ar
Feedback
የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ ትክክለኛ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት የቴሌግራም ቻናል ነው:: /በመምህር ሲራክ ሰሎሞን/ በዚህ የቴሌግራም ቻናል:- ➮አስተማሪ እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን ➮የቅዱሳን ገድላት ➮ መዝሙሮችን ➮መንፈሳዊ ትምህሮቶችን ያገኛሉ። የመወያያ ግሩፕ: https://t.me/+QKiTJYGJvYpmNWM0 የዚህ ግሩፕ ዓላማ ለበጎ ምግባር ቃለ እግዚአብሔርን መማማር ነዉ::

إظهار المزيد
1 100
المشتركون
+324 ساعات
+97 أيام
+1730 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from N/a
#ዳንኤል_ሠላም_አደረ ታማኝነትህ ብዙ ነው ወሰን ዳርቻ የሌለው ተቆጥሬያለሁ ከሰው ከትቢያ በሚያነሳው/2/
አዝ
አልሞትኩም ጉድጓድ ገብቼ ቢጨክኑም ወንድሞቼ ሞቷል ተረስቷል ያላችሁ አለሁኝ ደስ ይበላችሁ/2/
አዝ
ዳንኤል ሰላም አደረ የአንበሶቹም አፍ ተዘጋ ቀን አይጨልምም ፈጽሞ እግዚአብሔር ብሎ ካነጋ/2/
አዝ
ጴጥሮስ ከእስር ቤት ተፈታ ሮዴ ክፈች በሩን ቃሉን አያጥፍም እግዚአብሔር ተስፋውን ቃል ኪዳኑን/2/
አዝ
ጊንጡን እባቡን ይረግጣል ከአእላፋት ይበልጣል እግዚአብሔር የሆነው ተስፋ ይኖራል በምድር ሲሰፋ/2/ Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

እግዚአብሔርን ቆይተህ ስታውቀው! ሳታውቀው የኖርክበት ዘመን ይቆጭሀል:: የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ከሕሊና_የማይጠፉ_ተወዳጆች "ሰማዕትነት ስር ነው፡፡ ክርስቲያኖች ደግሞ ከዚኽ ስር የሚያቆጠቁጡ ምርጥ ዘሮች ናቸው፡፡ ብዙ ዛፍ የሚያቆጠቁጥበት ስር በለም አፈር ስለሚሸፈን አይታይም፡፡ ከዚያ በሚያቆጠቁጡ ዛፎች ግን ስሩ እንዴት እንደተመቸው ይታወቃል፡፡ ሰማዕታትም በግዙፉ ዓይናችን እንደምን ያለ አክሊል ሽልማት እንደተቀበሉ አይታየንም፡፡ ፍሬያቸው ግን እነርሱን መስለው እነርሱን አኽለው በሚጋደሉ ምርጥ ዘሮች ይታወቃል፡፡ ሰማዕታት አክብሩን ብለው አይናገሩም፡፡ ነገር ግን በክርስቲያኖች ልብ የሚዘሩት ፍሬ ምእመናንን በፍቅር ያስገድዳል፡፡ እነርሱን እንዲመስሉ ያሳስባል፡፡ ሰማዕታት እንደ ፍቅረኛ ናቸው፡፡ አንድ ሰው የፍቅረኛውን ስም በየአጋጣሚው ያነሣል፡፡ በዓይነ ሕሊናው ያስባል፡፡ በተለያየ መልኩ ያያል፡፡ ሰማዕታትም ለክርስቲያኖች እንደዚያ ናቸው፡፡ እጅግ የተወደዱና በፍጹም ከሕሊና የማይጠፉ ተወዳጆች ናቸው፡፡ የልጆቻችንን ስም በነርሱ ስም የምንሰይመው፣ ሥዕላቸውን ሥለን የምንተሻሸው የምንስመው ለሰማዕታቱ ያለንን ጥልቅ ፍቅር የምንገልጽበት መንገድ ስለኾነ ነው፡፡" Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ከዚህ_ዓለም_መለየትህን_አስብ «ለመተኛት ወደ አልጋህ ባመራህ በቀረብህ ጊዜ አልጋዬ፡ ምን አልባት በዚህ ሌሊት ለእኔ መቃብሬ ልትኾኚ ይኾን ይኾናል፤ በጊዜአዊው ዕንቅልፍ ፈንታ በዚህ ሌሊት ያኛው እንቅልፍ (ሞት) ይመጣብኝም እንደ ኾነ አላውቀውም በላት። ስለዚህ ነጻ እግሮች እያሉህ ከመልካም ሥራ በኋላ ሩጥ፤ ከታሠሩ መፈታት በማይችሉበት ማሰሪያ ከመታሠራቸው በፊት፡፡ የእጆችህ ጣቶችም እስካሉህ ድረስ ሞት ከመምጣቱ በፊት በጸሎት ፊትህንና መላ ሰውነትህን በትእምርተ መስቀል አማትብ፡፡ ዐይኖች እስካሉህ ድረስ በአቧራ ከመሽፈናቸው በፊት በእንብዕ(በእንባ) ምላቸው። ሰው ሆይ ከዚህ ዓለም መለየትህን አስብ፣ እንዲህም በል፡- እነሆ የታዘዘ መልአክ ከበር