የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Відкрити в Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Показати більше2 757
Підписники
+124 години
+37 днів
+4430 днів
Архів дописів
+5
የሰንበት ትምህርት ቤታችን ማዕከላውያን ክፍል የምድብ አሸናፊ አባላት እና አስተባባሪዎች በዓለ ደብረዘይትን ምክንያት በማድረግ ወደ "ተስፋ አዲስ ፓረንትስ ቻይልድሁድ ካንሰር ድርጅት (ታፕኮ)" በጎ አድራጎት ድርጅት የካንሰር ታማሚ ሕጻናትን በመሄድ ጠይቀዋል::
በዚህም የሰ/ት/ቤታችን አባላት ለሕጻናቱ ዝማሬ፣ ቃለ እግዚአብሔር፣ ተውኔት፣ እንዲሁም በጨዋታ አጽናንተው ሕገ ወንጌልን ፈጽመው መጥተዋል። ቅዱስ እግዚአብሔር ለታመሙ ሕጻናቱም ምሕረት ይላክልን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ደብረ ዘይት
ደብረ ዘይት ትርጉሙ የወይራ መብቀያ፣ በወይራ ዛፍ የተሸፈነ ተራራ ማለት ነው።
ደብር ማለት ተራራ ማለት ሲሆን ዘይት ማለት ደግሞ ወይራ ማለት ነው። "ደብረ ዘይት" ማለት ደግሞ የወይራ ዛፍ የሞላበት፣ የበዛበት፣ የወይራ ተራራ ማለት ይሆናል።
ደብረ ዘይት ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ አቅጣጫ የሚገኝ ተራራ ሲሆን ከግርጌው ጌቴ ሴማኒ የአትክልት ስፍራ ይገኛል።
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሥጋዋ ያረፈበት በዚህ ተራራ ግርጌ ጌቴ ሰማኔ ነው።
ጌታችን ስለ ቤተ መቅደሱ መፍረስ፣ ስለ ዓለም ፍጻሜና ስለ ዳግም ምጽአት በዚህ ተራራ ላይ ተናግሯል።
"እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው፦ ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት" ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ የዳግም ምጽአቱን፣ የዓለም ፍጻሜን፣ የትንሣኤ ሙታንን፣ ትምህርት በሰፊው አስተማራቸው። ጌታችን ምሥጢራትን በተለያየ ቦታ ገልጧል፡፡
ምሥጢረ ጸሎትን በጌቴሴማኒ፤ ምሥጢረ መንግሥቱን በደብረ ታቦር፤ ምሥጢረ ቊርባንን በቤተ አልዓዛር፤ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታንን በቤተ ኢያኢሮስ፤ ምሥጢረ ምጽአቱን ደግሞ በደብረ ዘይት ገልጧል ደብረ ዘይት ጌታችን ዳግም ለፍርድ መምጣቱንና ምሥጢረ ምጽአቱን ለደቀ መዛሙርቱ በሚገባ የገለጠበት ዕለት ነው በተጨማሪም ደብረ ዘይትን ጌታችን በመዋዕለ ስብከቱ ለማደሪያነት ተጠቅሞበታል ቀን ቀን በምኲራብ ያስተምራል፤ ሌሊት ሌሊት ደግሞ በደብረ ዘይት ያድራል፡፡
ይህንም ቅዱስ መጽሐፍ ‹‹ዕለት ዕለት በመቅደስ ያስተምር ነበር ሌሊት ግን ደብረ ዘይት ወደምትባል ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር ሕዝቡ ዅሉ ይሰሙት ዘንድ ማልደው በመቅደስ ወደ እርሱ ይመጡ ነበር›› (ሉቃ. ፳፩፥፴፯) ተብሎ ተገልጧል፡፡ በዚህ ለማደሪያነት ባገለገለው ተራራ ምሥጢረ ምጽአቱን ስለ ገለጠበት አምስተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት ደብረ ዘይት የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ደብረ ዘይት ጾሙ እኩል የሚኾንበት፤ አምላካችን በግርማ መንግሥቱ ለፍርድ በመጣ ጊዜ መልካም ለሠሩ ክብርን፣ ክፉ ለሠሩ ቅጣቱን የሚያስተላልፍ መኾኑ የሚነገርበት፤ ስለ ዓለም መጨረሻ እና ስለሚመጣው ሕይወት የምንማርበት ስለ ዳግም ምጽአት የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡
አምላካችን እግዚአብሔር በመጨረሻው ሰዓት በቀኝ ከሚቆሙት ኑ እናንት የአባቴ ብሩካን ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን መንግስት ውረሱ ከሚላቸው ወገኖች ያድርገን። አሜን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ኑ አብረን በጋራ እንማር
በደብረ ዘይት በዕለተ እሑድ ቀንደ መለከት የሚሰማበት አዋጅ በሚታወጅበት የመባርቅት ድምጽ በሚሰማበት ኃጥአን ለፍርድ ጻድቃን ለክብር በሚሰበሰቡበት እለት እኛም እንደ ጻድቃኑ በክብር ነጭ ለብሰን ለመቆም እንዲያበቃን የደብረ ዘይትን የጌታችን የመድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚመጣበትን ዕለት ኑ አብረን በጋራ እናመሰገን ኑ አብረን በጋራ እንማር
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን
''ሥርዓተ ቅዳሴ''
ክፍል ሁለት
በዲ/ን ቢኒያም አድማሱ
የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር
የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 13/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ።
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ኑ አብረን በጋራ እንማር
