የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®
Відкрити в Telegram
ይህ ትክክለኛ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት የቴሌግራም ቻናል ነው:: /በመምህር ሲራክ ሰሎሞን/ በዚህ የቴሌግራም ቻናል:- ➮አስተማሪ እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን ➮የቅዱሳን ገድላት ➮ መዝሙሮችን ➮መንፈሳዊ ትምህሮቶችን ያገኛሉ። የመወያያ ግሩፕ: https://t.me/+QKiTJYGJvYpmNWM0 የዚህ ግሩፕ ዓላማ ለበጎ ምግባር ቃለ እግዚአብሔርን መማማር ነዉ::
Показати більше1 115
Підписники
+124 години
+67 днів
+2530 день
Архів дописів
1 115
#እግዚአብሔርማ_አልረሳኝም
በጸሎት ኃይል የሚያምን አንድ ጽኑዕ ክርስቲያን ነበር፡፡ ይህም ክርስቲያን ጥሪት የሌለው ደሃ፣ የሚበላ የሚቸግረው ረሃብተኛ፣ ልብሱ በላዩ ላይ አልቆ የታረዘ ምስኪን ነው፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በጸሎት ሕይወቱ የነበረውን ትጋት በቅርበት ያውቅ የነበረው አንድ ወዳጁ እየተቆጣ 'ቢያንስ ለረሃብህ ማስታገሻ ቁራሽ ዳቦ እንኳን ማሰጠት ካልቻለ የአንተ ጸሎት ፋይዳው ምንድር ነው? ይቅርብህ በቃ! ፈጣሪህ አይሰማህም ማለት ነው' ሲል ተስፋ በሚያስቆርጥ ቃል ተናገረው፡፡ ያም ምስኪን ክርስቲያን እንዲህ ሲል መለሰለት፦ 'እግዚአብሔርማ አልረሳኝም። ለአንዱ ሰው ከዕለት እንጀራው የበለጠ አትርፎ በመስጠት ለእኔ እንዲያካፍለኝ መልእክተኛ አድርጎት ነበር፡፡ ነገር ግን ይህን አደራ የተቀበለው ሰው ዘነጋኝ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ሳይሆን አድራሹ ሰው ረስቶኛል!'
መጻሕፍት እንደሚያስተምሩን "የዕለት እንጀራችንን ስጠን" የሚለው ጸሎት ለመነኮሳት ሲሆን "ለዕለት"፣ በዓለም ለሚኖሩ ሰዎች ሲሆን ደግሞ "ለዓመት" የሚሆን እንጀራ ስጠን ማለት ነው። ታዲያ ለምን አንዳንዶች ከዓመት የሚተርፍ ብዙ እንጀራ ሲያገኙ፣ ሌሎች ደግሞ ለዕለት እንኳን የሚሆን ቁራሽ ያጣሉ ? መቼም 'ለሰው ፊት የማያዳላ' እግዚአብሔር "አድልዎ ቢኖርበት ነው" ብለን የድፍረት ቃል በእርሱ ላይ አንናገርም። (ሐዋ 10፥34) ይህ የሆነው እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርት አትርፈው ያገኙ ሰዎች ምንም የሌላቸውን እንዲረዱ እና መግቦት የባሕርይው የሆነውን አምላካቸውን በጸጋ እንዲመስሉት ነው። በዚሁም ላይ በፈጠራቸው ሰዎች መካከል ያለውን የመተዛዘንና የፍቅር ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ነው፡፡
'የዕለት እንጀራችንን ስጠን ለዛሬ' ብለን የለመንነው አምላክ ከዓመት እንጀራችን በላይ አትርፎ የሚሰጠን፣ የሚበቃንን ያህል ተመግበን በቀረው ለሌሎች አድራሽ መልእክተኞች እንድንሆን ነው። ስለዚህ ይህን የተጣለብንን አምላካዊ አደራ ባለመወጣት ድሆችን አንበድል፤ ተማርረው ከፈጣሪያቸውም ጋር እንዲጣሉ አናድርጋቸው።
የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
«ወደ_ቤታችን_ስንመለስ» ሉቃ ፩፭ ፥ ፲፩- ፳፬
✍🏽አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት። ከእነርሱም ታናሹ አባቱን "አባቴ ሆይ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን ክፍል ስጠኝ" አለው። ገንዘቡንም አካፈላቸው። ከጥቂት ቀንም በኋላ ታናሹ ልጅ ገንዘቡን ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ። ከዚያም እያባከነ ገንዘቡንም በተነ። ሁሉንም ከከሰረ በኋላ በዚያች አገር ጽኑ ራብ ሆነ እርሱም ይጨነቅ ጀመር። ሄዶም ከዚያች አገር ሰዎች ከአንዱ ጋር ተዳበለ እርሱም እሪያ (አሳማ) ሊያሰማራ ወደ ሜዳ ሰደደው። እሪያዎችም ከሚበሉት አሰር ሊጠግብ ይመኝ ነበር የሚሰጠውም አልነበረም። ወደ ልቡም ተመልሶ እንዲህ አለ "እንጀራ የሚተርፋቸው የአባቴ ሞያተኞች ስንት ናቸው? እኔ ግን ከዚህ በራብ እጠፋለሁ። ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና፤ አባቴ ሆይ በሰማይና በፊትህ በደልሁ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ " እለዋለሁ አለ። ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው። ልጁም " አባቴ ሆይ በሰማይና በፊትህ በደልሁ ወፈ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም" አለው። አባቱ ግን ባሪያዎቹን አለ "ፈጥናችሁ ከሁሉ የተሻለ ልብስ አምጡና አልብሱት ለእጁ ቀለበት ለእግሩም ጫማ ስጡ የሰባውንም ፊሪዳ አምጥታችሁ እረዱት እንብላም ደስ ይበለን ይህ ልጄ ሞቶ ነበርና ደግሞም ሕያው ሆኖአል ጠፍቶም ነበር ተገኝቶአልም። ልጁ በመመለሱ በአባቱ ጥልቅ ደስታ ሆነ።
#አባት የተባለው ስለእኛ ብሎ ፍቅር አሸንፎት ወደ ምድር የመጣው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው
#የጠፋው_ልጅ የተባለው እኛ ሰዎች ነን ከሞቀው ቤታችን ፍቅር ሰላም ረድኤት በረከት ከሞላበት ከአባትችን እቅፍ ከቅድስት ቤተክርስቲያን እርቀን በዚች ከንቱ ዓለም ስንባዝን ዓለም እንደ ሸንኮራ አገዳ መጣ ስጥለን አንድ ቀን መባዘናችን፣ ሀጢያት መስራታችን እና መበደላችን ታውቆን ወደ አባታችን ቤት ስንመለስ የቀድሞ ክፋታችንን የቀድሞ ሀጢያታችን የቀድሞ በደላችንን አያይም፤ እንዲህ አድርገሀል እንዲህ ሰርተሀል አይለንም። መድኃኒዓለም ደስ የሚለው ወደ ቤቱ መመለሳችን ነው። በንስሀ ሳሙና ታጥበን ፍቅር እና ሰላም ወደ አለበት ወደ ቤታችን ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን ስንመለስ በመንግስተ ሰማያት በእግዚአብሔር እና በመላእክት ዘንድ ትልቅ ደስታ ነው።
በድያለው ኃጢአት ሰርቻለሁ እንዴት ትችው ወደ ወጣሁት ቤት እመለሳለሁ አንበል። ልዑል እግዚአብሔር ያለፈውን በደላችንን ያለፈውን ክፋታችንን ያለፈውን ሀጢያታችንን አይመለከትም ያለፈውን አይቆጥርብንም ገብቶን መመለሳችን ብቻ ነው የምያው አቅፎ ስሞ ይቀበለናል የቀድሞውን ማንነታችን ቀይሮ አዲስ ሰው ያደርገናል የፍቅር አምላክ ስለሆነ። ስለዚህ ዛሬ ነገ ሳንል "ንስሀ" እንገባ መቼ እንደምናልፍ አናውቀውም። የመዳን ቀን አሁን ነው እንደሚል ቅድስ መፅሐፍ ንስሀ እንገባ። ነፍስ አባት የሌለን ነፍስ አባት እንያዝ።
ለንስሀ የተዘጋጀ ልቦና ለሁላችንም እንደ ቸርነቱ ያድለን። ንስሀ ገብተን ክቡር ደሙን ቅዱስ ስጋውን ተቀብለን ተስፋ የምናደርጋትን እርስት መንግስተ ሰማያትን እንድንወረስ የአምላካችን ቅዱስ ፍቃድ እንደ ቸርነቱ ይሁንልን።
የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
#ተጠንቅቀህ_ታውቃለህን?
