uk
Feedback
የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

Відкрити в Telegram

ይህ ትክክለኛ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት የቴሌግራም ቻናል ነው:: /በመምህር ሲራክ ሰሎሞን/ በዚህ የቴሌግራም ቻናል:- ➮አስተማሪ እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን ➮የቅዱሳን ገድላት ➮ መዝሙሮችን ➮መንፈሳዊ ትምህሮቶችን ያገኛሉ። የመወያያ ግሩፕ: https://t.me/+QKiTJYGJvYpmNWM0 የዚህ ግሩፕ ዓላማ ለበጎ ምግባር ቃለ እግዚአብሔርን መማማር ነዉ::

Показати більше
1 183
Підписники
+124 години
+77 днів
+4330 день
Архів дописів
#ኃጢአት_ሰርተሃልን? በቤትህ ያለው ዳቦ ለተራበው ሰው የሚውል(ንብረቱ) ነው፥ በልብስ ማስቀመጫህ ውስጥ ያለው የማትጠቀመው ኮት የችግረኛው ገንዘቡ ነው፥ በጫማ ማስቀመጫህ ውስጥ አልፈልገውም ብለህ ሊበላሽብህ የሆነው ጫማ የደሃው ጫማ (ጫማ ለሌለው ገንዘቡ) ነው ፥ ያከማቸኸው ገንዘብ ለድሃው የሚገባው ነው.... ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡ "ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡ አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ለመዳን፣ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ  መስራቱን አቁም፡፡ ✍️ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ዘወትር_እግዚአብሔርን_አመስግን "መንፈሳዊ ጥበብን የምትወድ ነፍስ ዘወትር እግዚአብሔርን ታመሰግናለች፡፡ ሰው ሆይ! ሰዎች ክፉ ነገር ሲያደርሱብህ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያን ጊዜም ክፉው መልካም
#ዘወትር_እግዚአብሔርን_አመስግን "መንፈሳዊ ጥበብን የምትወድ ነፍስ ዘወትር እግዚአብሔርን ታመሰግናለች፡፡ ሰው ሆይ! ሰዎች ክፉ ነገር ሲያደርሱብህ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያን ጊዜም ክፉው መልካም ይኾንልሃል፡፡ "እንዴት?" ብለህ የጠየቅኸኝ እንደኾነም፦ "በደል የሚፈፅመው ክፉ ነገር የሚቀበለው ሳይኾን ክፉ ነገር የሚያደርሰው ሰው ነውና" ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እመልስልሃለሁ፡፡ ስለዚህ ዘወትር እግዚአብሔርን አመስግን፡፡ ብትታመምም እግዚአብሔርን አመስግን፤ ሀብት ንብረት ብታጣም አመስግን፤ በሐሰት ቢከሱህም አመስግን፡፡ እንደ ነገርኩህ ተጎጂዎቹ ክፉ ተቀባዮች ሳይኾኑ ክፉ አድራሾች ናቸውና፡፡" የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

እንኳን አምላክን በድንግልና ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። #ድንግል_ማርያም_በሰማይ_የታየች_ታላቅ_ምልክት! =>በሰማይ ያለችውን ድን
እንኳን አምላክን በድንግልና ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። #ድንግል_ማርያም_በሰማይ_የታየች_ታላቅ_ምልክት! =>በሰማይ ያለችውን ድንግል ማርያምን ቅዱስ ዮሐንስ ታላቅ ምልክት በሰማይ ዐየሁ በማለት ይገልጻታል። "ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ፤ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራሷም ላይ የዐሥራ ኹለት ከዋክብት አክሊል የተቀዳጀች አንዲት ሴት ነበረች።" ራዕይ ፲፪: ፩። ነቢየ ልዑል ኢሳይያስ በትንቢት "ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች" ብሎ የተናገረላት ድንግል ማርያም ናት። ኢሳ ፯:፲፬። የነቢዩን ቃል የተረጎመው ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ ያየውን ጽፏል። ምልክት ብቻ ሳይኾን ታላቅ ይላታል። የማይታይ ምልክት የለምና የታየችውን ታላቅ ምልክት በመጽሐፍ ቅዱስ ዐይንነት ለእኛም አሳይቶናል። በሰማይ የታየችው ከሞት ስለተነሣች ነው። ትንሣኤዋ በመጽሐፍ አልተጻፈም ለሚሉ ይድረስ። ያውም ፀሐይን የምታክል ኃያል ፍጥረት እንደ ተራ ሸማ ተጎናጽፋ። ይኽም ክብሯና ንጽሕናዋ ነው። አባቷ ቅዱስ ዳዊት የወርቅ በመጎናጸፊያ ተሸፋፍና በቀኙ ቆማ ያያት ንግሥት እርሷ ናት። ወርቅ የተባለ ንጽሕና ቅድስናዋ ነው። በሰማይ ያልታየቻችሁ ቅዱስ ዮሐንስን ጠይቁት። ዛሬም በሕያው ቃሉ ጣት እየጠቆመ ወደ ሰማይ ያሳያችኋል። ድንግል ማርያምን በሰማይ አለማየት ፀሐይን አትታየኝም ከማለት በላይ ነው። ካልታየቻችሁ ድክመቱ የእናንተ ነውና ፀሐይዋ የለችም አትበሉ። ወይ በሙቀቷ ብሰሉ ወይም ዐይናችሁን ተኳሉ። Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ዐረገች_በስብሐት ዐረገች በስብሐት ዐረገች በእልልታ በስብሐት በእልልታ ዐረገች ዐረገች በእልልታ የጻድቃን እመቤት የኃጥአን ተስፋ ዐረገች ዐረገች በእልልታ የማይታበለው እንዲፈጸም ቃሉ ብታርፍም እመ አምላክ ቤዛዊተ ኩሉ ዐረገች ተነስታ ድንግል የእኛ እናት እልል በሉላት እልል በሉላት አዝ= = = = ሰማያት ተደንቀው በአዲሲቷ ሰማይ ያልቻሉትን ጌታ ወስናው ብትታይ ሊቀበሏት ወጡ በሐሴት በሙሉ ንዒ ንዒ እያሉ ንዒ ንዒ እያሉ አዝ= = = = = ዘመኗን በሙሉ ስለ ልጇ አልቅሳ የመከራ ሰይፍን አሳልፋ ነፍሷ በቀኙ ልትቆም ንግሥት እየተባለች ይኸው ዐርጋለች ይኸው ዐርጋለች አዝ= = = = በሐዋርያት አበው ትምሕርት የጸናችሁ የልጇ ምሥክር ከዘሯ የቀራችሁ ከሞት ተነሥታለች ቅድስት እናታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አላችሁ አዝ= = = = = እጅሽ በዳሰሰው በነካው ሰበን እንደ ባረክሻቸው ሐዋርያቱን ማርያም ማርያም ስንል ደጅሽ ላይ ቆመን እኛንም ባርኪን እኛንም ባርኪን መዝሙር ዲያቆን አማን ኡርጌሳ "በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።" መዝ ፵፬፥፱ Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ማርያም_አርጋለች ማርያም አርጋለች ወደ ገነት(፪) የሰማይ መላእክት እያረጋጓት እርሷም እንደ ልጇ ተነስታለች የአባቷን ዳዊት ትንቢት ልትፈፅም ወርቁን ተጎናፅፋ በቀኙ ልትቆም ወደ አምላክ ማደሪያ ወደ ሰማያት አረገለች በእልልታ ድንግል የእኛ እናት አርጋለች ማርያም ተነስታለች
አዝ= = = = =
ሰማያት ይከፈት ደመናም ይዘርጋ ዝምታም አይኖርም እመ አምላክ አርጋ አንደበት ይከፈት ማርያምን ያመስግን ከዘላለም ጥፋት በምልጃዋ እንድንድን አርጋለች ማርያም ተነስታለች
አዝ= = = = =
የአምላክ ማደሪያ ቅዱስ ስጋሽ አምላክን ያቀፉት እነዚያ እጆችሽ ሙስና መቃብር ይዞ አላስቀራቸው ተነስተዋል በክብር በእምነት አየናቸው አርጋለች ማርያም ተነስታለች
አዝ= = = = =
ሐዋርያት አበው እንኳን ደስ አላችሁ በክብር አረገች ማርያም ሞገሳችሁ ወደ ዓለምም ውጡ ሰበኑዋን ይዛችሁ የድንግል እርገቷን ንገሩ ተግታችሁ አርጋለች ማርያም ተነስታለች ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ "በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።" መዝ ፵፬፥፱ Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ሰላም_ለፍልሰተ_ሥጋኪ ✍🏽ፍልሰታ የሚለውን ቃል አለቃ አያሌው ታምሩ "የእመቤታችን ሥጋ ከጌቴሴማኒ ወደ ገነት መፍለሱን ኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ከነበረበት መነሣቱን ለሜመልከት የሚነገር ቃል ነው " በማለት ያብራራሉ። ስለ እመቤታችን ፍልሰት ነቢያት በትንቢት አስቀድመው ተናግረዋል ። "አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት(መዝ” 131÷8)። ነቢዩ ዳዊት " አንተና የመቅደስህ ታቦት ተነሥ" ሲል የተናገረው "አንተ " የተባለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን "ታቦት " የተባለችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መሆኗን መተርጕማነ መጻሕፍት ያስረዳልሉ።"ተንሥኢ ወንዒ ቅርብትየ፣እንቲአየ ሠናይት ርግብየ፣ውስተ ጽላሎተ ኰኵሕ ቅሩበ ጥቅም፣ አቅራቢያዬ መልካሟ ርግቤ ተነሽ ነዬ ፣በግንቡ አጠገብ ወዳለው ዋሻው ጥላ" (መኃ ፪÷፲-፲፬) የሚለው ነው። ሐዋርያት ከድንግል ማርያም በመለያየታቸው ሲያዘኑ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ እመቤታችን በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር እንዳለች ነገራቸው። እንዴት ዮሐንስ ዓይቶ እኛ ሳናይ እንቀራለን ብለው ነሐሴ አንድ ቀን  ቀኖና ገቡ። ያን ጊዜ ነሐሴ ጥር በባተበት ሰኞ ይብታል። ከሰኞ እስከ ሰኞ ስምንት፣ ከሰኞ እስከ ሰኞ አሥራ አምስት አንዱን ቀንሶ በአሥራ አራት እሑድ ሥጋዋን  አምጥቶ ሰጥቷቸው ቀብረዋት ዕለቱን ተነሥታለች። ያን ጊዜ ቅዱስ ቶማስ በቦታው አልነበረም። በሀገረ ስብከቱ ሕንድ ሲያስተምር ኖሮ በደመና  ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሔድ እመቤታችን ወደ ሰማይ ስታርግ አጅበዋት የነበሩ ቅዱሳን መላእክት እመቤታችን ናት ስገድላት አሉት። እሱም ትንሣኤዋን ሳላይ የቀረሁ መስሎት ከደመናው ወልቆ ሊወድቅ ሲል