የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Відкрити в Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Показати більше2 752
Підписники
-224 години
+197 днів
+5130 день
Архів дописів
https://youtu.be/WecrDoAaop4?si=Ym0GZ_RuFyUX-Rjs
ተለቀቀ
ሚካኤል ነህ
በሊንኩ እየገባችሁ መዝሙሩን አዳምጡ ለሌሎችም ይደርስ ዘንድ ሼር ያድርጉ!!
https://vm.tiktok.com/ZNR3YV39C/
ለሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በሙሉ
አስቸኳይ መልዕክት
በሰንበት ትምህርት ቤታችን ለሰኔ 12-2018 ዓ.ም ዝመሬ የተዘጋጀ መሆኑን ማሳወቃችን ይታወሳል እነሆ ነገ ሙሉ ዝማሬዉን በዩቱብ ገፃችን የምንለቅ መሆኑን እያሳወቅን ለአሁን በቲክቶክ አካዉንት ከላይ ያስቀመጥነዉን ሊንክ በመጠቀም የለቀቅነዉ እንድትሱሙ እና ለምዕመናን ተደራሽ እንዲሆን Like,Share እና Repost በማድርግ እንድንተባበር ስንል በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም እናሳስባለን።
https://vm.tiktok.com/ZNR3Yjhbc/
ለሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በሙሉ
አሰቸኳይ መልዕክት
በሰንበት ትምህርት ቤታችን ለሰኔ 12 2018 ዓም ዝማሬ እንደተዘጋጀ ቀድመን ያሳወቅን መሆኑ አይዘነጋም እነሆ አሁን በቲክቶክ የተወሰነ ክፍልየተለቀቀ መሆኑን እያሳወቅን ነገ በ ዩቱብ ሙሉዉን የምንለቅ ሲሆን እስከዚያዉ ድረስ የተለቀቀዉ በሊንኩ አማካኝነት በመግባት Like,Share እንዲሁም Repost በማረግና ድምጹን በመጠቀም በየራሳቹ አካዉንት ፖስት በማድረግ ለምዕመናን ተደራሽ እንዲሆን እንድታደርጉ በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም እናሳስባለን።
የሐዘን መግለጫ
የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን ቢኒያም አቤል አያት አርፈዋል። ሥርዓተ ቀብራቸው ነገ ሰኞ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም በቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤ/ክ ከቀኑ 5:00 የሚፈጸም በመሆኑ በቀብሩ ላይ መገኘት የምትችሉ ተገኝተን እንዲሁም መኖሪያ ቤታቸው 42 ጂምናዚየም አካባቢ በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን። ነፍሳቸውን ይማርልን ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
+5
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
እለታዊ የአገልግሎት መረጃ
በዛሬው እለት የሰንበት ት/ቤታችን የቀድሞ የሥራ አመራር አባላት አዲስ ከተመረጡት አመራሮች ጋር በጋራ ስላለፈው የአገልግሎት ጊዜ በመወያየት ወደ ፊት ጠንካራ ጎኖችን የማስቀጠልና መሻሻል የሚገባቸውን ጉዳዮች በማረም ሰንበት ት/ቤታችንን እና ቅድስት ቤተክርስቲያን በትጋት ስለማገልገል ተመካክረዋል።
በስብሰባው የሥራ አመራር ምክትል ሰብሳቢ የሆነው ወንድማችን አቶ ካሳሁን እሸቱ እና በሌሎች የሥራ አመራር አባላት አጠቃላይ ስለነበረው የአገልግሎት ጊዜ በሰፊው ገለጻ የተደረገ ሲሆን፣ ያከናወኑትን ተግባራትና የነበሩትን ድክመቶች በማንሳት ለአዲሱ አመራር ጠቃሚ የሆኑ ምክረ ሀሳቦችን አቅርበዋል።
በውይይቱም የተለያዩ ጥያቄዎችና ማብራሪያዎች ተነስተው ምላሽ የተሰጠባቸው ሲሆን፣ ወደፊት ሁላችንም በሚሰጠን የአገልግሎት ድርሻ ላይ በጋራ ተባብረንና ተጋግዘን በፍቅር ቅድስት ቤተክርስቲያንን እንድናገለግል በመመካከር ጉባኤው በጸሎት ተጠናቋል።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ
ሰኔ ሰባት በዚህች ቀን ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ እረፍቱ ነው። ይህም ቅዱስ አባት በቤተ ክርስቲያን ታሪክ በደራሲነታቸው በወንጌል አገልግሎታቸውና በቅድስናቸው ከተመሠከረላቸው ዐበይት ሊቃውንት አንዱ ነው።
ሊቁ የተወለደው መጋቢት 27 ቀን በ433 ዓ/ም ሲሆን ሃገሩ ሶርያ ነው:: ወላጆቹ ክርስቲያኖች ለዚያውም አባቱ ሊቀ ካህናት ነበር:: ቅዱስ ያዕቆብ ገና በልጅነቱ ጀምሮ ጸጋ እግዚአብሔር የጠራው ነውና በብዙ ነገሩ የተለየ ነበር::
አንድ ቀን በዕለተ ሰንበት ገና በ3 ዓመቱ እናቱ አቅፋ ወደ ቤተ መቅደስ ወሰደችው:: ምዕመናን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበሉ ሕጻኑ ያዕቆብም ይቆርብ ዘንድ ቀረበ:: ሊቀ ጳጳሱ ደሙን በዕርፈ መስቀል ሊያቀብለው ሲል መልአኩ መጥቶ "በጽዋው ጋተው" አለው።
የጌታን ደም በጽዋ ቢጠጣ ምስጢር ተገለጸለትና "አንሰ እፈርሕ ሠለስተ ግብራተ - እኔስ 3 ነገሮች ያስፈሩኛል" ሲል አሰምቶ ተናገረ። ጳጳሱና ሕዝቡ ወደ ሕጻኑ ያዕቆብ ቀርበው "ምን ምን?" አሉት። እርሱም:- ነፍሴ ከሥጋየ ስትለይ፣ ቅድመ እግዚአብሔር ለፍርድ ስቀርብ እንዲሁም ከፈጣሪየ የፍርድ ቃል ሲወጣ" አላቸው። ያን ጊዜ ሕዝቡና ሊቀ ጳጳሳቱ "እግዚአብሔር በዚሕ ሕጻን አድሮ ዘለፈን" እያሉ ለንስሃ በቅተዋል።
ቅዱስ ያዕቆብ 7 ዓመት ሲሞላው ይማር ብለው ወደ ጉባዔ አስገቡት። በ5 ዓመታት ብሉይ ከሐዲስ ጠንቅቆ በ12 ዓመቱ ሊቅ ሆኗል። በዚህ ወቅት የነበሩ ታላላቅ ሊቃነ ጳጳሳት ወደ እርሱ ተሰበብስበው "እንግዳ ድርሰት ድረስልን። አዲስ ምሥጢር ንገረን" አሉት። እርሱ ግን ሲቻለው ስለ ትሕትና "አልችልም" አላቸው። "እንግዲያውስ ትንቢተ ሕዝቅኤልን ተርጉምልን" ቢሉት ባጭር ታጥቆ አመሥጥሮላቸው ተደስተዋል። ፈጣሪንም አመስግነዋል::
ቅዱስ ያዕቆብ ከዚህ በኋላ ወደ ገዳም ገብቶ ትሕርምተ አበውን፣ ዕጸበ ገዳምን፣ ሕይወተ ቅዱሳንን በተግባር ተምሯል። በድንግልናው ጸንቶ ጾምና ጸሎትን እያዘወተረ ኑሯል። በፈቃደ እግዚአብሔር የሥሩግ (በኤፍራጥስና ጤግሮስ ወንዞች መካከል የምትገኝ የሶርያ ግዛት ናት) ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ ተሹሟል::
ቅዱስ ያዕቆብ በዘመኑም የ451ን የኬልቄዶን ጉባኤ አውግዟል፣ ብዙ መናፍቃንን ተከራክሮ ምላሽ አሳጥቷል፣ በወንጌል አገልግሎት መልካም እረኝነቱን አሳይቷል፣ዛሬ የምንገለገልበትን መጽሐፈ ቅዳሴውን ጨምሮ በርካታ መንፈሳዊ ድርሰቶችን ደርሷል::
በመጨረሻም ከብዙ የተጋድሎና የቅድስና ዓመታት በኋላ በተወለደ በ72 ዓመቱ በ505 ዓ/ም በዚህች ቀን አርፏል:: አንዳንድ ምንጮች ደግሞ ሰኔ 27 ቀን እንዳረፈ ይናገራሉ:: ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ለቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ተወዳጅ ልጇ ነውና በእጅጉ ታከብረዋለች።
ቅዱስ እግዚአብሔር አምላካችን ከቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
"ልጄ ሆይ፥ በእግዚአብሔር የተባረክሽ ሁኚ፤ "
ሩት 3 : 10
✨እግዚአብሔር ለምን ወንድ እና ሴት
አድርጎ ፈጠረን?