✍🏽አንድ በጣም ትልቅ ቆሻሻ የጫነ ጋሪ የሚገፋ ሰው ወደ ቤትህ መጥቶ "እባክህ በርህን ክፈትልኝና ይህን ቆሻሻ አንተ ቤት ላራግፈው?" ቢልህ፣ "ውይ የሚጥልበት ቢያጣ ነው። ባይቸገር ወደ እኔ አይመጣም ነበር" ብለህ ደጅህን ከፍተህ ታስገባዋለህ? በፍጹም፤ እንደውም "እንዴት ብታስበኝ ነው? ምነው ስታየው ቤት አልመሰለህም? እንዴት ሰው በሚኖርበት ቤት ቆሻሻ ካልደፋሁ ትላለህ? ስትል ለጠብ ትጋበዛለህ። መደፈርህ እያንገበገበህ "እምቢ!" ብለህ ትቆጣለህ። በእርግጥም ያስቆጣል።
ግን ሌላ የሚከፋ ሽታ ያለው ቆሻሻን ጭኖ ለመጣ ባላጋራ እኮ በፈቃድህ የከፈትከው ቤት አለ። "የምን ቤት?" ብለህ ብትጠይቀኝ "ልብህ ነዋ" ብዬ እመልስልሃለሁ፤ "ማን ይኖርበታል?" ካልኸኝም "እግዚአብሔር ነዋ" እልሃለሁ።
አንተ ለመኖሪያ ቤትህ ጽዳት የምትጠነቀቀውን ያህል የያዕቆብ አምላክ ለሚያርፍበት ኅሊናህ ተጠንቅቀህ ታውቃለህ? ሰይጣን ጭኖ የሚያመጣውን የኃጢአት ቆሻሻ ሁሉ እሺ ብለህ ወደ ልብህ በማስገባት የፈጣሪህን መቅደስ ለምን ታቆሽሻለህ? ንጹሑ እግዚአብሔር የሚያድርበትን ቤት ሊያቆሽሽ በመጣ ሰይጣን ላይ እንዴት አልተቆጣህም? ድፍረቱ ለምን አላብከነከነህም?
እግዚአብሔር አንተ ልትኖርበት ከምትፈልገው ንጹሕ ቤት የበለጠ ጽዱ መቅደስ የማይፈልግ ይመስልሃል?
የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ
እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የመድኃኒት እናት ሆይ በመዓልትም በሌሊትም አማላጅ ትሆኝኝ ዘንድ እሰግድልሻለሁ። እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ከእርሱ የሚገኘውን ኃይልን ይሰጠኝ ዘንድ ከአንቺ ወደ ተወለደው ልጂሽ እንድትለምኝልኝ እማጸናለሁ። በመወለዱ ድኅነት የተገባሽ ሆነሻልና። በሔዋን ውድቀት ሆነ። አብ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ሰላምን የላከልሽ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ሰላምታን ሰጠሽ ሰገደልሽም። ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ሰላምታ ይገባሻል። እነሆ ትጸንሻለሽ ልጅም ትወልጃለሽ፣ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ። የልዑል ኃይል ይጸልልሻል፤ ከአንቺ የሚወለደውም ቅዱስ ነው፤ እርሱም የልዑል ልጅ ይባላል አለሽ።
በተቀደሰው ስሙ ኅሊናዬን ልቡናዬን እንዲቀድስ ትለምኝው ዘንድ እማጸንሻለሁ። ንጽሕት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የሕይወት ቃል ከአንቺ ሰው ይሆን ዘንድ በሥጋ ከአንቺ ይወለድ ዘንድ የተገባሽ የመድኃኒት እናት እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ከአንቺ በመዋሐዱም እኛ ዳንን። እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። በእናታቸው ማሕፀን ሕፃናትን የሚስላቸው ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም ሁሉን የፈጠረው በማሕፀንሽ የተቀረጸብሽ የብርሃን እናት ሆይ እሰግድልሻለሁ። ረቂቅ ድንቅ ምሥጢርን ዓለምንም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣውን እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እለምንሻለሁ። በመንፈሳዊ ልደት ይወልደኝ ዘንድ ወደ እርሱ ዓለምና አዳኝ ወደ ሆነች ዕውቀት ከፍ ያደርገኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እለምንሻለሁ፣ አማጸንሻለሁ።
የሕይወት መገኛ የነገሥታት ንጉሥ የባለሥልጣናቱ ባለሥልጣን የአምላኮችን አምላክ በበረት ያስተኛሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። አዳኝ ስለሆነው ስለስምሽ እንዲረዳኝ ትለምኝልኝ ዘንድም ወደ አንቺ እለምናለሁ፤ እማልዳለሁም። በማየቱ አዳምንና ከእርሱ ጋር ያሉትን ሁሉ ነጻ ያወጣውን በክንድሽ የታቀፍሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ።
በረቂቅ መመልከቱ እንዲመግበኝ ከሰይጣን መሰናክልም እንዲያድነኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እለምንሻለሁ፤ እማጸንሽማለሁ። ዓለማትን ሁሉ ለሚመግበው ጡትሽን ያጠባሽው የመድኃኒት እናት እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ፤ የሰማይ ኃይላት የሚመገቡትም ከእርሱ ነው። ነፍሴን በፈቃዱ ከጸጋው ይመግባት ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ።
እመቤቴ ድግል ማርያም ሆይ ተወዳጁ ልጅሽ እንደ ፍጹም ፈቃዱ እንዲመግበኝ በየጊዜው በየሰዐቱ አማላጅ ሁኚኝ። ይህችም ወደ እርሱ የምትለምኝውን ልመና የተመላች መጽሐፍ ናት ። የለመንሁትን ሁሉ እርሱ ያደርግልሻልና። ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ። ሰላምን ስለሰጠሽ ስለ አብ ከአንቺ ስለተወለደው አንቺንም ስለተዋሐደው ከአንቺም ሰው ስለሆነው ስለወልድ ፣ ስለቀደሰሽ፣ ከሦስቱ ቅዱስ ለአንዱ ማደሪያ ለመሆን እስከሚገባሽ ድረስ ስላነጻሽ ስለመንፈስቅዱስም እለምንሻለሁ። አገልጋይሽን ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ። ለዘለዓለሙ አሜን።
#ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሳርያ
የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
#ልጅህን_ጾምና_ጸሎት_አስለምደዉ
=> ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ መጽሐፍ ከገጽ 122 እስከ 124 በተጻፈዉ ምንባብ ላይ ልጅህን ጾምና ጸሎት አስለምደዉ ይላል! ሁልጊዜ ሳይሆን በሳምንት ሁለት ቀን ይኸውም ረቡዕ እና ዓርብ መጾምን እና ጸሎት ማድረስን አስለምደው፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንዲሳለምም አድርገው፡፡
ተውኔት በሚያልቅበት በማታው ክፍለ ጊዜም ልጅህን ከተውኔት ቤት የሚወጡ ሰዎችን አሳየው፡፡ ትልልቅ ሰዎች እንደ ምን በዋዛና በፈዛዛ እንደ ተጠመዱ፣ ወጣቶችም እንደ ምን በምኞት ተቃጥለው እየወጡ እንደ ኾነ አሳየው፡፡ ልጅህንም እንዲህ ብለህ ጠይቀዉ፡- "እነዚህ ሰዎች ተዉኔት በማየታቸዉ ምን ጥቅም አገኙ? ከሐፍረት፣ ከሕሊና ወቀሳና ኵነኔ ውጭ ምንም አላገኙም፡፡" ከእንደዚህ ዓይነት ትርኢቶችና ጭፈራዎች መራቅና ራስን መጠበቅ በጎ ምኞት ብሎም ሌላ በጎ ምግባር እንዲኖር የሚያደርጉት አስተዋጽኦ እንዲሁ ቀላል እንዳልኾነ ንገረው፡፡
ዳግመኛም ከፍ ባለ ፍርሐት እና መንቀጥቀጥ መጸለይን አስተምረዉ፡፡ እንዲህ እንድታደርግ ስነግርህም ልጅ እንደዚህ ማድረግ እንደማይችል በፍጹም አትንገረኝ፡፡ ልጅ አስተዋይና ንቁ ከሆነ እነዚህን በእውነት ያለ ሐሰት ያደርጋቸዋልና፡፡ እንደ እነ ዳንኤልና ዮሴፍ የመሳሰሉ ለዚህ ማሳያ የሚሆኑን የጥንት ሰዎችም አሉ፡፡ ከዚያ በፊት ከሌሎች ከታላላቅ ወንድሞቹ ይልቅ በአባቱ ዘንድ ተወዳጅ ያደረገው ምን እንደ ሆነ አስብ፤ አሰላስልም እንጂ ዮሴፍ ዐሥራ ሰባት ዓመቱ እንደ ነበረ አትንገረኝ፡፡
“ዮሴፍ እንዲህ ያደረገው በዐሥራ ሰባት ዓመቱ ስለ ኾነ ትልቅ ነው” ብለህ ካልከኝም እኔም እንዲህ ብዬ እጠይቅሃለሁ፡- ያዕቆብ ከእርሱ ያነሰ አልነበረምን? ኤርምያስስ? ዳንኤልስ ቢኾን [ በባዕድ አገር ሆኖ ፊቱን ወደ ኢየሩሳሌም አዙሮ ሲጸልይ ] ገና ዐሥራ ኹለት ዓመቱ አልነበረምን? ሰሎሞንስ፡- “እርሱ በፊትህ በእዉነት እና በጽድቅ፣ በልብም ቅንነት ከአንተ ጋር እንደ ሄደ፤ ከአባቴ ከባርያህ ከዳዊት ጋር ታላቅ ቸርነትን አድርገሃል፡፡ ዛሬ እንደ ሆነም በዙፋኑ ላይ የሚቀመጥ ልጅ ሰጥተህ ታላቁን ቸርነትህን አቆይተህለታል፡፡ አሁንም አቤቱ አምላኬ ሆይ! እኔን ባሪያህን በአባቴ በዳዊት ፋንታ አንግሠኸኛል፡፡ እኔም መውጫዬንና መግቢያዬን የማላውቅ ታናሽ ብላቴና ነኝ፡፡ ባሪያህም ያለው አንተ በመረጥኸው ሕዝብህ ስለ ብዛቱም ይቈጠር ዘንድ በማይቻል በታላቅ ሕዝብ መካከል ነው፡፡ ስለዚህም ሰምቶ በሕዝብ ላይ መፍረድ ይችል ዘንድ መልካሙንና ክፉውንም ይለይ ዘንድ ለባሪያህ አስተዋይ ልቡና ስጠው፤ አለዚያ’ማ በዚህ በታላቅ ሕዝብ ላይ ይፈርድ ዘንድ ማን ይችላል?” በማለት ዕፁብ ድንቅ የኾነ ጸሎትን የጸለየው በዐሥራ ሁለት ዓመቱ አይደለምን? (1ኛ ነገ.3፡6-9)፡፡ ሳሙኤልስ የገዛ መምህሩን ራእይ በማየት የነገረው ገና በሕፃንነቱ ሳለ አይደለምን? (1ኛ ሳሙ.3፡17)፡፡ ስለዚህ “ልጅ ስለሆነ መጸለይ አይችልም” አትበል፡፡ በነፍሱ ሕፃን የሆነ ሰው አድጎም ቢሆን እነዚህን ነገሮች አያደርጋቸውምና፡፡
በመሆኑም ልጃችን በታላቅ ፍርሐት እና መንቀጥቀጥ ሆኖ መጸለይን ይልመድ፡፡ የቅድስና አኗኗር በሁለንተናው ላይ ይታተምበት፡፡ ከመሐላ፣ ከሚሰድቡት ሰዎች፣ የሌሎችን ስም ከማጥፋትና ከጥላቻ ከራቀ፣ ጎን ለጎንም ጾምንና ጸሎትን ገንዘብ ካደረገ እነዚህ ሁሉ ወደ ምግባር ወደ ትሩፋት ያደርሱት ዘንድ በቂ ናቸው፡፡
#በቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
✥••●◉ #ክፉ_ሃሳብን_እንዴት_እናሸንፍ ◉●••✥
💠 ክፉ ሀሳብ የሚባሉት ለምሳሌ የዝሙት ሀሳቦች፣ የሰውን መጥፎነት ማሰብ፣ ትንኮል እና ክፋትን ማሰብ፣ የቂምና በቀል ሀሳቦች፣ አሁን አሁን ደሞ የአብዛኛው ችግር እየሆነ የመጣው የሌሉ ነገሮችን እየፈጣጠሩ ዝምብሎ እያለሙ መደሰት (የቀን ቅዥት) ፣ የበዛ ሀዘን፣... ወዘት
💠 በአእምሮአችን የሚመላለሱ ክፉ ሀሳቦች ወደ ድርጊት ሳይደርሱ በፊት ማቆም ይገባል፤ ምናልባት ከሀሳብም አልፈን በድርጊት ለምናከናውናቸው ኃጢአቶችም እታች ያሉትን መንገዶች መከተል መፍትሄዎች ናቸው።
💠 ሰው ልተወው አልቻልኩም ይሄን ሀጥያት የሚለውን ሀጥያት በእነዚህ መንገድ መንገድ መተው ይችላል።
➊ ክፉ ሃሳብን በመልካም መተካት
🎚 ክፉ ሃሳብ ከኛ ዘንድ መጥተው እስኪያስጨንቁን እስኪያደክሙን መቆየት አይገባም አስቀድሞ ከእኛም ዘንድ እንዳይደርሱ እድል አለመስጠት ዋነኛ ማራቂያ መንገድ ነው፡፡
🎚 ይህውም በትርፍ ጊዜ ስራ ፈቶ እግር ዘርግቶ ከመቀመጥ ይልቅ መልካም በሆኑና ለነፍሳችን ሐሴት የሚሰጡ ነገሮችን በመስራት ማሳለፍ ያስፈልጋል፡፡
🎚 አእምሮን ዘወትር መልካም በሆኑ ተግባራት በሞላነው ቁጥር ጠላት ሰይጣን እኛን ለመጣል ሲመጣ አእምሮዋችን በመልካም ነገሮች ተይዞአልና ሊፈትነን አይቀርብም፡፡
🎚 ሰይጣን በከፉ ሃሳብ ሊጥለን ሲያደባ ክፍት ሆኖ ሲያገኘው የሰይጣንን ሃሳብ ለመቀበል የተመቸ ይሆናል፡፡
