማት፤ ✤5.1 #በደብረ_ዐባይ_አቡነ_ሳሙኤል_ገዳም_ /ሽሬ (እንዳባጉና) አጠገብ/ (#በኢትዮጵያ_የቅዳሴ_ዘደብረ_ዐባይ_ትምህርት_ዋና_ማስመስከሪያ)፤ እጅግ ደማቅ በኾነ ኹኔታ፡፡ ✤5.2 #በአብጠራ_(አብጠራህ) #አቡነ_ሳሙኤል_ገዳም_ /ጎንደር ፥ ደባርቅ/ (ከጎንደር ከተማ 100 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ የሚገኝ) ✤5.3 #በደብረ_ገነት_አቡነ_ሳሙኤል_ገዳም_ /አዲስ አበባ አቃቂ አጠገብ፥ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ያለበት ጋር/) በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡ ✤5.4 #በጎንደር_አዘዞ_አባ_ሳሙኤል_፡፡ ✤✤6. በተጨማሪም በስማቸው በታነጹ አብያተ ክርስቲያናት ይከበራል፤ ለአብነትም፤ በአዲስ አበባ በስማቸው በብቸኝነት በታነጸው #በቦሌ_ቡልቡላ_ምስካበ_ቅዱሳን_አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_ገዳም #በአዲስ_አበባ_ወረገኑ_ቅዱስ_ሚካኤል_እና_ጻድቁ_አቡነ_ሳሙኤል_ #በአዲስ_አበባ_ሲምሲ_ሚካኤል_(በድርብነት) #በታጠቅ_በዓለ_ወልድ_ቤ.ክ (በድርብነት ይከብራል) ፤/ ወደ መናገሻ መንገድ ሲሄዱ) #በአንጓ_ቀርነጃ_ታላቅ_ሴራ_ሳሙኤል_ #በነቀምቴ_አቡነ_ሳሙኤል_ #በዩኤስ_አሜሪካ_ቨርጂንያ_ሐመረ_ብርሃን_ቅዱስ_አባ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_ገዳም_ #ባርከኒ አባ እንሣእ በረከተከ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አባ ሳሙኤል/፫/ ባርከኒ እንሣእ በረከተከ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#እንኳን_ደስ_አለን_፤ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው #የሊቁ_የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ቤተ_ክርስቲያን_በደቡዊት_ኢትዮጵያ_ሌሾ_ማዞሪያ_፤ #ታኅሣሥ_12_ቀን 2012 ዓ.ም. የመሠረት ደንጊያ ይቀመጣል
+4
#እንኳን_ደስ_አለን_፤ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው #የሊቁ_የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ቤተ_ክርስቲያን_በደቡዊት_ኢትዮጵያ_ሌሾ_ማዞሪያ_፤ #ታኅሣሥ_12_ቀን 2012 ዓ.ም. የመሠረት ደንጊያ ይቀመጣል፡፡ #ሌሾ_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_፤ ቦታው፤ ከአ.አ. ወደ ወላይታ መንገድ፤ ወደ ዱራሜ መታጠፊያ፤ ከአደሮ ከተማ አጠገብ ሌሾ ማዞሪያ ጋር የሚገኝ፤ ሌሾ ማዞሪያ የሚገኘው፤ በደቡብ ክልል በከምባታ ጠንባሮና ሃላባ ሀገረ ስብከት፤ ከአ.አ 287 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ የሚገኝ ነው፡፡ #ብፁዓት_ከናፍረ_ዮሐንስ_እለ እምሥዕልኪ ተወደሳ፤ በቅድመ ርኵስ ንስጥሮስ በከመ ቀደሳ፡፡ አፈወ ተአምር ማርያም ጽጌ ፈርከሊሳ፤ ንሰግድ ለሥዕልኪ ወንገኒ ለንግሣ፤ ጽጌያት ዘሠረጽነ ለጥምቀት እምከርሣ፨ /ከደቂቀ አበው ገጽ የተወሰደ/

