ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (Orthodox Tewahedo)
Відкрити в Telegram
🔔 Welcome! Join us to see the power of ✝️ faith in action! We post Orthodox 🎥 videos and inspiring 📢 messages on YouTube ▶️, Facebook, and right here in our Telegram Group 💬. ቀሲስ ዶ/ር ብዙአየሁ አምባዬ ሲያትል ዋሽንግተን
Показати більше2 525
Підписники
-324 години
-77 днів
-930 день
Архів дописів
+1
የአፎምያ፣ የባሕራን ረዳት(ድርሳነ ሚካ.) ስለ ሕዝብ ልጆች በምልጃ የምትቆም ታላቁ አለቃ ሚካኤል ሆይ [ት.ዳን. ፲፪፥፩] ባላጋራዬ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና [፩ኛ ጴጥ ፭፥፰] ቀድሞ ዘንዶውን ተዋግተህ እንደጣልከው [ራዕ ዮሐ ፲፪፥፯] ካንተ በቀር የሚያጸናኝ የለምና [ት.ዳን. ፲፥፳፩] ትረዳኝ ዘንድ ወደ እኔ ና።[ት. ዳን.፲፥፲፫] ናና ናና ዛሬም ዘወትርም ናና አሜን።
Join 👇
youtube.com/@OrthodoxTewahedo-
Repost from elam
መዝሙር ዘምሩ
ዘምሩ ለእግዚአሔር ጻድቃኑ እስመ ተንሥአ ክርስቶስ እሙታን (ዘ) በህየ ሰበረ ኆኃተ ብርት ወበህየ አውጽአ ዘቀዳሚ ልሕኲቶ (ዘ) አርአዮ ለቶማስ ርግዘተ ገቦሁ ወለእንድርያስ ቅንዋተ እደዊሁ (ዘ) ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት በአርብዓ ዕለት ምስለ መላእክት ዘምሩ ለእግዚአብሔር ጻድቃኑ ወግነዩ ለዝክረ ቅድሳቱ
ትርጉም፦
ጻድቃን ለእግዚአብሔር ዘምሩ ክርስቶስ ከሙታን ተነሥቷልና በዚያ የብረት ደጅን ሰበረ በዚያ የመጀመሪያ ሥራውን አወጣ ለቶማስ የጎኑን መወጋት አሳየው ለእንድርያም የእጆቹን ችንካሮች አሳየው በአርባኛው ቀን ከመላእክት ጋር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ
የዕለቱ ምስባክ፦
ወበመንፈስ አዚዝ አጽንዐኒ
ከመ እምሐሮሙ ለኃጥአን ፍኖተከ
ወረሲዓን ይትመየጡ ኀቤከ መዝ ፶፥፲፪
ትርጉም፦
በጽኑ መንፈስ አጽናኝ
መንገድህን ለኃጥአን አስተምራቸው ዘንድ
ዝንጉዎች ወደ አንተ ይመለሱ ዘንድ
ምሥጢር፦
በመንፈሰ ረድኤት አንድም በልጅነት አጽናኝ።
እኔ ተምሬ ኃጥአንን አስተምራቸው ዘንድ ረሲዓንም ተምረው ወዳንተ ይመለሱ ዘንድ።
አንድም ከመ እምሐሮሙ ለኃጥአን ረሲዓን ወይትመየጡ ኀቤከ ብሎ ይገጥሟል። ሕግህን ለዘነጉ ለኃጥአን ሕግህን አስተምራቸው ዘንድ ወዳንተም ይመለሱ ዘንድ።
የዕለቱ ወንጌል፦
ዮሐ ፲፮፥፩ - ፲፯
ቅዳሴ፦ ዘዲዮስቆሮስ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
