uk
Feedback
አብዮት ቅድመ 1ኛ:1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Abiot Pre-primary, Primary and Medium school

አብዮት ቅድመ 1ኛ:1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Abiot Pre-primary, Primary and Medium school

Відкрити в Telegram

✨በዚህ ትምህርት ቤት ቻናል ታማኒና ወቅታዊ መልእክቶች ፣ሞዴል ፈተናዎች ፣ ወርክሽቶች እንድሁም አስተማሪ መልዕክቶችን ያገኛሉ። ✨ለተማሪዎች ባህሪና ውጤት መሻሻል እንተጋለን✨

Показати більше
2 338
Підписники
Немає даних24 години
+227 днів
+5430 день
Архів дописів
✔️ጉዳዩ፡- የ2019 ዓ.ም የ9ኛ ክፍል ቅበላ ድልድል ይመለከታል፡፡ ➡️ከላይ በርዕሱ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በክፍለ ከተማቸን የ2019 ዓ.ም የ2ኛ ደ/ት/ቤቶችን የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ ለማመጣ
+1
✔️ጉዳዩ፡- የ2019 ዓ.ም የ9ኛ ክፍል ቅበላ ድልድል ይመለከታል፡፡   ➡️ከላይ በርዕሱ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በክፍለ ከተማቸን የ2019 ዓ.ም የ2ኛ ደ/ት/ቤቶችን የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ ለማመጣጠንና የመማር ማስተማሩን ስራ በአግባቡ ለማስቀጠል ያግዝ ዘንድ የ9ኛ ክፍል የተማሪዎቸን ቅበላ ድልድል መስራት አስፈልጓል፡፡ ➡️በመሆኑም ሁሉም የመንግስት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የ9ኛ ክፍል ቅበላ በተደለደላችሁት እና በት/ት ካላንደሩ መሰረት ምዝገባ እንድታከናውኑ እናሳስባለን፡፡

✔️የትምህርት እድል ✅ለ6️⃣ኛእና8️⃣ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች
✔️የትምህርት እድል ✅ለ6️⃣ኛእና8️⃣ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች

✅የትምህርት እድል ✅ለ6ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች
+1
የትምህርት እድል ለ6ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች

የ2018 የትምህርት ዓመት የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል።
ተማሪዎች ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ ! በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2018 የትምህርት ዘመን 100% የት/ቤቱ ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መዘዋወራቸውን ትምህርት ቤቱ ያሳውቃል ። ተፈታኝ ተማሪዎች ይህን ሊንክ https://aa6.ministry.et/#/result በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ። አዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ/ም