🎚 ክፉ ሃሳብ በአእምሮዋች ተፈጥሮም ከሆነ መልካም ነገሮችን በማሰብ መተካት ያስፈልጋል፤ አእምሮዋችን በአንድ ጊዜ ሁለት ነገሮች አእምሮዋችንበተመሳሳይ ተመስጦ (ጥልቀት) ሊያስብ አይችልም፡፡
🎚 ስለዚህም በክፉ ሃሳብ ፈንታ የምናስበው ሃሳብ ክፉውን ሃሳብ ለማጥፋት ይችል ዘንድ ጥልቅ ሊሆን ይገባዋል፡፡
🔘ለምሳሌ
🎚 በስራ ሊጠምዱ የሚችሉ የሚያመራምሩ ጥያቄዎች የሃይማኖት ጥያቄዎችና ትምህርቶች የቀደሙ መልካም ገጠመኞችን በማሰብ መመሰጥ የመሳሰሉት ጠቃሚ መንገዶች ናቸው፡፡
➋ ማንበብ
💠 አንድን ነገር በተመስጦ በምናነብት ጊዜ አእምሮዋችን በንባብ ይያዝና ክፉውን ሃሳብ ይረሳዋል፡፡
💠 መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፣ መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ ያላነበብናቸውን መጻህፍት ለምሳሌ፦ ልብወለድ የታሪክ መጻህፍት... ማንበብ ጠቃሚ ናቸው፡፡
💠 ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንዳንዶቻችን ሰነፎች ነን እና ለማንበብ ስብከቶችን፣ ትምህርቶችን ማዳመጥ።
➌ በጸሎትና በስግደት
🎚 እግዚአብሔርን ክፉ ሃሳብን እንዲያርቅልን በመማጸን በፊት በመንበርከክ ስግደትን በማቅረብ መማጸን ያስፈልጋል፡፡
🎚 ጌታ በወንጌል
✍️"እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኀለሁ" ብሎናልና ችግራችንን በጸሎት በልመና መጠየቅ አለብን፡፡
📖ማቴ 11፥28
🎚 ዳግመኛም ቅዱስ ጳውሎስ
✍️"በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ" ተብሏልና ሁሉ ወደ ሚቻለው ጌታ ጸሎት ምልጃን ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡
📖ፊልጵ 4፥6
➍ በስራዎች በመጠመድ
💠 በስራዎች መጠመድ የሰውን ትኩረት ወደ አንድ በመወሰን ሃሳቡ ወደ ሌላ እንዳይሄድ ያደርጋል፤ ምንም ሳይሰሩ ተዘልሎ መቀመጥ ግን በክፉ ሃሳብ ለመውደቅ ክፍት ይሆናል፡፡
💠 ለዚህም ነው አበው "ሰው ስራ ሲሰራ አንድ ሰይጣን ይፈትነዋል፤ ሳይሰራ ተዘልሎ ሲቀመጥ ግን በብዙ ሰይጣናት ይፈተናል" የሚሉት፡፡
💠 በገዳም ያሉ አባቶችም ስራን በመስራት ከኃጢአት ለመራቅ ይጠቀማሉ "ስራ ያጣ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል" የሚለውም ምሳሌያዊ አነጋገር የገደማውያ አበውን በስራ መጠመድ ህይወት ያሳያል፡፡
➎ ከሰው ጋር በማውራት
🎚 ክፉ ሃሳብ ባስጨነቁን ጊዜ ከወዳጆቻችን ጋር ስለ ልዩ ልዩ ጉዳዮች በማውራት ክፉውን ሃሳብ መርሳት ይቻላል፤ እያወሩ ማሰብ አይቻልምና፤ ራስን በማዝናናት በመጻፍ በማንበብ ክፉ ሃሳብን መርሳት ይቻላል፡፡
በሕይወታች የሚመጡብን ክፋ ሃሳቦች አምላከ ቅዱሳን ያርቅልን፤ የእናቱ ምልጃና ጸሎት ይጠብቀን::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን!
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
ድኻ ነኝ የምትለኝ ለምንድን ነው?
ሌሎች ሰዎችን ከማያድን ክርስቲያን በላይ የከፋ ምንም የለም፡፡ አንተ ሰው! ድኻ ነኝ የምትለኝ ለምንድን ነው? ኹለት ዲናር የጣለችዋ ሴት ትፋረድባሃለች፡፡ ከምናምንቴ ቤተሰብ እንደ ተወለድክ የምትነግረኝስ ለምንድን ነው? ሐዋርያትም ምናምንቴዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ታላላቅ መኾን ተችሏቸዋል፡፡ አለመማርህን ሰበብ አድርገህ አትንገረኝ፤ ሐዋርያትም ያልተማሩ ነበሩና፡፡
ባሪያ ብትኾንም እንኳ፣ ስደተኛ ብትኾንም እንኳ ሥራህን መሥራት ይቻልሃል፤ ሌሎችን መርዳት ይቻልሃል፤ ሰዎችን ማዳን ይቻልሃል፥ አናሲሞስም እንደ አንተ ዓይነት ሰው ነበርና (ፊልሞ.1፥10-11)፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ምን ወዳለ ማዕረግ ከፍ እንዳደረገውና ምን ብሎ እንደ ጠራው አድምጥ፡- “በእስራቴ ስለ ወለድሁት፡፡”
ወዳጄ ሆይ! እኔ እንኳን ሕመምተኛ ነኝ ብለህ አትንገረኝ፤ ጢሞቴዎስም እንደ አንተ ዘወትር ይታመም ነበር፡፡
ፍሬ የማያፈሩ ዛፎች እንደ ምን ብርቱዎችና ተወዳጆች፣ ግዙፋንና ሐመልማላውያን እንደዚሁም ረጃጅም እንደ ኾኑ አላየህምን? የፍራፍሬ ቦታ ቢኖረን ግን ፍሬ የሚያፈሩት ሮማንንና ወይራን እንተክላለን እንጂ እነዚህ ፍሬ የማይሰጡንን ዛፎች አንተክልም፡፡ ምክንያቱም እንዲሁ ለዓይን ማረፊያ ለማየት ካልኾነ በስተቀር ሌላ ጥቅም የላቸውምና፡፡
የራሳቸውን ጥቅም ብቻ የሚመለከቱ፣ ሌሎች ሰዎችንም የማይረዱ ክርስቲያኖችም እንደ እነዚህ ዛፎች ናቸው፡፡ እንዲያውም ከእነዚህ ዛፎችም የባሱ ናቸው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ሰዎች የሚቆረጡት ለእሳተ ገሃነም ነው፡፡ ዛፎቹ ግን ቢያንስ ቢያንስ ጠረጴዛም ወንበርም ለመሥራት ይጠቅማሉ፡፡ ለቤት መሥሪያ ይጠቅማሉ፡፡ አጥር ቅጥር ኾነው ያገለግላሉ፡፡
እነዚያ አምስቱ ደናግል እንደዚህ ነበሩ (ማቴ.25፥1)፡፡ ርግጥ ነው ንጽህናቸውን የጠበቁ ነበሩ፡፡ ለሚያያቸው ኹሉ ግሩም የኾነ ጠባይ የነበራቸው ነበሩ፡፡ ሥርዓት ያላቸው ነበሩ፡፡ ይህ ኹሉ ግን ምንም አልጠቀማቸውም፡፡ ወደ እሳተ ገሃነም ከመጣ’ል አልታደጋቸውም፤ ዘይት የተባለው ምጽዋት አልነበራቸው’ማ! ክርስቶስን በነዳያን አማካኝነት የማይመግቡትም ዕጣ ፈንታቸው ጽዋ ተርታቸው ይኸው ነው የሰነፎቹ ደናግል ዕጣ!
አንተ ሰው ልብ ብለህ አስተውል! እነዚህ ደናግል በግል ኃጢአታቸው አልተነቀፉም፡፡ በዝሙት ወይም በሐሰት ምስክርነት አልተወቀሱም፡፡ በፍጹም! ይልቁንም የተነቀፉትና የተወቀሱት ሌሎች ሰዎችን ባለመጥቀማቸው ነው፡፡
እንደዚህ ከኾነ ታዲያ ሰዎች ክርስቲያን ተብለው ሊጠሩ የሚችሉት በምን መመዘኛ ነው? እኮ በምን መስፈርት? አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ! በሊጥ ውስጥ የተጨመረ እርሾ ሊጡን እንዲቦካ ካላደረገው እንዲሁ እርሾ ተብሎ መጠራት ብቻውን ምን ይረባዋል? ዳግመኛም ወደ እርሱ የቀረቡትን ሰዎች መዓዛው ካልሸተታቸውና ቤቱን ካላወደው በቀር ከርቤ በከርቤነቱ ምን በቁዔት አለው?
ሌሎች ሰዎችን መርዳት አይቻለኝም ብለህ አትንገረኝ፡፡ እንዲያውም ልንገርህ፤ አንተም ስማኝ፡- አንተ በእውነት ክርስቲያን ከኾንክ ሌሎች ሰዎችን አለመርዳት የማይቻል ነው፡፡ ዕጣን መዓዛ እንዲኖረው፣ እርሾም ሊጥን እንዲያቦካ ተፈጥሮው እንደ ኾነ ኹሉ፥ አንድ ክርስቲያንም በስም ክርስቲያን ከመባል አልፎ በእውነት ያለ ሐሰት ክርስቲያን ከኾነ ሌሎች ሰዎችን መርዳት መቻሉ፣ ሌሎችን የሚጠቅም ሥራ መሥራቱ ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነው፡፡
ስለዚህ አይኾንልኝም፤ አይቻለኝም በማለት እግዚአብሔርን አታማርር፡፡ ፀሐይ ብርሃኗን በእኔ ላይ ማብራት አይቻላትም ካልክ ፀሐይን እየሰደብካት ነው፡፡ ልክ እንደዚሁ አንድ ክርስቲያንም ሌሎች ሰዎችን ሊጠቅማቸው አይችልም የምትል ከኾነ እግዚአብሔርን እየሰደብክ [ሎቱ ስብሐትና] ሐሰተኛም እያደረግኸው ነው፡፡ ምክንያቱም አንድ ክርስቲያን ሌሎች ሰዎችን ካለመርዳትና ካለመጥቀም ይልቅ ፀሐይ ሙቀትና ብርሃን ባትሰጥ ይቀላል፡፡ እንደዚህ ከሚኾን ብርሃን ወደ ጨለማ መቀየር ይቀላል፡፡
እናስ? እና’ማ አይቻለኝም አትበለኝ፡፡ የማይቻለው መርዳት አለመቻል ነውና፡፡ አይኾንልኝም እያልክ በከንቱ እግዚአብሔርን አታማርር፡፡
ሕይወታችንን በአግባቡና በሥርዓቱ የምንመራ ከኾነ እነዚህን ነገሮች ኹሉ በቀላሉ ማድረግ ይቻለናል፤ እነዚህ ነገሮች ሊደረጉ ግድ ነው፡፡ በመቅረዝ ላይ የተቀመጠ ሻማ ብርሃኑን መደበቅ እንደማይቻለው ኹሉ ክርስቲያንም የእውነት ክርስቲያን ከኾነ ብርሃኑም መሸሸግ አይቻለውም፡፡ ስለዚህ እውነተኞች ክርስቲያኖች ከኾንን ሌሎች ሰዎችን መርዳት መጥቀምም ችላ አንበል፡፡
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
#ቅዱስ_ባሕራን_ቀሲስ
✍🏽የደጋግ ክርስቲያኖች ግን የድሆች ልጅ:
¤=> በሕጻንነቱ በግፍ ወደ ባሕር የተጣለ:
¤=> በእግዚአብሔር ጥበብ አድጎ የግፈኛውን ንብረት የወረሰ:
¤=> በመልካም ትዳር በቅስና ያገለገለ:
¤=> ምጽዋትን ያዘወተረ: አብያተ ክርስቲያናትን ያሳነጸ ደግ ክርስቲያን ነው::
¤=> በዚህች ቀን አርፎ ቅዱስ ሚካኤል ወዳጁ በዕረፍተ ገነት አኑሮታል::
"በሰማይም ሰልፍ ሆነ:: ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉ:: ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ:: አልቻላቸውምም:: ከዚያም ወዲያ በሰማይ ሥፍራ አልተገኘላቸውም:: ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ወደ ምድር ተጣለ::" (ራዕይ. 12:7)
አምላካችን እግዚአብሔር ከቅዱስ ባሕራን ቀሲስ በረከት ይክፈለን:: አሜን::
የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
#ቅዱስ_ላል_ይበላ_ንጉሥ
✍🏽በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ ላይ በሃገራችን የነገሠው ቅዱስ ላሊበላ:-
¤=> በብሥራተ መልአክ ተወልዷል
¤=> ቅዱሳት መጻሕፍትን ገና በልጅነቱ አጥንቷል
¤=> የንጉሥ ዘር ቢሆንም በጾምና ጸሎት: በትሕርምት አድጓል
¤=> በወንድሙ ቢገረፍም ቂም አልነበረውም
¤=> ስለ ወዳጆቹ ፍቅር መርዝ ጠጥቷል
¤=> በዙፋን ላይ የኢትዮዽያ ንጉሥ ሆኖ ቢቀመጥም እርሱስ አኗኗሩ ገዳማዊ ነበር
¤=> ከተባረከች ሚስቱ ቅድስት መስቀል ክብራ ጋር አንዲት ማዕድ ብቻ በቀን ይቀምሱ ነበር:: ለዛውም ለምለሙን ለነዳያን ሰጥተው እነርሱ የሚበሉት የእንጀራውን ቅርፍት (ጠርዝ) ብቻ ነበር::
በአካለ ሥጋ ወደ ሰማያት ተነጥቆ ብዙ ምሥጢራትን አይቷል
¤=> በምሳሌውም ሃገረ ሮሃን (ላስታን) ገንብቷል
¤=> ዛሬም ድረስ ምስጢር የሆኑት ፍልፍል አብያተ መቃድስ የእጆቹ ሥራዎች ናቸው::
ሥራውን ከፈጸመ በኋላ መንግሥቱን ለቅዱስ ነአኩቶ ለአብ አውርሶ: በመንኖ ጥሪትና በቅድስና ኑሮ በዚሕች ቀን አርፏል:: ጌታችን ስምህን ያከበረ: ዝክርህን የዘከረ: ከቤትህ ያደረውን: ከርስተ መንግስተ ሰማያት አካፍለዋለሁ ሲል ቃል ኪዳን ገብቶለታል::
በረከቱን: ክብሩን ያድለን::
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
#ቅዱስ_ሚካኤል_ሊቀ_መላእክት
✍🏽ቅዱስ ሚካኤል በጥንተ ተፈጥሮ በኢዮር: ኃይላት በተባሉት ነገደ መላእክት ተሹሞ ነበር:: ሳጥናኤል በካደ ጊዜ እግዚአብሔር ባወቀ: አንድም በትሕትናውና ደግነቱ በ99ኙ ነገደ መላእክት ላይ ሁሉ ተሹሟል::
ከፍጥረት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የቅዱስ ሚካኤልን ያሕል ክብርና ርሕሩሕ የለም:: በምልጃውም: በረዳትነቱም የታወቀ መልአክ ነው:: መጽሐፍ "መልአከ ምክሩ ለእግዚአብሔር" ይለዋል:: "ወስሙ መስተሣሕልም" ይለዋል:: ቂም የሌለው: ለምሕረት የሚፋጠን: ደግ መልአክ ነውና::
በብሉይ ኪዳን በመከራ ለነበሩ ቅዱሳን ሁሉ ሞገስ: ረዳትና አዳኝ ቢሆናቸው "መጋቤ ብሉይ" ተሰኝቷል:: እሥራኤልን 40 ዘመን በበርሃ መርቷል: መግቧልም:: ቅዱስ መጽሐፍ ስለ እርሱ ብዙ ይላል:: (ዘፍ. 48:16, ኢያ. 5:13, መሳ. 13:17, ዳን. 10:21, 12:1, መዝ. 33:7, ራዕይ. 12:7)
ደስ የሚለው ደግሞ ርሕሩሑ መልአክ ከእመቤታችን ጋር ልዩ ፍቅር አለው:: ከእናቷ ማሕጸን ጀምሮ እስከ ዛሬ እነሆ አብሯት አለ:: ደስ ብሎት ይታዘዛታል:: ማማለድ ሲፈልግም "እመቤቴ ሆይ! ቅደሚ" ይላታል:: ወደ እሳት መጋረጃ አብረው ገብተው ለዓለም ምሕረትን: በረከትን ያወርዳሉ::
ቅዱስ ሚካኤልን በዚሕች ዕለት ስለ እነዚህ ነገሮች እናከብረዋለን:-
1. በመላእክት ሁሉ ላይ አለቃ ሆኖ መሾሙን
2. ቅዳሴ ቤቱን (ግብፅ ውስጥ)
3. ቅድስት አፎምያን መርዳቱን
4. ቅዱስ ባሕራንን መጎብኘቱን
5. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን
6. ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረት የሚጠይቅበት ዕለት ነውና::
ሊቀ መላእክት በክንፈ ረድኤቱ ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን::
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
#ቅዱስ_ሚካኤል_ሊቀ_መላእክት
✍🏽ቅዱስ ሚካኤል በጥንተ ተፈጥሮ በኢዮር: ኃይላት በተባሉት ነገደ መላእክት ተሹሞ ነበር:: ሳጥናኤል በካደ ጊዜ እግዚአብሔር ባወቀ: አንድም በትሕትናውና ደግነቱ በ99ኙ ነገደ መላእክት ላይ ሁሉ ተሹሟል::
ከፍጥረት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የቅዱስ ሚካኤልን ያሕል ክብርና ርሕሩሕ የለም:: በምልጃውም: በረዳትነቱም የታወቀ መልአክ ነው:: መጽሐፍ "መልአከ ምክሩ ለእግዚአብሔር" ይለዋል:: "ወስሙ መስተሣሕልም" ይለዋል:: ቂም የሌለው: ለምሕረት የሚፋጠን: ደግ መልአክ ነውና::
በብሉይ ኪዳን በመከራ ለነበሩ ቅዱሳን ሁሉ ሞገስ: ረዳትና አዳኝ ቢሆናቸው "መጋቤ ብሉይ" ተሰኝቷል:: እሥራኤልን 40 ዘመን በበርሃ መርቷል: መግቧልም:: ቅዱስ መጽሐፍ ስለ እርሱ ብዙ ይላል:: (ዘፍ. 48:16, ኢያ. 5:13, መሳ. 13:17, ዳን. 10:21, 12:1, መዝ. 33:7, ራዕይ. 12:7)
ደስ የሚለው ደግሞ ርሕሩሑ መልአክ ከእመቤታችን ጋር ልዩ ፍቅር አለው:: ከእናቷ ማሕጸን ጀምሮ እስከ ዛሬ እነሆ አብሯት አለ:: ደስ ብሎት ይታዘዛታል:: ማማለድ ሲፈልግም "እመቤቴ ሆይ! ቅደሚ" ይላታል:: ወደ እሳት መጋረጃ አብረው ገብተው ለዓለም ምሕረትን: በረከትን ያወርዳሉ::
ቅዱስ ሚካኤልን በዚሕች ዕለት ስለ እነዚህ ነገሮች እናከብረዋለን:-
1. በመላእክት ሁሉ ላይ አለቃ ሆኖ መሾሙን
2. ቅዳሴ ቤቱን (ግብፅ ውስጥ)
3. ቅድስት አፎምያን መርዳቱን
4. ቅዱስ ባሕራንን መጎብኘቱን
5. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን
6. ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረት የሚጠይቅበት ዕለት ነውና::
ሊቀ መላእክት በክንፈ ረድኤቱ ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን::
1 115
ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎምያ ያዳነበት ዕለት፡-
ታሪኩ እንዲህ ነውቅድስት አፎምያ ሀገሯ ኪልቅያ ነው፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ መስፍነ ኪልቅያ ነበረ፡፡ እርሷም በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ደገኛ ሴት ናት፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ ነበር፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደ ደረሰባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እርሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ ባሏም ታሞ ሞቶ ከሀብቷ ከንብረቷ እየሰጠች እየመጸወተች በጾም በጸሎት ተወስና ትኖር ነበር፡፡ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ደግ መነኩሴ መስሎ አጋንንትን መነኮሳይያት አስመስሎ መጥቶ ከደጅ ሆኖ አስጠራት፡፡
እርሷም "ከቤትገብታችሁ በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ፊት ጸልዩልኝ" አለቻቸው፡፡ ሰይጣናቱም "እኛማ በነግህ ጸልየናል?" አሏት፡፡ ቀጥሎም ሰይጣን."... እንደው አንቺ ግን ይህ ሁሉ ጾም ጸሎት ምን ያደርገልሻል? ሀብትሽን ሰጥተሸ መጨረስሽስ ስለምንድን ነው? በዚያ ላይ አንቺ ስትደክሚ የሚደግፍሽ ስታረጂ የሚጦርሽ ልጅ የለሽም ሁለተኛ ማግባት ኃጢአት መስሎሻልን? እነ አብርሃም እነ ዳዊት ከብዙ ሴቶች ብዙ ልጆች ወልደው የለምን? አሁንም ቤት ሰሪ ጎመን ዘሪ ልጅ ያስፈልግሻልና ባል አግቢ፣ እሺ በይኝ" አላት፡፡
ቅድስት አፎምያም "አባ ቆብህ መልካም ነበር ንግግርህ ግን ክፉ ነው፣ አትጹሚ አትጸልዩ ያልከኝ ጌታ ምጽዋት አበድር እመስዋዕት ብሎ የለምን? ሁለተኛ ባል አግቢ ማለትንስ ከምን አገኘኸው? እርግቦች እንኳን ባሎቻቸው ከሞቱባቸው ከሌላ ወንድ አይቀርቡም ታዲያ ጥንት በንጽሕና ሊኖር የተፈጠረ ሰው ሁለተኛ አላገባም ቢል ዕዳ ፍዳ ሊሆንበት ነውን?" ብላ ሞገተችው፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ አይቷታልና ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ ከላይ እንዳየነው ..በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ ሌላ ባል አግብታ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ እነርሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እርሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡
በሰኔ 12 ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድር ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታበቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና "የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?" በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው "በእኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም" ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ። ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእርሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ በመቀጠልም ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ሰይጣናዊ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን "ድረስልኝ" እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደ የመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሰኔ 12 ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ: ላሊበላ: ቅድስት አፎምያ እና ቅዱስ ባሕራን ቀሲስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣አደረሰን።
#ሰኔ_12
በዚህች ቀን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል አፎምያን ከሰይጣን እጅ ያዳነበት ቀን ነው።
ዳግመኛም በዚህ ዕለት ቅዱስ ሚካኤል ባሕራንን የሞቱን ደብዳቤ ወደ ሕይወት የቀየረበት ዕለት ነው።
ይህ ዕለት ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ላልይበላ ያረፈበትም ቀን ነው።
አፎምያን ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ የታደጋት ቅዱስ ሚካኤል እኛንም በጥበቃው አይለየን::
የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
#ይህን_ማወቅ_ትወዳለህን?
"ሰው ሆይ! የሚጎዳህ ሀብትህ አይደለም፣ ድኽነትህም አይደለም። ሰው የሚጎዳው ክፉ ልብ ነው። ክፉ ልብ ደግሞ በሀብትም ሀብት በማጣትም የሚመጣ አይደለም።
ክፉ ልብ ሌሎች ክፉ ልቦችን ይወልዳል። እሳት እሳትን እየወለደ ብዙ ዕንጨቶችን እንደሚበላ ኹሉ ክፉ ልብም እንደዚህ ነው።
አንተ ሰው! ይህን ማወቅ ትወዳለህን? ክፉ ምግባር ወይም በጎ ምግባር በተፈጥሮ የሚገኙ አይደሉም። እነዚህ ኹለቱ ከክፉ ልብ ወይም ከመልካም ልብ የሚገኙ ናቸው።"
የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
#ሰድበውኛልና_ልበቀላቸው_አትበል
"አንድ ሐኪም አእምሯቸውን የሳቱ ሰዎች ቢሰድቡት፥ ስድባቸውን ከቁም ነገር አይቆጥረውም፡፡ እንዲህ አእምሯቸውን እንዲስቱ ያደረጋቸውን ምክንያት ያስወግድላቸው ዘንድ ይተጋል እንጂ፡፡ 'ሰድበውኛል' ብሎ የራሱን ጥቅም አያይም፤ የሕሙማኑን እንጂ፡፡ በጥቂቱም ቢኾን ሻል ካላቸውና ራሳቸውን መግዛት የሚችሉ ከኾነም እጅግ ደስ ይሰኝባቸዋል፡፡ ውስጡ በፍጹም ሐሴት ይሞላል፡፡ መድኃኒት መስጠቱን በፊት ከሚያደርግላቸው ይልቅ ተግቶ ይሰጣቸዋል፡፡ 'ከዚህ በፊት ሰድበውኛልና ልበቀላቸው' ብሎ በፍጹም አያስብም፡፡ ይበልጥ እንዲጠቀሙና ወደ ቀድሞ ጤናቸው ይመለሱ ዘንድ ተግቶ ይሠራል እንጂ፡፡
"እግዚአብሔርም እንደዚህ ነው፡፡ ምንም እንኳን እጅግ ጥልቅ በኾነ ኃጢአት ውስጥ ብንወድቅም፥ ኹሉንም ነገር የሚያደርገው እኛን ከመቅጣት አንጻር አይደለም፤ የሚቀጣን ስለ ሠራነው የኃጢአት ዓይነት አይደለም፡፡ ከዚህ ሕመማችን እንድንፈወስ ብሎ ነው እንጂ፤ በዚሁ መንገድ ሊመለሱ ይችላሉ ብሎ በማሰብ ነው እንጂ፡፡"
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
“#በፍቅር_ተመላለሱ”
ኤፌ. 5:12
#ፍቅር የሁሉም ነገር መሠረት ነው! ፍቅር ባለበት ቦታ ቁጣ፣ ጩኸት፣ ስድብ የለም፡፡ እነዚህ ሁሉ ነገሮች ተወግደዋል፡፡ ጳውሎስ አሳዳጅ ሳለ በእግዚአብሔር ፍቅር ድኗል፡፡ አንተስ ስለምን የእግዚአብሔር ልጅ ሆንክ? ምክንያቱም ይቅር ስለተባልክ ነው፡፡ እንደዚህ አይነት ዋጋው የማይተመን ስጦታ ተቀብለህ፣ እንዴት ለሌሎች አላካፍልም ትላለህ?
ይህን አስብ! ስፍር ቁጥር የሌላቸው ወንጀሎች ተሸክመህ በእስር ቤት ተጣልክ፤ እናም አንድ ስው ከዚህ አውጥቶ ቤተ መንግሥት አስገባህ። ወይም ሌላ ምሳሌ ለመጠቀም፣ በጠና ታምመህ ለሞት ተቃርበህ ነበርና አንድ ሰው በመድኃኒት አዳነህ። ያን ሰው ከማንም በላይ ከፍ አድርገህ አትመለከተውም? የመድኃኒቱን ስም ስትሰማ እንኳ ደስ አይልህም? ከሥጋ ስቃይ ያዳነንን ከፍ አድርገን የምንወደው ከሆነ፣ ነፍሳችንን የሚያድኑትን መንፈሳዊ ስጦታዎች ምን ያህል እንወዳቸው ይሆን?