#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፬፡፡ Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ለምን እንፈተናለን፤ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋ
+1
#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፬፡፡ Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ለምን እንፈተናለን፤ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋቸው፤ …. ……እንዳያመልጣችሁ፤ በሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ በብዙ ጕባኤያት ላይ ያልተዳሰሱ ርዕሶች የሚዳሰሱበት ጕባኤ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ፤ #ደግመን_እንላለን_ይህ_ትምህርት_በፍጹም_እንዳያመልጣችሁ!!!!! ለተከታታይ ሳምንታት፤ ትምህርቱ ተከታታይነት ስላለው መቅረትና ማርፈድ አይመከርም!!፡፡ (፻፶፫ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ) #ዐርብ_ታኅሣሥ_፲፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት አሁንም በድጋሚ እንላለን ለሕይወታችን ወሳኝና በብዙ የትምህርት ጕባኤያት ላይ የማይዳሰሱ ትምህርቶች ስለሆኑ እንዳያመልጣችሁ!!!! የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

አዲስ አበ ቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ገዳም፤ በአ.አ በአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ስም የተገደመ ብቸኛው ገዳም፡፡ ታኅሣሥ 12 የአቡነ ሳሙኤል በዓለ ዕረፍት ይከበራል፡፡ ቦታው፤
+1
አዲስ አበ ቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ገዳም፤ በአ.አ በአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ስም የተገደመ ብቸኛው ገዳም፡፡ ታኅሣሥ 12 የአቡነ ሳሙኤል በዓለ ዕረፍት ይከበራል፡፡ ቦታው፤ ከሳሪስ አቦ ጀርባ ኮንደሚነየሙ ጋር፤ (ታክሲ ከሳሪስ አቦ ቡልቡላ መድኀኔ ዓለም ድረስ ይዞ በፊት ለፊት ባለው አስፋልት ገባ ሲሉ ይገኛል)

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (#ተዋስኦተ_ጳውሊ_ምስለ_ሰይጣን_)፤ #ክፍል፪_ #ሰይጣን_ምንጊዜም_ቢሆን_እንደየሰው_ምኞትና_ፍላጎት፥ #እንደ_ጊዜውና_እንደ_ሰዐቱ፥ #እንደ_ዘመኑና_እንደ_ወቅቱ_ተጨባጭ_ሁኔታ_የማሳት_ጥበቡን_እየለዋወጠ_ይጠቀማል፡፡ (ሳኦል የአማሌቃውያንን ምርኮ ባገኘበት ወቅት፣ ሐናንያ ገንዘብ በእጁ በገባበት ወቅት ሰይጣን እንደፈተናቸው ልብ ይሏል /ሐናንያ ሆይ መንፈስ ቅዱስን ታታልል ዘንድ ከመሬቱ ሽያጭ ታስቀር ዘንድ ሰይጣን በልብህ ስለምን ሞላ?፡፡›› ሐዋ. ፭፥፫/ እኛንም እንዲሁ እንደ ዘመናችን ሁኔታ መልኩን እየለዋወጠ ይፈትነናል፡፡ እርሱ የ7511 ዓመታት የመፈተን የሥራ ልምድ ያለው ነውና!!፡፡ ##መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣውና መጽሐፍ ቅዱስም የተጻፈበት ዐቢይ ጉዳይ ሰይጣን በሰው ልጆች ላይ እያደረሰ ካለው ጉዳትና ጥፋት ለመታደግና ችግሩንም በዝርዝር ለማሳወቅና ሰዎችም የሰይጣንን ክፉ ሥራ ዐውቀው እንዲርቁ ለማድረግ ነው፡፡ /‹‹የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ፡፡›› ፩ዮሐ. ፫፥፰/ ‹‹በእኔም የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፡፡›› ዮሐ. ፲፪፥፵፮ ***ነገር ግን ጌታችን ወደዚህ ዓለም በመምጣቱ፤ ሰው በመሆኑ ይህ የሕይወት ብርሃን ለዓለም ቢበራም፤ ሁሉም #ሰው ነፃ ፈቃዱን ተጠቅሞ ከዲያብሎስ ሽንገላ ለመላቀቅ ፈቃደኛ አለመሆኑን ተመልክቶ /‹‹ወደ ሕይወት የሚወስደው በር የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና የሚገቡትም ጥቂቶች ናቸው፡፡›› ብሏል ማቴ. ፯፥፲፬/ ጌታችን እንዲህ ያለው ሰዎች ነፃ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው የሰይጣንን ፈቃድ በመፈጸም በፈቃደ ሥጋቸው ስለሚመሩና የእርሱን ትዕዛዝ ለመፈጸም ደስተኛና ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ለመግለጽ እንጂ ወደ ሕይወት የሚወስደው መንገድ የሚጠብ ሁኖ አይደለም፡፡ ይህ የሕይወት መንገድ የሚሰፋው የራስ ፈቃደኝነት ሲታከልበት ነው፡፡ #ለሰው ልጅ ወደ ሕይወት ለመግባት ወሳኙ ነገር ፈቃደኝነት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ ቢሆንም የሰውን ልጅ ሲፈጥረው ነጻ ፈቃድ ያለው አድርጎ ስለፈጠረው መልካሙን ነገር ሊያደርግ በሚፈልግበት ጊዜ ፈቃደኝነታቸው ይጠይቃል፡፡ /ድውያንን ሲፈውስ ልትድን ትወዳለህን እያለ የሚጠይቃቸውን ልብ ይሏል፡፡ ዮሐ. ፭፥፮/ #የራስ ፈቃደኝነት ካለ ትእዛዛትን መጠበቅ ቀላል ይሆናል፡፡ /የዘለዓለምን ሕይወት እወርስ ዘንድ ምን ላድርግ ብሎ ለጠየቀው ሀብታም ጎልማሳ ‹‹ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ትእዛዛትን ጠብቅ … ፍጹም ልትሆን ብትወድ ሂደህ ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ፤ መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ፡፡›› ነገር ግን ሀብታሙ ጎልማሳ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ታላቅ ሐዘን ተሰምቶታል፡፡ ማቴ. ፲፱፥፳፩/ #ጽድቅ፣ ቅድስናና ሰይጣንን ማሸነፍ የሚመጣው በራስ ፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ #አንድ_ሰው_በፍጹም_ትሕትና_ትእዛዛትን_ለመጠበቅ_የራስ_ፈቃደኝነት_ካለውና_ንስሐ_ከገባ__በቀላሉ_ሰይጣንን_የሚያሸንፍበት_ኀይል_ከእግዚአብሔር_ያገኛል፡፡ ሰይጣንም የብዙ ዘመን ልምድ ስላለው ይህን ሁኔታ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ሰዎች፤ ++ሰዎች ትእዛዛትን ለመጠበቅ የራስ ፈቃደኝነት እንዳይኖራቸው የተለያየ ምክንያት በመፍጠር አጥብቆ ይዋጋቸዋል፡፡ ++ሰዎች ትእዛዛትን ሊጠብቁና ንስሐ ሊገቡ ሲያስቡ በታላቅ ፍርሃትና ስጋት እንዲያዙ ያደርጋቸዋል፡፡ ++ሰዎችን ሕግና ትእዛዛትን መፈጸም ከባድና ጭንቅ፥ በሩም የጠበበ፥ ፈጽሞም የማያሳልፍ አድርጎ ያሳያቸዋል፡፡ ++ሰዎች ትእዛዛትን የሚጠብቁና በቁርጠኝነት ንስሐ የሚገቡ ከሆነ በዚህ ምድር ላይ መኖር እንደማይችሉና ታላቅ ጉዳት እንደሚደርስባቸው ደጋግሞ በማሳሰብና በማስፈራራት ያሳምናቸዋል፡፡ … ነገር ግን በፍጹም ትሕትናና በራስ ፈቃደኝነት ትእዛዙን በመጠበቅና ንስሐ በመግባት ከዚህ ሰይጣናዊ ውጊያ ነጻ ይወጣሉ፤ ነጻ ሲወጡም በሰይጣን አሳሳቢነትና ማስፈራርት ከባድ መስሎ ይታያቸው የነበረው ትእዛዛት ለእነርሱ የደስታና የሰላም ምንጭ ይሆንላቸዋል፡፡ /ይህንንም በሐዋርያትና በቅዱሳንና ቅዱሳት ሕይወት ታውቋል ማቴ. ፲፩፥፳፰/ ከእውነተኛ (መንፈሳዊ) ሕይወት ርቀው የሚኖሩ ሰዎች በጥቂት የፈተና ሰዐት ስንኳ መታገሥና መረጋጋትን፥ ሰላማዊነትንና አስተዋንትን አጥተውና ተስፋ ቆርጠው ለከፋ ችግር የሚጋለጡት አስቀድሞ የጠጠጋቸው ሰይጣናዊ መንፈስ ስለሚያስጨንቃቸውና ስለሚያስፈራራቸው ነው፡፡ #የሰው ልጅ በምድር ላይ እስካለ ድረስ በጥንተ ጠላቱ ሰይጣን በየጊዜው መፈተኑ አይቀሬ በመሆኑ /ዘፍ. ፫፥፲፭/ ውጊያውም ከደምና ከሥጋ ጋር ሳይሆን ከጨለማ ዓለም ገዦች፣ ከአለቆችና ከሥልጣናት እንዲሁም ከረቂቃን ሰይጣናት ከዲያብሎስ ሠራዊት ጋር በመሆኑ፤ ፈተናውን ለማለፍ የሰይጣን መግቢያ የሆኑ ቀዳዳዎችን ለመድፈን እንዲያስችለው መንፈሳዊ ዝግጅት ማድረግ አለበት፡፡ ከኃጢአት ንጹሕ ሁኖ ሀብተ መንፈስ ቅዱስን ገንዘብ ያደርግ ዘንድ ስለሰይጣን አስከፊነት በእጅጉ መማርና ማወቅ፥ መረዳትና ማስተዋል ይገባዋል፡፡ +‹‹ከሚመጣው ሁሉ መዳን ትችሉ ዘንድና በሰው ልጅ ፊትም ለመቆም እንድትችሉ ሁል ጊዜ በጸሎት ትጉ፡፡›› ሉቃ. ፳፩፥፮ +‹‹ለጸሎት ትተጉ ዘንድ … ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ፡፡›› ፩ቆሮ. ፯፥፭ +‹‹የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ፡፡›› ኤፌ. ፮፥፲፩ +‹‹በመጠን ኑሩ፥ ንቁም ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፡፡›› ፩ጴጥ. ፭፥፰ +‹‹በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፤ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት፡፡›› ኤፌ. ፬፥፳፯ #አንድ ሰው ካመነና ከተጠመቀ በኋላ ስለሰይጣን ክፋትና ተንኮል ጥልቅ እውቀት ከሌለውና በመንፈሳዊ ትሩፋት የማይተጋ ከሆነ በቀላሉ ተመልሶ በሰይጣን አገዛዝ ሥር ይወድቃል፡፡ ከዚያ በኋላም ሕይወቱ በእጅጉ የከፋ ይሆንበታል፡፡ /‹‹ርኩስ መንፈስ ከሰው ከወጣ በኋላ ዕረፍት ለማድረግ ፈልጎ ውኃ ወደሌለበት ምድረ በዳ ይዞራል፤ አያገኝም፡፡ ከዚህም በኋላ እንግዲህስ ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል፡፡ በመጣም ጊዜ ባዶ ሁኖ ተጠርጎና ተጊጦ ያገኘዋል፤ ከዚህም በኋላ ይሄዳል፤ ከእርሱም የሚከፉ ሌሎች ሰባት አጋንንትን ያመጣል፤ ገብተውም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያም ሰው የኋላ ኑሮው ከፊተኛው የከፋ ይሆናል፡፡›› ማቴ. ፲፪፥፵፫ ‹‹በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርሷ ተጠልፈው ከተሸነፉ ከፊተኛው ኑሯቸው ይልቅ የኋለኛው ኑሯቸው የባሰና የከፋ ይሆንባዋቸዋል፡፡›› ፪ጴጥ. ፪፥፳/፡፡ ሰዎች ዳግመኛ በሰይጣን ሽንገላ ተታለው በዓለም ርኵሰት እንዳይወድቁ የሚረዳ እውቀት ማግኛ የሚሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብና ማወቅ እንዲረዳ መምህረ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ ፲፭፥፬ ላይ .. መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፏልና ብሎ እንደተናገረው፤ ርዕሰ ባሕታውያውን ቀሲስ ቅዱስ አባ ጳውሊ ከሰይጣን ጋር ያደረገውን ምልልስ ከብራና ገልብጠው ከግእዝ ወደ አማርኛ የሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም አሳተመው፡፡ #ቀሲስ_ጳውሊ_ወደ_ጭፈራ_ቤት_የሚሄዱትን_ሰዎች_የሚያስተውን_ሰይጣን_በዙ_ጥያቄዎችን_ሊጠይቀው_እንደገዘተው፤ #ሰይጣን_ሰዎችን_እንዴት_እንደሚፈትንና_ኃይል_እንዴት_እንደሚያገኝ_፤ #ክፍል_፫ _.… #ይቀጥላል_ይጠብቁን_/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

የጠቅላላ ጕባኤ ጥሪ፤ ለአባላት በሙሉ፡፡ ቅዳሜ ታኅሣሥ 11 ከቀኑ በ10 ሰዐት ከደብራችን ሰበካ ጕባኤ ጋር፤ ፠ በመማር ማስተማር፣ ፠ በአገልግሎት አሰጣጥና ፠ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ስብሰባ ስላለን
የጠቅላላ ጕባኤ ጥሪ፤ ለአባላት በሙሉ፡፡ ቅዳሜ ታኅሣሥ 11 ከቀኑ በ10 ሰዐት ከደብራችን ሰበካ ጕባኤ ጋር፤ ፠ በመማር ማስተማር፣ ፠ በአገልግሎት አሰጣጥና ፠ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ስብሰባ ስላለን ሁላችሁም እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ ፠ (በዕለቱ ዝክረ ቅዱስ ያሬድም አብሮ የሚካሄድ ይሆናል፡፡) ፠ (ጥሪውን ላልሰሙ በስልካችሁ በመደወል፣ LIKE, SHARE በማድረግ አስተላልፉ!!)፡፡ ፠•፠ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ወይም https://www.facebook.com/kechenemedihanaelem.finotehiwot ወይም FINOTE HIWOT ፠•፠ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ FINOTE HIWOT ወይም https://t.me/medihanaelem

