የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Відкрити в Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Показати більше2 604
Підписники
+324 години
+87 днів
+2430 день
Архів дописів
+4
የጸሎተ ሐሙስ ሕጽበተ እግር ሥነ ስርዓት በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ የደብራችን አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃናት አዕምሮ ምስጋናው በተገኙበት ተከናወነ ።
እኔ እግርህን ካላጠብኩህ ከእኔ ጋር ዕድል ፈንታ የለህም›› (ዮሐ.፲፫፥፰)
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
ሐሙስ
1.ጸሎተ ሐሙስ ይባላል
ጌታችን ለአይሁድ ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ ሲጸልይ በማደሩ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።
2.ሕጽበተ ሐሙስ
ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል።
3.የምስጢር ቀን ይባላል
ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የሆነው የቅዱስ ቁርባን ምስጢር በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምስጢር ቀን ይባላል።
4. የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል
መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድኅነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።
5.የነጻነት ሐሙስ ይባላል።
ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነ የነጻነት ሐሙስ ይባላል።
6.አረንጓዴ ሐሙስ ይባላል።
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጌቴሴማኔ በአረንጓዴው የአትክልት ስፍራ ስለጸለየ አረንጓዴው ሐሙስ ይባላል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
ዕለተ ረቡዕ
የምክር ቀን (ምክረ አይሁድ)
-የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚችሉ ምክር የጀመሩበት ቀን ነው።
- መልካም መዓዛ ያለው ቀንም ይባላል። ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ ዕፍረት (ባለ ሽቱዋ ማርያም) ከእንግዲህ ወዲህ በኃጢአት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ፣ ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ፣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የሞላ ሽቱ ይዛ በመሄድ በፀጕሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ነው።
- የዕንባ_ቀንም ይባላል። ይህም ስያሜ የተሰጠበት ምክንያት ይህችው ማርያም እንተ ዕፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲልላት በዕንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፤ በፀጕሯም በዕንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና። በፀጕሯም ማበሷ አክሊሌ_ነህ ስትል ነው።
ይህን ሳምንት ፀሐይ እስክትጠልቅ በመጾም በጸሎት በስግደት የጌታችንን ሕማም የምናስብበት ሳምንት ነው።
መልካም የሕማማት ሳምንት ይሁንልን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የሕማማት ሳምንት
ዕለተ ሰሉስ(ማክሰኞ)
የጥያቄና የትምህርት ቀን ይባላል።
በዕለተ ሰኑይ ጌታችን አንጽሖተ ቤተ መቅደስ አድርጎ ስለነበር ይህን ስላደረገበት ስልጣን እና ሌሎችንም ጥያቄዎች የተጠየቀበት እንዲሁም በስፋት ትምህርት ያስተማረበት ቀን በመሆኑ በዚህ ተሰይሟል።
ሳምንቱ ፀሐይ እስክትጠልቅ በመጾም በጸሎት በስግደት የጌታችንን ሕማም የምናስብበት ሳምንት ነው።
መልካም የሕማማት ሳምንት ይሁንልን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
#የሰሙነ_ሕማማት_ሰኞ
#መርገመ_በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው
ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሆሣዕና ዕለት ቢታንያ አድሮ በማግሥቱም ከቢታኒያ ሲመጡ ተራበ፡፡ (ማር.11፤11-12) ቅጠል ያላት በለስ ከሩቅ አይቶ ወደ በለሲቱ ቀረበ፤ ነገር ግን ከቅጠል በቀር አንዳች ፍሬ አላገኘባትም፡፡ ከአሁን ጀምሮ ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ ብሎ ረገማት። በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ናት፤ ፍሬ የተባለች ሃይማኖትና ምግባር ናት፤ ከእስራኤል ፍቅርን፤ ሃይማኖትን፤ ምግባርን ፈለገ አላገኘም፤ እስራኤል (ሕዝበ እግዚአብሔር) መባልን እንጂ፤ ደግ ሰው አይገኝብሽ ብሎ ረገማት፤ በመርገሙ ምክንያት እርሱ ከለያቸው በስተቀር ደግ ሰው ጠፋባት፡፡
በለስ ኦሪት ናት፤ ኦሪትን በዚህ ዓለም ሰፍና ቢያገኛት ኦሪትና ነቢያትን ልሽር አልመጣሁም ልፈጽም እንጂ በማለት ፈጸማት፤ ሕገ ኦሪትን ከመፈጸም በቀር በእርሷ ድኅነት አላደረገባትምና፤ ፍሬ በአንቺ አይሁን አላት፤ ደኅነት በአንቺ አይደረግብሽ ብሏታልና እንደመድረቅ ፈጥና አለፈች፡፡
በለስ ኃጢአት ናት፤ የበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነች ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አገኛት፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣል፤ ቆይቶ ግን ይመራል፤ ኃጢአትም ሲሰሩት ደስ ደስ ያሰኛል፤ ኋላ ግን ያሳዝናል፤ ወደ እርሷም ሄዶ ማለትም ከኃጥአን ጋር ዋለ፤ ኃጥእ ከመባል በቀር በአንደበቱ ሐሰት፤ በሰውነቱ ክፋት እንዳልተገኘበት ለማመልከት ፍሬ አላገኘባትም አለ፤ በአንቺ ፍሬ አይገኝ የሚለውም፤ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ የሚቀር አይኑር ለማለት ነው፤ ስትረገም ፈጥና መድረቋም፣ በአዳም ምክንያት ያገኘችን ዕዳ በደል በእርሱ ካሣነት እንደጠፋችልን ለመግለጽ ነው፡፡
#አንጽሆተ_ቤተ_መቅደስ የተፈጸመበት ዕለት ነው፦
ጌታችን በለስን ከረገማት በኋላ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ፤ ቤተ መቅደስ፣ ቤተ ጸሎት፣ ቤተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቤተ ምስያጥ (የንግድ ቤት) ሆኖ ቢያገኘው ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች፤ እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት ብሎ የሚሸጡበትን ሁሉ ገለበጠባቸው፤ ገርፎም አስወጣቸው፤ ይህም የሚያሳየው ማደሪያው ቤቱ የነበርን የአዳም ልጆች ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታችንን ሁሉ እንዳራቀልን የሚገልጽ ነው፡፡
በዚህ በሰሙነ ሕማማት ካህናትና ምእመናን በቤተክርስቲያን ተገኝተው ወዛቸው ጠብ እስኪል ድረስ በነግህ፤ በሠለስተ፣ በስድስቱ ሰዓት፤ በተሰዓቱ ሰዓትና በሠርክ መላልሰው ሲሰግዱና ሲጸልዩ ይሰነብታሉ፤ በተለይም ካህናት በማንኛውም አገልግሎት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፤ ምክንያቱም የደረሰብን መከራ ኀዘኑን እና 5ሺ ከ5መቶ ዘመን የሰው ልጅ በጨለማ ይኖር እንደነበረ ለማዘከር ነው፡፡
ሰሙነ ሕማማት
ሰሙነ ሕማማት ተብሎ የሚጠራው ወቅት ከዐቢይ ጾም መጨረሻ ከሆሣዕና ዋዜማ ጀምሮ እስከ ትንሣኤ ባሉት ቀናት ውስጥ ያለው ሳምንት ነው፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ ይህንን ወቅት አስመልክቶ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ‹‹ውእቱ ነሥአ ደዌነ ወጾረ ሕማመነ፤ እርሱ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፤ ሕማማችንንም ተሸከመ፤›› በማለት የነገረ ሕማማቱን ምሥጢር አስቀድሞ ተናግሮአል፡፡ በዚህም መሠረት በኋለኛው ዘመን እግዚአብሔር ወልድ ስለኛ ስለ ሰው ልጆች ድኅነት ሲል ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋም ነፍስ ነሥቶ በፈቃዱ ሰው ሆኖ በፈቃዱ መከራ መስቀልን ተቀበለ፡፡ በመስቀሉም ላይ ሳለ በፈቃዱ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጠ፡፡ በዚህም መሠረት እኛም በእርሱ በአምላካችን የሆነበትን መከራ መስቀሉን ሁሉ የምናስብበት ሳምንት በመሆኑ ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡
በዓለ ሆሣዕና በደብራችን ጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በዛሬው እለት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቤተ ፋጌ ወደ ኢየሩሳሌም በአህያና ውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ በገባ ጊዜ ሕዝቡ ሲዘምሩና ሲያመሰግኑ የአይሁድ አለቆች በመቆጣታቸው አመስጋኙ ሕዝብ ዝም ሲሉ ሕጻናቱ የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘዉ ''ሆሣዕና በአርያም'' እያሉ በደስታ ያመሰገኑበት እነዚህ ሕጻናት ዝም ቢሉ እነዚህ አፍ የሌላቸው ድንጋዮች ያመሰግኑኛል ብሎ የተናገረበት ''እም አፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ በእንተ ጸላዒ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ
ከህፃናት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ
የጠላት ዲያቢሎስ ምክሩን ታፈርስበት ዘንድ'' ተብሎ የተነገረበት ታላቁ የሆሣዕና በዓል
የደብራችን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃን አዕምሮ ምስጋናው ፣ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የሰንበት ቤታችን ሕጻናት አባላት እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
ሆሳዕና በአርያም
ሆሳዕና ማለት ቃሉ ሆሼዕና ከሚለው ከዕብራይስጥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ መድኃኒት፣ አቤቱ አሁን አድን ፣አቤቱ አሁን አቅና ማለት ነው፡፡
ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ዓበይት በዓላት አንዱ ሲሆን ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊው ሊቅ በሰየመው የዐቢይ ፆም ሳምንታት ስያሜ ስምንተኛ ሳምንት ሆኖ ተሰይሟል።
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቤተ ፋጌ ወደ ኢየሩሳሌም በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም መግባቱን በማሰብ ዛሬም ድረስ በታላቅ ክብር ቤተክርስቲያን በዓሉን ታከብራለች። ጌታችንም ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ጠርቶ እንዲህ አላቸው “በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ ያን ጊዜም የታሰረች አህያ ከውርንጭላዋ ጋር ታገኛላችሁ፤ ፍቱና አምጡልኝ” አላቸው፡፡
ደቀ መዛሙርቱም እንዴት የሰው ንብረት ዘርፈን እናመጣለን? ብለው ፈሩ ያንጊዜ “ምን ታደርጋላችሁ? የሚላችሁ ቢኖር ጌታቸው ይሻቸዋል በሉ፤ ያን ጊዜ ይሰዱአችኋል” አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ሄደው ጌታችን ኢየሱስ እንዳዘዛቸው አደረጉ፡፡
“አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልል በዪ፤ እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያ በአህያይቱም ግልገል በውርንጫይቱ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል፡፡” ትን.ዘካርያስ 9፥9
ተብሎ በነቢያት የተነገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችንም በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም በሚገባ ጊዜ ሕዝቡም ልብሶቻቸውን በመንገድ ላይ እያነጠፉ ፤ ዘንባባ ይዘው የዛፎችንም ጫፍ ጫፍ እየቆረጡ “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም” እያሉ ይጮሁ ነበር፡፡ ያን ጊዜ የሕዝቡና የሕጻናቱ የደስታ ጩኸትና ምስጋና ያስቆጣቸው ፈሪሳዊያን ዝም እንዲያሰኛቸው ጌታችንን ጠየቁት እርሱም መልሶ “እነርሱ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ያመሰግኑኛል” ብሎ መለሰላቸው።
''እም አፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ
በእንተ ጸላዒ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ
፡ ከህፃናት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ
የጠላት ዲቢሎስ ምክሩን ታፈርስበት ዘንድ''
ጌታችን በአህያ ላይ ለምን ተቀመጠ?
• ትህትናን ለማስተማር
• የሰላም ዘመን ነው ሲል
• ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል ነው
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ ሕዝቡ ዘንባባ ይዘው
“ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር፤ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረክ ነው።’’
በማለት ስለተቀበሉት ይህን በማሰብ እስከ አሁን ድረስ ቤተ ክርስቲያናችን ዘንባባ ለሕዝበ ክርስቲያኑ በመስጠት እንዲሁም በአራቱም ማዕዘናት ከአራቱም የወንጌል ክፍል ዕለቱን የሚመለከቱ ምንባባት እየተነበበ በዓሉ ይከበራል፡፡
በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሐት ስለማይፈጸም በዚሁ እለት ጸሎተ ፍትሐት ይከናወናል ፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
