uk
Feedback
እውነት ለሁሉ [truth for all]

እውነት ለሁሉ [truth for all]

Відкрити в Telegram

ይህ ቻናል ዓላማው በማስረጃና በመረጃ በመታገዝ እውነትን ከውሸት በመለየት፣ በአላህ ፈቃድ በጨለማ የሚኖሩ ወገኖችን ብርሃን ወደሆነው ኢስላም መጣራት ነው። قُلْ جَاءَ الْحَقُّ وَمَا يُبْدِئُ الْبَاطِلُ وَمَا يُعِيدُ [ ሱረቱ ሰበእ - 49 ] «እውነቱ መጣ፡፡ ውሸትም መነሻም መድረሻም የለውም (ተወገደ)» በላቸው፡፡

Показати більше
3 008
Підписники
+224 години
+137 днів
+6130 день
Архів дописів
🚫ልቅ የሆኑ የወሲብ ፊልሞችና ምስሎችን በመመልከት ለተለከፉ ሁሉ! ♻️እነዚህ ፊልሞችና ምስሎች የጀሀነም በሮች ናቸው! 📵እነዚህን የበከቱና የተግማሙ ዝሙተኞችን በማየት እስረኛ የሆንክ/ሽ ሁሉ በዚህ ሰበብ ምን እንደሚከተልህ/ሽ ተከታዩን እስተውለህ/ሽ አንብብ/ቢ! ☞ለላጤዎችና ለባለትዳሮች መጨረሻ  ላይ የተቀመጠውን መፍትሄ በጥሞና አንብቡት! ☞የተራቆቱ ዝሞተኞችን ማየት እጅግ ከባባድ ወንጀሎች ውስጥ እንደሚካተቱ ታውቃለህ? ☞እነዚህን ዝሙተኞች መመልከት ውርደትና ደካማነት እንደሚያወርስ ታውቃለህ? ☞እነዚህን ዝሙተኞች መመልከት በሰዎች አይን ያነስክና ወራዳ እንደሚያደርግህ ታውቃለህ? ☞እነዚህን አፀያፊ ምስሎችና ቪድዮዎች በማየት የተለከፈ ወጣት በቀላሉ ካገኘው ተቃራኒ ፆታ ጋር ሁሉ ዝሙት ላይ  የሚወድቅ ይሆናል። እንዲሁም ራስን ወደ ማርካት (masturbation) ሱስና የስንፈተ ወሲብ አደጋ ተጋላጭ የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው። ☞እነዚህን የዝሙት ዌብሳይቶችና የቪድዮ ምስሎች መመልከት በአእምሮህና በአይንህ ላይ ድክመትን እንደሚከስት ታውቃለህ?  ይህን በመመልከት ሱሰኛ የሆነ ሰው ቀለል ያሉ ጉዳዮችን በቀላሉ ይረሳል። ይህ አደጋ እያደገ ሲሄድ የአእምሮ ድክመት አስከትሎበት እንዴት መናገር እንዳለበት ሁሉ ላያውቅ ይችላል! ሌሎችም ብዙ የጤና እክሎች ያጋጥሙታል! ☞ይህ ወንጀል አላህ ዘንድ ወራዳ ሰው እንደሚያደርግህ ታውቃለህ? ☞የእነዚህ ዝሙተኞች ምስል አእምሮህ ላይ ተቀርፇል?  (ይህ የአላህ ቁጣ ምልክት ነው!) ☞እነዚህን ነገሮች መመልከት ትንንሽ ነገሮችን ሁሉ የምትሰጋ ፈሪና ልፍስፍስ እንደሚያደርግህ ታውቃለህ? ☞ይህን እርቃን ብልግና የምትመለከት ሆይ!  የሸሪዓ እውቀትን ብርሃን በፍፁም ማግኘት እንደማትችል ታውቃለህ? ☞በዚህ ወንጀልህ ከምትወዳትና ከምትወድህ የህይወት አጋርህ ባለቤትህ ጋር የተረጋጋ ህይወት መኖር እንደምትነፈግ ታውቃለህ? ☞ይህን አስቀያሚ ተግባር የምትመለከት ከሆነ ደጋግ የአላህ ባሪያዎች ይህን ቀፋፊ ተግባርህን ባትነግራቸውም እንኳን ሊጠሉህ እንደሚችሉ ታውቃለህ? ☞እነዚህን ዝሙተኞችን ማየት ግዴታ የሚሆንብህ በዝሙት ወንጀላቸው በድንጋይ ተወግረው ሲገደሉ ብቻ እንደሆነ ታውቃለህ? ☞ ከዚህ ከምትመለከተው ቀፋፊ ምልከታ እውነተኛ ተውበት አድርገህ ወደ አላህ ካልተመለስክ እጅግ ከባድ ዋጋ ለወደፊት እንደሚያስከፍልህ ታውቃለህ? ☞እጅግ የምትወደውና የምትቀርበው ሰው ሞት ዜና ይህን ነገር እየተመለከትክ ብትሰማ ትወዳለህ? ☞ ከዚህ ወንጀል አፀያፊነት የተነሳ አላህ መሬትን ደርምሶ ሊያስውጥህ እንደሚችል ታውቃለህ? ☞በዚህ ቀፋፊ ምልከታ ላይ ሆነህ ሞት ሊመጣህ እንደሚችል ታውቃለህ? አስከፊ ኻቲማ ሊያስደነግጥህ እንደማይችል እርግጠኛ ነህ? ☞ጌታህ ቻይ ነው!  ለግዜው ይተውኃል፤ ነገር ግን በምትሰራው ወንጀል ደስተኛ ሆኖ እንዳይመስልህ!  ከዚህ ወንጀልህ ተውበት ካላደረክ ለወደፊትም ቢሆን ከባድ መከራ ትጋረጣለህ! ☞ የዒባዳህን ጥፍጥና እንደሚያሳጣህ አምልኮ ላይ ደካማ እንደሚያደርግህ ታውቃለህ?  ለዒባዳ በቆምክ ቁጥር የምታያቸው ምስሎች አዕምሮህን ተቆጣጥረው እንደሚፈታተኑህ ታውቃለህ? በዚህም ከአምልኮ መሸሽና ተስፋ ቢስነት ሊሰማህ ይችላል። ይህ ደግሞ ወደ አደገኛው አዘቅት ክህደት የሚጎትት ጠንቅ ነው። ☞ ራስህን የምትጠላ የወንጀል ምርኮኛ እንደሚያደርግህ ታውቃለህ? ☞ለአላህ ብሎ አንዳች ነገርን የተወ ሰው አላህ የተሻለ መልካም ነገር እንደሚተካለት ታውቃለህ? ☞አላህ በባሪያው መመለስ የሚደሰት የተብቃቃና ምስጉን ጌታ መሆኑን ታውቃለህ? ☞ከወንጀል ጥብቅ ከሆንክ አላህ ከችሮታው እንደሚያብቃቃህ ታውቃለህ? ☞ለደቂቃዎች (ሻህዋ) ስሜት ተብለው የሚሰሩ ወንጀሎች የአመታት ቅጣት እንደሚያመጡ ታውቃለህ?  ☞ዛሬ በዱንያ ላይ የምትሰራቸው ወንጀሎች፦ የተከለከለን ማየት፣ መስራትና ሌሎችንም በዱንያ ላይ ቅጣቱን በድህነት፣ በአደጋ፣ ሪዝቅህን በመከልከል በቤተሰብህ፣ በልጆችህና በቅርብ ሰዎች ላይ አደጋ ሊከስት እንደሚችል ታውቃለህ? ☞ይህ ወንጀል አእምሮህን ተቆጣጥሮ ከምትመለከታት ሴት ሁሉ ቀፋፊው ዝሙት ላይ ለመወደቅ እንደሚገፋፋህ ታውቃለህ? ✅✅✅✅✅ ☞ለላጤዎች ምክር! ♻️ያላገባህ እንደሆነ በተቻለህ መጠን ለማግባት ሞክር! ♻️ስለ ትዳር በቂ እውቀት ይዘህ ወደ ትዳር ግባ! ♻️ ማግባት ካልቻልክ ትርፍ የምትለውን ግዜህን በመልካም ነገር አሳልፍ፦ በፆም፣ በንባብ፣ ስፖርት በመስራት፣  መልካም ኢስላማዊ ትምህርቶችን በመማር፣ በመስማትና በማየት....... ♻️በብዛት ብቻህን ከመሆን ተቆጠብ ♻️አላህን ከዚህ ቀፋፊ ወንጀል ነፃ እንዲያደርግህ ተማፀን! ♻️መልካም ሰዎች ጋር ለመቀማመጥ ሞክር! ♻️ሸይጣን ይህን ወንጀል ባስታወሰህ ቁጥር ቆራጥ ሆነህ ላለመመለስ ሞክር!  መጀመሪያው ቢከብድብም በሂደት አላህ ይረዳሃል! ☞ለባለ ትዳሮች ምክር ♻️አግብተህ ከሆነ ከትዳር  አጋርህ ጋር ስለ  ህይወታቹህ ያለ እፍረት በግልፅ በመነጋገር የምትፈልጉትን እርካታ ሁሉ ማግኘት እንደምትችል እውቅ! ♻️ በኢስላም ጥላ ስር ያሉ ታማኝ ከትዳር ህይወት ጋር የተያያዙ አስፈላጊ ትምህርቶችንና ጥናታዊ ፅሁፎችን አንብብ! ♻️ በዚህ ላይ የተሻለ እውቀት ያላቸውን አላህን የሚፈሩ ብለህ የምታስባቸውን ወንድሞችህን አማክር! ♻️ ሚስትም የዘመኑን ክፋት ልትረዳና ነቃ ብላ ከትዳር አጓሯ ጎን ልትቆም ይገባል። በግልፅ ማውራትና ፍላጎቱን ማሟላት ብልግና ሳይሆን ብልጠት መሆኑን አውቃ በተቻለ መጠን ውበቷን በመጠበቅ የባሏ ልብ እንዳይሸፍትና እንዳይሰላች የበኩሏን ጥረት ሁሉ በማድረግ ባለቤቷን ማስደሰት አለባት! ✖️እነዚህ የተግማሙና የበከቱ ዝሙተኞች ይህችን አጭር ህይወትን እንዲያበላሹ አትፍቀድ!  ጀግና ሁን/ሁኚ! ♻️በመጨረሻም የመልካም ሰዎችን ታሪክ አንብብ! እንዴት አላህን እንደሚጠነቀቁ አስተውል። አስተንትን! በዚህ ወንጀልህ የሰማያትና የምድር ጌታን እያመፅክ መሆኑ ይሰማህ!  ኮምፒዩተሮችህና ስማርት ስልኮችን የመዋረጃህ ሰበብ አታድርጋቸው! ኢብኑ'ል ወርዲይ በግጥማቸው እንዲህ ብለዋል ፦ إنَّ أحلى عيشةٍ قضيتُها ذهبتْ لذاتُها والإثمُ حلْ ስሜቴን ያራገፍኩባቸው ጣፋጭ ግዜያቶች ጥፍጥናቸው ሄዷል ወንጀሉ ቅን ቀርቷል/ተመዝግቧል ©️opy ♻️ሁላችንንም አላህ ለሚወደው ይምራን! 🔗SHARE 🔗SHARE
https://t.me/iwnetlehullu1