ፍቅርን የምትወድ ሁን፤ የዳንከው የእግዚአብሔር ልጅ ባደረገልህ ፍቅር ነውና! ሌላውን የማዳን፣ የመርዳት እድል ካለህስ ይህን ተመሳሳይ መድኃኒት አትሰጠውምን? “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤" እንደተባለው (ማቴ. 6፥14) በዚህ መንገድ አንዳችን የሌላኛችን አበርቺ፣ የሌላኛችን አመስጋኝ መሆናችን የተከበረ እና የለጋስ ልብ ምልክት ይሆንልናል።
ጳውሎስ በመቀጠል “ክርስቶስ ደግሞ እንደ ወደዳችሁ" ይለናል፡፡ እኛ ይቅር ማለት ያቃተን ወዳጆቻችንን ነው፡፡ ክርስቶስ ግን ጠላቶቹን ይቅር ብሏል፡፡ ከጌታችን የተቀበልነው ስጦታ ምንኛ ይበልጣል! ክርስቶስ እንደወደደን መውደድ ከፈለግን ለጠላቶቻችን እንኳን መልካም ማድረግ አለብን፡፡
ጳውሎስ “ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።" በማለት አክሎ ተናግሯል፡፡
ተመልከት… ስለሌሎች መከራ መቀበል ለጠላቶችም ቢሆን ጥሩ መዓዛ ያለው መባ ሲሆን፣ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት ነው፡፡ ለሌሎች ብትሞት በእውነት መስዋእት ትሆናለህ፡፡ እግዚአብሔርን መምሰል ማለት ይህ ነው፡፡ እስከ መሥዋዕት መውደድ፣ በነጻ ይቅር ማለት፤ ክርስቶስ እንደ ተመላለሰ በፍቅር መመላለስ፡፡
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
“#በፍቅር_ተመላለሱ”
ኤፌ. 5:12
ይህ የሁሉም ነገር መሠረት ነው! ፍቅር ባለበት ቦታ ቁጣ፣ ጩኸት፣ ስድብ የለም፡፡ እነዚህ ሁሉ ነገሮች ተወግደዋል፡፡ ጳውሎስ አሳዳጅ ሳለ በእግዚአብሔር ፍቅር ድኗል፡፡ አንተስ ስለምን የእግዚአብሔር ልጅ ሆንክ? ምክንያቱም ይቅር ስለተባልክ ነው፡፡ እንደዚህ አይነት ዋጋው የማይተመን ስጦታ ተቀብለህ፣ እንዴት ለሌሎች አላካፍልም ትላለህ?
ይህን አስብ! ስፍር ቁጥር የሌላቸው ወንጀሎች ተሸክመህ በእስር ቤት ተጣልክ፤ እናም አንድ ስው ከዚህ አውጥቶ ቤተ መንግሥት አስገባህ። ወይም ሌላ ምሳሌ ለመጠቀም፣ በጠና ታምመህ ለሞት ተቃርበህ ነበርና አንድ ሰው በመድኃኒት አዳነህ። ያን ሰው ከማንም በላይ ከፍ አድርገህ አትመለከተውም? የመድኃኒቱን ስም ስትሰማ እንኳ ደስ አይልህም? ከሥጋ ስቃይ ያዳነንን ከፍ አድርገን የምንወደው ከሆነ፣ ነፍሳችንን የሚያድኑትን መንፈሳዊ ስጦታዎች ምን ያህል እንወዳቸው ይሆን?
ፍቅርን የምትወድ ሁን፤ የዳንከው የእግዚአብሔር ልጅ ባደረገልህ ፍቅር ነውና! ሌላውን የማዳን፣ የመርዳት እድል ካለህስ ይህን ተመሳሳይ መድኃኒት አትሰጠውምን? “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤" እንደተባለው (ማቴ. 6፥14) በዚህ መንገድ አንዳችን የሌላኛችን አበርቺ፣ የሌላኛችን አመስጋኝ መሆናችን የተከበረ እና የለጋስ ልብ ምልክት ይሆንልናል።
ጳውሎስ በመቀጠል “ክርስቶስ ደግሞ እንደ ወደዳችሁ" ይለናል፡፡ እኛ ይቅር ማለት ያቃተን ወዳጆቻችንን ነው፡፡ ክርስቶስ ግን ጠላቶቹን ይቅር ብሏል፡፡ ከጌታችን የተቀበልነው ስጦታ ምንኛ ይበልጣል! ክርስቶስ እንደወደደን መውደድ ከፈለግን ለጠላቶቻችን እንኳን መልካም ማድረግ አለብን፡፡
ጳውሎስ “ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።" በማለት አክሎ ተናግሯል፡፡
ተመልከት… ስለሌሎች መከራ መቀበል ለጠላቶችም ቢሆን ጥሩ መዓዛ ያለው መባ ሲሆን፣ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት ነው፡፡ ለሌሎች ብትሞት በእውነት መስዋእት ትሆናለህ፡፡ እግዚአብሔርን መምሰል ማለት ይህ ነው፡፡ እስከ መሥዋዕት መውደድ፣ በነጻ ይቅር ማለት፤ ክርስቶስ እንደ ተመላለሰ በፍቅር መመላለስ፡፡
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
#በመንገድም_ሆነ_በሥራ_ቦታችሁ
ጸሎት ኃይል አላት። ጸሎት የነቢዩ ኤልያስን ቃል ሰምታ ሰማይን ዘግታለች፣ ደግሞም ከፍታለች። ጸሎት አንበሶችን አፍ ዘግታለች፣ እሳትንም አቀዝቅዛለች። በአንተም ሕይወት ውስጥ የኃጢአትን እሳት የምታጠፋው ጸሎት ናት። ተስፋ በቆረጥክ ጊዜ ጸልይ፤ ብርሃን ታገኛለህ። በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ጸልይ፤ መነሳትን ታገኛለህ። እግዚአብሔር 'ለምኑ ይሰጣችኋል፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል' ብሏል። እርሱ መስጠት ሰልችቶት አያውቅም፤ እኛ ግን መለመን እንሰለቻለን።
ወንድሞቼ ሆይ! በቤተ-ክርስቲያንም ሆነ በቤታችሁ፣ በመንገድም ሆነ በሥራ ቦታችሁ ልባችሁ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይ። ጸሎት ዘወትር በእጃችሁ ያለች መሣሪያ ናት። ንስሐ የገባች ነፍስ በጸሎት ካልታጠበች እድፏ አይለቅም። ስለዚህ ጸሎታችሁ ከምጽዋት ጋር ይሁን። ጸሎትና ምጽዋት በአንድነት ሆነው ወደ እግዚአብሔር ሲወጡ በፊቱ እንደ ጣፋጭ ዕጣን ይሆናሉ። በጸሎት መለመንን፣ በንስሐ መመለስን፣ በምጽዋት ማረጋገጥን አታቋርጡ።"
Telegram:
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 115
Repost from N/a
#ዳንኤል_ሠላም_አደረ
ታማኝነትህ ብዙ ነው ወሰን ዳርቻ የሌለው
ተቆጥሬያለሁ ከሰው ከትቢያ በሚያነሳው/2/
አዝአልሞትኩም ጉድጓድ ገብቼ ቢጨክኑም ወንድሞቼ ሞቷል ተረስቷል ያላችሁ አለሁኝ ደስ ይበላችሁ/2/
አዝዳንኤል ሰላም አደረ የአንበሶቹም አፍ ተዘጋ ቀን አይጨልምም ፈጽሞ እግዚአብሔር ብሎ ካነጋ/2/
አዝጴጥሮስ ከእስር ቤት ተፈታ ሮዴ ክፈች በሩን ቃሉን አያጥፍም እግዚአብሔር ተስፋውን ቃል ኪዳኑን/2/
አዝጊንጡን እባቡን ይረግጣል ከአእላፋት ይበልጣል እግዚአብሔር የሆነው ተስፋ ይኖራል በምድር ሲሰፋ/2/ Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