✨ሴት ማለት?
✨መንፈሳዊ ሴት ማን ናት? ከእግዚአብሔር
ጋር የሚኖራት ግኑኝነት
✨መንፈሳዊት ሴት በእጮኝነት ህይወት
✨መንፈሳዊት ሴት በትዳር ህይወት
✨መንፈሳዊት ሴት በልጅ አስተዳደግ
ህይወት
✨መንፈሳዊት ሴት በማህበራዊ ህይወት ....እና ሌሎችም ርዕሰ ጉዳዮች የምንዳስስበት
የእህቶች ጉባኤእነሆ ተዘጋጀ!!! የዚህ ወር ጉባኤያችን:- 👉 እሁድ ሰኔ 7 👉 ከጠዋቱ 3:30 👉 በሰንበት ት/ት ቤቱ ህንፃ እህቴ ሆይ እህትሽን ይዘሽ ነይ!!! በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
+2
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
እለታዊ የአገልግሎት ዜና!
በሰንበት ት/ቤታችን ፍኖተ ብርሃን ግንቦት 16/2018 ዓ.ም በተደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ለቀጣይ ሦስት ዓመት ሰንበት ት/ቤታችንን በሥራ አመራርነት እና በኦዲትና ኢንስፔክሽን የሚያገለግሉ አባላትን መምረጡ ይታወቃል። በትላንትናው ዕለት ሰኔ 06/2018 ዓ.ም አዲሱ ሥራ አመራር የመጀመሪያውን የሥራ አመራር ስብሰባውን የደብራችን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃናት አእምሮ ምስጋናው በተገኙበት በአባታዊ ቡራኬና በጸሎት አስጀምረዋል።
በመቀጠልም ክቡር አስተዳዳሪያችን በአገልግሎት የሚገጥሙንን ፈተናና ውጣ ውረድ ከመጽሐፍ ቅዱስ የሎጥን ታሪክ መነሻ በማድረግ "ወደ ኋላ አትመልከቱ" በሚል ርዕስ የቃለ እግዚአብሔርና አባታዊ ምክር አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም አዲሱ ሥራ አመራር የጽ/ቤት አካላትን ( የሰንበት ት/ቤቱን ሰብሳቢ፣ ምክትል ሰብሳቢና ጸሐፊ (መ/ር ኢ/ር ዳዊት አበበን፣ አቶ ላቀው ይርጋን እና ወ/ሮ ዮርዳኖስ ገብረሚካኤልን) በመምረጥ፤ መላው አባላትም አገልግሎታችንን በአግባቡ መፈጸም እንችል ዘንድ በጸሎት እንዲያስቡን፣ በአገልግሎትም አብረውን እንዲራዱን ሲሉ መረጃውን እንድናደርስ ልከውልናል። ጉባኤው በቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖአምላክ አማካኝነት በጸሎት ተጠናቋል።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አንሸራትተው ከሚደፉህ ሀሳቦች ባሻገር በተሰፋ ሞልተው የሚያቆሙህ ተውህቦ ምህረት የተሰጠው የዋህ ብርቱ በጥበብና በሞገሰ የሚሞላ ሚካኤል አለ
'' ነገረ ክርስቶስ በሥርዓተ ቅዳሴ''
ክፍል - 1
በመ/ር ዲ/ን ሽመልስ መልአክ
የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር
ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 6/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ።
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com/
ሚካኤል ነህ
💡ሁሌም ቢሆን ጥቁር ብቻ መስሎ ከሚታይህ ቀን ጀርባ የታዘለ ደማቅ ብርሃን ሚካኤል አለ፣ ሊገፈትሩህ ከበረቱ እልፍ ክንዶች ኋላ ሊያቀኑህ የቆሙ ብርቱ መዳፎች ያሉት ሚካኤል አለ፣ አንሸራትተው ከሚደፉህ ሃሳቦች ባሻገር በተስፋ ሞልተው የሚያቆሙህ ተውቦህ ምህረት የተሰጠው የዋህ ብርቱ በጥበብና በሞገሰ የሚሞላ ሚካኤል አለ