ዘንድሮ ለተመዘገበው ውጤት ከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ስራዉ ልዩ ትኩረት በመስጠት መንቀሳቀሱ ፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሀ ግብር ተጠናክሮ መቀጠሉ ፣ የሂሳብና እንግሊዘኛ ትምህርት ስትራቴጂ ተነድፎ በትኩረት መስራት መቻሉ ፣ የመማሪያና የማስተማሪያ ግብዓቶች መቅረባቸው እንዲሁም ከትምህርት ባለድርሻ አካላት ጋር በተለይም ከወላጆች ጋር በቅንጅት መሰራቱ ተጠቃሽ መሆናቸውን ኃላፊው አብራርተዋል:: በከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ስርአቱ የብዝሀ ቋንቋ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ አማርኛ እና አፋን ኦሮሞ እንደሁለተኛ ቋንቋ የተማሩ ተማሪዎች በትምህርት አይነቶቹ ፈተና መውሰዳቸውን ዶክተር ዘላለም አስታውሰው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናን ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች መካከል 543 ያህሉ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸውን አስታውቀዋል። ተፈታኝ ተማሪዎች ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ተጠቁሟል። https://aa6.ministry.et/#/result ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2018 የትምህርት ዘመን 97.48% የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ ተዘዋወሩ፡፡ (ሰኔ 29/2018 ዓ.ም) በአ
+2
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2018 የትምህርት ዘመን 97.48% የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ ተዘዋወሩ፡፡ (ሰኔ 29/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 97.48 % የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ አስታወቁ። ኃላፊው የ2018 የትምህርት ዓመት የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑን በማስመልከት ለተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በጋዜጣዊ መግለጫቸው በከተማ አስተዳደሩ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 84,257 ተማሪዎች መካከል 82,137 የሚሆኑ ተማሪዎች 50 በመቶ እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የትምህርት እርከን መሸጋገራቸውን አስታውቀዋል። ኃላፊው አያይዘውም ዘንድሮ 97.48% የሚሆኑ ተማሪዎች 50 እና በላይ በማምጣት ወደ ዘጠነኛ ክፍል ያልፉበት ውጤት በ2017 ዓ.ም ከነበረው 95% አንጻር እድገት ማሳየቱን ገልጸው ውጤቱ እንዲመዘገብ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ መምህራን ፣ የትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ለወላጆችና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ጠዋት ይፋ ይሆናል፡፡ (ሰኔ 28/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ201
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ጠዋት ይፋ ይሆናል፡፡ (ሰኔ 28/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ጠዋት ይፋ ይደረጋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመንን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ አርሞ ይፋ ማድረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ነው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 -10 /2018 ዓ.ም ድረስ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 199 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሶስት ቀናት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

⭐️ተማሪዎች ሆይ ለቀጣይ አመት አሁኑኑ ጥናት ጀምሩ መጽሀፍት ለማግኘት :- ✅የቅድመ 1ኛ መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3693?single ✅የቅድመ አንደኛ የእንግሊዘኛ መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/4609?singleየ1ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3716?singleየ2ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3709?singleየ3ኛ ክፍል  መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3702?singleየ4ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3685?singleየ5ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3678?singleየ6ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3670?singleየ7ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3659?single ➡️የ8ኛ ክፍል መጽሀፍ ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3641?singleAfan Oromo Grade 3-8 text books ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3099?singleከ9ኛ-12ኛ ክፍል መጽሀፍ ለማግኘት ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76/3720

ለትምህርት ቤቱ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሙሉ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ማጠቃለያ መርሃ-ግብር የፊታችን እሁድ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም በይፋ የደረጋል፡፡ ስለዚህ ሁሉም የትምህርት ቤቱ ተ
ለትምህርት ቤቱ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሙሉ
የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ማጠቃለያ መርሃ-ግብር የፊታችን እሁድ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም  በይፋ የደረጋል፡፡ ስለዚህ  ሁሉም  የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ከጠዋቱ 2፡30 በት/ቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት በመዝጊያ መርሃግብሩ ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ ት/ቤቱ እያሳወቀ በእለቱ ለመደበኛ ተማሪዎች የውጤት መግለጫ ካርድ በፕሮግራሙ ፍፃሜ ላይ  ለወላጆቻቸው የሚሰጥ ይሆናል፡፡

Repost from Yeka Education
🔠🔠🔠 ✔️በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡ (ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ
+2
🔠🔠🔠 ✔️በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡     (ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና  የሚሰጥበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡   📌በዚህ መሰረትም ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም ✅እንዲሁም የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና  ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሰጥ ይሆናል፡፡   📌ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሰጠው በዚህ ከተማ አቀፍ ፈተና በ6ኛ ከፍል 84,882 ተማሪዎች 199  የመፈተኛ ጣቢያዎች  እንዲሁም በ8ኛ ከፍል 86,808 ተማሪዎች 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች  ፈተናዉን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡    መልካም  ፈተና✅ 🔠🔠🔠🅰️  🔤🔤🔤🔤  🔠🔠🔠 🔤🔤🔤 ቻናላችን ይህ ነው 👇👇👇👇👇👇 ❤️❤️❤️❤️❤️ https://t.me/dam76