uk
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Відкрити в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 380 підписників, посідаючи 5 579 місце в категорії Релігія і духовність та 2 192 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 380 підписників.

За останніми даними від 08 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 38, а за останні 24 години на 2, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 22.59%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 9.42% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 476 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 449 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 20.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 09 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

15 380
Підписники
+224 години
-87 днів
+3830 день
Архів дописів
፠ #የማንቂያ_ደወል_፤ (ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያናችንና የሃገራችንን ሁኔታ የምንማርበት፤ በቅርቡ ሰማዕታት የሆኑትን በብርሃን (በጧፍ የምናሰብበት) ፠ ዐርብ የካቲት 6/2012 ዓ.ም. ፠ በቦሌ ደብረ
+3
፠ #የማንቂያ_ደወል_፤ (ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያናችንና የሃገራችንን ሁኔታ የምንማርበት፤ በቅርቡ ሰማዕታት የሆኑትን በብርሃን (በጧፍ የምናሰብበት) ፠ ዐርብ የካቲት 6/2012 ዓ.ም. ፠ በቦሌ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወዮሐንስ መጥምቅ፡፡ ፠፠፠ የአቤልን የግፍ ሞት፤ የዘካርያስን በግፍ መገደል የተበቀለ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በቤተ ክርስቲያናችንና በምዕመኗ ላይ የደረሰውን ግፍ፣ ቅትለት (ግድያ)፣ ማስፈራሪያ፣ ዛቻ፣ ሥልጣንን ተገን በማድረግ የሚሠራ ደባ፣ ሙስና፣ ……. እርሱ ይበቀልልን፤ እርሱ ፍርዱን ይስጥ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

በዮሐንስ ራዕይ ምዕራፍ 12 ያለውን ኀይለ ቃል መሠረት በማድረግ በ19090ዎቹና 2000ዎቹ (ከ10ር ዓመታት በላይ) በታላቁ ደብር በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ.ክ. የዐርብ ሠርክ ጕባኤ ላይ፤ እንደ ዕንቊ ፈርጥ ያስተማረከን ፥ በርካቶችን ከባዕድ አምልኮ ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር የመለስከውን፥ ከአሕዛብነት ወደ ሕዝብነት የቀየርከውን ፥ … መምህራችን ምሕረት አብን መቼም ቢሆን አንረሳህም፤ *የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም መንገድህን ሁሉ ያቅናልህ፤ *በሰላምና በጤና ፤ በፍቅርና በአንድነት እድሜህን የተባረከ ያድርግልህ፤ **በማስተዋልና በጥበብ መንገድ ሁሉ ይምራህ፡፡ *ጠላቶችህን ከእግርህ በታች ይጣልልህ፤ *የመንግሥትን ሥልጣን መከታ አድርገው ግፍ ለማድረግ ፥ መንገድህን ለማሰናከል ፥ የሚሠሩትን ግፍ እንዳይጋለጥባቸው የሚሯሯጡትን ሁሉ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ቀድሞ ሐሳባቸውንና ሥራቸውን ሁሉ እንደ ሰናዖር ግንብ ያፍርሰው፥ የተመኩበትን ሥልጣንና ሹመት እንደ ዐመድ ጠፍ ያድረገው፡፡ *እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ ማርያም ድንግል በሕይወትህ ሁሉ ከአንተ አትልይ፡፡ * ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልና ቅዱስ ሚካኤል ከፊትህ መሪ፥ ከኋላ ከለላ፥ ከጎን ድጋፍ፥ ከላይ ጥላ ከለላ፥ ከሥር መሠረት ይሁኑህ፡፡ *ሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከዓን ጥቅሻ በሚፈጥን ደራሽነቱ ይድረስልህ፤ የስብከት ጕዞህን ለማሠናከል የሚነሱትን ሁሉ ሐሳባቸውንና ክፋታቸውን እንደ ጉም ያብነው፤ እንደ ጢስም ይበትነው፤ እንደ አቧራም ዝርው ያድርገው፡፡ *ገብረ ክርስቶስና አረጋዊ፤ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔርና ቶማስ ዘመርዓስ፤ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራና አቡነ ተክለ ሃይማኖት አማላጅ ረዳት፤ አጋዥ ፤ … ይሁኑህ፡፡ ፠ ‹‹በሰማይም ሰልፍ ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉ። ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ፥ አልቻላቸውምም፥ ከዚያም ወዲያ በሰማይ ስፍራ አልተገኘላቸውም። ፠ ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ። ፠ ታላቅም ድምፅ በሰማይ ሰማሁ እንዲህ ሲል፦ አሁን የአምላካችን ማዳንና ኃይል መንግሥትም የክርስቶስም ሥልጣን ሆነ፥ ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሏልና። ፠ እነርሱም ከበጉ ደም የተነሣ ከምስክራቸውም ቃል የተነሣ ድል ነሡት፥ ነፍሳቸውንም እስከ ሞት ድረስ አልወደዱም። ስለዚህ፥ ሰማይና በውስጡ የምታድሩ ሆይ፥ ደስ ይበላችሁ፤ ለምድርና ለባሕር ወዮላቸው፥ ዲያብሎስ ጥቂት ዘመን እንዳለው አውቆ በታላቅ ቍጣ ወደ እናንተ ወርዷልና። ፠ ዘንዶውም ወደ ምድር እንደ ተጣለ ባየ ጊዜ ወንድ ልጅ የወለደችውን ሴት አሳደዳት። ፠ ከእባቡም ፊት ርቃ አንድ ዘመን፥ ዘመናትም፥ የዘመንም እኵሌታ ወደ ምትመገብበት ወደ ስፍራዋ ወደ በረሀ እንድትበር ለሴቲቱ ሁለት የታላቁ ንሥር ክንፎች ተሰጣት። ፠ እባቡም ሴቲቱ በወንዝ እንድትወሰድ ሊያደርግ ወንዝ የሚያህልን ውኃ ከአፉ በስተ ኋላዋ አፈሰሰ። ፠ምድሪቱም ሴቲቱን ረዳቻት፥ ምድሪቱም አፍዋን ከፍታ ዘንዶው ከአፉ ያፈሰሰውን ወንዝ ዋጠችው።›› /የዮሐንስ ራዕይ 12/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ሠናይ ዜና፤ ይበል ነው፡፡ ፠ የካቲት ፱ኝ/፳፻፲፪ ዓመተ ምሕረትንና ኅዳር ፱ኝ/፫፻፳፭ ዓመተ ምሕረትን ታሪክ ሊያገናኛቸው ነው፡፡ ፠ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጕባኤ በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያናችን ጉዳይ ላይ ለመነጋገር ለሰኞ የካቲት 9 ቀን 2012 ዓ.ም አስቸኳይ የስብሰባ ጥሪ ማድረጉን ቋሚ ሲኖዶስ ገልጿል፡፡ ፠ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም በጥበብና በማስተዋል መንገድ ይምራችሁ፡፡ ፠ ‹‹በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፡፡›› /የሐዋርያት ሥራ 20፥28/ ፠ ቋሚ ሲኖዶስ ማለት፤ ፯ት አባቶችን (ቅዱስ ፓትርያርኩን በሰብሳቢነትና በቋሚነት፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊን በጸሐፊነት ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅን በአባልነት እንዲሁም በየወቅቱ የሚፈራረቁ ተጨማሪ 4ት አባቶች ጳጳሳትን ያቀፈ)ና በየሳምንቱ 2ት ጊዜ ስብሰባ በማድረግ ከሃገረ ስብከትና ከጠቅላይ ቤተ ክህነት በላይ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ውሳኔን የሚያስተላልፍ የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር ሰጪ አካል ነው፡፡ ፠፠ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጕባኤ፤ ማለት በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉ የኤጲስ ቆጶሳ፣ ጳጳሳት፣ ሊቃነ ጳጳሳትና፣ ፓትርያርክ በአንድነት የሚያደርጉት ስብሰባ ሲሆን ከቋሚ ሲኖዶስ በላይ የሆኑ ነገሮች ላይ ውሳኔን የሚሰጥና ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክም በላይ የቤተ ክርስቲያናችን የበላይ አካል ነው፡፡ በመደበኛነት በዓመት 2ት ጊዜ (በጥቅምት 12 በሐዋርያው ቅ/ማቴዎስ በዓለ ዕረፍትና በርክብ ካህናት /ትንሣኤ በዋለ በ25ኛው ቀን/) የሚደረግ ሲሆን፤ አስቸኳይ ጉዳዮች ሲያጋጥሙና ሲከሰቱ ለቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ መግቦት ሲባል አቸኳይ ስብሰባ ያካሄዳል፡፡ ፠፠፠ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም እንደ ኀጢአታችን ሳይቈጥር ስለ እናታችን ማርያምና ስለ ቅዱሳን መላእክት፤ ስለ ቅዱሳንና ቅዱሳት ነቢያት ወሐዋርያት ፥ ጻድቃን ወሰማዕታት፥ ደናግል ወመነኰሳት፥ መምህራን ወሊቃውንት፥ ጳጳሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ብሎ ተለምኖ መልካሙን ነገር ሁሉ ያሰማን ፥ ያሰማችሁ፨ *+* ‹‹ሰላም ወፍቅር ኮነ ለቤተ ክርስቲያን ወለኵሎሙ እለ ይነብሩ በዝንቱ ሥርዐት (ሰላምና ፍቅር ለቤተ ክርስቲያንና በሥርዐቷም ጸንተው ለሚኖሩ ሁሉ ሆነ፡፡)›› /ቅዳሴ አትናቴዎስ፤ ዲድስቅልያ፤ ሉቃ. 2፥14 ገላ. 6፥16) ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

‹‹ሊቃውንትን ጠይቅ ያስታውቁህማል፤ አባትህን ጠይቅ ይነግርሃል፡፡›› (ተሰአሎ ለአቡከ ወይነግረከ፤ ወለሊቃውንቲከ ይዜንዉከ፡፡›› /ዘዳ. ፴፪፥፯/ ልዩ ዓመታዊ ጕባኤ በጾመ ነነዌ (#ከየካቲት 2-4)
+1
‹‹ሊቃውንትን ጠይቅ ያስታውቁህማል፤ አባትህን ጠይቅ ይነግርሃል፡፡›› (ተሰአሎ ለአቡከ ወይነግረከ፤ ወለሊቃውንቲከ ይዜንዉከ፡፡›› /ዘዳ. ፴፪፥፯/ ልዩ ዓመታዊ ጕባኤ በጾመ ነነዌ (#ከየካቲት 2-4) ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ፤ እንደ አምላክ ፈቃድ ዐበይት ሊቃውንት መምህራን የሚገኙበት እንደ አምናውና ካችአምናው ተዘጋጅቷል፡፡ በጽርሐ ጽዮን ጰራቅሊጦስ ቤ.ክ. (ኋላ ጎላ ቅዱስ ሚካኤል በሚል እየተጠራ በሚገኘው) ቦታው፤ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አጠገብ፡፡ (መርካቶ ተክለ ሃይማኖት ጀርባ፡፡)

የጾመ ነነዌ የጸሎተ ምሕላና የትምህርት መርሐግብር ሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍኖተ ሕይወት እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ እያለ ሱባኤውን አስመልክቶ ከየካቲት 2-4 (ከሰኞ - ረቡዕ) ጠዋትና
የጾመ ነነዌ የጸሎተ ምሕላና የትምህርት መርሐግብር ሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍኖተ ሕይወት እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ እያለ ሱባኤውን አስመልክቶ ከየካቲት 2-4 (ከሰኞ - ረቡዕ) ጠዋትና ማታ ልዩ የጸሎትና የትምህርት መርሐ ግብራትን አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል፡፡ ከሰኞ እስከ ረቡዕ ጠዋት ጠዋት፤ ከ12፡00 - 1፡00 ሰዐት የማኅበር ጸሎት ከሰኞ እስከ ረቡዕ ማታ ማታ፦ ማታ ከ12፡00 - 2፡00 ሰዐት የምሕላ ጸሎትና ትምህርት በመርሐግብራቱ ላይ በመሳተፍ በረከት ይካፈሉ ፥ መንፈሳዊ ሕይወትዎን ያሳድጉ፡፡

፠ ‹‹ ልጆቼ የእኛ ሰማዕትነትና ውጊያ በላያችን ካሉ ነገሥታት ጋር ነው፤ ፠ የእኛ ሰማዕትነት ከምኞቶቻችን ጋር ነው፤ ፠ የእኛ ሰማዕትነት ከስግብግብነት፥ ከእንቅልፍ ፥ ከዋዛ ፈዛዛ ፥ ከስንፍና ፥
፠ ‹‹ ልጆቼ የእኛ ሰማዕትነትና ውጊያ በላያችን ካሉ ነገሥታት ጋር ነው፤ ፠ የእኛ ሰማዕትነት ከምኞቶቻችን ጋር ነው፤ ፠ የእኛ ሰማዕትነት ከስግብግብነት፥ ከእንቅልፍ ፥ ከዋዛ ፈዛዛ ፥ ከስንፍና ፥ ከውሸት ፥ ከሐሜት ጋር ነው፤ ፠ የእኛ ሰማዕትነት በጧት ተነሥቶ ለጨዋታ ለተርታ ነገር ሳይሆን ለጸሎት ፥ ለስግደት ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ነው፤ ፠ የእኛ ሰማዕትነት ወንበራችን እስኪጎደጕድ ድረስ ፊልም ማየት ሳይሆን ቃለ እግዚአብሔር ማንበብና ማዳመጥ ነው፡፡ ፠ ፠ ፠ … ስለዚህ ልጆቼ ነፍሳችንን ከአምላኳ ጋር ከሚያጣሉ ደግሞም ለጊዜው ሳይሆን ለዘለዓለም ከሚለይዋት ፍላጎቶቻችን ጋር እንጋደል፡፡ /ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/ ፠ #ክርስቲያንን_መግደል_ይቻል_ይሆናል፤ #ክርስትናን_መግደል_ግን_አይቻልም_!!፤ ፠ #ሰባኪን_ማጥፋት_ይቻላል፤ #ስብከትን_ግን_ማጥፋት_አይቻልም፡፡ ፠ ክርስቲያኖችን ማሠር ይቻላል፤ ወንጌሉን ግን ማሠር አይቻልም፡፡ ፠ #ካህናትን_መግደል_ይቻል_ይሆናል፤ #ክህነትን_ግን_መግደልና_ማጥፋት_አይቻልም፡፡!! ፠ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያንን ማፍረስና ማቃጠል ይቻል ይሆናል፤ የቤተ ክርስቲያንን መሥራች ክርስቶስን ግን ማፍረስና ማቃጠል አይቻልም፡፡!! …. ምክንያቱም፤ ቤተ ክርስቲያንን አምላካችን ሞቶ በመኖር ላይ በክቡር ደሙ ስለመሠረታት ነው!!!፡፡ ሰ.ት.ቤት፡፡/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

የነነዌ ሰዎችም ኃጢአታቸውን አምነው (ከኃጢአቱ የሌሉበትም ቢሆን መከራው ስለማይቀርላቸው) ከመሪ እስከ ተመሪ፤ እንደ አንድ ልብ መካሪ፥ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሁነው፤ ንጉሡም በከተማዋ የጾም አዋጅ አስነግሮ፥ ከዙፋኑ ወርዶ፤ ሕዝቡም ማቅ ለብሰው፥ አመድ ነስንሰው፥ በፍጹም ልባቸው አዝነው አልቅሰው፥ ሕፃናት ከጡት፥ ከብቶችም ከሣር መሠማራት ተከልክለው፥ ያለምግብ በበረት ተዘግተው፤ ጾሙንም በልባዊ ጸጸት፥ ራስን ዝቅ በማድረግና በማዋረድ ንስሓ ገቡ /“የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ” ዮናስ 3፡5 ‹‹... ለጾም ዐዋጅ ነገሩ፤ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ፡፡ ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፡፡ እርሱም ከዙፋኑ ተነሥቶ መጎናጸፊያውን አወለቀ፤ ማቅም ለበሰ፤ በአመድም ላይ ተቀመጠ...” ዮናስ 3፥5-9፡፡/ እንዳለ ከአምላካችን ምሕረትን አገኙ፡፡ ነቢዩ ዮናስም ይህን አይቶ በየዋሕነቱ ‹‹እንግዲህማ ሊምራቸው ነው፣ እኔም ሐሰተኛ ነቢይ ልባል ነው›› ብሎ እያዘነና ከሕይወት ሞት ይሻላል ነፍሴን ከእኔ ውሰድ እያለ ከከተማ ወጥቶ ዳስ ሠርቶ ተቀመጠ፡፡ እግዚአብሔርም በውኑ ትቆጣ ዘንድ ይገባሃልን አለው፡፡ /ዮናስ. 4፥3-11/ አምላካችን መሐሪ በመሆኑ /አባት ለልጆቹ እንደሚራራ እንዲሁ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ይራራል ፍጥረታቸውን እሱ ያውቃልና መዝ. 102፥8-14፡፡ ጥበብ 3፡፡/ ብለዋል፤ አምላካችንም /እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን ካወቃችሁ በሰማይ ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን አይሰጣቸው ብሏል ማቴ. 7፥12/ ቀጥሎም ነቢዩ ዮናስ እንቅልፍ እንቅልፍ ብሎት ተኝቶ ቢነቃ ከራስጌው ቅል በቅላ ፀሐይ ስትከለክልለት አየና እጅግ ደስ አለው፡፡ ሁለተኛም ተኝቶ ቢነሣ ቅሏ ጠውልጋ፥ ደርቃ አገኘና አዘነ፡፡ እግዚአብሔርም ‹‹አንተ ላልተከልካትና ውኃ ላላጠጣሃት ቅል እንዲህ ስታዝን እኔስ በዝናም አብቅዬ፥ በፀሐይ አብስዬ ለምመግባቸው ሕዝቤ አላዝንምን?›› አለው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር የዮናስን ፈቃዱን ይፈጽምለት (ሐሳዊ ነቢይ እንዳይሉት) ለምልክት እንዲሆን በሦስተኛው ቀን እሳት ከሰማይ ወርዶ ከፍ ከፍ ያሉትን ዕፅዋት ጫፍ ጫፋቸውን በልቶ ተመልሷል፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ዮናስ በቀሪ ዘመኑ ፈጣሪውን እያገለገለ ኑሮ፤ በመልካም ሽምግልና በ170 ዓመት እድሜም መስከረም 25 አርፏል፡፡ ዮናስ በሕይወት ሥጋ ሣለ ሰማርያንና ነነዌን ብቻ ነበር ያስተማረው፤ ከሞተ በኋላ ግን ዛሬ ዓለምን የሚያስተምር ነቢይ ነው፡፡ /ከጾሙ ረድኤት በረከት ይክፈለን፤ የቀ.ደ.ሰ. መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት፡፡/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ጾመ ነነዌ፤ ከየካቲት 2-4 (ከሰኞ-ረቡዕ) #ነነዌ በጤግሮስ ወንዝ ምሥራቃዊ ቆሬ፥ ከዛሬዋ የሞሱል ከተማ በተቃራኒ ከባግዳድ በሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ 350 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የነበረች ታላቅ ከተማ ነች፡፡ ነነዌን በመጀመሪያ የቆረቆራት ናምሩድ ነው፡፡ /ዘፍ. 10፥11/ በጣም ሰፊ ነበረች “የቅጥሯም ዙሪያ በእግር የሦስት ቀን መንገድ ያህል ነበረ” /ዮና. 3፥3/ እግዚአብሔር አምላካችን ነነዌን “ታላቂቱ ከተማ” በሚል ቅጽል ጠርቷል፤ /ዮናስ 3፥2፤ 4፥11/ ስለ መጥፋቷ ነቢዩ ሶፎንያስ “...ነነዌንም ባድማ እንደ በረሃም ደረቅ ያደርጋታል” በማለት ትንቢት ተናግሮባታል፡፡ /ትን. ሶፎ 2፥13/፡፡ እንደ ነቢያቱ ትንቢት ታላቋ ነነዌ ከ300 ዓመታት በኋላ ጠፍታለች፡፡ የነነዌ ሰዎች በስብከተ ዮናስ አምነው፥ ንስሐ ገብተው ድነዋል፤ በዚህም ጌታችን በወንጌል ላይ ስለ ንስሓቸውና ስለ እምነታቸው /‹‹...የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፡፡›› በማለት አመስግኗቸዋል፡፡ ማቴ 12፥41/ #ዮናስ_ነቢየ_አሕዛብ_ወሕዝብ ዮናስ ማለት ርግብ፥ የዋኅ ማለት ነው፡፡ በዳግማዊ ኢዮርብአም ዘመነ መንግሥት /825-784 ቅ.ል.ክ./ በሰማርያ የነበረ ነው፡፡ /2ነገሥ. 14፥25/፡፡ ቊጥሩ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ነው፡፡ ነገዱ ከነገደ ይሳኮር ወገን ሲሆን፤ #አባቱ_አማቴ_እናቱም_ሶና(የሰራፕታዋ ደግ ሴት የሆነችውና ቅዱስ ኤልያስን በዚያ በረሃብ ዘመን የመገበችው ናት)፡፡ ኤልያስ በረሃቡ ዘመን ወደ ሰራፕታዋ መበለት ቤት በመሄድ "ውኃ አጠጪኝ ጥቂት ቁራሽም አምጪልኝ" አላት፡፡ ‹‹ሕያው እግዚአብሔርን እፍኝ ዱቄት አለችኝ ጋግሬያት አንተም እኔም ልጄም (ዮናስ) በልተናት እንሞታለን›› አለችው፡፡ ኤልያስም "የረሀቡ ዘመን እስኪያልፍ ይበርክት" አላት፤ ከቤቷ ብትገባ ዱቄቱ በማድጋው፣ ዘይቱ በማሰሮው መልቶ አገኘች፡፡ ከጥቂት ጊዜም በኋላ ልጇ ዮናስ ታሞ ሞተ፡፡ እናቱም ሄዳ ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን "ሳይገባኝ ከቤቴ ገብተህ ኀጢአቴን ተመራምረህ ልጄን ትገድልብኝ?" አለችው፡፡ ነቢዩ ኤልያስም ወደ አምላኩ ሰባት ጊዜ ጸሎት አድርሶ ዮናስን ከሞተ በኋላ አስነሥቶታል፡፡ ዮናስ ትንሽ ከፍ ባለ ጊዜም ከነቢያት ጓደኞቹ አብድዩና ኤልሳዕ ጋር ሆነው የታላቁ ነቢይ የኤልያስ ደቀ መዛሙርት ሆኑ፡፡ /1ነገ.17፥1-24፤ 18፥10-24/ ነቢዩ ኤልያስ ካረገ በኋላ ደግሞ ሁሉም በተሰጣቸው አገልግሎት ተሠማርተው እግዚአቤሔርን አገለገሉ፡፡ ነቢዩ ዮናስ አርባ ዓመት ሲሞላው ሀብተ ትንቢት ተሰጥቶት ማስተማር ጀመረ፡፡ የሰማርያውን ንጉሥ ኢዮርብአምን ጠቃሚ ምክር በመለገስ የእሥራኤልን ድንበር ከሔማት እስከ ዐረብ ባሕር ድረስ እንዲይዝ አድርጎታል፡፡ /2ነገሥ. 14፥25/፡፡ ነቢዩ ዮናስ ምንም እንኳን የእስራኤል ነቢይ ቢኾንም ከምድረ እስራኤል ውጪ በነነዌ ስላስተማረ #ነቢየ አሕዛብ ወሕዝብ ይባላል፡፡ የትንቢት መጽሐፉም ዋና መልእክት እግዚአብሔር የእስራኤል ብቻ ሳይሆን የአሕዛብም አምላክ እንደሆነና በንስሐ ወደ እርሱ የተመለሱትን ሁሉ በምሕረት እንደሚጐበኝ ማሳየት ነው፡፡ #ዮናስና_ነነዌ_ የነነዌ ሰዎች ኀጢአት ከመሥፈርቱ በማለፉ፤ የእግዚአብሔር ቃል ወደ አማቴ ልጅ ወደ ዮናስ መጣ “ተነሥተህ ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፤ የክፋታቸውም ጩኸት ወደ ፊቴ ወጥቷልና ለእነርሱ ስበክ” አለው፤ ዮናስ ግን የፈጣሪው መሐሪነት፥ ቸርነት መስፈርት እንደሌለው ያውቃልና፤ እርሱ ቢምራቸው ማን ለቃሉና ለትንቢቱ ይገዛል፤ እኔም ሐሰተኛ ነቢይ ልባል አይደለምን? ብሎ አልሔድም አለ፤ እግዚአብሔር እየደጋገመ ሲናገረው ግን ዮናስ የዋሕ ነበረና እንዲህ የሚዘበዝበኝ ከፊቱ ብቀመጥ አይደል ብሎ ከፊቱ ለመሰወር ወደ ተርሴስ በመርከብ ኮበለለ፡፡ ዮናስ ወደ መርከብ ገብቶ ጕዞ ከተጀመረ በኋላ በእርሱ ምክንያት ታላቅ ማዕበል ተነሳ፤ በመርከቡ ውስጥ የተሣፈሩትም ሊያልቁ ሆነ፤ ሌሎች እንዲያ እየተናወጡ እርሱ ግን የእምነት ሰው፥ የዋሕና ቅን ስለሆነ ተረጋግቶ በመርከቡ ውስጥ ተኝቶ ነበር፡፡ መርከበኞቹም እጅግ ሲጨንቃቸው እያንዳንዳቸው ወደ አምላካቸው ጮሁ፤ መርከቢቱም እንድትቀልላቸው በውስጧ የነበረውን ዕቃ ሁሉ እያወጡ ወደ ባሕር ጣሉ፡፡ ባሕሩ ጸጥ ሊል ስላልቻለ ዮናስንም ቀስቅሰው “ይህ ክፉ ነገር በማን ምክንያት እንዳገኘን እናውቅ ዘንድ፤ ኑ ዕጣ እንጣጣል ተባባሉ፡፡” /ዮናስ 1፥7/፡፡ እጣ ቢጥሉ በዮናስ ላይ ወጣ፤ ዮናስም በራሱ ተጠያቂነት፤ ‹‹የእኔ ጥፋት ስለ ሆነ ወደ ማዕበሉ ጣሉኝ›› አላቸው፡፡ መርከበኞች ግን ዮናስን ለመታደግ የሚችሉትን ሁሉ አደረጉ፡፡ መርከቢቱ ወደ ምድር ትጠጋላቸው ዘንድ አብዝተው ቀዘፉ፤ የእርሱ ወደ ባሕር መጣል ፈቃደ እግዚአብሔር ስለሆነ ልፋታቸው ሁሉ ከንቱ ሆነ፡፡ ሁሉም አንድ ሆነው ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፡፡ “አቤቱ! አንተ እንደ ወደድህ አድርገሃልና ስለዚህ ሰው ነፍስ አታጥፋን፤ ንጹሕ ደምንም አታድርግብን፡፡” በማለት እያዘኑ በሐምሌ 15 ቀን ወደ ባሕሩ ጣሉት፤ ባሕሩም ከመናወጥ ጸጥ አለ፡፡ ነቢዩ ወደ ባሕር ቢጣልም የእግዚአብሔር ጥበቃ አልተለየውምና ዮናስን ይውጠው ዘንድ ታላቅ ዓሣ አንበሪን አዘዘለት፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር የቀባውን እንዳዳነው ዛሬ ዐወቅሁ›› እንዳለ /መዝ. 19፥6/ የመረጠውን ነቢይ ለማዳን ዓሣ አንበሪን አዘጋጀለት፡፡ *ዮናስም በአሣ አንበሪ ሆድና በማዕበል ውስጥ ሆኖ ለ3 ቀናት ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ በመጽሐፍ ቅዱስም በዓሣ ሆድ ተጕዞ ያስተማረ፥ ትንቢትም የተናገረ የመጀመሪያ ነቢይ ሆነ፡፡ ዓሣ አንበሪው ዮናስን በሆዱ ቋጥሮ የሦስት ቀን ጎዳና በባሕር ውስጥ ገስግሶ በ3ኛው ቀን ነነዌ ዳር ደረቅ መሬት ላይ አራግፎ ተፋው፡፡ /ዮናስ 1፥4-16፤ 2፥1-11፣ መዝ. 138፥7-10/፡፡ ዮናስ በግዙፉ አሣ አነበሪ ውስጥም ያለ እንቅልፍ በጾም፥ በጸሎትና በምስጋና ለ3 ቀናት መቆየቱ ለክርስቶስ ትንሣኤ ምሳሌ ነው፤ ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ 3 ቀን 3 ሌሊት ኑሮ፥ ሙስና (ጥፋት) ሳያገኘው መውጣቱ አዳምና ልጆቹን ለማዳን የመጣው ጌታችንም 3 መዓልትና 3 ሌሊት በከርሠ መቃብር አድሮ ከሙታን ተለይቶ የመነሣቱ ምሳሌ ነው፡፡ ለዚህም ራሱ ጌታችን በወንጌል ‹‹ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፡፡ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም፡፡ ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ 3 ቀንና 3 ሌሊት እንደ ነበረ፤ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ 3 ቀንና 3 ሌሊት ይኖራል፡፡ የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፡፡ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፡፡ እነሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ፡፡›› /ማቴ. 12፥39/ **እግዚአብሔር አምላክም ለሁለተኛ ጊዜ ዮናስን ወደ ነነዌ እንዲሄድ አዘዘው፤ “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፤ የነገርሁህንም የመጀመሪያውን ስብከት ስበክላት” አለው፡፡ ዮናስም እንቀድሞው ሳያንገራግር ወደዚህች ከተማ ገብቶ እንዲህ እያለ ‹‹እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታእ ነነዌ ዐባይ ሃገር›› (እስከ ሦስት ቀን ድረስ ነነዌ ትገለበጣለች) ንስሐን ሰበከ፥ አስተማረ፡፡

፠፠ በአዲስ አበባ ፖሊስ በሌሊት ቤተ ክርስቲያን አፈረሰ፣ ሁለት ሰዎችንም ገደለ፡፡ ፠ አዲስ አበባ 22 መንገድ ቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል አካባቢ አፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን ጎን ካለው ቦታ ላይ የቅዱ
+3
፠፠ በአዲስ አበባ ፖሊስ በሌሊት ቤተ ክርስቲያን አፈረሰ፣ ሁለት ሰዎችንም ገደለ፡፡ ፠ አዲስ አበባ 22 መንገድ ቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል አካባቢ አፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን ጎን ካለው ቦታ ላይ የቅዱስ ገብርኤል እና የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያንን ፖሊስ (ጥር 26 ለ27 አጥቢያ ከሌሊት 7:00 ላይ) ለማፍረስ ባደረገው ጥረት ሁለት ሰዎች ተገደሉ፡፡ ፠ አድማ በታኝ ኃይልን በሌሊት በመጠቀም ለማስለቀቅ ከመሞከር ባለፈ አስለቃሽ ጭስ ሲጠብቁ በነበሩ እናቶች፣ ወጣቶች እና የእምነቱ ተከታይ የሆኑ ልጆችም ጭምር ላይ» መወርወሩን እንዲሁም ጥይት መተኮሱንና ሰዎች መገደላቸውን ለማወቅ ተችሏል። ፠ 22 አካባቢ ሰዎች በጅምላ መታፈሳቸው ታውቋል። ፠ ጋዜጠኛ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ እንዳለው «ድሆች ቆጥበው የሰሩትን ኮንዶሚኒየም ወርሮ የያዘ ዱርዬን ማስለቀቅ አቅቶት ከአቅሜ በላይ ነው ብሎ መግለጫ የሚሰጠው መንግሥት፣ "የመሬት ወረራ በአዲስ አበባ ላይ ተጧጡፏል እርምጃ ልወስድ ነው" ካለ በኋላ "ትቼዋለሁ ውረሩት" ያለው መንግሥት» የኦርቶዶክስ ጉዳይ ሲሆን እንዲህ የኃይል ርምጃ መውሰዱ ሲታይ ዓላማው «ሕገ ወጥ ቤት ማፍረስ» ሳይሆን «ቤተ ክርስቲያንን ማዋረድ» እንደሆነ ሁሉም ሊያውቅ ይገባል፡፡ «በቤት ለቤት አፈሳ ብዙ ምእመናን ተግዘዋል፤ የተያዘው ኦርቶዶክሳውያንን ማጥቃትና ቤተ ክርስቲያንን ማዋረድ ነው። ከመሬት ወረራ ጋር አታመሳስሉት» ሲል አክሏል። ፠ ርምጃው ሌሊት ላይ ለምን ተደረገ? ያለ ፍርድ ቤትስ ትዕዛዝ ፖሊስ ለማፍረስና ምዕመናን ለመግደል ለምን ፈለገ? መልስ ያልተገኘላቸው ጥያቄዎች ናቸው፡፡

፠ #✤#መድኀኔዓለም ተወከፍ እንተ አቅረብኩ ንስቲተ፤ ዘሰተይከ በእንቲአየ ከርቤ ወሐሞተ፤ በሞተ ዚአከ ከመ ትቅትል ሞተ፡፡ ✤ፈጣሪዬ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሆይ፤ በሞትህ ሞትን ታጠፋው ዘንድ ከርቤ
+3
፠ #✤#መድኀኔዓለም ተወከፍ እንተ አቅረብኩ ንስቲተ፤ ዘሰተይከ በእንቲአየ ከርቤ ወሐሞተ፤ በሞተ ዚአከ ከመ ትቅትል ሞተ፡፡ ✤ፈጣሪዬ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሆይ፤ በሞትህ ሞትን ታጠፋው ዘንድ ከርቤ የተቀላቀለበትን መራራ ሐሞትን ስለኔ ሕይወት የጠጣህ የአቀረብኳትን አነስተኛ የምስጋና መባዕ በቸርነትህ ተቀበል፡፡ ፠ ማኅደረ ሰላምነ ቅድስት ደብረ ሰላም፤ ንዑ ንስግድ ኵልነ ኀበ ማርያም እምነ፡፡ (#የሰላም_ማደሪያችን_የሆነችው_ቅድስቲቱ_የተለየችው_ደብረ_ሰላም_፤ ሁላችን ወደ እናታችን ማርያም እንሰገድ፡፡) (በታላቁ ደብራችን የነበሩ ቀደምት ሊቃውንት፤ ለደብራችን ለቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም /ውዳሴና ቅዳሴ ከዓመት እስከ ዓመት ለማይታጎልበት፤ ማኅሌት እንደ ወንዝ ለሚፈስበት፤ የዐበይት ሊቃውንት መናኸሪያ ለሆነው/ ብቻ ከደረሱት ከ850 በላይ ወረቦች መካከል አንዱ ነው፡፡ (ደብራችን ቀጨኔ ደብረ ሰላም ያለበትን ቦታ ለጠየቃችሁን ሁሉ፤ 1ኛ. ከፒያሳ ፤ መድኀኔ ዓለም ፣ ችሎት በሚለው 1ድ ታክሲ ያደርሳችኋል፡፡ 2ኛ) ከጎጃም በረንዳ (ከመርካቶ)፤ ቀጨኔ መድኀኔ ዓለም በሚለው 1ድ ታክሲ ያደርሳችኋል፡፡ # ፠በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ # ፠በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ስብስትያኖስ_ሰባስትያኖስ_ሰማዕት_ጥር_25 ፠ በሕመም፥ በጭንቅ፥ በመከራ፥ በስቃይ፥ #በደዌ_ዳኛ፥ #በአልጋ_ቁራኛ_ላይ_ያላችሁ_ሁሉ በእምነት የሰማዕቱ የቅዱስ ስብስትያኖስን ስሙን ጥሩት፥ ገድሉን አድምጡ ተሻሹ፥ እምነቱን ተቀቡ፥ ቤተ ክርስቲያኑን ተሳለሙ #ፈዋሽ_ሰማዕት_ነው፡፡ #ፈትለ_ሥላሴ በመባል በሚጠራው ቤ.ክ. (ከአዲስ አበባ በሞጣ/በደብረ ድማኅ/ በኩል ወደ ባሕር ዳር ሲሄዱ አዴት ከተማ ከመድረስዎ በፊት ዠማ ወንዝ ለመድረስ ሲቃረቡ ያገኙታል)፡፡ ጥር 25 ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ይከበራል፡፡ እንዲሁም በጥንታውያን ታላላቅ ገዳማትና አድባራት የብራና ገድሉ ስላለ አስነብቡ፥ ተሻሹ፤ ፍጹም ፈውስን ታገኛላችሁ፡፡ ፠ ሰባ(ስብ)ስትያኖስ ሰማዕት፤ በስዕሉ ላይ እንደምንመለከተው በጽኑ ሕማምና ስቃይ ሰማዕትነትን የተቀበለ ነው፡፡ በተለይም በሕመም፤ በጭንቅ መከራ፤ በስቃይ ውስጥ ኾኖ ያለ ሰው አምላከ ሰብስትያኖስ ብሎ ለጠራኝ እደርስለታለሁ ብሎ በማይታበል ቃሉ እግዚአብሔር አምላካችን ቃል ኪዳን የሰጠው ሰማዕት ሲኾን ለጠሩትም ፈጥኖ የሚደርስ ሰማዕት ነው፡፡ ፠ የስብስትያኖስ አባቱ የሮሙ ንጉሥ ሲሆን ሃይማኖቱ የቀናና እግዚአብሔርንም የሚወድ ስለነበር ልጁን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እያስተማረ ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማረ አሳደገው፡፡ አባቱም ከሞተ በኋላ ከሃዲያኑ ዲዮቅልጥያኖስና መክስምያኖስ ነገሡ፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስንም አገረ ገዥ አድርገው ሾሙትና እንደ አባቱ እጅግ አድርገው አከበሩት፡፡ ፠ ቅዱስ ስብስትያኖስ በጥበብና በማስተዋል የሚጓዝ ነው፡፡ በተጋድሎ ሕይወቱ የተመሰገነ ሆነ፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቹ የተለያዩ ተአምራትን ገለጠ፡፡ ድውያንን ይፈውሳል፤ በጸሎቱም የዕውራንን ዐይኖች ያበራል፡፡ በእንዲህም ዓይነት በተጋደሎ ሲኖር ዲዮቅልጥያኖስ እግዚአብሔርን ክዶ በዓለም ላይ ያሉ ክርስቲያኖችን እያሳረደ አብያተ ክርስቲያናትንም ማቃጠል ጀመረ፡፡ ይኸውም ከሃዲ አገረ ገዥ አድርጎ ሾሞትና በእጅጉ አክብሮት የነበረውን ቅዱስ ስብስትያኖስን አሁን ለጣዖት እንዲሰግድ ግድ አለው፡፡ ፠ ቅዱስ ስብስትያኖስ ግን የከሃዲውን ንጉሥ ትእዛዝ ቸል በማለት በፊቱ ቆሞ የጌታችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፤ ጣዖታቶቹንም ረገመበት፡፡ ንጉሡም በዚህ ጊዜ በታላቅ ቁጣ ሆኖ ቅዱስ ስብስትያኖስን ብዙ አሠቃየው፡፡ ከግንድ ጋር አሥሮ በብዙ ፍላጻዎች(ቀስቶች) ሰውነቱን አስነደፈው፤ በዚህም ጊዜ እንደሞተ አስበው ትተውት ሄዱ፡፡ ምእመናንም ሥጋውን ለመውሰድ በሌሊት ቢመጡ በሕይወት አገኙትና ወስደው በደሴት መካከል አስቀመጡት፡፡ ፠ ዲዮቅልጥያኖስም የቅዱስ ስብስትያኖስን በሕይወት መኖር ሲሰማ ድጋሚ አስመጣውና በብረት ዘንጎች ሲያስደበድበው ዋለ፡፡ ለብዙ ቀናትም እንዲሁ በብረት ዘንግ ሲያስደበድበው ቆየ፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስም በጥር 25 ቀን ነፍሱ ከሥጋው ተለየችና የሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ ጌታችንም መታሰቢያውን ለሚያደርግና ስሙን ለሚጠራ የቸነፈር ሕመም፥ የሕመም ስቃይና መከራ እንዳይቀርበው ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስም ካረፈ በኋላ ውሉዱስና ለምትባል ለአንዲት ቅድስት ሴት ተገለጠላትና ቅዱስ ሥጋው ያለበትን ነገራት፡፡ እርሷም ወደ ከበሩ ቅዱሳን ጴጥሮስና ጳውሎስ መቃብር ወስዳ ቀበረችው፡፡ #ሰላም_ለዝክረ_ስምከ_ዘይትበደር እምብሩር፤ ወይጥዕም እም ሶከር፡፡ ሰባስትያኖስ ንጹሕ ትሩፈ ምግባር፤ በዝክረ ስምከ ተማኅጸንኩ ኢትኅድገኒ ለገብር፤ አመ ትወፅዕ ነፍስየ እምሥጋ በግብር፡፡ #ሰላም_ዕብል_ለፍጽምከ_መአድም፤ በስመ ሥላሴ ኅቱም፡፡ ሰባስትያኖስ አቡየ ሰላም ሰላም፡፡ በፍጽምከ ተማኅጸንኩ ኢይቅርበኒ ሕማም፤ ማዕተበ ፍጽምከ በፍጽምየ ሢም፡፡ #ሰላም_ለመልክዕከ_ዝብጠታተ ኀጺን ዘተወክፋ፤ ወትዕግስታተ አዝለፋ፡፡ ሰባስትያኖስ ጻማዊ ሱታፌ ሕማሙ ለዘልፋ፤ መልክዐ ገጽከ ኀበ ተጽሕፋ፥ ለመለክዕየ ጸሐፋ፤ ውስተ ምዕራፍከ ረሲ ምዕራፋ፡፡ **ዳግመኛም በዚህ ዕለት፤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_መርቆሬዎስ_በሥዕሉ_ላይ_አድሮ_ቅዱሳን_የሆኑ_ባስልዮስንና_ጎርጎርዮስን_በመርዳት_ከሃዲውን_ንጉሥ_ዑልያኖስን_የገደለበት_ዕለት_ነው፡፡ #ራሱን_የሸጠው_ቅዱስ_ጴጥሮስ_ዕረፍቱ_ነው፡፡ #ከበሬ_ጋር_ተጠምደው_በማረስ_ሰማዕትነትን_የተቀበሉት_አቡነ_ሕፃን_ሞዐ_ልደታቸው_ነው፡፡ (የስብስትያኖስ ቤተ ክርስቲያን ከአዴት በተጨማሪ ያለበትን ጠቁሙን ቢቻል በፎቶ ጭምር፤ አዴት አካባቢ የምትገኙ የፈትለ ሥላሴን ገዳም ፎቶ ላኩልን) ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

፠ ዛሬ ጥር 22 ቀን፤ #ርዕሰ_መነኰሳት_ቅዱስ_አባ_እንጦንስ_ልደቱና_ዕረፍቱ ነው፡፡ በፎቶ ላይ የምትመለከቷቸው ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት፤ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙት የቅዱስ እንጦንስ ገዳማት፡፡
+5
፠ ዛሬ ጥር 22 ቀን፤ #ርዕሰ_መነኰሳት_ቅዱስ_አባ_እንጦንስ_ልደቱና_ዕረፍቱ ነው፡፡ በፎቶ ላይ የምትመለከቷቸው ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት፤ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙት የቅዱስ እንጦንስ ገዳማት፡፡ 1ኛ) #ጎንደር_ደብረ_እንጦንስ፤ በጻድቁ አፄ ዮሐንስ /ከ1659-1674/ የተመሠረተ፥ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱና ዋነኛው፡፡ ጎንደር ከ300 ዓመታት በላይ የኢትዮጵያ መዲና ከተማ ሆና በቆየችባቸው ዘመናት የአቡን (የጳጳስ) ቤት (መንበረ ጵጵስና) ሆኖ ያገለገለ፡፡ 2ኛ) #እንጦንስ_ኢየሱስ፤ በጣና ላይ ከሚገኙ የደሴት ገዳማት አንዱ፡፡ 3ኛ) መንበረ ፓትርያርክ ቅዱስ እንጦንስ ገዳም፡፡ (አሁን ቅድስት ማርያምበመባል የሚጠራ) እንዲሁም 4ኛ) #ግብጽ_እንጦንስ_ገዳም ናቸው ‹‹ኀጢአታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል፤ ኃጢአታችንን እኛ ረስተን የምንጽናና ከሆነ ግን እግዚአብሔር ያስብብናል፡፡›› /ቅዱስ እንጦንስ/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ዛሬ ጥር 22 ቀን፤ #የብርሃን_መልአክ_ከሣቴ_ምሥጢር_የሆነው_ቅዱስ_ዑር/ራ/ኤል_በዓለ_ሢመቱ ነው፤ እንኳን አደረሰን፡፡ በፎቶ ላይ የምትመለከቷቸው አብያተ ክርስቲያናት፤ 1ኛ) በአዲስ አበባ የሚገኘው
+5
ዛሬ ጥር 22 ቀን፤ #የብርሃን_መልአክ_ከሣቴ_ምሥጢር_የሆነው_ቅዱስ_ዑር/ራ/ኤል_በዓለ_ሢመቱ ነው፤ እንኳን አደረሰን፡፡ በፎቶ ላይ የምትመለከቷቸው አብያተ ክርስቲያናት፤ 1ኛ) በአዲስ አበባ የሚገኘውና ጥንታዊው ደብር #ደብረ_ጽጌ_ቅዱስ_ዑርኤል 2ኛ) #ግሸን_ቅዱስ_ዑርኤል 3ኛ) #ጎንደር_ደብረ_ኀይል_ቅዱስ_ዑርኤል_ወበዓታ፤ /ዛሬ ታቦተ ሕጉ ወደ ጠበል በመውረድ ይከብራል/ 4ኛ) አዲስ አበባ አዲስ ሰፈር አንፎ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ዑራኤልና መጥምቁ ዮሐንስና ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ.ክ. (ኮልፌ_ቀራንዮ_ክፍለ_ከተማ 5ኛ) ፉሪ ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል (የቤተ ክርስቲያኑ ፎቶ ካላችሁ ላኩልን) 6ኛ) ኤ(የ)ረር ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ዑርኤል (የቤተ ክርስቲያኑ ፎቶ ካላችሁ ላኩልን)

#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፯፡፡ #ዐርብ_ጥር_22፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ለምን እንፈተናለን፤ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፈተና
#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፯፡፡ #ዐርብ_ጥር_22፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ለምን እንፈተናለን፤ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋቸው፤ …. ……እንዳያመልጣችሁ፤ በሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ በብዙ ጕባኤያት ላይ ያልተዳሰሱ ርዕሶች የሚዳሰሱበት ጕባኤ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ፤ #ደግመን_እንላለን_ይህ_ትምህርት_በፍጹም_እንዳያመልጣችሁ!!!!! ለተከታታይ ሳምንታት፤ ትምህርቱ ተከታታይነት ስላለው መቅረትና ማርፈድ አይመከርም!!፡፡ (፻፶፰ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ) #ዐርብ_ጥር_፳፪፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት አሁንም በድጋሚ እንላለን ለሕይወታችን ወሳኝና በብዙ የትምህርት ጕባኤያት ላይ የማይዳሰሱ ትምህርቶች ስለሆኑ እንዳያመልጣችሁ!!!! የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ለአባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ አስቀድመን መንፈሳዊ ሰላምታችንን በመድኃኔዓለም kርስቶስ ስም እያቀረብን ሰ/ት/ቤታችን ከደብራችን ሙሉ ማኅበረ ካህናት እና የሰበካ ጉባኤ አባላት ጋር የፊታችን ቅ
ለአባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ አስቀድመን መንፈሳዊ ሰላምታችንን በመድኃኔዓለም kርስቶስ ስም እያቀረብን ሰ/ት/ቤታችን ከደብራችን ሙሉ ማኅበረ ካህናት እና የሰበካ ጉባኤ አባላት ጋር የፊታችን ቅዳሜ 23/05/2012 ከቀኑ 9፡30 ጀምሮ በወቅታዊ የሰ/ት/ቤታችን ጉዳይ ጠቅላላ ጉባኤ እንድናደርግ ቀጠሮ ተይዟል፡፡ ስለሆነም ሁላችሁም የሰ/ት/ቤቱ አባላት ይህንን ጥሪ ቸል ሳትሉ በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ እንድንገናኝ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ ሰዓት ይከበር!! ላልሰሙ አባላት መልእክቱን እናድርስ!!

#ጥር21_አስተርእዮ_ማርያም_ ( #በዓለ_ዕረፍታ_ለማርያም_ለሶልያና ) #እመቤታችን_በ64_ዓመቷ_ጥር_21_በ49ዓም_ያረፈችበት_ዕለት_መታሰቢያ_ክብረ_በዓል_ነው፡፡ #ተናገራ_ዕዝራ_ተናገራ_ዳዊት_ዘመራ፤ #ዕዝራ_በመሰንቆ_ዳዊት_በበገና_እያጫወቷት፤ #ሳታውቀው_አለፈች_ያንን_መራራ_ሞት፡፡ ፠ ጌታችን ለእናታችን ለቅድስት ማርያም ብዙ ቃልኪዳንን ከገባላት በኋላ፤ ቅድስት ነፍሷን ከክብርት ሥጋዋ ለይቶ በቃለ አቅርንት፥ በዝማሬ መላእክት አሳረጋት፡፡ ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት ደመና ጠቅሶ እመቤታችሁን ቅበሩ አላቸው፡፡ በአጎበር አድርገው እናትና አባቷ ወደተቀበሩበት ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲወስዷት አይሁድ አይተው፤ ልጇ ተነሳ፥ አረገ እያሉ ሲያውኩን ኖሩ አሁን ደግሞ እሷ ተነሳች፥ አረገች እያለ ሉያውኩን አይደለምን? ንዑ ናዓውያ ሥጋሃ ለማርያም /ኑ ሥጋዋን እናቃጥልባቸው/ ብለው ተነሱ፤ ለዚሁም ከመካከላቸውም ታውፊኒያ የተባለውን የጎበዝ አለቃ መረጡ፤ እርሱም የአልጋዋን ሸንኮር ሊያቃጥል ሲይዝ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ሁለት እጁን በሰይፍ ቀጣው፡፡ በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማፀናት እራሷን ዘምበል አድርጋ ቅዱስ ጴጥሮስን እንደነበረው አድርግለት ብላ አዘዘችው፤ እርሱም እጁን አድኖለታል፡፡ ከዚህ በኋላ ጌታችን ከመካከላቸው ነጥቆ ከገነት ከዕፀ ሕይወት ስር አኑሯታል፡፡ ….. ሐዋርያት የቀበሯት ግን ከ6 ወር በኋላ በነሐሴ 14 ነው /ሌላውን ታሪክ በፍልሰታ ጾም ላይ ያንብቡ፤ ‹‹ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር እንዲሉ፡፡››/ ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና(ለማርያም) ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ፡፡ #ሶልያና_የእመቤታችን_የማርያም_ሌላ_ስሟ_ነው፡፡ *የእመቤታችንን ዕረፍት ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ‹‹ሞትሰ ለመዊት ይደሉ፥ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኵሉ፡፡ /ሞት ለሚሞት ሰው ሁለ የተገባ ነው፥ የማርያም ሞት ግን ሁለን ያስደንቃል፡፡›› በማለት አደንቆ ጽፏል፡፡ *እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠቀሙበት ዘንድ የላይ ቤት (የግምጃ ቤት ማርያም) አብነትና የታች ቤት(የበዓታ) አብነትን ሁለቱንም አዘጋጅተንላችኋል፡፡ መልካም ክብረ በዓል፡፡ **ክብረ በዓሉ በሃገራችንና በዓለማችን ክፍሎች ባሉ የእመቤታችን አብያተ ክርስቲያናት የሚከብሩ ቢሆንም ግን፤ በልዩ ሁኔታ እንደ ጎንደር አዘዞ ሎዛ ማርያም ባሉት አብያተ ክርስቲያናት ግን እንደ ጥምቀት በዓል፤ ከዋይዜማው ጀምሮ ወደ ጥምቀተ ተወርዶ በማደር ክብረ በዓሉ በልዩ ሁኔታ መከበሩን ልብ ይሏል፡፡ (የሎዛ ማርያምና የጥር 21 በዓል አከባበሯን ፎቶ ያላችሁ ላኩልን፡፡) ፠ በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የሚቆመውን ማኅሌ እነሆ ብለናል፡፡ ፠ ወረቦቹን በድምፅ ከፈለጉ በቴልገራም አድራሻችን ያገኛሉ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ HYPERLINK "https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት- ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤  HYPERLINK "https://t.me/medihanaelem