ታኅሣሥ 7/2012 ዓ.ም. ‹‹የዜማ ቀን ክብረ በዓል›› በአ.አ. ደብረ ይባቤ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲህ ተከብሮ ውሏል፡፡ ይህን ሁሉ ላደረገ ለመድኀኔ ዓለም ክብር ይሁን፡፡ ‹‹..... ልጅ የለኝም፤
+4
ታኅሣሥ 7/2012 ዓ.ም. ‹‹የዜማ ቀን ክብረ በዓል›› በአ.አ. ደብረ ይባቤ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲህ ተከብሮ ውሏል፡፡ ይህን ሁሉ ላደረገ ለመድኀኔ ዓለም ክብር ይሁን፡፡ ‹‹..... ልጅ የለኝም፤ የእኔ ወራሼ ቅዱስ ያሬድ ነው..›› /ክብርት ወ.ሮ. ደስታ ሞላ (ወለተ ማርያም)/፤ የአ.አ. ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ጽላት ከቡልጋ አስመጥተው በግላቸው ቦታ ላይ ከ948-1952 ዓ.ም. ቤተ ክርስቲያንኑ የተከሉ ታላቅ እናት፡፡

#ወአርአይከኒ_ፍኖተ_ሕይወት (#የሕይወትን_መንገድ_አሳየኸኝ_፡፡) መዝ. ፲፭፥፲፩ ፠•፠ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያ
+3
#ወአርአይከኒ_ፍኖተ_ሕይወት (#የሕይወትን_መንገድ_አሳየኸኝ_፡፡) መዝ. ፲፭፥፲፩ ፠•፠ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ወይም https://www.facebook.com/kechenemedihanaelem.finotehiwot ወይም FINOTE HIWOT ፠•፠ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ FINOTE HIWOT ወይም https://t.me/medihanaelem (ገጾቻችንን ለሌሎችም ያስተዋውቁልን፡፡)

ታኅሣሥ 7/2012 ዓ.ም. ‹‹#የዜማ_ቀን_ክብረ_በዓል_›› ንዑ ንሑር ኀበ ደብረ ይባቤ፤ ዛሬ ታኅሣሥ 7/2012 ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዱስ ያሬድ ዜማ በቤተ ክርስቲያናችን አገልግሎት የተጀመረበትን በማስመልከት፤ ‹‹#የዜማ_ቀን_ክብረ_በዓልን_›› #በደብረ_ይባቤ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤ/ክ #ለመጀመሪያ_ጊዜ_ክብረ_በዓሉ_ታቦቱ_ወጥቶ_ይከበራል_፡፡ (አድራሻ፤ ጎተራ ከአጎና ሲኒማ ከ,ወደ መስቀል ፍላወር በሚወስደው መንገድ፡፡) ፠ (#ቅዱስ_ያሬድን_ያልዘከረ_ኢትዮጵያዊ_ምኑን_ኢትዮጵያዊ_ኾነ!?) ፠ (#ቅዱስ_ያሬድን_ያልዘከረ_ካህን_ምኑን_ካህን_ኾነ!?) ፠ (#ቅዱስ_ያሬድን_ያልዘከረ_ሰንበት_ተማሪ_ምኑን_ሰንበት_ተማሪ_ኾነ!?) ፠ ጥዑመ ልሳን፤ ፠ የሱራፌል አምሳያ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን እንዚራ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን፤ ፠ መዓርዒረ ዜማ፤ ፠ ካህን (ካህነ ስብሐት) ፠ ማኅሌታይ፤ ፠ መዘምር ዘበድርሳን፤ ፠ ሊቅ (ርእሰ ሊቃውንት) ፠ ዓርከ ሊቃውንት፤ ፠ ደራሲ፤ ፠ የመጽሐፍ መምህር፤ (ብሉያትንና ሐዲሳትን የሊቃውንትንም መጻሕፍት አስማምቶ የተረጐመ) ፠ ባለቅኔ (የቅኔ ጀማሪ)፤ ፠ የቤተክርስቲያን ጌጧና መሠረቷ ሕይወቷና እስትንፋሷ ፠ ልዑለ ስብከት፤ ፠ ሰማዕት፤ ፠ ባሕታዊ፤ ፠ መናኝ ፠ የዜማ አባት፤ ፠ የኢትዮጵያ ብርሃን፡፡ ፠ አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም) የኾነ:: ፠ እግሮቹ በመልካም መንገድ የሚጓዙና ወደ መልካም መንገድ የሚያስጕዙ ፠ ልቡናው የቅድስና ማኅደር የኾነ:: ፠ ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ የኾነ:: ፠ አእምሮው የመጠቀ፤ ፠ ድርሰቱ የተራቀቀ፤ ፠ እስከ አርያም ተነጥቆ ዕፁብ ድንቅ ምሥጢራትን የተመገበ፤ …… ማን እንደርሱ:: …... •፠ሃሌ ሉያ ንዑ ንትፈሣህ በመኃልይሁ፤ ወንንግር ለካህን ውዳሴሁ፤ ከመ ሱራፌል ለያሬድ ክላሁ፤ ለክርስቶስ ሰበከ ትንሣኤሁ፤ ማኅበረነ ይባርክ በእዴሁ፡፡ •፠ሶበ ኤዶምሃ መሠጥዎ፥ ግናየ ትንሣኤ መልዕዎ፤ ለያሬድ ካህን አስተብፅዕዎ፡፡ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ታኅሣሥ_6_የአርሴማ_ቅድስት_ወሰማዕትና_የእርሷ_ማኅበርተኞች_ድል_አድራጊዎች_27_ሰማዕታት_ሥጋቸው_በክብር_የፈለሰበትና_ቤተ_ክርስቲያኗ_ቅዳሴ_ቤት_የተከበረበት_ዕለት ነው፡፡ 1ኛ. አርሴማ፤ ቅድስት ወሰማዕት ኃያል ተጋዳሊት 2ኛ. ኢያሚኖስ፤ ጸሎትን የሚያሳርግ ካህን 3ኛ. አፍጢኖስ፤ ከብዙዎች የተመረጠ 4ኛ. በርቲኖስ፤ ጻድቅና ቸር 5ኛ. ጢሞና፤ በመላላክ ሥራ አገልጋይ የኾነ 6ኛ. ጢሞዓና፤ ተአጋሽና ጸዋሚ 7ኛ. ዘኬዎስ፤ ከከበሩ የከበረ 8ኛ. እስጢፋኑ፤ ተጋዳይና የበደሉትን ይቅር ባይ 9ኛ. አርሞና፤ ከጎልማሶች ይልቅ ደም ግባቱና መልኩ ያማረ 10ኛ. ኪርያኮስ፤ ሥጋውን ያላረከሰ ንጹሕ 11ኛ. አንጥያኮስ፤ ቡሩክ የኾነ የአቡሪ ልጅ 12ኛ. ያዕቆብ፤ የእግዚአብሔር ታማኝ የኾነ 13ኛ. ቡራኬሌስ፤ በሰው ዘንድ ተወዳጅ የኾነ 14ኛ. አስቂርያቆስ፤ ክርስቶስን የሚወደው 15ኛ. አስኪርያኖስ፤ ባለሟል የኾነና ግርማው የሚያስፈራ 16ኛ. ሚርያኖስ፤ ፊቱና መልኩ ደስተኛ የኾነ 17ኛ. ትትግርጦስ፤ ወደ ንስሐ የተመለሰ 18ኛ. ያስቲኖስ፤ የሚፈርድና የሚበይን 19ኛ. ጥልያኖስ፤ ያላመኑ ሰዎችን የሚገስጽ 20ኛ. ዑልያኖስ፤ የዚህ ዓለም ጥበብ መምህር የኾነ 21ኛ. ጴርቅላስ፤ በስም አጠራርና በሽምግልና መልካም የኾነ 22ኛ. ኬብያኖስ፤ ተጋዳይ የኾነ 23ኛ. ጴጥሮስ፤ የጠራ የባሕርይ ዕንቊ 24ኛ. ጰኵንዮስ፤ የሮምያ ሹም 25ኛ. ሐናንያ፤ የዋህና ሽንገላ የሌለው 26ኛ. ሐሊባኖስ፤ ጾምና ጸሎትን የሚወድ 27ኛ. ኤስያኖስ፤ በመንፈስ ቅዱስ ጎልማሳ የኾነ 28ኛ. ኤልያብ፤ በረኛና የሰማዕት መጀመሪያ፡፡ ሰላም ለዘአዕረፉ ምስሌኪ ፳ወ፯ቱ ሰማዕታት፤ ረድኤቶሙ ትረድ ላዕሌየ ዘምስለ ብዙኅ ምሕረት፡፡ ወኀበ ሀለወ ስሞሙ ምስለ ስምኪ ቅድስት፤ ዓዲ ኢይቅረብ አርሴማ ሕማመ ብድብድ ወሞት፤ በኵሉ አዝማን ወበኵሉ ዓመታት፡፡ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem