T Educational info 🌿🌿🌿🌿🌿
Відкрити в Telegram
1 338
Підписники
+224 години
-27 днів
+830 день
Архів дописів
Repost from Arada education office
ተመራቂዎች፦ በአሰላ እና በደብረ ብርሃን ኮሌጅ የተማሩት የቅድመ-1ኛ ደረጃ መምህራን ቅዳሜ ማለትም በ20/10/2018ዓ.ም ጠዋት በአደዋ 00 ግቢ ውስጥ የሚመረቁ መሆኑን እየገለፅን። ተመራቂዎች አርብ በ19/10/18 2:30 ሚኒሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተገኝታችሁ ኦረንቴሽን እና መግቢያ ካርድ እንድትወስዱ ጥሪ እናስተላልፋለን።
ማሳሰቢያ
ካርድ ሳይዙ ወደ አዳራሽ መግባት አይቻልም
የ2018 ዓ.ም ተማሪዎች የውጤት መግለጫ ካርድ(certificate) እንድትወስዱ ማሳወቅን ይመለከታል
የአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር ትምህርት ቢሮ በስሩ ለሚገኙ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ትምህርት ተቋማት ለሚገኙ ተማሪዎች ዓመታዊ የውጤትመግለጫ ካርድ በማሳተም የማሰራጨት ስራ እንደሚሰራ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የ2018 ዓ.ም የውጤት መግለጫ ( report card ) ስለመጣ ነገ ማክሰኞ በ16/10/18 ዓ.ም ሁሉም የመነግስት እና የግል ት/ቤቶች ቀራኒዮ መድሃኒ አለም ቁ-2 ት/ቤት መጥታችሁ እንድትወስዱ እያሳወቅን ስትመጡ ሞዴል እና የት/ቤቱ ህጋዊ ደብዳቤ ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን ፡፡
Repost from Information channel
አንድ ቀን ጠዋት መምህሩ አሮጌና አቧራ የለበሰ ፋኖስ ይዞ ቀስ ብሎ ወደ ክፍል ገባ።
ተማሪዎቹ ግራ ተጋብተው ይተያዩ ነበር።
“መምህር” አለ አንድ ተማሪ “ይህንን ድሮ ድሮ መብራት በሌለበት የገጠር አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች ለመብራትነት የሚጠቀሙበትን አሮጌ ነገር ለምን አመጣኸው?” ሲል ጠየቀ።
መምህሩ ፈገግ አለ።
ፋኖሱን ጠረጴዛው ላይ እያስቀመጠ
“ውድ ተማሪዎቼ”፣ ዛሬ ስለ ትምህርት ልነግራችሁ እፈልጋለሁ - ወደፊት የጥሩ ደመወዝ ተከፋይ ለመሆን የምትማሩት አይነት ሳይሆን ለህይወታችሁ ብርሃንን ሊያጎናፅፋችሁ ስለሚችል ትምህርት ነው የምነግራችሁ።” ብሎ ንግግሩን ጀመረ።
--------------------
"ከብዙ ዓመታት በፊት" ከአዲስ አበባ ብዙም በማይርቅ ትንሽ መንደር ውስጥ አብረው ያደጉ ሦስት ልጆች ነበሩ።
ሦስቱም ትምህርት ቤት ገብተው ይማሩ ነበር።
የመጀመሪያው ልጅ "ሥራ አግኝቼ ጥሩ ገቢ ማግኘት እንድችል ጠንክሬ እማራለሁ' ይል ነበር።
ሁለተኛው ልጅ ደግሞ ' የምማረው ሰዎች እንዲያከብሩኝ ነው' ይል ነበር።
ሦስተኛው ልጅ ደግሞ 'የምማረው ዓለምን ለመረዳት እና ለአካባቢዬ ብሎም ለአለም ለውጥ የበኩሌን አስተዋፅኦ ለማድረግ ነው' ይል ነበር።
ዓመታት አለፉ። ሶስቱም ትምህርታቸውን ጨርሰው በጥሩ ውጤት ተመረቁ።
የመጀመሪያው ልጅ ጥሩ ክፍያ ያለው ሥራ አገኘ። ነገር ግን ከአመታት የስራ ላይ ቆይታ በኋላ ባልታሰበ ሁኔታ ስራውን አጣ። ስራውን ሲያጣ በራስ መተማመንም አጣ። ህይወቱ ምስቅልቅል አለ።
ሁለተኛው ልጅ ሶስተኛ ድግሪውን (የዶክትሬት ድግሪውን) እስኪይዝ ድረስ በትምህርቱ ውጤታማ ስለነበርና የተለያዩ ሽልማቶችን በማግኘቱ እንዳሰበው ለጥቂት አመታት ያህል አክብሮትን እና ዝናን አገኘ። ነገር ግን በጊዜ ሂደት የተማረው ትምህርት ያስገኘለት ክብርና ዝና እየቀነሰና ሰዎች በተለያዩ ጉዳዮች ትችት እያበዙበት ሲመጡ ባዶነት እየተሰማው መጣ፣ ደስታውንም አጣ።
ሦስተኛው ልጅ ግን ቀድሞ እንዳሰበው ችግር ፈቺ ሆነ። ያደገበት መንደር ነዋሪዎች የተለያዩ ችግሮች ሲገጥማቸው መፍትሄዎችን እየፈለገ ማህበረሰቡን መርዳትን ዋና ስራው አደረገ። ግጭቶች ሲፈጠሩ በጥበብ ያሸማግላል። ልጆች በትምህርት ሲቸገሩ በፈቃደኝነት ያስተምርና የተለያዩ ስራዎችን ይሠራል።
ይህ ሶስተኛው ልጅ ምኞቱ ባለጸጋ መሆን አልነበረም። በጣም ታዋቂና ዝነኛ መሆን አልነበረም። ነገር ግን በጣም ጠቃሚ ሰው መሆን ቻለ። በህይወቱ በጣም ደስተኛ ሰው መሆን ቻለ ።"
------------
መምህሩ ንግግሩን ገታ አድርጎ ተማሪዎቹን ተመለከታቸው። ሁሉም ተመስጠው ያዳምጡት ነበር።
ንግግሩን በመቀጠል
“ትምህርት” አለ በለስላሳ ድምፅ፣ “ሥራ ተቀጣሪ ለመሆን የሚረዳ ትኬት አይደለም። የትምህርት ዋና አላማ የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት ነው።”
በሰሌዳው ላይ ሦስት ቃላትን ጻፈ፡-
ክህሎት/skill፣ ዝና/status፣ ጥበብ/wisdom
👉 “ክህሎት ሥራ ሊያስገኝልህ ይችላል።
👉 ዝና በሰዎች ዘንድ ትኩረትን እንድታገኝ ሊረዳህ ይችላል።
👉 ጥበብ ግን - የህይወት አቅጣጫን ይሰጥሃል።”
“አስቡት” መምህሩ ቀጠለ፣ “ትምህርት ሥራ ስለማጎኘት ብቻ ቢሆን ኖሮ ኢኮኖሚው ሲለወጥ፣ ቴክኖሎጂ የተለመዱ ሥራዎችን ሲተካ፣ የጡረታ ጊዜህ ሲመጣ የተማርከው ትምህርት፣ ያገኘኸው ድግሪ ምን ይሆናል?"
ፋኖሱን አነሳ።
“ይህ ፋኖስ በአንድ ወቅት አስፈላጊ ነበር። ዛሬ አምፖሎች አሉን። ግን ብርሃን ራሱ አሁንም አስፈላጊ ነው።”
“ሥራዎች ሊለወጡ ይችላሉ። ማዕረጎች ሊለወጡ ይችላሉ። ኢንዱስትሪዎች ሊነሱና ሊወድቁ ይችላሉ። የሰለጠነ አእምሮ፣ በስርአት የተገነባ ባህሪ እና የማወቅ/የመማር ጉጉት - እነዚህ ፈጽሞ ጊዜ አያልፍባቸውም።”
---
የትምህርት_እውነተኛው_ዓላማ
“ትምህርት ምን ማሰብ እንዳለባችሁ ሳይሆን እንዴት ማሰብ እንዳለባችሁ ያስተምራችኋል።
ትምህርት:-
👉 በፍጥነት የሚሰራጩ ሃሰተኛ መረጃዎችን አምኖ ከመቀበል ይልቅ ጠያቂ መሆን እንድትችሉ፣
👉 ግጭቶችን ከመፍጠር ይልቅ ግጭት ፈች እንድትሆኑ፣
👉 ሌሎችን በጭፍን ከመከተል ይልቅ የመርህ ሰው እንድትሆኑ ያደርጋችኋል።”
መምህሩ ንግግሩን ቀጠለ፦
“ኔልሰን ማንዴላ በአንድ ወቅት ‘ትምህርት ዓለምን ለመለወጥ ልትጠቀምበት የምትችለው በጣም ኃያል መሣሪያ ነው’ ብለዋል። ‘ሥራ ለማግኘት የሚረዳህ’ አላሉም። ‘ዓለምን ለመለወጥ’ አሉ እንጅ።”
ክፍሉ ጸጥ ብሏል።
የመጨረሻው_ጥያቄ
መምህሩ እያንዳንዱን ተማሪ በጥንቃቄ ተመለከተ።
“ውድ ተማሪዎቼ፣ ግባችሁ ጥሩ ገቢ ያለው ሥራ ለማግኘት ከሆነ፣ በተቀጠራችሁበት ቀን መማር ታቆማላችሁ።
ነገር ግን ግባችሁ የእድሜ ልክ እድገት ከሆነ፣ መማርን መቼም ቢሆን አታቆሙም - ከስኬት በኋላም ቢሆን።”
ፋኖሱን ለመጨረሻ ጊዜ አነሳ።
“ይህ ፋኖስ ብርሃን አይፈጥርም። ስራው ብርሃንን መሸከም ብቻ ነው።
ትምህርት የወደፊት ሕይወትን አይፈጥርም።
ህይወትን መሸከም እንድትችሉ ብቻ ያዘጋጃችኋል እንጅ።”
ፈገግ ብሎ ንግግሩን ቀጠለ።
“ስለዚህ ጥሩ ገቢ ያለው ስራ ለማግኘት ብቻ ሳይሆን እራሳችሁን ብሎም አለምን ለመረዳት፣ ማህበረሰብን ለማገልገል፣ ጥበብን የተላበሰ ሰው ለመሆን ተማሩ/አጥኑ።"
ከዚያም አንድ የመጨረሻ ጥያቄ ጠየቀ፡-
“ትምህርታችሁን ጨርሳችሁ ስትመረቁ፣ የተዘጋጀላችሁን ስራ የምትሠሩ ወይስ ነገሮች እንዲሰሩ ማድረግ የምትችሉ ሰው ትሆናላችሁ…?”
ደወሉ ተደወለ።
ነገር ግን ከተማሪዎቹ መካከል ማንም አልተንቀሳቀሰም።
ምክንያቱም በዚች ቀን፡-
ትምህርት ለሥራ ሳይሆን
ለሕይወት ራስን ማዘጋጀት እንደሆነ ተረድተዋል።
ይህ መልእክት ትውልዱን ያስተምራል ብላችሁ ካሰባችሁ #ሼር በማድረግ ለበርካቶች አድርሱት 🙏
✍ እንዳልካቸው አደም
በድጋሚ የተጋራ
+1
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል።
(ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞ በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል።
ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
በ2018 ዓ/ም አዲስ አበባ ከተማ የማስተማር ሙያ ስልጠና ያላጠናቀቁ መምህራን የደረጃ እድገት ጥያቄን ይመለከታል።
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