ቆሞአል (ደርሶአል)፣ እኔንም ይከተለኛል። ለምን ሊል ዘሊል እኾናለሁ? መመለሻ የሌለው ዘለዓለማዊ መንገድ አለ፡፡ ከመለኮት ደግነት የተነሣ የሰውን ልብ የሚገዛውና ነፍስን ወደ ሕይወት የሚመራት የመጀመሪያው ትምህርት ተዘክሮተ ሞት ነው። ተዘክሮተ ሞት በሰይጣን እጅግ በብዙ ይጠላል፡፡ እርሱም ከሰው ተዘክሮን ለመንቀል በሙሉ ኃይሉ መሞከርን አይተዉም፡፡ የሚቻለውስ ቢኾን በምድራዊ ሕይወት አሳብ ተብትቦ ተዘክሮተ ሞትን ከሰው ልብ (አእምሮ) ለማስወገድ ምድራዊ መንግሥታትን ለሰው በሰጠው ነበር፡፡ አታላዩ ሰይጣን ተዘክሮተ ሞት በሰው ሁልጊዜም ካለ፣ አሳቡ ለአሁኑ ሕይወት መታለሎች የተጣበቀ ኾኖ እንደማይቀር አልያም የሰይጣን ማታለሎች ሰውን ሊቀርቡት እንደማይችሉ ያውቃል፡፡" የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ስጠኝ_ስትሰጥ_አይቼሃለሁ! የእናቴ የሁልጊዜ ጸሎት ነች። አንድ ቀን እንዲህ ብዬ ጠየኳት? “የሽዬ ይችን ጸሎት ትወጃታለሽ ለምንድን ነው የምትደጋግሚያት?” “አይ ልጄ ይስጠኝ ሲሰጥ.... አይቸዋለሁ” “አምላክን ነው?” “እና አባትህን ነው?” ስቄ ዝም አልኩ .....ከትንሽ ቆይታ በኋላ እንዲህ ተረከችልኝ “ድሮ ነው ያኔ በደጉ ዘመን አንድ ድሃ ገበሬ ነበር። ጫካ ገብቶ እንጨት ሰብሮ ተሸክሞ ከተማ አምጥቶ ሸጦ ቤተሰቡን የሚያስተዳድር .... አንዴ ታዲያ እንደተለመደው እንጨቱን ሰብሮ ተሸክሞ ወደ ቤቱ ሊሄድ ሲል ይደክመውና አንዱ ዛፍ ስር ደገፍ ይላል። ከቆይታዎች በኋላ ሙዳ ስጋ የያዘ ትልቅዬ አሞራ ሰውዬው ከተቀመጠበት ዛፍ ፊት ለፊት ካለ ዛፍ ያርፍና በማንቁርቱ ሊበላ ሲጣደፍ ድንገት ስጋው ይወድቃል ይሄኔ እጥፍጥፍ ብሎ ተኝቶ የነበረ አንድ ከሲታ ውሻ አይኖቹን ባለማመን ሙዳ ስጋ ው ላይ ዘሎ ይከመርና እየተጣደፈ መብላት ሲጀምር ያ ምስኪን ሰው ይመለከታል ወደ ሰማይ አንጋጦም እንዲህ ይላል። “አይ እግዛብሄር አንተኮ ታላቅ ነህ .....በርሃብ ሊሞት የነበረውን ውሻ እንዲህ በጥበብ ትመግበው ....ስራህ ግሩም ነው። እግዚአብሄር ሆይ እንግዲህ ስትሰጥ አይቼሃለሁና ለኔም ስጠኝ ....ስጠኝ ስትሰጥ አይቼሃለሁ” ብሎ ተናግሮ እንጨቱን ትቶ ባዶ እጁን ቤቱ ይደርሳል ባለቤቱም ያየችውን ባለማመን “አንተ ሰውየ ቤት ውስጥ የሚበላ ነገር እንደሌለ እያወክ እንዴት የሚሸጥ እንጨት ሳትይዝ ትመጣለህ?” “አይዞሽ አትፍሪ ይስጠኝ ሲሰጥ አይቸዋለሁ” ብሎ ጠፍር አልጋ ላይ ወጥቶ ተኛ። ሚስት በቁጣ እየለፈለፈች ቀኑ መሸ። ሊነጋጋ ሲል በአቆማዳ የሞላ ጠገራ ብር ሰርቆ ሲሮጥ የነበረ ሌባ አባራሪዎቹ እየደረሱበት እንደሆነ ሲያውቅ ከሰውዬው ጎጆ በራፍ ላይ አስደግፎት ይሮጣል። በማለዳ ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ የምትወደው የምስኪኑ ገበሬ ሚስት የጎጆዋን በራፍ ስትከፍት በአቁማዳ የሞላው ጠገራ ብር ወደቤቷ ግልብጥ ብሎ ይደፋል። ይሄኔ ሃይለኛ እንቅልፍ ላይ የነበረውን ባለቤቷን ጸሎትህን ሰምቶሃል ተነስ ብላ ቀሰቀሰችው ምስኪኑም ያየውን ባለማመን “እግዚአብሄር ሆይ አመሰግንሃለሁ .... አሁንም ስጠኝ ሰትሰጥ አይቸሃለሁ” አለ ይባላል ልጄ፡፡ #በSamuel_Ayalneh Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