በደብረ ዘይት በዕለተ እሑድ ቀንደ መለከት የሚሰማበት አዋጅ በሚታወጅበት የመባርቅት ድምጽ በሚሰማበት ኃጥአን ለፍርድ ጻድቃን ለክብር በሚሰበሰቡበት እለት እኛም እንደ ጻድቃኑ በክብር ነጭ ለብሰን ለመቆም እንዲያበቃን የደብረ ዘይትን የጌታችን የመድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚመጣበትን ዕለት ኑ አብረን በጋራ እናመሰገን ኑ አብረን በጋራ እንማር
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን
ሰላም እብል ለዘይቀድም ፆታሁ
እምእለ ቅውማን ገጻት ለብሉየ መዋዕል ታሕተ ክነፊሁ፤
ሚካኤል ካህን ለመልእክተ ዲያቆን በአምሳሊሁ ፤
ያትክል ዕድወ ነፍስየ እኂዞ በእዴሁ፤
ከመ ርእዮሙ ካልዓን ይፍርሑ።
ለተልዕኮ በሚፋጠን አገልጋይ አምሳል የነፍሳችንን ጠላት ሰይጣንን ፈጥኖ ያጠፋልን ዘንድ፤ ሌሎችም አይተው ይፈሩ ዘን፤ ዘመን በማይቆጠርለት በአምላክ ፊት ቆመው ከሚያመሰግኑ መላእክት ከፍ ከፍ ያለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልን ሰላም እላለሁ።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ሐገራችን ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿንና ቅድስት ቤተክርስቲያንን በክንፈ ረድኤትህ ጠብቅልን በአልጋ ቁራኛ በደዌ ዳኛ ተይዘው የሚጨነቁትን ማርልን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
+1
እንኳን ለዐቢይ ጾመ ጾመ ኢየሱስ አራተኛው ሰንበት ደብረ ዘይት(ለእኩለ ጾም) አደረሰን አደረሳችሁ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ እንደቀጠለ ነው አሁን ደግሞ በቀን ሁለት ምዕራፍ የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት የሮሜ መልእክትን መጀመራችን ይታወቃል አሁንም በቀን ሁለት ምዕራፍ ከ2ኛ ቆሮንጦስ ምዕራፍ 11እስከ ኤፊሶን መልእክት ምዕራፍ 5 ድረሰ ንባባችንን እንቀጥል
መልካም የንባብ ጊዜ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
እጸ መስቀል
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ ሊያወጣ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ በቀራንዮ አደባባይ በመካነ ጎልጎታ በፈቃዱ ተሰቀለ። ሞተ ጥልንም በመስቀሉ ገደለ። ከፍተኛ ወንጀል የሠሩ ሰዎች ብቻ ይሰቀሉበት የነበረው መስቀል ከጌታችን ስቅለት በኋላ የድኅነት ምልክት ሆነ::
ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ተአምር በማድረጉ የተመቀኙ አይሁድ መስቀሉን ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት መስቀሉ የተቀበረበትን ስፍራ የቆሻሻ መጣያ አደረጉት።
ንግሥት እሌኒ ልጇ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ከሆነላት ወደ ኢየሩሳሌም ሔዳ መስቀሉን ለመፈለግ እንዲሁም በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ለማሳነፅ ለእግዚአብሔር ተሳለች፡፡
ከዚህ በኋላ ልጇ ቆስጠንጢኖስ አምኖ በ337 ዓ.ም ተጠመቀ፡፡ ንግስት እሌኒም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች የጌታችንን መስቀል መፈለግ ብትጀምርም ያለበት ስፍራ የሚነግራት ሰው ልታገኝ አልቻለችም፡፡ አይሁድ የተቀበረበትን ቦታ ለማሳየት ፍላጎት ባይኖራቸውም አንድ ኪራኮስ የሚባል አረጋዊ ሰው አስጨንቃ ስለያዘችው መስቀሉ የሚገኝበትን ስፍራ ጠቆማት ነገር ግን ለዘመናት ቆሻሻ ሲጣልበት የነበረ ስፍራ በመሆኑ ተራራ ሰርቷል በቦታው ከነበሩት ከሦስቱ ተራሮች ውስጥ መስቀሉ የሚገኝበት የትኛው እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ አልተቻለም፡፡
ንግሥት እሌኒ ከሦስቱ ተራሮች የቱ እንደሆነ ለመለየት በእግዚአብሔር ረዳትነት ደመራ አስደምራ ብዙ እጣንም በመጨመርና በማቃጠል ጸሎት ተያዘ፡፡ የእጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ በመውጣት በቀጥታ ተመልሶ መስቀሉ ወዳለበት ተራራ ላይ በማረፍ መስቀሉ ያለበትን ትክክለኛ ስፍራ አመለከታት፡፡
መስከረም አስራ ስድስት ቀን ቁፋሮው ተጀምሮ መጋቢት አስር ቀን ሦስት መስቀሎች ተገኙ፡፡ ነገር ግን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ተቸገሩ፡: መስቀሎቹን ወስደው ሙት ላይ ቢያስቀምጡ ጌታችን በዕለተ አርብ የተሰቀለበት መስቀል የሞተውን ሰው አስነሳው ሌሎቹ ሁለቱ መስቀሎች ግን ሙትን ማስነሳት ባለመቻላቸው የጌታችንን መስቀል ለይቶ ማወቅ ተችሏል። ንግስት እሌኒና ክርስቲያኖች ሁሉ ለመስቀሉ ሰገዱለት
የመስቀሉ በረከት በሁላችንም ላይ ይደርብን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
''ሥርዓተ ቅዳሴ''
ክፍል ሁለት
በዲ/ን አማኑኤል አሽኔ
የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር
የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 13/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ።
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