ያላየኸው ነገ ብዙ አዲስ የህይወት ገፆችን ይዞ ይጠብቅሃል ካጎነበስክበት ቀና ትላለህ ሀዘንህ በሳቅ ይተካል ሚካኤል አለ ስለዚህ ሁሌም ወደ አምላክ ለመድረስ ምልጃው የማይለየው ሚካኤልን በዝማሬ ሚካኤል ነህ ብለህ እንድትዘምር የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል ምክንያት በማድረግ ይህን ልዩ ዝማሬ ይዞ መጥቷል ኦርቶዶክሳዊያን ሁላችን ይህ ድንቅ ዝማሬ ለሁሉ እንዲዳረስ ሼር ሼር አድርጉት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የሐዘን መግለጫ
የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን ፍቅሩ ንጋቱ ልጅ አርፋለች። ሥርዓተ ቀብሯ ዛሬ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም በቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤ/ክ ከጠዋቱ 3:00 -4:00 የሚፈጸም በመሆኑ በቀብሩ ላይ መገኘት የምትችሉ ተገኝተን እንዲሁም መኖሪያ ቤታቸው ከኤክስትሪም ወደ ካቴድራል ት/ቤት በሚወስደው መንገድ ላይ በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን። አምላከ ቅዱስ ሚካኤል ነፍሷን በክብር ይቀበልልን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን (ቅዱስፍሬምናጦስ)
አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በኋላ በ245 ዓ.ም በቅድስት ሐገር ኢየሩሳሌም ኅዳር 26 ቀን ተወለዱ።
አቡነ ሰላማ ሲወለዱ ታላቅ ብርሃን ከሰማይ ወርዶ ለ7 ቀናት አብርቷል፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ወደ ምድር ወርደው በመወለዳቸው ታላቅ ደስታን አድርገዋል፡፡
በተወለዱም ጊዜ ‹‹ለአብ ፣ ለወልድ፣ ለመንፈስ ቅዱስ ስግደት ይገባል፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጡኝ ቅድመ ዓለም ለነበሩ ዛሬም ላሉ ዓለምን አሳልፈው ለሚኖሩ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል ብለው ዳግመኛም አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ብለው ፈጣሪያቸውን በአንድነት በሦስትነት አመስግነዋል፡፡
ቅዱስ አባታችን አባ ሰላማ በሌላኛው ስማቸው ፍሬምናጦስ እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ በ40 ቀናቸው ጌታ በተጠመቀበት በዮርዳኖስ ያጠመቋቸውና ስመ ክርስትና የሰጧቸው ሊቀ ጳጳስ ‹‹ይህ ሕፃን ለኢትዮጵያውን ሁሉ ብርሃን ይሆንላቸዋል›› በማለት ትንቢት ተናግረዋል፡፡ በሊቀ ጳጳሱ በቅዱስ አትናቴዎስ በሚገባ ተምረው ካደጉ በኋላ በ257 ዓ.ም ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ ስሙ ሜርጵዮስ ከሚባል ከአንድ ነጋዴ ጋር መጡ፡፡ ከእነሱም ጋር አድስዮስ የሚባል ልጅ ነበር፡፡ ወደ ሀገራችንም ሊመጡ የቻሉት መጀመሪያ ለሰባት ወራት በአንድ ሌላ አገር ኖረው ወደ ኢየሩሳሌም ሊመለሱ ሲሉ የበረሃ ሽፍቶች ሜርጵዮስንና ሌሎች መንገደኞችን ገደሏቸውና ሁለቱን ልጆች ማርከው ወስደው ስሙ አልአሜዳ ለሚባል ለአክሱም ንጉሥ ሰጡት፡፡ እርሱም አድስዮስን የቤተክርስቲያን የአልባሳትና የዕቃ ቤት ጠባቂ አድርጎ ሲሾመው ፍሬምናጦስን ደግሞ የቤተክርስቲያንና የሕግ ጠባቂ አደረገው የቤተክርስቲያንን ሥርዓቷንና አገልግሎቷን ጠንቅቆ ያውቅ ነበርና፡፡
በአክሱምም በተጋድሎና በትጋት ኖረ፡፡ ቅዳሜና እሑድ የዛፍ ቅጠሎችን ከመመገብ በቀር ሌላ ምግብ አይቀምስም ነበር፡፡ በየቀኑም አምስት ሺህ ስግደትን ይሰግድ ነበር፡፡ በእርሱም የተጋድሎ ዘመን ደጋግ የሆኑ ነገሥታት አብርሃና አጽብሓ ነገሡ፡፡ እነርሱም ሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍሬምናጦስን በጣም ይወዱት ነበር፡፡ አንድ ቀን ፍሬምናጦስ የአክሱሙን ኤጲስ ቆጶስ ቅዱስ ሚናስን ‹‹ግዝረትና እምነት በእናንተ ዘንድ አለ ነገር ግን ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ መቀበል በእናንተ ዘንድ የለም›› አለው፡፡ ቅዱስ ሚናስም ‹‹ግዝረትንስ አባቶቻችን ሌዋውያን አመጡ፣ በክርስቶስ ማመንን ሕንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት ጃንደረባ አመጣልን፡፡ ስለ ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ ሐዋርያ ወደ እኛ አልተላከም ነገር ግን ያልከውን ሁሉ የሚያደርግልን የሚባርከንና የሚቀድሰን ጳጳስን ታመጣልን ዘንድ ሊቀ ጳጳሱ ወዳለበት ወደ እስክንድሪያ አገር አንተ ሂድ›› አለው፡፡ ጥምቀትስ በጃንደረባው በኩል አገራችን ገብቶ ነበር ነገር ግን ገና ስላልተጠናከረ ብዙ ሕዝብም አልተጠመቀም ነበርና አባታችን ፍሬምናጦስ አጠናክሮ ያልተጠመቀውን ሁሉ አጥምቆአል፡፡
ፍሬምናጦስም ወደ እስክንድሪያ ለመሄድ አስቦ ሳለ እንደተኛ ድንግል ማርያም ተገልጣለት ‹‹ዲቁናና ቅስናን መቀበል ይገባሃል፣ ለጵጵስና ተዘጋጅ፣ እግዚአብሔር ይህችን ከፍ ያለችውን ማዕረግ ሰጥቶሃልና የልጄ ወዳጅ ሆይ በጸሎትህና በልመናህ በስብከትህም የኢትዮጵያ ሰዎች ሁሉ ይድናሉ፣ በእጅህ ጥምቀትንና ሥጋ ወደሙን ይቀበላሉ›› አለችው፡፡ ጌታችንም እንዲሁ ተገልጦለት ‹‹ወደ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አትናቴዎስ ሄደህ ከፍ ያችውን ማዕረግ ተቀብለህ የኢትዮጵያን ሰዎች አጥምቅልኝ፣ ነቢዩ ዳዊት ስለ እነርሱ ‹ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች› ብሎ ተናግሯልና›› አለው፡፡ እርሱም ቅዱሳኑን ነገሥታት አብርሃንና አጽብሓን አግኝቶ ከእነርሱም ጋር ተማክሮ ወደ እስክንድሪያ ሄዶ በቅዱስ አትናቴዎስ እጅ በአገራችን ላይ የመጀመሪያው ሊቀ ጳጳስ ሆኖ ታኅሳስ 18 ቀን ተሾመ፡፡ ስሙንም ሰላማ ከሣቴ ብርሃን አለው፡፡ ሰላማ ማለት እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያስታርቅ ማለት ነው፡፡ ከሣቴ ብርሃን ማለትም ሃይማኖትን ገልጦ የሚያስተምር ማለት ነው፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስም ከሾመው በኋላ ታቦትን በጣም ብዙ ንዋያተ ቅድሳትንና መገልገያ ዕቃዎችን ሰጥቶ መርቆ በሰላም ወደ ኢትዮጵያ ላከው፡፡ አባታችን በ330 ዓ.ም ታኅሣሥ 18 በሐዋርያው ቅዱስ አትናቴዎስ እጅ ጵጵስና ተሹሟል ፡፡
የአባታችን የአባ ሰላማ በረከት አይለየን አሜን!!
ልጄ ሆይ፥ በእግዚአብሔር የተባረክሽ ሁኚ፤ "
ሩት 3 : 10
✨እግዚአብሔር ለምን ወንድ እና ሴት
አድርጎ ፈጠረን?
✨ሴት ማለት?
✨መንፈሳዊ ሴት ማን ናት? ከእግዚአብሔር
ጋር የሚኖራት ግኑኝነት
✨መንፈሳዊት ሴት በእጮኝነት ህይወት
✨መንፈሳዊት ሴት በትዳር ህይወት
✨መንፈሳዊት ሴት በልጅ አስተዳደግ
ህይወት
✨መንፈሳዊት ሴት በማህበራዊ ህይወት ....እና ሌሎችም ርዕሰ ጉዳዮች የምንዳስስበት
የእህቶች ጉባኤእነሆ ተዘጋጀ!!! የዚህ ወር ጉባኤያችን:- 👉 እሁድ ሰኔ 7 👉 ከጠዋቱ 3:30 👉 በሰንበት ት/ት ቤቱ ህንፃ እህቴ ሆይ እህትሽን ይዘሽ ነይ!!! ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