እመቤታችን ትንሣኤዋን እሱ እንጂ ሌሎች ሐዋርያት እንዳላዩ ነገረችና የተገነዘችበትን ሰበን ሰጠችው። ቶማስ ከሐዋርያት ሲገናኝ ምሥጢሩን ነገራቸው። እነሱም በዓመቱ ቶማስ እንዳየ እናያለን ብለው ነሐሴ አንድ ቀን ሱባኤ ገቡ። ነሐሴ ማክሰኞ ይብታል። ከማክሰኞ እስከ ማክሰኞ ስምንት፣ ከማክሰኞ እስከ ማክሰኞ አሥራ አምስት  አንድ ቀን ጨምሮ ረቡዕ ነሐኤ አሥራ ስድስት ጌታ ሠራዒ ካህን፣ ጴጥሮስን ተራዳኢ ቄስ፣ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ ቈርቦ አቍርቧቸዋል። የመልክአ ማርያም ደራሲ" ሰላም ለግንዘተ ሥጋኪ በእደ ሐዋርያት አርጋብ በአፈወ ዕፍረት ቅድው ዘሐሳበ ሤጡ ዕፁብ ማርያም ድንግል ወለተ ኅሩያን ሕዝብ ረሰይኩኪ እግዝእትየ ህየንተ እም ወአብ ይሕፅነኒ ከመ ጥብ ፍቅርኪ ሐሊብ፣ እመቤቴ ማርያም ሆይ! ዋጋው እጅግ ውድ በሆነና መዓዛው በሚጣፍጥ ሽቱ በሐዋርያት እጅግ ለተገነዘው ንጹሕ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል።ድንግል ሆይ ! የተመረጡና የተባረኩ ወገኖችሽ የሆኑ ቡርክት ልጅ ነሽ። እመቤቴ ሆይ! ቸርነትሽ እንደ ጡት ሁኖ ያሳድገኝ ዘንድ አንቺን እናት አባት አድርጌሻለሁ"ይላታል። "ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ደባትረ ብርሃን ኅበ ተተክሉ። ለገነተ ጽባሕ በማእከሉ ውድስት አንቲ ወስብሕት በአፈ ኵሉ ።እምነ ጻድቃን ዘታሕቱ ወእምትጉሃን ዘላዕሉ ።ማርያም ለኪ ስብሐተ አደሉ፣ እመቤቴ ማርያም ሆይ! በምሥራቅ ተክል በበዛበት በገነት መካከል የብርሃን ድንኳኖች ወደ ተተከሉበት ላረገ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል። ድንግል ሆይ! በሁሉ አንደበት መመስገን የተገባሽ ስለሆነ በሰማይ ካሉ መላእክትና በምድር ከሚኖሩ ደቂቀ አዳም ሁል ጊዜ ምስጋና ይቀርብልሻል” በማለት ያደንቃል።ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን የድንግል ማርያም ፍልሰተ ሥጋ እና ንሣኤ ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ የምንኖረውን ዘለዓለማዊ ሕይወት አመላካች መሆኑን  ታምናለች፣ታሳምናለች። ይኸውም ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ " በጌታ የሚሞቱ. ብፁዓን ናቸው።ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ ሥራቸውም ይከተላቸዋል (ራእ፲፬÷፲፫) በማለትበ የገለጠው ነው። ቤተ ክርስቲያናችን ፍልሰታን በውዳሴ፣ በቅዳሴ፣ በጾም በጸሎት ታከብራለች። “ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ” (ዮሐ 11÷25)  በማለት የተናገረውን የሕይወትን እናት ሞት ይዞ ማስቀረት አይቻለውም። ቅዱስ ያሬድ “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኲሉ፣ የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል”  ያለውም ለዚህ ነው። ቅዱስ አግናጥዮስ “ከተቻለ በኢየሩሳሌም የሚኖረውን የአማኞች ጉባኤ ለማየት ለመካፈል እመጣለሁ፡፡ በተለይም የኢየሱስን እናት ለማየት፡ እርሷ የተከበረች፣ትሑት፣ በሁሉም አስደናቂበመሆኗ እርሷን ለማየት የማይሻ የለም፡፡ እርሷ የእግዚአብሔር እናት ሁላችንን ትባርካለች፤•••፡፡ያያት ሁሉ ይደነቃል፤ይደሰታል” በማለት መስክሯል፡፡ ቅዱስ ያሬድ " የሰው እጅ ያልሰራት ድንኳን ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረላት እመቤታችን አባቷ ዳዊት በመሰንቆው እያመሰገናት ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም ሔደች" በማለት አመስግኗታል። እኛም ክርስቲያኖች ቅዱሳን አባቶቻችንን  አብነት አድርገን በጾም፣ በጸሎት፣ በማሕሌት እና በቅዳሴ እናመሰግናታለን። ከትንሣኤዋ በረከት ያድለን። አሜን! Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

ጌታን ሲያርግ ዐይተው የነገሩን ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው። ድንግልም ስታርግ ዐይተው የነገሩን ራሳቸው ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው። ስለ ጌታ ዕርገት የነገሩንን አምነን ስለ እመቤታችን ዕርገት ሲነግሩን አና
ጌታን ሲያርግ ዐይተው የነገሩን ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው። ድንግልም ስታርግ ዐይተው የነገሩን ራሳቸው ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው። ስለ ጌታ ዕርገት የነገሩንን አምነን ስለ እመቤታችን ዕርገት ሲነግሩን አናምንም ማለት አይቻልም። ሐዋርያት ያልነገሯቸው ስለማይገባቸው ነውና ሊያውቁት አይችሉም። የዓለም ብርሃን የተባሉት የነገሩንን ትተን የጨለማ ልጆች የሚሉንን አንከተልም። በእነርሱ ዐይን ያየናቸውን ዕርገቶች ስናከብራቸው እንኖራለን። የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

እንኳን አምላክን በድንግልና ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም የእርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። 👉 https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv ቃለ እግዚአብሔር ለ
እንኳን አምላክን በድንግልና ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም የእርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። 👉 https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv ቃለ እግዚአብሔር ለሁሉም ይዳረስ ዘንድ ለወዳጆችዎ ያካፍሉት።

እንኳን አምላክን በድንግልና ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም የእርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። #የእመቤታችን_ትንሣኤና_ዕርገት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር የኖረችው ስልሳ አራት ዓመት ነው፡፡ እነዚህ ዓመታት ሲተነተኑ ሦስት ዓመት በወላጆቿ ሐናና ኢያቄም ቤት፣ ዐሥራ ሁለት ዓመት በቤተ መቅደስ፣ ሠላሣ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አሥራ አምስት ዓመት ከሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር ነው ያረፈችውም ጥር 21 ቀን በ50 ዓ.ም ነው፡፡ ባረፈችበት ወቅት ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡር ሥጋዋን ለማሳረፍ ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲሔዱ አይሁድ "ቀድሞ ልጇ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፤ በአርባኛውም ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ተመልሶም ይህን ዓለምን ለማሳለፍ ይመጣል እያሉ በማስተማር ሕዝባችንን ወስደውብናል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷም እንደ ልጇ ተነሳች እያሉ በማስተማር ሊያውኩን አይደለምን? ኑ! ተሰብስበን በእሳት እናቃጥላት" ብለው ክፉ ምክር ተማከሩ ከመካከላቸውም ብርቱ ሰው የሆነው #ታውፋንያ የተባለ ቅድስት ሥጋዋን ከሐዋርያት ነጥቆ ለማስቀረት ክቡር ሥጋዋ ያለበትን የአልጋ ሸንኮር ሲይዝ በመልአከ እግዚአብሔር እጁ ተቆርጣ ከአልጋው ላይ ተንጠልጥላ ቀረች፤ ከዚህ የጥፋቱ ሥራው ተምሮ እመቤታችንን በመለመኑ እመቤታችን የተቆረጠች እጁን መልሳለታለች ከዚህ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር የእመቤታችንን የተቀደሰ ሥጋዋን ጌታችን ይወደው የነበረ ተብሎ የተነገረለት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስን ይዞ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጠው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም የሆነውን ሁሉ ለወንድሞቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ነገራቸው፡፡ እነሱም የእመቤታችን ሥጋ በክብር ለማሳረፍ ካላቸው ጉጉት የተነሣ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምሮ ሱባኤ ገቡ ከሁለተኛ ሱባኤ ቆይታቸው በኋላ በአሥራ አራተኛ ቀናቸው ጌታችን የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ ሰጣቸው፡፡ ሐዋርያትም በዝማሬና በታላቅ ምስጋና በጌቴ ሴማኔ ቀበሯት፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት› › ተብሎ ትንቢት የተናገረውን ሲተረጉሙት ‹‹ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ሆይ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታሳርፈው የመቅደስህ ታቦት የሆነችውን ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ›› ብለው ያመሰጥሩታል፡፡ /መዝ. 131፥8/ የእመቤታችንን ቅድስት ሥጋዋን ሐዋርያት ሲቀብሯት በሀገረ ስብከቱ ሕንድ የነበረው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ ሲመለስ እመቤታችን ስታርግ ያገኛታል ለምልክት እንዲሆነው ሰበኗን (የመግነዟን ጨርቅ) ተቀብሏት ይለያያሉ፡፡ ለወንድሞቹ ሐዋርያት ያየውን ይነግራቸዋል ለበረከት የሰጠችውንም ሰበን ያካፍላቸዋል፤ ሐዋርያት ‹ ‹ዕርገቷን እንዴት እሱ ብቻ ተመልክቶ ለምን እኛ ይቀርብናል› › ብለው በዓመቱ ነሐሴ አንድ ቀን ሱባኤ ገቡ፡፡ ነሐሴ 16 ቀን የልባቸው መሻት ተፈጸመላቸው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቀ (ረዳት) ቄስ፣ ቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ (ዋና ዲያቆን) አድርጎ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው በትኅትና የያዙት ሱባኤም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዕርገቷን ለማየት አበቃቸው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ይህን መሠረት አድርጋ ከነሐሴ 1-16 ጾመ ፍልሰታ በማለት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ አድርገን እንድንጠቀምበት ሥርዐት ሠራችልን በነቢያና በሐዋርያት መሠረት ላይ የታነጽን ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች በየዓመቱ ይህን ጾም በሱባኤ በማሳለፍ ከእመቤታችን ጸጋና በረከት ተሳታፊዎች እንሆናለን፤ ሆነናልም፡፡ #ጽንዕት #በድንግልና #ሥርጉት #በቅድስና #እመቤታችን #ጸጋውን #ክብሩን #እንዳይነሳን #ለምኚልን፤ #አእምሮውን #ልቡን #በልቡናችን #ሳይብን #አሳድሪብን:: የቴሌግራም #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! #Join 👉 https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv ቃለ እግዚአብሔር ለሁሉም ይዳረስ ዘንድ ለወዳጆችዎ ያካፍሉት።

እንኳን አምላክን በድንግልና ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም የእርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። የቴሌግራም #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! #Join 👉 https:/
እንኳን አምላክን በድንግልና ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም የእርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። የቴሌግራም #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! #Join 👉 https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv ቃለ እግዚአብሔር ለሁሉም ይዳረስ ዘንድ ለወዳጆችዎ ያካፍሉት።

እንኳን በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።         💠 አበው ስለ እመቤታችን እንዲህ አሉ 💠 "አምላክ ከንጉሥ ሔሮድስ ሴት ልጅ ቢወለድ ኖሮ አልጋ ወራሽ በሆነና ባልተሰደደ ነበር። እርሱ ግን የድሆች ልጅ የሆነችውን ድንግል መረጠ"    አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ "ታላቁ ተራራ ሆይ ታናሽዋ ብላቴና የተሸከመችህ ራስህን በሚቻላት መጠን አድርገህላት ነው ፣ ታላቁ እሳት ሆይ ታናሽዋ ብላቴና ተሸክማህ ያልተቃጠለችው ኃይልን ትችል ዘንድ አጽንተሃት ነው "    ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ "ይህ ዓለም የእግዚአብሔርን ልጅ በቀጥታ ከእግዚአብሔር አብ እጅ ለመቀበል የተገባ ሆኖ ስላልተገኘ ፣ ዓለም ከእርስዋ ይቀበል ዘንድ አንድያ ልጁን ለድንግል ማርያም እናት ትሆነው ዘንድ ሠጣት"    ቅዱስ አውግስጢኖስ "ሔሮድስ የማይያዘውን ይይዝ ዘንድ ተነሣ ፣ ዓውሎ ነፋስንም በቤቱ አስገብቶ ሊዘጋ ታገለ"     አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ "ጌታ ሆይ እናትህን ማን ብለን እንጥራት? እናት ብቻ እንዳንላት ድንግል ሆና አገኘናት ፣ ድንግል እንዳንላት ልጅ ታቅፋ አየናት። ጌታ ሆይ እናትህን ለመጥራት እንዲህ የሚያስቸግር ከሆነ አንተን ከቶ ምን ብለን እንጠራሃለን??"      ቅዱስ ኤፍሬም የቴሌግራም #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! 👇👇👇 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን:: ነሐሴ ፲፭ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልእክታት፣ ወንጌልና ምሰባክ 🔊ዲያቆን 📖1ኛ ቆሮ 12፥18.... 🔊ንፍቅ ዲያቆን 📖ይሁዳ 1
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን:: ነሐሴ ፲፭ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልእክታት፣ ወንጌልና ምሰባክ 🔊ዲያቆን 📖1ኛ ቆሮ 12፥18.... 🔊ንፍቅ ዲያቆን 📖ይሁዳ 1፥17.... 🔊ንፍቅ ካህን 📖ግብረ ሐዋርያት 1፥12-15 🔊ምስባክ 📖መዝ 18፥4-5 ✍️"ውስተ ኩሉ ምድር ወጽአ ነገሮሙ ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ ወውስተ ፀሐይ ሤመ ጽላሎቶ" 🔊ትርጉም 👉"ድምፃቸው ወደ ምድር ኹሉ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ በነርሱ ውስጥ የፀሐይ ድንኳን አደረገ" 🔊ወንጌል 📖ማቴ 10፥1-15 🔊ቅዳሴ ዘሐዋርያት የቴሌግራም #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! #Join 👉 https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv ቃለ እግዚአብሔር ለሁሉም ይዳረስ ዘንድ ለወዳጆችዎ ያካፍሉት።

✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" 📖ምሳ 1፥33 #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! 👇 #Join 👉 https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ዘመዳችን_ማርያም_/_አንቲ_ውእቱ_ዘመድ♡ ዘመዳችን ማርያም ከዳዊት ዘር የሆንሽ አምላክን በስጋ በማህፀን ወሰንሽ የመመኪያችን ዘውድ የክብር አክሊላችን ልጅሽን ታቅፈሽ አይተናል በዓይናችን /2
አዝ
ባንቺ ድልድይነት የመጣው ወደኛ በጎቹ የገደሉት ነው መልካም እረኛ በጠበብ ደረትሽ ፈቅዶ ተወሰነ ፋሲካችን ታርዶ ዓለም በእርሱ ዳነ
አዝ
ሠረገላው እሳት ሰማይ ዙፋኑ ነው በስጋ ተገልጦ በእቅፍሽ ያየነው ካንቺ በፊት ይሁን እንዲሁም በኃላ አልተሰማ አልታየ ይህ ተአምር ከሌላ
አዝ
በነፃ ጠጥተን የህይወትን ውሃ ልምላሜ ሸፍኖን ወጣን ከበረሃ ባንቺ ስለሆነው ይገባል አንክሮ ጨው ያገኘንብሽ የኤልሳዕ ማሰሮ
አዝ
ዘመዳችን ድንግል ነውር የሌለብሽ የእምነት ምሳሌ ፀጋን የሞላብሽ ንጉሥ ውበትሽን አየና ወደደው ከሰማያት ስቦ ፍቅር አወረደው 🤲🏽👏🏽#ሊቀ_መዘምራን_🤲🏽👏🏽ዲ/ን_ቴዎድሮስ_ዮሴፍ🤲🏽👏🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

❇️ #ጌታ_ሆይ_ከታቦር_አታውርደን! ❇️ ጴጥሮስ በታቦር ተራራ ላይ ጌታን ተማጸነ ፤ ከዚያች ተራራ ላለመውረድና በዚያ ለመኖር ለመነ፡፡ እርግጥ ነው አባ ጊዮርጊስና ቅዱስ ኤፍሬም እንዳሉት ጌታ ከተራራው ወርዶ ካልተሰቀለና ካልተቸነከረ ዓለም ሊድን አይችልምና የጴጥሮስ ጥያቄ ተቀባይነት አላገኘም፡፡ ጥያቄው ግን ተራ ልመና አልነበረም፡፡ እኛም ብንሆን ይህንን ስሜት የምንረዳበት ብዙ አጋጣሚ አለ፡፡ ጴጥሮስ በዚያ ተራራ የጌታውን ክብር አየ ፤ የነቢያቱን ምስክርነት ተረዳ ፤ በዚህ ልቡ ቢነካ ምድር ላይ ሆኖ ሰማይ ናፈቀው ፤ ስለዚህ ጌታ ሆይ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው አለ፡፡ ግዴለህም ጌታ ሆይ ወርደን ምን እንሠራለን? አንተን ይዘን ነቢያትህን አይተን ምን ቀረን ብለን ከተራራው እንወርዳለን? እባክህን አንመለስ እባክህን በዚህ እንኑር ብሎ ለመነ፡፡ በዚህ እንኑር እንጂ ይመቸን አንልህም፡፡ ለአንተ ለሙሴና ለኤልያስ ሦስት ዳስ ሠርተን እኛ ከደጅ እንቀመጥ፡፡ ብቻ ከታቦር አታውርደን ብሎ ለመነ፡፡ አንዳንድ ቀን አለ የእግዚአብሔር ክብሩ የሚታይህ ቀን! አንዳንድ ቀን አለ በወንጌል መካከል የምትሰጥምበት ቀን ፤ በደመና ባትጋረድ በዕጣን ጢስ ውስጥ የምትዋጥበት ቀን ፤ የአብን ድምፅ ባትሰማ የቅዳሴ ድምፅ የምትሰማበት ቀን አለ፡፡ ከዚያ ደስታ ፣ ከዚያ ተመስጦ ፣ ከዚያ ሰላም ውስጥ ከገባህ መውጣት አትፈልግም፡፡ ምናለ እዚሁ ብቀር ምናለ አሁን የሚሰማኝ ሰላም ሁልጊዜም ቢሰማኝ ትላለህ፡፡ የጌታህ ፊት ከፀሐይ አብርቶ ይታይህና ሌላ ፀሐይ መሞቅ ያስጠላሃል፡፡ በሙሴ ሕግጋት ውስጥ እየተመላለስህ የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ልብህን ይሰውረዋል ፤ እንደ ኤልያስ ያሉትን መናኞች ቅዱሳንን ታሪክ እያነበብህ ልብህ ይመንናል፡፡ ማቋረጥ የማትፈልገው የነፍስ እርካታ ታገኛለህ ፤ ሰማያዊ ሕልም እያየህ ነውና እንዳትነቃ ትሰጋለህ፡፡ ከዚያ ተራራ ፣ ከዚያ ከፍታ መውረድ ያስፈራሃል፡፡ ስለዚህ ጌታን ትማጸናለህ ፤ ጌታ ሆይ በእዚህ መሆን ለእኔ መልካም ነው፡፡ እባክህ አልውረድ ትለዋለህ፡፡ ከዚህ ተራራ ከወረድሁ ምን እንደምሆን ምን እንደምሠራ አውቀዋለሁና ጌታ ሆይ እባክህ እዚሁ ብቀር ይሻለኛል፡፡ ወርጄ ሦስቴ ከምክድህ እዚህ ሦስት ዳስ ሠርቼ አንተን ባገለግል እመርጣለሁ፡፡ ወርጄ አላውቅህም ከምልህ እዚሁ ፊትህን እያየሁ ልቆይ! እባክህን ከዚህ ከፍታ አልውረድ፡፡ ይህ ነው የጴጥሮስ ልመና፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ መቆየት እየፈለገ ከዚያ ተራራ ሲወርድ ምን ይሰማው እንደሆን አላውቅም፡፡ ግን እናቶቻችንን ከገዳም ቆይተው ሲመለሱ የሚዘምሩትን መዝሙር ሃሳብ ሳይጋራው አይቀርም ፦ ለነፍሴ ሀገሯን አሳየኋት ለነፍሴ ሀገሯን አሳየኋት ከተማ ገብቼ ካላበላሸኋት! Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

❇️ #ጌታ_ሆይ_ከታቦር_አታውርደን! ❇️ ጴጥሮስ በታቦር ተራራ ላይ ጌታን ተማጸነ ፤ ከዚያች ተራራ ላለመውረድና በዚያ ለመኖር ለመነ፡፡ እርግጥ ነው አባ ጊዮርጊስና ቅዱስ ኤፍሬም እንዳሉት ጌታ ከተራራው ወርዶ ካልተሰቀለና ካልተቸነከረ ዓለም ሊድን አይችልምና የጴጥሮስ ጥያቄ ተቀባይነት አላገኘም፡፡ ጥያቄው ግን ተራ ልመና አልነበረም፡፡ እኛም ብንሆን ይህንን ስሜት የምንረዳበት ብዙ አጋጣሚ አለ፡፡ ጴጥሮስ በዚያ ተራራ የጌታውን ክብር አየ ፤ የነቢያቱን ምስክርነት ተረዳ ፤ በዚህ ልቡ ቢነካ ምድር ላይ ሆኖ ሰማይ ናፈቀው ፤ ስለዚህ ጌታ ሆይ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው አለ፡፡ ግዴለህም ጌታ ሆይ ወርደን ምን እንሠራለን? አንተን ይዘን ነቢያትህን አይተን ምን ቀረን ብለን ከተራራው እንወርዳለን? እባክህን አንመለስ እባክህን በዚህ እንኑር ብሎ ለመነ፡፡ በዚህ እንኑር እንጂ ይመቸን አንልህም፡፡ ለአንተ ለሙሴና ለኤልያስ ሦስት ዳስ ሠርተን እኛ ከደጅ እንቀመጥ፡፡ ብቻ ከታቦር አታውርደን ብሎ ለመነ፡፡ አንዳንድ ቀን አለ የእግዚአብሔር ክብሩ የሚታይህ ቀን! አንዳንድ ቀን አለ በወንጌል መካከል የምትሰጥምበት ቀን ፤ በደመና ባትጋረድ በዕጣን ጢስ ውስጥ የምትዋጥበት ቀን ፤ የአብን ድምፅ ባትሰማ የቅዳሴ ድምፅ የምትሰማበት ቀን አለ፡፡ ከዚያ ደስታ ፣ ከዚያ ተመስጦ ፣ ከዚያ ሰላም ውስጥ ከገባህ መውጣት አትፈልግም፡፡ ምናለ እዚሁ ብቀር ምናለ አሁን የሚሰማኝ ሰላም ሁልጊዜም ቢሰማኝ ትላለህ፡፡ የጌታህ ፊት ከፀሐይ አብርቶ ይታይህና ሌላ ፀሐይ መሞቅ ያስጠላሃል፡፡ በሙሴ ሕግጋት ውስጥ እየተመላለስህ የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ልብህን ይሰውረዋል ፤ እንደ ኤልያስ ያሉትን መናኞች ቅዱሳንን ታሪክ እያነበብህ ልብህ ይመንናል፡፡ ማቋረጥ የማትፈልገው የነፍስ እርካታ ታገኛለህ ፤ ሰማያዊ ሕልም እያየህ ነውና እንዳትነቃ ትሰጋለህ፡፡ ከዚያ ተራራ ፣ ከዚያ ከፍታ መውረድ ያስፈራሃል፡፡ ስለዚህ ጌታን ትማጸናለህ ፤ ጌታ ሆይ በእዚህ መሆን ለእኔ መልካም ነው፡፡ እባክህ አልውረድ ትለዋለህ፡፡ ከዚህ ተራራ ከወረድሁ ምን እንደምሆን ምን እንደምሠራ አውቀዋለሁና ጌታ ሆይ እባክህ እዚሁ ብቀር ይሻለኛል፡፡ ወርጄ ሦስቴ ከምክድህ እዚህ ሦስት ዳስ ሠርቼ አንተን ባገለግል እመርጣለሁ፡፡ ወርጄ አላውቅህም ከምልህ እዚሁ ፊትህን እያየሁ ልቆይ! እባክህን ከዚህ ከፍታ አልውረድ፡፡ ይህ ነው የጴጥሮስ ልመና፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ መቆየት እየፈለገ ከዚያ ተራራ ሲወርድ ምን ይሰማው እንደሆን አላውቅም፡፡ ግን እናቶቻችንን ከገዳም ቆይተው ሲመለሱ የሚዘምሩትን መዝሙር ሃሳብ ሳይጋራው አይቀርም ፦ ለነፍሴ ሀገሯን አሳየኋት ለነፍሴ ሀገሯን አሳየኋት ከተማ ገብቼ ካላበላሸኋት! Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

❇️ #ጌታ_ሆይ_ከታቦር_አታውርደን! ❇️ ጴጥሮስ በታቦር ተራራ ላይ ጌታን ተማጸነ ፤ ከዚያች ተራራ ላለመውረድና በዚያ ለመኖር ለመነ፡፡ እርግጥ ነው አባ ጊዮርጊስና ቅዱስ ኤፍሬም እንዳሉት ጌታ ከተራራው ወርዶ ካልተሰቀለና ካልተቸነከረ ዓለም ሊድን አይችልምና የጴጥሮስ ጥያቄ ተቀባይነት አላገኘም፡፡ ጥያቄው ግን ተራ ልመና አልነበረም፡፡ እኛም ብንሆን ይህንን ስሜት የምንረዳበት ብዙ አጋጣሚ አለ፡፡ ጴጥሮስ በዚያ ተራራ የጌታውን ክብር አየ ፤ የነቢያቱን ምስክርነት ተረዳ ፤ በዚህ ልቡ ቢነካ ምድር ላይ ሆኖ ሰማይ ናፈቀው ፤ ስለዚህ ጌታ ሆይ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው አለ፡፡ ግዴለህም ጌታ ሆይ ወርደን ምን እንሠራለን? አንተን ይዘን ነቢያትህን አይተን ምን ቀረን ብለን ከተራራው እንወርዳለን? እባክህን አንመለስ እባክህን በዚህ እንኑር ብሎ ለመነ፡፡ በዚህ እንኑር እንጂ ይመቸን አንልህም፡፡ ለአንተ ለሙሴና ለኤልያስ ሦስት ዳስ ሠርተን እኛ ከደጅ እንቀመጥ፡፡ ብቻ ከታቦር አታውርደን ብሎ ለመነ፡፡ አንዳንድ ቀን አለ የእግዚአብሔር ክብሩ የሚታይህ ቀን! አንዳንድ ቀን አለ በወንጌል መካከል የምትሰጥምበት ቀን ፤ በደመና ባትጋረድ በዕጣን ጢስ ውስጥ የምትዋጥበት ቀን ፤ የአብን ድምፅ ባትሰማ የቅዳሴ ድምፅ የምትሰማበት ቀን አለ፡፡ ከዚያ ደስታ ፣ ከዚያ ተመስጦ ፣ ከዚያ ሰላም ውስጥ ከገባህ መውጣት አትፈልግም፡፡ ምናለ እዚሁ ብቀር ምናለ አሁን የሚሰማኝ ሰላም ሁልጊዜም ቢሰማኝ ትላለህ፡፡ የጌታህ ፊት ከፀሐይ አብርቶ ይታይህና ሌላ ፀሐይ መሞቅ ያስጠላሃል፡፡ በሙሴ ሕግጋት ውስጥ እየተመላለስህ የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ልብህን ይሰውረዋል ፤ እንደ ኤልያስ ያሉትን መናኞች ቅዱሳንን ታሪክ እያነበብህ ልብህ ይመንናል፡፡ ማቋረጥ የማትፈልገው የነፍስ እርካታ ታገኛለህ ፤ ሰማያዊ ሕልም እያየህ ነውና እንዳትነቃ ትሰጋለህ፡፡ ከዚያ ተራራ ፣ ከዚያ ከፍታ መውረድ ያስፈራሃል፡፡ ስለዚህ ጌታን ትማጸናለህ ፤ ጌታ ሆይ በእዚህ መሆን ለእኔ መልካም ነው፡፡ እባክህ አልውረድ ትለዋለህ፡፡ ከዚህ ተራራ ከወረድሁ ምን እንደምሆን ምን እንደምሠራ አውቀዋለሁና ጌታ ሆይ እባክህ እዚሁ ብቀር ይሻለኛል፡፡ ወርጄ ሦስቴ ከምክድህ እዚህ ሦስት ዳስ ሠርቼ አንተን ባገለግል እመርጣለሁ፡፡ ወርጄ አላውቅህም ከምልህ እዚሁ ፊትህን እያየሁ ልቆይ! እባክህን ከዚህ ከፍታ አልውረድ፡፡ ይህ ነው የጴጥሮስ ልመና፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ መቆየት እየፈለገ ከዚያ ተራራ ሲወርድ ምን ይሰማው እንደሆን አላውቅም፡፡ ግን እናቶቻችንን ከገዳም ቆይተው ሲመለሱ የሚዘምሩትን መዝሙር ሃሳብ ሳይጋራው አይቀርም ፦ ለነፍሴ ሀገሯን አሳየኋት ለነፍሴ ሀገሯን አሳየኋት ከተማ ገብቼ ካላበላሸኋት! Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ድንግል_ሆይ ! ❝አንቺን የወለደ ማህጸን እንዴት ያለ ብሩክ ነው❞ አንቺን የታቀፉ ክንዶችስ እንዴት ያሉ ድንቅ ናቸው ! አስራ ሁለት ዓመት ወደ ቤተመቅደስ የተመላለሱ እግሮችሽስ እንዴት የከበሩ ናቸ
#ድንግል_ሆይ ! ❝አንቺን የወለደ ማህጸን እንዴት ያለ ብሩክ ነው❞ አንቺን የታቀፉ ክንዶችስ እንዴት ያሉ ድንቅ ናቸው ! አስራ ሁለት ዓመት ወደ ቤተመቅደስ የተመላለሱ እግሮችሽስ እንዴት የከበሩ ናቸው ! የቅዱሱን መልአክ ብሥራት የሰሙ ጆሮዎችሸስ እንዴት ያሉ ንቁ ናቸው ! ❝የቃልን ሰው መሆን ያመነው ልብሽ እንዴት ያለ ንጹሕ ነወ ! ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ጌታን የተሸከመው ማሕፀንሽ እንዴት ያለ ግሩም ነው ! ይህን ታላቅ አምላክ የታቀፉ ክንዶችሽስ እንዴት ያሉ ጽኑ ናቸው ! ጌታዬን ያጠቡት ጡቶሽን እንዴት የለመለሙ ናቸው ! ድንግል ሆይ ክብርሽ ከፍ ያለ ነውና አከብርሻለሁ❞ ሰላሳ ሶስት ዓመት ከሶሶት ወር ከጌታ ጋር ያኖረሽን እምነት እኔ ልጅሽ ለአንድ ሰዓት እንኳ የለኝምና እጅግ ጎስቋላ ነኝ ። አስራ ሁለት ዓመት ከወንጌላዊው ዮሐንስ ቤት ያኖረሽን ልበ ሰፊነት እኔ ደካማው ልጅሽ ለአንድ ሰዓት እንኳ ከምወደው ጋር ለመሆን አልታደልኩምና እጅግ ደካማ ነኝ ! ቅድስት ሆይ የምልጃሽ በረከት የእግዚአብሔርን እገዛ ይላክልኝ ። ፍልሰትሽ መጪውን የምዕመናንን ትንሳኤ ጎልቶ ያሳያል ።  ዕርገትሽ መጪውን የምዕመናን ዕርገት በግልጥ ያስተምራል ። ከሚታስበው በላይ  ቅድስት ፣ ከሚነገረው በላይ ትሁት ፣ ከምሰማው በላይ ቡሩክት ፣ ከጻፉልሽም በላይ ንጽህት ፣ ከተረኩሽም በላይ ልዕልት ነሽና ልቤ ታመሰግንሻለች ! የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን:: ነሐሴ ፲፬ (14) በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ ወንጌልና ምስባክ 🔊ዲያቆን 📖1ኛ ቆሮ 1÷10-19 🔊ንፍቅ ዲያቆን 📖ያዕ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን:: ነሐሴ ፲፬ (14) በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ ወንጌልና ምስባክ 🔊ዲያቆን 📖1ኛ ቆሮ 1÷10-19 🔊ንፍቅ ዲያቆን 📖ያዕ 1÷12-22 🔊ንፍቅ ካህን 📖ግብረ ሐዋርያት 1÷30-34 🔊ምስባክ 📖መዝ 43፥4-6 ✍️"ዘአዘዝከ መድኀኒቶ ለያዕቆብ ብከ ንወግኦሙ ለኩሎሙ ፀርነ ወበስምከ ናኀስሮሙ ለእለ ቆሙ ላዕሌነ" 🔊ትርጉም 👉"ለያዕቆብ መድኀኒትን እዘዝ ባንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን በስምክም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን" 🔊ወንጌል 📖ማቴ 17÷14-24 🔊ቅዳሴ ዘእግዝእትነ የቴሌግራም #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! #Join 👉 https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv ቃለ እግዚአብሔር ለሁሉም ይዳረስ ዘንድ ለወዳጆችዎ ያካፍሉት።