"በአርሲ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን" የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች (#EOTCTV ሰኔ ፪ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም ) የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በተፈጠረው የኦርቶዶክሳውያን ግድያና የቤተ ክርስቲያን መቃጠል ኃዘናቸውን ገልጸው በብፁዕነታቸውን መመሪያ ሰጪነት የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ፈቃደኛ መሆናቸውን አሳወቁ። አስተዳዳሪዎቹ ይህንን ያሉት በዛሬው ዕለት በተካሄደው የጋራ ስብሰባ ለጽድቅና ለመንግሥተ ሰማይ ዓላማ የሚሰበሰብ የቤተክርስቲያን ገቢ አስመልክቶ ውይይትና ምክክር በተደረገበት ስብሰባ ላይ ነው። በስብሰባው ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የሀገረ ስብከቱ ወና ሥራ አስኪያጅ ፣ መጋቤ ትፍስሕት ሙሉጌታ ቸርነት የሀገረ ስብከቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ፣ የሀገረ ስብከቱ የዋና ዋና ክፍል ሐላፊዎች ፣ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አክኪያጆች፣ የገዳማትና አድባራት እእተዳዳሪዎች የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነትና የአድባራት የሒሳብ ሹሞች ተገኝተዋል። የስብሰባው ጉዳይ እውነተኞች ምዕመናን የሰጡትንና በተለያዩ የሰዋዊና ቁሳዊ ልማት ምክንያት ለቤተ ክርስቲያን ገቢ ያደረጉትን ገንዘብ ሕግና አሠራርን በመጠበቅ ቤተ ክርስቲያን ለተመሠረተችበት ሕያው ዓላማና መንፈሳዊ ሥራ ላይ አገልግሎት ላይ ይውል ዘንድ ምክክር ለማድረግ የተጠራ ስብሰባ እንደሆነ ተገልጿል። በጉባኤውም በሀገረ ስብከቱ የሒሳብና በጀት ዋና ክፍል ሐላፊ ሊቀ ኅሩያን አስናቀ ሸዋየ አጭር ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በዚህ መነሻነትም ከሀገረ ስብከቱ ጀምሮ እስከ አጥቢያ ክርስቲያናት የያሉ ተሳታፊዎች ሐሳብና አስተያየት ሰጥተዋል። አስተያያት ሰጪዎቹ እንዳሉት የቤተ ክርስቲያን ገቢዎችን ሕግና አሠራርን ጠብቆ ለተገቢው ዓላማ መዋል፣ ተቋማዊ ተናብቦትና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ባለችበት ሁሉ የተፈጠሩ ችግሮችና ቁስሎችን የጋራ በማድረግ ከግል ፍላጎትና ሐሳብ ይልቅ ቤተ ክርስቲያን በማስቀድም መሥራት በሚሉ ጉዳዮች ላይ አስተያያቶች ቀርበዋል። በተለይም በሀገረ ስብከቱ ደረጃ እየተለመዱ የመጡ ዘመኑን ያነበቡና ችግር በችግር ሳይሆን በመፍትሔ እናክማቸውን በሚል መንገድ የተጀመሩ የውስጥ አሠራሮችና የተጨባጥ የሆኑ የራስ አገዝ ልማቶች በእጅጉ የሚበረታቱና የሚያስመሰግኑ መሆናቸውን ከከፍተኛ አድናቆት ጋር ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስና መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱን የሥራ ሐላፊዎች አመስግነዋል። በሌላ በኩል አስተዳዳሪዎቹ በገጠሪቱ ያለቸው ቤተ ክርስቲያን ስታነባ ያመናል ፤ ቁስሏም ይጠዘጥዘናል፤ በመሆኑም በሰሙኑ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ መመሪያ ሰጪነት ተባብረን ለመሥራት ፈቃደኛ መሆናችን እንገልጻለን ብለዋል። የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ በበኩላቸው በብፁዕነታቸው የሚመራው ሀገረ ስብከት ነገን በማሰብ ዛሬ ላይ አቅዶ እየሠራ በመሆኑን በማስታወስ በዚህ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችን የሥራ ሐላፊዎች ድርሻቸው ሰፊ ነው ብለዋል። አክለውም የተቀበልነው ሕያው ተልእኮ ቤተ ክርስቲያንን የመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በታማኝነት በመንፈሳዊ ትርፍ ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለቀጣዩ ትውልድ በክብር የማስተላላፍ ድርሻ አለብን ለዚህ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ገቢ በአግባቡ መጠበቅና ቤተ ክርስቲያን ጠቀም ሥራዎችን በመሥራት መሆን አለበት ብለዋል። የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የተሰጠንን ሐላፊነት በአግባቡ መተርጎምና ለቤተ ክርስቲያን ብልጫ ላለው አገልግሎት ማውል ይኖርብናል ያሉ ሲሆን በተለይም አሠራራችን ዘመኑን የዋጀ፣ ለምእምናን ቅርብ የሆነና ዘላቂ ለውጥ ላይ መሠረት ያደረገ መሆን አለበት ብለዋል። ቀጥለውም የቤተ ክርስቲያን ገቢ ከምእመናን መቀነት እስከ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሚደርስ መስመር ያለው ተቋማዊ አሠራር ያለው በመሆኑ አልቅሳ አንብታ ለሐጢአት ሥርየት ብላ የምትሰጥውን የአንዲት ምእመን ስጦታና ዛሬን ለነገ እናሻግር በሚል መርሕ የተሠሩ የራስ አገዝ ልማቶች ገቢዎች በሰዓቱ መሰብሰብና ለታለመው ዓላማ ማዋል ይገባናል ብለዋል። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሁሉም አህጉረ ስብከት ደጋፊ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና መጋቢ የሁሉ መጠጊያ እንደሆነ የገለጹት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ ሊቀ ጳጳስ በቤተ ክርስቲያናችን ተቋማዊ ህልውና እና ተልእኮ ማስፈጸም ረገድ ድርሻው ሰፊ ነው ብለዋል። በመሆኑም የሰው ልማት ላይና የተቋማት ዕድገት ላይ በእጅጉ መሥራት እንደሚገባው የተጠቆሙት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የሚሠሩ ወንጌልን የሚስፋፋባቸው፣ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት የሚረዱበት እና ራሳቸውን ያልቻሉ አህጉረ ስብከት የሚደጎሙበት ሁሉን አቀፍ የራስ አገዝ ልማቶች ላይ በማገዝ ትልቁን ድርሻ እንደሚወጣ ተስፋቸውን ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በተለያዩ አህጉረ ስብከት በበምእመናንና በአብያተ ክርስቲያናት ጉዳት ሲያጋጥም ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያዘው በፍጥነት ለችግር የሚደርስ ሀገረ ስብከት መሆኑ ይታወቃል። በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ግንቦት 23/2018 ዓ/ም ጀምሮ በተፈጠረው ጥቃት ንጹሐን ምእመናን በግፍ እንደሞቱና ከመቶ ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እንደተቃጠለ የሚታወስ ነው ነው። @የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ https://t.me/ardssu

https://www.youtube.com/watch?v=KzVtmmpqekY አስታግስልን በዘማሪት ፋሲካ ድንቁ የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ወደ_እግዚአብሔር_ቤት እንዲሮጥ አድርጉት "እውነተኛ ክርስቲያን አባቱ ክርስቶስን ይመስላል፡፡ ይሰደዳል እንጂ አያሳድድም፡፡ ይሰደባል እንጂ አይሳደብም፡፡ የጠፉትን ፍለጋ ይደክማል እንጂ ይባስ ብሎ
#ወደ_እግዚአብሔር_ቤት እንዲሮጥ አድርጉት "እውነተኛ ክርስቲያን አባቱ ክርስቶስን ይመስላል፡፡ ይሰደዳል እንጂ አያሳድድም፡፡ ይሰደባል እንጂ አይሳደብም፡፡ የጠፉትን ፍለጋ ይደክማል እንጂ ይባስ ብሎ አይገፈትርም፡፡ በወንድሙ ውድቀት ያለቅሳል እንጂ አይደሰትም፡፡ እንዲህ ካልሆነ ግን አባቱ ሌላ ነው፡፡ ለእግዚአብሔር የምናቀርበው ምስጋና በጊዜውም ያለ ጊዜውም ሊሆን ይገባል፡፡ ባገኘን ጊዜ ብቻ ሳይሆን ባጣንም ጊዜ፤ ባለጤና በሆንን ጊዜ ብቻ ሳይሆን በታመምንም ጊዜ፤ ሲሳካልን ብቻ ሳይሆን ባልተሳካልንም ጊዜ ማመስገን መለማመድ አለብን፡፡ የምስጋናችን ምንጭ የሁኔታዎች መለዋወጥ ሳይሆን ስለ አምላካችን ብቻ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ይህን ማድረግ ስንለማመድ በክብር ላይ ክብር ይጨመርልናል፤ እንደ አባታችን ኢዮብ የዲያብሎስን አፍ እንዘጋለን፡፡ ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋላችሁን?” እንኪያስ "በዘፈን የደነቆረን ጀሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርጉት፡፡ ሴትን በመመኘት የታወረው ዐይን ፈጣሪውን እንዲያይ አድርጉት፡፡ በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርጉት፡፡ ወደ ኃጢአት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርጉት፡፡ ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፈር መልካም ንግግርን እንዲናገር አድርጉት፡፡ ከተአምራት ሁሉ የበለጠ ተአምር ይሄ ነው፡፡" Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ማረኝ አቤቱ፥ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ፤ እንደ ምሕረትህም ብዛት መተላለፌን ደምስስ። ከበደሌ ፈጽሞ እጠበኝ፥ ከኃጢአቴም አንጻኝ፤ እኔ መተላለፌን አውቃለሁና፥ ኃጢአቴም ሁልጊዜ በፊቴ ነውና። አሜን የልበ አምላክ የቅዱስ ዳዊት አምላክ ሆይ አቤቱ ይቅር በለን ማረን በምሕረት አይኖችህ ተመልከተን።🤲 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ሰኔ_እና_ሰኞ_ሲገጥሙ... ምን እናድርግ❓❓❓ ​በማህበረሰባችን ዘንድ «#ሰኔ እና #ሰኞ ሲገጥሙ #ክፉ_ቀን ነው፣ #አደጋ_አለው፣ #መጥፎ_ነገር_ይከሰታል» የሚል የተለመደ ወሬ እናስተውላለን። ይህ አስተሳሰብ ግን ከቤተ-ክርስቲያናችን እምነት እና ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ አንጻር ሲታይ ምን ይመስላል? ​1. ቀናትን የፈጠረ ማን ነው? እግዚአብሔር አምላክ ሰማይንና ምድርን፣ ቀናትንና ዘመናትን የፈጠረ አምላክ ነው። «ቀኑ የአንተ ነው ሌሊቱም የአንተ ነው  አንተ ፀሐይንና ጨረቃን ፈጠርህ» (መዝሙር ፸፫፥፲፮-፲፯)። ስለዚህ እግዚአብሔር የፈጠረው ቀን "#ክፉ" ሊሆን አይችልም። ​2. ምን መፍራት አለበት? በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት፣ ክርስቲያን ሊፈራ የሚገባው «ቀኑን» ሳይሆን «ክፉ ሥራን» ነው። ኮከብ ቆጠራ፣ እድል ፈንታ እና በዕለታት መገጣጠም ማመን እንደ ክርስቲያን የማይጠበቅ፣ ሟርተኝነትን የሚመስል አጉል እምነት ነው። ​3. እንግዲህ ምን እናድርግ? ​=>በእግዚአብሔር ታመኑ፡ ሕይወታችን በእግዚአብሔር እጅ እንጂ በቀን አቆጣጠር አይደለም።  ት.ኤ: ፲፯÷፭-፯ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹንም ክንዱ የሚያደርግ ልቡም ከእግዚአብሔር የሚመለስ ሰው እርጉም ነው። =>​ጸሎት አድርጉ፡ ቀን ሲገጥም መፍራት ሳይሆን፣ "አምላኬ ሆይ ዕለቱን በሰላም አሳልፍልኝ" ብሎ መጸለይ ትልቅ ጥበብ ነው።  