የ ፕሮፌሰር ባርት የአዲስ ከዳን ህያሳ ሊቅ ንግግር ለኔ መነሻ ለጽሁፌ የሆነው .... የዮሐንስ ወንጌል መግቢያ 1:1-18 በመጀመሪያ ቃል ነበረ ቃል በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ ይህ ክፍል ከሙሉ መጽሐፍ ጋር ወጣ ያለ እሳቤ ያለው የማይመሳሳል በይዘቱ ለየት ያለ ከወንጌሉ በመሆኑ በቀድሞ የወንጌሉ አካል ያልነበረ የተጨመረ እንደሆነ በብዙ ሙሁራን ዘንድ የታመነ ነው

የዮሐንስ ወንጌል መግቢያ (Prologue of Jhon) መግቢያ በመጽሐፍ ሕየሳ (biblical criticism) ላዕላይ (Higher criticism) እና ታህታይ (Lower criticism) ተብለው ይከፈላሉ በታህታይ ጽሑፋዊ ሕያሴ (Textual Criticism) እናገኛለን በዚህ ዘርፍ እንደ ወንድም ሳላህ ኡስታዝ ቃል አሚን ስራቸውን አላህ ይቀበላቸው ብሎም የበለጠ የምንጠቀም ያድርገን እና ዘርፉን ቃርመውታል ብለን ማለት እንችላለን ። ዛሬ አዲስ በር ልክፈት እና በላዕላይ ሕየሳ ካሉ ዘርፎች ምንባባዊ ህየሳ (Literary criticism) አንዱን የጥናት መስክ ነው የሚያተኩረው የጽሁፉን አወቃቀር ትረካዊ ገለጻ ይዘት የአመለካከት ነጥብ ላይ ያጠነጥናል በሰፊው ትኩረት ሰጥተን አላህ ከረዳን የምናየው ይሆናል ኢንሻአላህ ። ወደ ዛሬው ርዕስ እናምራ ... የዩሐንስ ወንጌል መግቢያ (ዩሀ 1:1-18) ብዙን ጊዜ .. ልል አስቤ ኧረ ሁሌም ክርስትያኖች ኢየሱስ አምላክ መሆኑን አሳዩን ሲባሉ በመጀመሪያው ቃል ነበረ ... የሚለውን ጥቅስ በፍቅር ይሰብካሉ ! እናስ ይሄ ክፍል በዮሐንስ ወንጌል ላይ የተጨመረ ነው ቢባሉ .. ይቅር በሉኝ ወለም ብሎኝ ነው ብንባል ምን ይመስላቹሐል ... በታህታይ የመጽሐፍ ሕየሳ የጽሑፍ ህየሳ በእደ ክታባት ተጠብቆ ለመኖሩ አያጣራጥርም በደንገል66 ደንገል75 በብራና አሌፍ ... መገኘቱ እርግጥ ነው ተዐማኚም ነው ። ታድያስ እንዴት ተጨመረ ብለህ ትሞግታለህ ነገሩ እንዲህ ነው የዮሐንስ መግቢያ 1:1-18 እንዲሁ ላነበበ ከተቀረው የወንጌሉ ክፍል የአጻጻፍ ስልቱ ወጣ ያለ ሆኖ እናገኛዋለን በዚህም የተነሳ ሙሁራን በቀድሞው የወንጌሉ ክፍል ያልነበረ በኋላ ቆይቶ ከዋናው በኩረ ጽሁፍ በጻህፍት የተጨመረ መሆኑን ምሁራን አበክረው ይናገራሉ ። የስነ መለኮት እንዲሁም የአዲስ ኪዳን ሙሑር ሩዶልፍ ቦልትመን የዮሐንስ ወንጌል መግቢያ ከሙሉ ወንጌሉ ለየት ያለ ትምህርን የያዘ ለዚህም ኢየሱስ ሎጎስ (ቃል) ተብሎ መወሳቱ በዚሁ በወንጌሉ መግቢያ እንጂ ሌላ ቦታ አለመኖሩ ብሎም “ቅድመ ክርስትና” ኖስቲካዊ መዝሙር ከግሪክ አፈታሪክ የተወረሰ ሳይሆን እንዳልቀረ እና ወንጌላዊያኑ ጻህፍት በወንጌል ውስጥ ከጨመሩዋቸው ቀደምት ሥነ-መለኮታዊ ወጎች እንደሆነ ተከራክሯል። ¹ የአዲሱ የመጽሐፍ ቅዱስ መደበኛ እትም በዮሐንስ ወንጌል መግቢያ ላይ እንዲሁ በወንጌሉ ከግሪክ አፈታሪክ ኑፋቄ የሆኑ ትምህርቶች እንዳለበት ማመኑ ልብ ይለዋል ። ሬመንድ ብራውን በመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያው ይህኑን አስረግጦ ይገልጻል በመጀመሪያው መጽሐፉን በማዳራጀት ላይ ባለው (Readactor) አካል የተጨመረ እና ከቅድመ ክርስትና እሳቤዎች የተቀዳ የሆነ እና ከዋናው ወንጌላዊ ጽህፈት የተለየ በመሆኑ የርሱ ለማስለሰል የመጥምቁ ዮሐንስ ታሪክ እንደተጨረበት በአንከር የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያ በተሰኘው ትልቅ እውቅና ካለው መጽሐፉ አኑሯል ² ። ሌሎችም ሙሑራን ልክ እንደ ጄምስ ዲ. ጂ.³ እና ዶድ ⁴ ይሄንኑ ያሰፍራሉ ። ማጠቃልያ የዮሐንስ ወንጌል መግቢያ በመጽሐፉ ሊህቃን እና በዘርፉ ጠበብቶች ጥያቄን የያዘ እና የዮሐንስ ወንጌል አካል እንዳልሆነ የሚታመን መሆኑ የተረጋገጠ የታመነ ነው እንደ ቅድ መነሻ የ ፕሮፌሰር ባርት ሙግት ከ ዋለስ ጋር ላይ በመነሳት እንዲሁም ከፕሮፌሰሩ ፖድካስት በመነሳት ለጥናት ተነሳስሼት የተጻፈ ነው ብዙ በመጽሐፉ ላይ የተጨመሩ ትምህርቶች ኖረው ትዮሎጂው ላይ ችግር አያመጣም ለምትሉ ክርስቲያኖች ... እውነት በሉ እስኪ.. ✍️ ወንድም student 1 The Gospel of John: A Commentary Rudolf Bultmann page 13-28 2 Gospel According to John (Anchor Bible)Raymond E. Brown introduction 3 Christology in the Making James D. G. Dunn 4 The Interpretation of the Fourth Gospel C. H. Dodd

-✨ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ (العبادة في الهرج كهجرة إلي) «በችግር  በፈተና ወቅት የሚደረግ ዒባዳ ወደኔ እንደመሰደድ ነው!» [📙ሶሒሕ ሙስሊም 2948] በዚህ ፊትና በበዛበት ግዜ ፖለቲካውን ለፖለቲከኞት ትተን በሚጠቅመን ነገር ዒባዳ ላይ እንጠነክር እንበርታ በተለይ ያለንበት ወር ታላቅ ወር ነውና ዒባዳ ላይ እንበርታ አንዘናጋ ባረከላሁ ፊኩም
https://t.me/iwnetlehullu1

ሚስጢር ሹክ ልበላቹህ 🌸 لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الْحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْ
ሚስጢር ሹክ ልበላቹህ 🌸 لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الْحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ ✨ ላኢሏሐኢለሏሁ ዋህደሁ ላሸሪከ ለህ ለሑል ሙልክ ወለሑል ሐምድ ወሑወ አላ ኩሊ ሸይዒን ቀዲር ከአሏህ በቀር በሐቅ ሊመለክ የተገባው የለም ብቸውን ያለ አንዳችን ተጋሪ ሥልጣን ሁሉ ለርሱ ነው ምስጋናም ሁሉ ለርሱ ይገባል እርሱ በሁሉ ነገር ላይ ቻይ ነው ✨ ይህን ዚክር በቀን 100 ጊዜ ያለ 🌴10 በባርነት የተያዙ ሰዎችን ነጻ እንዳወጣ 🌴100 ምንዳ 🌴100 ሐጥያት 🌴እንዲሁም ከሰይጣን ጉትጎታ ቀኑን ይጠበቃል ይህን ካለ ሰውም የተሻለ የሰራ በቂያማ ቀን የለም ከርሱ በላይ ያለ ቢሆን እንጂ💐 በርቱ ተበራቱ ረመዳን የእዝነት የምህረት ወር 🌙

رمضان مبارك 🌙 أسأل الله أن يتقبل منا ومنكم الصيام والقيام. وإن كان بدر مني تقصير أو خطأ، فإني أستغفر الله وأطلب منكم العفو والسماح.

photo content

➤➤መልዕክት ለሙስሊሞች በተለይ ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች➤➤ በገና እና  በመሳሰሉት የከሀዲያን በዓላት ላይ የሚዘጋጀውን ልዩ የካፌ ምግብ መብላትን በተመለከተ: 1: እንደ አጠቃላይ በነርሱ በዓል የተዘጋጀን ምግብ መብላት አይቻልም። ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎች ያዘጋጁት ምግብ ክልክል ስለሆነ ሳይሆን የተዘጋጀው ምግብ በዓሉን አስመልክቶ የተዘጋጀ  ስለሆነ አይፈቀድም። ክልክል ነው። ከበዓል ውጭ ባለግዜ ግን ከላይ እንደተጠቀሰው ሀላል የሆነ ምግብ እስከሆነ ድረስ መብላት የተፈቀደ ነው። 2: ነገር ግን ካፌ ተጠቃሚ የሆናችሁ ሁሉ ማድረግ ያለባችሁ ነገር: የተለያዩ አማራጮች ካላችሁ አትብሉ። ለምሳሌ: ውጭ ላይ ቤተሰብና ዘመድ ካላችሁ ከነርሱ ዘንድ በመሄድ አሳልፉ፣። ውጭ ላይ ገዝታችሁ መጠቀም የምትችሉ ከሆነም አትብሉ። እነዚህና መሰል አማራጮች ከሌሏችሁ ግን፣ አላህ ከምንችለው በላይ አስገዳጅ ያልሆነ ውስጥ አዋቂ አምላክ ነውና ካፌ ብትጠቀሙ ችግር የለውም። " ክርስቲያን ወገኖችንም ሆነ የካፌ ሰራተኞችን ፣ << እንኳን አደረሳችሁ! >> ማለት አይቻልም። " እንኳን አደረሳችሁ!" ሲሉንም መመለስ የለብንም። የካፌ ምግቡን በተመለከተ ሸይኽ ባሲጢይን አላህ ይዘንላቸውና በህይዎት ሳሉ እኛ የግቢ ተማሪ በነበርን ጊዜ ጠይቀናቸው ይህ ይዘት ያለው መልስ ነበር የመለሱልን። በተረፈ አላህ ይበልጥ አዋቂ ነው! Ⓒ
https://t.me/iwnetlehullu1

አምላካችን አላህ በተከበረው ቃሉ ሱረቱል ኢብራሒም አንቀፅ 24-26 የአማኝና የከሐዲዎችን ምሳሌ እንዲህ ያስቀምጣል፦ 🔼ስለ አማኞች! አማኞች ማለት መልካም ፍሬ ባላት ዛፍ ሲመሰሉ፤ ይህች ዛፍ ስርዋ ወደ መሬት በደንብ የሠደደ እና መሰረትዋ የማይናወጥ ሲሆን ቅርንጫፎችዋም ከመርዘማቸው የተነሳ ሠማይ የሚደርሱ ናቸው። ፍሬዋም በአላህ ፍቃድ ያለማቋረጥ ቀንም ሌሊትም ለተመጋቢ ዝግጁ ሲሆን ማፍራቷን አታቆምም። ይህም የተባረከ፣ የሚያምር፣ ጤነኛ፣ ንፁህና ጠቃሚ ፍሬ ነው። ይሕች ውብ ዛፍ የአማኞትምሳሌ ናት። Ibrahim 14:24-25 (24) أَلَمۡ تَرَ كَيۡفَ ضَرَبَ ٱللَّهُ مَثَلࣰا كَلِمَةࣰ طَيِّبَةࣰ كَشَجَرَةࣲ طَيِّبَةٍ أَصۡلُهَا ثَابِتࣱ وَفَرۡعُهَا فِي ٱلسَّمَآءِ (25) تُؤۡتِيٓ أُكُلَهَا كُلَّ حِينِۭ بِإِذۡنِ رَبِّهَاۗ وَيَضۡرِبُ ٱللَّهُ ٱلۡأَمۡثَالَ لِلنَّاسِ لَعَلَّهُمۡ يَتَذَكَّرُونَ (24) አላህ መልካምን ቃል ሥርዋ (በምድር ውስጥ) የተደላደለች ቅርንጫፍዋም ወደ ሰማይ (የረዘመች) እንደሆነች መልካም ዛፍ አድርጎ ምሳሌን እንዴት እንደገለጸ አላየኽምን (25) ምግቧን (ፍሬዋን) በጌታዋ ፈቃድ በየጊዜው ትሰጣለች፡፡ አላህም ለሰዎች ይገሰጹ ዘንድ ምሳሌዎችን ይገልጻል፡፡ 🔽በሌላ በኩል ስለ ከሐዲዎች! ጌታችን አላህ ከላይ ካለው ገለፃ በኋላ በተቃራኒው ስለ ከሐዲዎች በሚገርም ሁኔታ እንዲህ ገልፆልናል። Ibrahim 14:26 وَمَثَلُ كَلِمَةٍ خَبِيثَةٖ كَشَجَرَةٍ خَبِيثَةٍ ٱجۡتُثَّتۡ مِن فَوۡقِ ٱلۡأَرۡضِ مَا لَهَا مِن قَرَارٖ የመጥፎም ቃል ምሳሌ ከምድር በላይ የተጎለሰሰች ለእርሷ ምንም መደላደል የሌላት እንደኾነች መጥፎ ዛፍ ነው፡፡ ይህቺ መጥፎ ዛፍ ናት! ከታች ምንም አይነት ስር ወይም መሠረት የላትም፣ ፍሬዎችዋም በጣም መራራ የሆኑ፣ የተጎለሰሰችና 'basement' የሌላት ዛፍ ናት። ይህቺም የከሐዲዎች ምሳሌ ናት! ሱብሐን አላህ! ለሚያስተነትኑ ምን ያማረ ምሳሌ ነው!

ክርስትና አስተምህሮ በጥቅሉ .... አንድ አምላክ እግዚአብሔር ራሱን ሰዋ ለእግዚአብሔር፣ ከእግዚአብሔር ፍጡራኑን ይድኑ ዘንድ ። እግዚአብሔር ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ እንዲያድነው ! ግን እግዚአብሔር እግዚአብሔርን አላደነውም። በሰዎች ትብብር እግዚአብሔር እግዚአብሔርን ገደለ። እግዚአብሔር የእራሱ አባት በተመሳሳይ የራሱም ልጅ ነው ። እርሱ ዘለላማዊ ሆኖ ሳለ ግን (ገና) የተባለ የልደት በዐል ይከበርለታል እርሱም ሰው ለሆነው አብርሀም የዘር ግንድ ነው።  እርሱ እራሱን ወደ ምድር ልኮ ሰው ልጆች ጋር አብሮ በመኖር የሰው ልጆች እንዲገሉት ጫና በማድረግ ተገድሏል። ምክንያቱም ይህ ያለው ብቸኛ አማራጭ ነበረ የሰው ልጆችን በአንዲት ከ6000 አመት በፊት የኖረችን ሴት(ሔዋንን) ለሀጢያቷ ምህረትን ያደርግላት ዘንድ !

በሠሞንኛው የሐጂ ዑመር ገነቴ ህልፈት ትንሽ የማያስማማና አለመግባባት ቢኖርም የአንዳንድ ቡድኖች በዚሁ አጋጣሚ ጭንብላቸው ተገልጦ ትክክለኛ ፊታቸውን ያሳየ ሆኗል። በእርግጥ ክርስትያን ወገኖች በሙስሊሞችና በኢስላም ሀይማኖት ዙሪያ እውቀቱም ሆነ መብቱም ስለሌላችሁ ቅቤ አንጓች መሆን አያስፈልግም፤ ብዙ ማታውቁትና ያልገባችሁ ነገር ስላለ ጡልቅ ጡልቅ ማለቱ አይበጅምና አድቡ። እንዲሁ በእንዲሁ እንዳለ ሙስሊም ነኝ የሚለው ሙሽሪኩ አካል ገና ካሁኑ የገሃነም ጓዱን ከወሐብያ እገሌ ይሻለኛል በማለት ወዳጅነቱን አጠናክሯል። እንግዲህ እኛም ዘመድ ከዘመዱ አህያ ካመዱ እንዲሉ ስትቀሰቀሱ አላህ አብሮ ይቀስቅሳችሁ ከሞት በኋላም አይለያችሁ ብለናል። 🙌

●ቤትና መስጂዶችን ለቀብር አገልግሎት ማዋል ✨ውዱ ነቢያችን ﷺ እንዲህ ይላሉ ﴿ألا وَإِنَّ مَنْ كَانَ قَبْلَكُمْ كَانُوا يَتَّخِذُونَ مِنْ قُبُورِ أَنْبِي
+1
ቤትና መስጂዶችን ለቀብር አገልግሎት ማዋል ✨ውዱ ነቢያችን እንዲህ ይላሉ ﴿ألا وَإِنَّ مَنْ كَانَ قَبْلَكُمْ كَانُوا يَتَّخِذُونَ مِنْ قُبُورِ أَنْبِيَائِهِمْ مَسَاجِدَ أَلا فَلَا تَتَّخِذُوا القُبُورَ مَسَاجِدَ فَإِنِّي أَنْهَاكُمْ عَنْ ذَلِكَ﴾ “አዋጅ! ከናንተ በፊት የነበሩ ህዝቦች የነቢያቶቻቸውን መካነ መቃብሮች መስጊድ አድርገው ይይዙ ነበር፡፡ እኔ ደግሞ የቀብር ቦታዎችን መስጊድ አድርጋችሁ እንዳትይዙ በጥብቅ እከለክላችኋለሁኝ፡፡” [📙ሙስሊም ዘግበውታል፡ ሐዲስ 532] ✨በሌላ ሐዲሳቸው ነቢያችን እንዲህ ይላሉ لا تجعلوا بيوتكم مقابر «ቤታችሁን መቃብር አታድርጉ።» [📓ሙስሊም ዘግበውታል ሐዲስ 780] https://t.me/iwnetlehullu1

"እሰልምልሻለሁ" ብሎ አግብቶ ካስወለዳት በኋላ ወይም ክርስትናን ተቀበይ አለበለዚያ ልጄን ትተሽ ጥርግ ማለት ትችያለሽ ይላታል። እርሷም የዓይን ማረፊያ ልጇን እና የሞቀ ትዳሯን ትታ መሄድ ይከብዳትና
"እሰልምልሻለሁ" ብሎ አግብቶ ካስወለዳት በኋላ ወይም ክርስትናን ተቀበይ አለበለዚያ ልጄን ትተሽ ጥርግ ማለት ትችያለሽ ይላታል። እርሷም የዓይን ማረፊያ ልጇን እና የሞቀ ትዳሯን ትታ መሄድ ይከብዳትና ፍጡር እያመለከች ፍጡር ማምለኳ ስህተት እንደሆነም እያወቀች ወደ እሳት ትጓዛለች💔 ወደዚህ ጣጣ ውስጥ ከመግባቷ በፊት መጀመሪያ ከካሐዲ ወንድ መራቅ ነበረባት! ይህ ጉዳይ በብዙ እኅቶቻችን ላይ እየሆነ ያለ ጉዳይ ነው። وَلَن تَرْضَىٰ عَنكَ الْيَهُودُ وَلَا النَّصَارَىٰ حَتَّىٰ تَتَّبِعَ مِلَّتَهُمْ ۗ قُلْ إِنَّ هُدَى اللَّهِ هُوَ الْهُدَىٰ ۗ وَلَئِنِ اتَّبَعْتَ أَهْوَاءَهُم بَعْدَ الَّذِي جَاءَكَ مِنَ الْعِلْمِ ۙ مَا لَكَ مِنَ اللَّهِ مِن وَلِيٍّ وَلَا نَصِيرٍ [ አል-በቀራህ - 120 ] አይሁዶችና ክርስቲያኖችም ሃይማኖታቸውን እስከምትከተል ድረስ ካንተ ፈጽሞ አይወዱም፡፡ «የአላህ መምራት (ትክክለኛው) መምራት እርሱ ብቻ ነው» በላቸው፡፡ ከዚያም እውቀቱ ከመጣልህ በኋላ ዝንባሌያቸውን ብትከተል ለአንተ ከአላህ (የሚከለክልልህ) ዘመድና ረዳት ምንም የለህም፡፡ ✍ ሙከሚል ሙሥሊም ልጅ። https://t.me/mukamil12

"እሰልምልሻለሁ" ብሎ አግብቶ ካስወለዳት በኋላ ወይም ክርስትናን ተቀበይ አለበለዚያ ልጄን ትተሽ ጥርግ ማለት ትችያለሽ ይላታል። እርሷም የዓይን ማረፊያ ልጇን እና የሞቀ ትዳሯን ትታ መሄድ ይከብዳትና
"እሰልምልሻለሁ" ብሎ አግብቶ ካስወለዳት በኋላ ወይም ክርስትናን ተቀበይ አለበለዚያ ልጄን ትተሽ ጥርግ ማለት ትችያለሽ ይላታል። እርሷም የዓይን ማረፊያ ልጇን እና የሞቀ ትዳሯን ትታ መሄድ ይከብዳትና ፍጡር እያመለከች ፍጡር ማምለኳ ስህተት እንደሆነም እያወቀች ወደ እሳት ትጓዛለች💔 ወደዚህ ጣጣ ውስጥ ከመግባቷ በፊት መጀመሪያ ከካሐዲ ወንድ መራቅ ነበረባት! ይህ ጉዳይ በብዙ እኅቶቻችን ላይ እየሆነ ያለ ጉዳይ ነው። وَلَن تَرْضَىٰ عَنكَ الْيَهُودُ وَلَا النَّصَارَىٰ حَتَّىٰ تَتَّبِعَ مِلَّتَهُمْ ۗ قُلْ إِنَّ هُدَى اللَّهِ هُوَ الْهُدَىٰ ۗ وَلَئِنِ اتَّبَعْتَ أَهْوَاءَهُم بَعْدَ الَّذِي جَاءَكَ مِنَ الْعِلْمِ ۙ مَا لَكَ مِنَ اللَّهِ مِن وَلِيٍّ وَلَا نَصِيرٍ [ አል-በቀራህ - 120 ] አይሁዶችና ክርስቲያኖችም ሃይማኖታቸውን እስከምትከተል ድረስ ካንተ ፈጽሞ አይወዱም፡፡ «የአላህ መምራት (ትክክለኛው) መምራት እርሱ ብቻ ነው» በላቸው፡፡ ከዚያም እውቀቱ ከመጣልህ በኋላ ዝንባሌያቸውን ብትከተል ለአንተ ከአላህ (የሚከለክልልህ) ዘመድና ረዳት ምንም የለህም፡፡ ✍ ሙከሚል ሙሥሊም ልጅ። https://t.me/mukamil12

Repost from N/a
የነብስ እና ስጋ(አካል) ምሳሌ ለትስጉት ከ ሥነ ህልዎት (ሜታፊዚክስ) አንጻር ያለው ቅራኔ ካረጁ ካፈጁ ምሳሌዎች መሀከል በክርስትያን ሥነ መለኮት ሊሀቃን ውስጥ ነው ትምህርተ ስጋዌን ለማሳመን ከሚሞግቱበት መሳሪያ ዋነኛ ነው ከነርሱ መሀል ጎርጎሪዮስ ዘኑሲስ፣ ዮሀንስ ዘደማስቆ እንዲሁም ቶማስ አኩዋይነስ " ኢየሱስ የክልታዊ መለኮት እና ሰው ተዋህዶ ማንነት ነው ይሉናል" ልክ ቁስ አካል ያልሆነው ነብስ ቁስ አካል የሆነውን አካል(ሰውነት) እንደተዋሀደ እንዲሁ ኢየሱስ መለኮት + ስጋ(አካል) ውህድ ነው ። ይህቺ ፎርሙላ የኬልቄዶን ጉባኤን ("ሁለት ምንነት በአንድ ማንነት") ክልታዊ ነው ያለመነጣጠል ለማስረጽ ግብ ያደረገች ናት ። ነገር ግን ይህ አስተምህሮ ስናስተነትነው በሥነ ፍልስፍናው ይፈራርሳል በአመክንዮ ሲፈተሽ ይጋለጣል ቀደምት ከሚባሉ የግሩክ ኒዎ ፕሎቶኒክ እንዲሁም አርስቶትላዊ (አርስጣጣሊስ) ሜታፍዚካላዊ መነጸር ቦታ የለውም ። ነብስ እና ስጋ ለመለኮት እና ስጋ መዋሀድ የሚቀርበው ምሳሌ ሱህት ነው !። የመደብ ግልጽ አለመሆን (Category Confusion) የተፈጠረ ነገር ካልተፈጠረ ነገር በ አሪስጣጣሊስ ስለ ነገሮች ህልውና አወቃቀር ጥናት (Aristotle’s hylomorphic ontology) "ነብስ" የሰውነት አንዱ ውቅር ሁና ለሰዎች ህያው የመሆን የመንቀሳቀስ ችሎታ ይኖረው ዘንድ የምታደርግ ውቅር ናት፤ ይህ መጣመር በአንድ ህልውና ህያው ለመሆን እንደሚረዳ የታወቀ ነገር ነው ። መለኮት ከውቅርነት ከውህደት የጸዳ ነው (actus purus) (Metaphysics Λ, 1072a) መለከት እንደ ውቅር በመሆን አያገለግልም መዋሀድ በራሱ ወደ ውስንነት ስለሚያመራ መለኮት ደሞ በተቃራኒ ያልተወሰነ ቅድመ ሁኔታ የማይሻ ነው !። በፕሌቶ (Plotinus)" አንዱ እና ብቸኛው መለኮት ከነገሮች ጋር አይዋሀድም ምክንያቱም መዋሀዱ ከፍጡር መደብ ስለሚመድበው"(Enneads VI.9.3) ስለዚህ ነብስ እና አካል የሚለውን ምሳሌ መስጠት ለ ትምህርተ ሥጋዌ የመደብ ህጸጽ መስራት ነው (Catagory Error) ምክንያቱም ያልተፈጠረውን ጥገኛ ያልሆነው ምንነት ( መለኮት ) የተፈጠረ የአንድ ቁስ አካል መዋቅር አድርጎ መውሰድ ስህተት ነው ይህን ለማስረጽ ደሞ ምንም አይነት የግሪክ ፍልስናዊ አረዳድ አይፈቅደም !። መዋቅራዊ ስህተት : አንድ ባህሪ እና ክልታዊ ባህሪ በሰው ልጅ የነብስ እና የ አካል ስጋ (መዋቅር) ለ አንድ ባህሪ ውቅር ናቸው (ለሰውነት ምንነት) የሁለቱ ውቅር ለአንድ ነጠላ ማንነት ግብዐት ናቸዉ ። ነገር ግን በነገረ ክርስቶስ የኬልቄዶኑ ፎርሙላ ሁለቱ ባህሪያት በግልጽ የተለያዩ ናቸው ምንም ያህል በአንድ ማንነት (hypostasis) ተዋሀዱ ቢባልም ። ("ይህንን ለመፈተሽ መለኮት ስጋን ተዋህዷል ወይ በሏቸው ?" መልሱ ያለመነጣጠል ያለመበላለጥ "አዎ" ይሏችኋል በመስቀል ላይ መለኮት ሙቷል ወይ ስትሏቸው እራሳቸው አልተዋሀዱም ብለው መልሰው ምላሽ ይሰጣሉ) ምሳሌው ውድቅ ነው ከመዋቅራዊ አረዳዱ ምክንያት ( ግልጽ ለማድረግ ነብስ ተለይቶ ራሱን የቻ የተለየ ነገር አይደለም በሰው ልጅ "የሰው ልጅ አንድ መዋቅር ነው ነብስ ከስጋ ሲለይ ሞት ይባላል ነብስ ያለ ስጋ ስጋ ያለ ነብስ ማንነት የለም በተቃራኒ መለኮት ያለ ስጋ ስጋ ያለ መለኮት ለኢየሱስ ምሳሌው ይጣጣማልን? ) አኩዋይነስም ቢሆን ነካክቶት ምላሽ ሳይሰጥ ማለፉ ልብ ይለዋል " የነብስ እና የአካል መዋሀድ አንድ ባህሪ (ሰው) ነው: ግን የቃል እና የሰው መዋሀድ አንድ ባህሪን ብቻ አይሰጠንም አንድ ማንነት እንጂ " (Summa Theologica III q.2 a.5) አሉ ከሚባሉ የዚህ አስተምህሮ ዕቅብት እንኳ ምሳሌው የማይጣጣም እንደሆነ ይነግረናል መለዋወጥ በአርጌንስ ዘመን ከተነሱ ጥያቄዎች "አምላክ በስጋ ከመጣ እንግዲያውስ ዙፋኑን ትቶ ወደ ሰው ተቀይሯል" Origen, Contra Celsum I.27 መቀያየር እንዳየነው ለመለኮት የተገባ አይደለም የዘመናችን የስነ መለኮት ፍልስፍና አጥኚዎች በትምህርተ ስጋዌ የሥነ አመክንዮ መጻረር Logical Problem of the Incarnation (LPI) ይሉታል ይህ ምሳሌን እንዲህ ብለው ይሞግታሉ የትስጉት አመክንዮ ችግር (LPI) ቀላል ግን ጥልቅ ጥያቄ ይጠይቃል፡- አንድ ሰው (ኢየሱስ) እንዴት ሁለት ባሕርይ ሊኖረው ይችላል - አንዱ መለኮት እና አንዱ ሰው - እነዚያ ሁለቱ ባሕርያት የሚጻረሩ ሁነው? ለምሳሌ፡- መለኮታዊ ባህሪይ (ተፈጥሮ) ሁሉን አዋቂ ነው (ሁሉን ያውቃል)። የሰው ተፈጥሮ በእውቀት የተገደበ ነው (ሁሉንም ነገር አያውቅም)። መለኮታዊ ተፈጥሮ የማይደክም የሚያይታመም  ነው  የሰው ልጅ ተፈጥሮ ይህን ሊተላለፍ የሚችል ነው (ሊሰቃይ, ሊያድግ, ሊለወጥ ይችላል)። ኢየሱስ በእውነት ሁለቱም ካለው፣ ሁሉንም ነገር የሚያውቅ እና ሁሉንም ነገር የማያውቅ፣ ሊሰቃይ የማይችል እና ሊሰቃይ የሚችል ነው ይህ ደሞ (LOGICAL CONTRADICTION) የሥነ አመክንዮ መጻረር ነው። ክርስቲያን ሊቃውንት ታድያ እነዚህ ተቃራኒ ባሕርያት የኢየሱስ ናቸው - እርሱ እንደ አምላክ ሁሉን አዋቂ እና እንደ ሰው የተገደበ ነው። ይህ “qua” (እንደ) ትስስር ይባላል - ኢየሱስ qua God (እንደ አምላክ) ወይም qua man (እንደ ሰው) ብለው ይናገራሉ። ግን የኢየሱስን መለኮት ከ ሰዋዊነቱ ጋር ምን ያገናኘዋል ሰውነቱ ሲደክም መለኮቱ ይደክማል ? ካልደከመ ምኑን ተዋህዶ እውን ሆነ ? J. R. Sijuwade argues in “The Logical Problem of the Incarnation” (Religious Studies, Cambridge) "No known model of composition or substance dualism solves this without either compromising divine simplicity or fragmenting personal unity." ምንም አይነት ምሳሌ ለትስጉት ትምህርት  አይቀርብለትም ! ሁለት የተጻረሩ ምንነቶችን በአንድ ማንነት ማዋሐድ ሥነ አመክንዮ ሊፈታው የማይችል መጣረስ መፋለስ መጋጨት መላተም ነው ። "መንፈስ ቅዱስ ካልገለጠልህ" ...የሚሏት ነገር ቀላል ማምለጫ አድርጋችሁታል "ያውቋታል" ! ✍️𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸

ክፍል ሁለት መለኮት ጥገኛ ያልሆነ በራሱ ቋሚ፣ ዘላለማዊ፣ የማይለወጥ እኒህ ባህሪያት Necessary (የግድ) መለኮትን ገላጭ እንጂ አማራጭ ባህሪያት አይደሉም መለኮትን ጠቋሚ ናቸው لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡ -- ቁርዐን 112:3 “ተራሮች ሳይወለዱ፥ ምድርም ዓለምም ሳይሠሩ፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ አንተ ነህ።”   — መዝሙር 90፥2 ውስን የሚለወጥ ጥገኛ የሚሆን አካል መቼም መለኮት አይሆንም አይደለም ! መለኮት ጅማሮ የለውም ማብቂያም ። ኢየሱስ ተወለደ፣ አደገ፣ ሞተ፣ በሚል ኡደት ታጥሯል (ሉቃ 2:7; 23:46) Omniscience (ሁሉን አዋቂነት )ፈጣሪ ሁሉን አዋቂ ሆኖ ሳለ ኢየሱስ አላዋቂ ነው (ማር 13:32) በራሱ ቋሚ ራሱን ቻይ በምንም ነገር ላይ ጥገኛ አይሆንም፤ ኢየሱስ ደሞ በምግብ በእረፍት በመጠለያ ላይ ጥገኛ ነበረ ። በተመሳሳይ ሰዐት ራሱን ቻይ ኑባሬ እንዲሁ ጥገኛ መሆን አይችልም የሚማር ምንነት ሁሉን አዋቂ አይደለም እድሜ የሚቆጠርለት አካል ዘላለማዊ አይሆንም አመክንያዊ (logical) አይደለም። የሥነ አመክንዮ የተጻራሪነት ህግ  ክርስቲያኖች ሁሌም ኢየሱስ ሁለት ምንነት አለው ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው በአንድ ማንነት ላይ ተዋሀደ ብለው ይሞግታሉ መጽሐፍ ቅዱሳዊነቱ እናቆየውና (የሚባል ነገር ስለሌለ)... ከሥነ አመክንዮ(Logic) አንጻር ሲፈተሽ ይህ አስተምህሮ እርስ በርሱ የሚጻረር ሆኖ እናገኘዋለን ምክንያቱም ሁለቱ ምንነቶች በራሳቸው የሚቃረኑ ናቸውና [ፍጡር ወ ፈጣሪ] ! የሥነ አመክንዮ ተጻራሪነት ህግ  በሥነ አመክንዮ አንድ አባባል የሚያጸድቅ ሆኖ በተመሳሳይ ሰዐት አፍራሽ ሊሆን አይችልም ! ለምሳሌ አንድ ኑባሬ ያልተወነ ነው ብለን በተመሳሳይ ሰዐት ውስን ነው በተመሳሳይ ሰዐት አላዋቂ ነው ብለን እንደገና አዋቂ መሆን አይችልም ኢየሱስ በተመሳሳይ ሰዐት አዋቂ እና አላዋቂ ከሆነ ሁለት ሥነ አመክንያዊ ድምዳሜ ይኖረናል ! 1, መለኮታዊ ምንነቱ ሰዋዊ ምንነቱ በላይ ነው ያ ማለት ፍጹም ሰዉ አይደለም (ንስጥሮሳዊነት) 2, ወይም ፍጹም ሰውነቱ መለኮታዊ ማንነቱን ውስን ያደርገዋል ያ ደሞ ፍጡር እንጂ ፈጣሪ አያደርገውም ስለማይታወቅ ሁለቱም የክልታዊነት ኑባሬ እይታወች ከተጻራሪነት የሚድኑ የዳኑ አይደሉም ተጸራሪ ናቸው ጥገኝነት ወደ መላምትነት ያመራል ጥገኝነት የሰው ልጅ መለዮ ነው ኢየሱስ የሚበላ የሚያርፍ የሚተኛ የሚጸልይ የሚቸገር የሚታመመም የሚጎዳ ከሆነ እኒህ የምርጫ ጉዳይ አይደሉም ማለትም እኛ የምንበላው የምተኛው ... መርጠን ሳይሆን በህይወት እንድንቆይ ዘንድ ግዴታ ስለሚሆንብን ነው ! የሌላ ነገር መኖር ለርሱ መኖር የግድ ከሆነ ያ አካል መለኮት አይደለም መለኮት በራሱ ላይ እንጂ በሌላ ጥገኛ ያልሆነ ነው ! ኢየሱስ ጥገኛ ሆኖ አምላክ ሊሆን ይችላል እውነታው ሳይሆን መላምት ነው ! አምላክ ሰው ሆነ = "አምላክ ጥገኛ ሆነ" ያኔ ከመለኮትነት ያ ምንነት ውጪ ይሆናል !። “እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።”   — መዝሙር 121፥4 وَمَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ ۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا الظَّنَّ ۖ وَإِنَّ الظَّنَّ لَا يُغْنِي مِنَ الْحَقِّ شَيْئًا ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡ ቁርዐን 53:28 የክልታዊ ኑባሬ ውዥንብር የክርስትና ሥነ መለኮት ሊህቃን ቶማስ አኩዋይነስ እንዲሁም አትናትዮስ ኢየሱስ "የሁለት ምንነት ጣምራ ማንነት" ያለመጻረር ነው ይሉናል ነገር ግን የኢየሱስ ማሰብ መናገር መተኛት በማንነተችን የምንተገብረው እንጂ በሚስጥራዊ ክልታዊ  ምንነት የሚከወን አይደለም ! ኢየሱስ የሚባለው ማንነት ከተረባ ከፈራ አላዋቂ ከሆነ መለኮት ያን ማንነት አልተዋሐደውም ማለት ነው ! ። ተዋሀዶ ይህ አረዳድ ክርስቲያኖችን ወይ ኑፋቄ (ንስጥሮሳዊ) ያደርጋቸዋል ወይ ከአይምሮቸው ጋር እንዲጋጩ ይዳርጋቸዋል * ንስጥሮስ መለኮታዊው ማንነት ከ ሰዋዊ ማንነት የገዘፈ ነው (ማር ባህር እደመክተት ያህል ነው በውስጡ እንደሚሟው) ብሎ ያምን ነበረ ይህ እምነቱ በኬልቄዶን ጉባኤ ውግዝ ሆኖ አርም ተብሏል ይህን ያለበት ምክንያት ፍጹም ሰው ፍጹም መለኮት ተዋሀደ ከሚለው ቅዠት አይምሮውን ለማዳን የጣረ መሆኑን ልብ ይለዋል .... በጥልቀት ይቀጥላል

ክፍል 1፦ ማ     ሟ    ሻ መለኮት እና ሰብዐዊነት ይህ መጣጥፍ ትምህርተ ስጋዌ ላይ ሒስ ይሰጣል። በመለኮት እና በሰውነት መካከል ያለውን ልዩነት በመግለጥ አስተምህሮ አምላክ ሰው ሆነ የሚለውን እምነት ከፍልስፍና፣ ከሥነ መለኮት አንጻር ይመረምራል። የመለኮት አስፈላጊ እና ገላጭ ባህሪያት (እንደ ዘላለማዊነት፣ ሁሉን አዋቂነት እና ራስን መቻል) ከሰው ልጅ ገላጭ ባህሪ (እንደ ልደት፣ እድገት፣ ድንቁርና እና ሟችነት) የማይታረቁ ናቸው ሲል ይሞግታል።ቁርኣናዊውን እና መጽሐፍ ቅዱሳዊውን የሰው ልጅ ተፈጥሮን በማነፃፀር፣ “እግዚአብሔር ሰው ሆነ” የሚለው አባባል ከመለኮታዊ ፍጽምና ጋር የማይጣጣም ብቻ ሳይሆን ምክንያታዊም ራሱን የሚቃረን መሆኑን ያሳያል።ድምዳሜው ዒሳ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ነብይ እና መልእክተኛ ነበር - በአላህ ከፍ ከፍ ያለ ቢሆንም ከሰውነት ሌላ ኑባሬ የለውም። لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ (42:11) ይህ ርዕስ ሥነ መለኮታዊ ብቻ ሳይሆን ሥነ አመክንዮዊ መረዳት ፍልስፍናዊ ትንታኔን የሚሻም ጉዳይ ነው ፦ የማይወሰነው ፣ ዘላለማዊ እና ሁሉን አዋቂ የሆነ መለኮታዊ ኑባሬ ውሱን፣ ጊዜያዊ እና አላዋቂ  በተመሳሳይ ጊዜ እንዴት ሊሆን ይችላል ? ሰብአዊነት በውስንነት፣ ጥገኝነት እና የመለወጥ ባህሪያት የሚገለጽ ነው ይህ ባህሪ በጊዜ ያልተቀየረ በሰው ልጅ አኗኗር ቢሂል የሚታይ እና እሙን ቅቡል የሆነ ሀቅ ነው ! وَاللَّهُ أَخْرَجَكُم مِّن بُطُونِ أُمَّهَاتِكُمْ لَا تَعْلَمُونَ شَيْئًا وَجَعَلَ لَكُمُ السَّمْعَ وَالْأَبْصَارَ وَالْأَفْئِدَةَ ۙ لَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ አላህም ከእናቶቻችሁ ሆዶች ምንም የማታውቁ ሆናችሁ አወጣችሁ፡፡ ታመሰግኑም ዘንድ ለእናንተ መስሚያን ማያዎችንም ልቦችንም አደረገላችሁ ቁርዐን 16:78 ጥገኝነት ልደት፣ ማደግ፣ መድከም፣ መታመም፣ መሞት ይህ ኡደት ሰው ሁሉ ያለ የሚሰለጥን ነው። አየር፣ መብልና ረፍት ላይ ጥገኛ ነን ይህ ሁናቴ ፍጡርነታችንን እንዲሁም መወሰናችንን ይገልጣል ። ኢየሱስ ተርቧል (ማቲ 4:2) ተጠምቷል (ዮሀ 19:28) ደክሞታል (ዮሀ 4:6) ... እኒህ ፍጡርነትን ገላጭ ባህሪያት ናቸው። ለነገሮች ጥገኛ የሆነ ኑባሬ ለዐጽናፈ አለሙ መጠጊያ መሆን አይችልም ። مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ وَأُمُّهُ صِدِّيقَةٌ ۖ كَانَا يَأْكُلَانِ الطَّعَامَ ۗ انظُرْ كَيْفَ نُبَيِّنُ لَهُمُ الْآيَاتِ ثُمَّ انظُرْ أَنَّىٰ يُؤْفَكُونَ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ እናቱም በጣም እውነተኛ ናት፡፡ (ሁለቱም) ምግብን የሚበሉ ነበሩ፤ አንቀጾችን ለነርሱ (ለከሓዲዎች) እንዴት እንደምናብራራ ተመልከት ከዚያም (ከእውነት) እንዴት እንደሚመለሱ ተመልከት፡፡ ቁርዐን 5:75 መብላት፣ መተኛት፣ መቸገር .. የፈላጊነት መሻቶች የፍጡር መለዮ ሲሆን በራስ ቋሚ ፍጹም የተብቃቃ መሆን ለመለኮት ብቻ ነው ! اللَّهُ الصَّمَدُ አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው፡፡ ቁርዐን 112:2 ኢየሰስ ባህሪ የሚገልጠው ሰብአዊነቱን እንጂ መለኮት አደለም ! ተለዋዋጭነት ፍርሀት፣ ሐዘን፣ ጸጸት፣ አላዋቂነት .. እኒህ ሰዋዊ እንጂ መለኮታዊ ያልሆኑ መለዮ ናቸው። ኢየሱስ አዝኗል (ዮሀ 11:35) ፈርቷል ተጨንቋል (ሉቃ 22:44) አላዋቂ ነበር (ማር 13:32) ይህ መቀየር መለወጥ አመልካች ነው ! “እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም፤”   — ሚልክያስ 3፥6 የሞራልና መንፈሳዊ ሙሉዕነት መጎደል የሞራል መልካሙን ከክፉ የመለየት ብይን የመስጠት በራሳችን አቅም የሌለን መሆናችን አንዳንዴ መልካም አንዴ ወደ ክፋት ልናዘነብል ይዳርገናል ቁርዐን 91:7-8 وَنَفْسٍ وَمَا سَوَّاهَا በነፍስም ባስተካከላትም፤ فَأَلْهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقْوَاهَا አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡ አዲስ ኪዳን ኢየሱስ መፈተኑን አስረግጦ ይነግረናል ( ማቲ 4:1 ፤ ዕብ 4:15) መፈተን መቻል ማለት በራሱ ስህተት የመስራት ዕድል እንዳለ አመልካለች ነው ( ምሳሌ ካልኩሌተር መደመር ማባዛት.. ይችላል እንዴ ተብሎ ይፈተናል ...) እግዚአብሔር በክፉ አይፈተንም፤ እርሱም ማንንም አይፈትንም ያዕቆብ 1:13 ኢየሱስ አምላክ ነውም ተፈትኗል አምላክ በክፉ ተፈተነ እንደማለት ነው ያ ደሞ ፍጹም የማይሆን ነው! ✍️ 𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸

"አምላክ ሰው ሆነ" መለኮት እና ሰብአዊነት ለየቅል መሆን ከፍልስፍና እንዲሁም መለኮታዊ አስተምህሮት አንጻር ሲመዘን ! በቅርብ ቀን ! https://t.me/student_comparative ✍️ 𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸

➩ የነብዩ "ﷺ" ልጅ ኢብራሒም በሞተበት ቀን የጸሀይ ግርዶሽ ተከስቶ ነበር። ሰዎቹ ክስተቱን ከሳቸው ልጅ መሞት ጋር በማገናኘት የሀዘን ምልክት አድርገው ወስደውት ነበር። ኃላ ነብዩ ሙሐመድ "ﷺ" ሲ
የነብዩ "ﷺ" ልጅ ኢብራሒም በሞተበት ቀን የጸሀይ ግርዶሽ ተከስቶ ነበር። ሰዎቹ ክስተቱን ከሳቸው ልጅ መሞት ጋር በማገናኘት የሀዘን ምልክት አድርገው ወስደውት ነበር። ኃላ ነብዩ ሙሐመድ "ﷺ" ሲሰሙ ግን መሳሳታቸው ገልጸው ገሰጿቸው። ጸሀይና ጨረቃ የአሏህ ﷻ ተአምራት/ምልክቶች መሆናቸውን የጸሀይ ግርዶሽም በአንድ ሰው ሞትም ሆነ ህይወት ምክንያት የሚፈጠር እንዳልሆነ አብራርተው ስህተታቸውን አረሙ። ምንጭ [📙bukhari hadith 1060] ● አንድ ሀሰተኛ ነብይ ቢሆን መሠል ወርቃማ እድልን ፈጽሞ አያሳልፍም ነበር። ክስተቱን ተመርኩዞ አይደለም በተቃራኒው ሊናገር ይቅርና ሀሳቡን በማጠናከር "ተመልከቱ በልጄ መሞት ሰማይ እንዴት እንዳዘነ" በሚል ለዚህ ሀሳብ መጀመሪያውኑ የቀረቡ ሰዎችን በተሻለ ለማሳመን እድሉን ይጠቀምበት ነበር። ግን ለእውነተኛ ነብይ ከእውነት በላይ ማስረጃም ጉዳይም የለውምና ይህንን የሚያደርጉበት ምክንያት ስልነበራቸው ፈጽሞ አላደረጉትም፣ ማድረግም አይጠበቅባቸውም ነበር..! ሰላሏሁ ዐለይሂ ወሰለም" ✍የሕያ ኢብኑ ኑሕ https://t.me/Yahyanuhe