ፊልጵስዩስ ፬፥፮ እግዚአብሔር ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋራ በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ። =>​አጉል ወሬን አትስሙ፡ በእንደዚህ ዓይነት ቀናት ሰዎችን የሚያሸብር ወሬ ከሚያወሩ ሰዎች ይልቅ፣ በአምላክ ቸርነት የሚመኩ ሰዎች እንሁን። የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#ሰኔ_እና_ሰኞ_ሲገጥሙ... ምን እናድርግ❓❓❓ ​በማህበረሰባችን ዘንድ «#ሰኔ እና #ሰኞ ሲገጥሙ #ክፉ_ቀን ነው፣ #አደጋ_አለው፣ #መጥፎ_ነገር_ይከሰታል» የሚል የተለመደ ወሬ እናስተውላለን። ይህ አስተሳሰብ ግን ከቤተ-ክርስቲያናችን እምነት እና ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ አንጻር ሲታይ ምን ይመስላል? ​1. ቀናትን የፈጠረ ማን ነው? እግዚአብሔር አምላክ ሰማይንና ምድርን፣ ቀናትንና ዘመናትን የፈጠረ አምላክ ነው። «ቀኑ የአንተ ነው ሌሊቱም የአንተ ነው  አንተ ፀሐይንና ጨረቃን ፈጠርህ» (መዝሙር ፸፫፥፲፮-፲፯)። ስለዚህ እግዚአብሔር የፈጠረው ቀን "#ክፉ" ሊሆን አይችልም። ​2. ምን መፍራት አለበት? በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት፣ ክርስቲያን ሊፈራ የሚገባው «ቀኑን» ሳይሆን «ክፉ ሥራን» ነው። ኮከብ ቆጠራ፣ እድል ፈንታ እና በዕለታት መገጣጠም ማመን እንደ ክርስቲያን የማይጠበቅ፣ ሟርተኝነትን የሚመስል አጉል እምነት ነው። ​3. እንግዲህ ምን እናድርግ? ​=>በእግዚአብሔር ታመኑ፡ ሕይወታችን በእግዚአብሔር እጅ እንጂ በቀን አቆጣጠር አይደለም። ት.ኤ: ፲፯÷፭-፯ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹንም ክንዱ የሚያደርግ ልቡም ከእግዚአብሔር የሚመለስ ሰው እርጉም ነው። =>​ጸሎት አድርጉ፡ ቀን ሲገጥም መፍራት ሳይሆን፣ "አምላኬ ሆይ ዕለቱን በሰላም አሳልፍልኝ" ብሎ መጸለይ ትልቅ ጥበብ ነው። ፊልጵስዩስ ፬፥፮ እግዚአብሔር ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋራ በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ። =>​አጉል ወሬን አትስሙ፡ በእንደዚህ ዓይነት ቀናት ሰዎችን የሚያሸብር ወሬ ከሚያወሩ ሰዎች ይልቅ፣ በአምላክ ቸርነት የሚመኩ ሰዎች እንሁን። የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

#የሚቻለንን_ኹሉ_እናድርግላቸው ⛪️“ልጆቼ! ሰዎች ክፋትን እየሠሩ ብትመለከትዋቸው በፍጹም አትጥሏቸው፡፡ ሰው ክፋቱ እንጂ እርሱ ራሱ አይጠላምና፡፡ የሐሰት ትምህርቱ እንጂ እርሱ ራሱ አይጠላምና፡፡ ምክንያቱም እርሱ ራሱ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ እጅግ መልካም ፍጥረት ነው፡፡ ክፉ ሥራው ግን ከዲያብሎስ ነው፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር ሥራና የዲያብሎስ ሥራ ለይተን እንወቅ፤ እንረዳ፤ ከዚያም ማቀላቀልን እንተዋለን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ወገኖቹ አይሁድ ክርስቶስን እንዳንገላቱት፣ እንደዘበቱበት፣ እንዳሳደዱት፣ እልፍ ወትእልፊት ጸያፍ ነገርም እንደተናገሩበት ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ግን እንዲህ በማድረጋቸው ጠላቸው? በፍጹም! እንደውም ስለ እነርሱ ይረገም ዘንድ ይጸልይ ነበር /ሮሜ.9፥3/፡፡ ነቢዩ ሕዝቅኤል እነዚህ ሰዎች በነቢያት ደም የሰከሩ መኾናቸውን ጠንቅቆ ቢያውቅም ይጸልይላቸው ነበር /ሕዝ.9፥8/፡፡ ሙሴ እነዚህ ሰዎች ኃጢአት እንደ ሠሩ ቢያውቅም ስለ እነርሱ ከሕይወት መጽሐፍ ይደመሰስ ዘንድ ይለምን ነበር /ዘጸ.32፥32/፡፡ ለምን? ሰዎቹ መዳን የሚገባቸው /ሮሜ.10፥1/ ደግሞም በሥላሴ አምሳል የተፈጠሩ እጅግ ግሩማን ናቸውና የሥላሴ ፍጥረት አይጠላም፤ ክፉ ሥራቸው ግን ከክፉው (ከዲያብሎስ) ነውና ይጠሉታል፡፡ ልጆቼ! አንድ የጤና ባለሙያ ታማሚውን ጠልቶ ፊቱ የሚያዞርበት ከኾነ፣ ታማሚውም ሐኪሙን አታሳዩኝ እያለ ከጠላው እንደምን ከበሽታው መዳን ይቻለዋል? እኛስ ክፉ የሚሠሩትን የምንጠላቸው ከኾነ እንደምን ከክፉ ሥራቸው ልናወጣቸው እንችላለን? ልጆቼ! እንግዲያውስ በክፉ በሽታ የተያዘውን ወንድማችን ከበሽታው እንዲፈወስ ልንረዳው ይገባናል እንጂ ጤነኞች የምንኾን እኛ ሌላ በሽታ የምንጨምርበት ልንኾን አይገባንም፡፡ ከበሽታው ምንም የማይፈወስ ቢኾን እንኳ ከእኛ የሚጠበቀውን ኹሉ በማድረግ እስከ መጨረሻው ልንጥርለት ይገባናል፡፡ እስኪ ይሁዳን አስታውሱት! የታመመው ሊድን በማይችል በሽታ ነበር፡፡ ግን መፈወስ የማይችል ነው ብሎ ክርስቶስ ተወው? በፍጹም! እስከ መጨረሻይቱ ደቂቃ ታገሠው፤ ደግሞም እንዲመለስ ይገስጸው ነበር እንጂ፡፡ እኛም ይህን ከአባታችን ልንማር ይገባናል፡፡ ክፋትን የሚሠሩ ሰዎች ስናይ ፈጥነን አንተዋቸው፡፡ የሚቻለንን ኹሉ እናድርግላቸው እንጂ፡፡ ባይመለሱ እንኳ ሽልማታችን አይቀርብንም፡፡ ይህም ብቻ ሳይኾን ክፋትን የሚሠራት እኁ በእኛ እንዲደነቅ እናደርገዋለን፡፡ ምክንያቱም እንዲህ በክፋት የሰከሩ ሰዎች ተአምራትን አድርገን፣ ሙትን አስነሥተን ከምናሳያቸው ይልቅ በትኅትናችን፣ በጨዋነታችን፣ በትዕግሥታችን እጅግ ይማረካሉና፡፡ አንድ ሙት ማስነሣት ምን ይደንቃል? ዓለም ኹሉ በከመ ቅጽበት ይነሣ የለምን? ሰዎች ከፍቅር በላይ በምንም መንገድ ከክፋታቸው ልንመልሳቸው አንችልም፡፡ ፍቅር ሰዎችን ከአውሬነታቸው መልሳ ሰዎች እንዲኾኑ የምታደርግ ታላቅ መምህርት ናት፡፡ እንግዲያውስ ብዝሕ ያላቸውን በረከቶች በእኛ ላይ እንዲጐርፉ፣ ደግሞም መቼም የማይገማና የማይበላሽ ፍሬአቸውን በጊዜው እንድንበላ የግብረገብነት ኹሉ ራስ የምትኾንን ፍቅር በልባችን ውሳጤ እንትከላት፡፡ ይህን እንድናደርግ ሰውን በመውደዱ ሰው የኾነው ክርስቶስ ይርዳን አሜን፡፡” Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

የቅዱስነታቸው በዓለ ዕረፍት በሶዶ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ መንክራት አቡነ ተክለሃይማኖት አንድነት ገዳም ተከበረ ! የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሦስተኛ ፓትርያርክ የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት 38ኛ ዓመት የዕረፍታቸው መታሰቢያ በወላይታ ሀገረ ስብከት በሶዶ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ መንክራት አቡነ ተክለሃይማኖት አንድነት ገዳም ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የሀገረ ስብከቱ የየመመሪያው ሓላፊዎች ፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ድባብ መከበሩን የሀገሩ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ቦክቻ ኤንጋ ለሚዲያችን አሳውቀዋል። መልአከ ሰላም እንዳሉት የቅዱስነታቸው መታሰቢያ ላለፉት ዓመታት ሻማ በማብራት ብቻ ሲታሰብ ቢውልም የሀገረ ስብከቱ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ አባቶች ካህናት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በመወያየት ክብረ በዓሉ በደመቀ ሁኔታ በማኅሌት፣ በቅዳሴ ተከብሮ እንዲውል በወሰንነው መሠረት ተከብሯል ብለዋል። አክለውም ቅዱስነታቸው ግንቦት 12 ቀን 1980 ዓ.ም. በሕመም ላይም ሆነው ብዙ በደከሙበት ቦታቸው መጥተው ከሕመማቸውጋ እየታገሉ የመሠረት ድንጋይ ጥለው ሕመሙ ሲበረታባቸው ወደ አዲስ አበባ አቅንተው ግንቦት 28/1980 ዓ.ም ቢያርፉም በሀገረ ስብከቱ ለበርካታ ዓመታት ዕረፍታቸው ሲታወስ መቆየቱንና አሁን ግን ብፁዕ አባታችን በተገኙበት መልኩ በደማቅ ሁኔታ መከበሩን ገልጸዋል።

#አቃጥሏት_ግዴለም              🔥 ⛪️⛪️⛪️🔥 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ቤተ ክርስቲያን ቅድስት እመ ኵሉ፣ የወንጌል ማኅደር የጸናብሽ ቃሉ፣ ስብከትሽ ሰላም ነው ለዓለም በሙሉ፤ አፅራረ ሰላም ግን አንቺን ይጠላሉ፤ ተልእኮሽ ፈውስ ነው ለታመሙ ኹሉ፤ መዳን የማይወዱ ከአንቺ ይሸሻሉ፤ ጭራሽ ሊያሳድዱሽ ይመካከራሉ፤ አጥፍቶ ጠፊዎች ሊያጠፉሽ ይሻሉ። የጥፋት ልዑካን ለጽድቅ ያልታደሉ፣ ሕንፃሽን በእሳት አቃጠሉት አሉ፤ ጣሪያ ግድግዳዉን አፈረሱት አሉ፤ ባያውቁት ነው እንጂ ቢጠፋቸው ውሉ፣ በአንቺ እሳትነት አብረው ይጨሳሉ፤ በማገዱት እንጨት ኋላ ይነዳሉ፤ ዛሬ እንዳፈረሱሽ ነገ ይፈርሳሉ፤ በሠፈሩት መጠን ዋጋን ያገኛሉ። አህዛብ ግብዞች ሆይ የሰይጣን ፈረሱ፣ ደስ ካሰኛችሁ እሳት መለኮሱ፣ አቃጥሏት ግዴለም ጣሪያዋን አፍርሱ፤ ግድግዳ ወለሉን ብሎኬቱን አንሡ፤ ለጊዜውም ቢኾን ቅፅሮቿን ደምስሱ፤ ልጆቿን በሙሉ ደም ዕንባ አስለቅሱ። ነገር ግን ጌታዋ ሲቆጣ ንጉሡ፣ መቃጠላችሁን ፈጽሞ እንዳትረሱ፤ ጽዋ ተርታችሁን ዘወትር አስታውሱ፡፡ ጌታ ችሎ ችሎ መዓቱን ሲያመጣ፣ ቅፅሩን ለማስከበር ሲፈርድ በቁጣ፣ በተራ መንደድ ነው የኹላችሁ ዕጣ፡፡ እስከዚያው ድረስ ግን እስኪመጣ ጌታ፣ የዓለምን መድኀኒት የሕዝብን አለኝታ፣ ቤተ ክርስቲያንን አፍርሷት በአንድ አፍታ፤ አቃጥሏት ግዴለም አንድዷት በተርታ፡፡ እርሷ በትረ ወንጌል የሾለ ብረቱ፣ ብትቆሙ ደፍራችሁ በኃያል ስለቱ፣ ደዌው ለእናንተ ነው ሕመሙ ጉዳቱ። ጣሪያና ግድግዳው አካሏ ቢደማ፣ ብትነድ ብትቃጠል በክፉዎች ፊርማ፣ መቅደስ ማኅሌቱ ቢመስልም ባድማ፣ አትፈርስም በፍጹም በግብዞች ዐድማ፤ እሳት የሚያነዳት አይደለችም እማ፤ በክርስቶስ ፍቅር ተቃጥላለች ቀድማ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ይቺ ምድራዊቷ፣ መለኮት እሳት ነው ጥንትም መሠረቷ፣ የክርስቶስ ደም ነው እስትንፋስ ሕይወቷ፣ አቃጥሏታልና ክርስቶስ እሳቷ፣ አጽንቷታልና አምላክ ባለቤቷ፣ በፍጹም አትፈርስም ጽኑ ነው ዐለቷ፤ በጠላት ዘመቻ አይኾንም ኅልፈቷ፡፡ ቅድስት ቤተ-ክርስቲያናችንን እግዚአብሔር አምላክ ይጠብቅልን:: በየጊዜው ሰማዕትነትን የሚቀበሉ ኦርቶዶክሳዊያንን ነፍስ እግዚአብሔር አምላክ በሰማዕታት አክሊል ያሳርፍልን፤ ከዚህ ክፉ ዘመን የተረፉትንና ሜዳ ላይ የቀሩትን ደግሞ አምላክ በምህረቱ ይጎብኛቸው። የራሄልን እንባ ያበሰ አምላክ እንባቸውን ያብስልን😭😭😭 ሀገራችን ኢትዮጵያን ሰላም ያድርግልን! አሜን:: Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

በምስራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት የሞቱትን ኦርቶዶክሳዊያን ነፍስ #እግዚአብሔር በሰማዕታት አክሊል ያሳርፍልን፤ ከዚህ ክፉ ዘመን የተረፉትንና ሜዳ ላይ የቀሩትን ደግሞ አምላክ በምህረቱ ይጎብኛቸው። የራሄልን እንባ ያበሰ አምላክ እንባቸውን ያብስልን😭😭😭ሀገራችን ኢትዮጵያን ሰላም ያድርግልን! አሜን:: የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv