ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
Відкрити в Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Показати більше1 719
Підписники
-224 години
-77 днів
-1830 день
Архів дописів
ከጠበቅነው በላይ እስከ አሁን 26 ተወዳዳሪዎች በማግኘታችን እየተወዳደራችሁ ያላችሁትን እና ውድድሩን እየተከታተላችሁ ድምጽ እየሰጣችሁ ያላችሁትን ሁሉ እናመሰግናለን! የቤተሰባችን ቁጥርም 1000ን በመሻገሩ ደስታችን ግዙፍ ነው!!!
ይህንንም በማስመልከት ሁለተኛ እና ሶስተኛ ለሚወጡ ግጥሞችም የመጽሐፍት ሽልማት እንደምናበረክት እወቁልን!
አይ ሰው
ከስር ከስራቸው እየተከተልን
ሲጠሩን ስንመጣ ሲላቸው ሲያባሩን
እኔ ነኝ ያለውን እነሱን ሊነካ
ነክሰን እየያዝን ጥበቃው ቢሳካ
የኖሩ ኖሩና ተምሳሌትን ቢያጡ
ግብሩን እየሰሩ ስሙን ለኛ ሰጡ
እጅጉንም ሳኩኝ ሆዴን አሻሽቼ
ውሻ ብሎ ስድብ ከሰዎች ሰምቼ
@sarinamard
"ህይወት....🤔 ጢባ ጢቤ..."
ከፍታ ላይ 'ምታወጣ
አንዲት ቅጠል ጥላ ትታ!
አልያም ደ'ሞ የምትጥል
ትንሽ ድልን አስገኝታ!!
ወይም ደሞ..የለገመች...
ከፍ ላትል ላትረታ
ለሞከሯት.. ጠዋት ማታ!!!
@ZionismT
መልካም ዜና ለሱ ሀዘኔን ላልካሰኝ
ሳላለቅስ የቻልኩት ለ"ምነው?" ሆድባሰኝ
ስወጣ ጠንካራ ተደብቆ አልቃሻ
(ተብረክርኮም መቆም፤ቢዝልም ትከሻ)
ሲፈሩት ይደፍራል ሃዘን እና ውሻ!
@Guadyeee
ወዲህም
ካየሽ ፈሶ ደም
ወዲያም
ካየሽ ፈሶ ደም
ሌላው ሌላው ቢቀር
"እኔን"ንን ለማለት ፤ አፍሽ አይሎገም
።።።።።።።።።።።።።።።፡።።።
✍ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
መንታ ፍልስፍና....
የሚንከራተተው ያ'ዳም ዘር በሙሉ:
ሲዳፋ ሲቃና ሲዋትት መዋሉ:
የመፈጠሩን ቅድ ሊደፍን ነው አሉ።
@NikoTheGreat
.......የሞኝ ኑዛዜ......
ፈውስማ አለፈኝ፣ ምክኒያት ደንታን አልፎ
ተቅበዝባዥ አረገኝ፣ ከፍርሃት እብደት ተርፎ
ሃሳቤ ራስ ስቶ፣ ንግግሬ በዝቶ
ይገላምጠኛል፣ እውነቴ ተብቶ
.
ውብ ብያለሁና፣ ደማቋ ደመራ
ጭልም የሆንሽውን፣ የግሃነም ጮራ።
-ኖኔም
ትናንት ትዝ እንዳይለኝ- ከራሴ ጋ ማልኩኝ
ትናንትን ስረሳ- ለዛሬም አልኖርኩኝ
ካላየሁዋት የነገ ፀሐይ ተወዳጀሁ
እምነትን ይዤ ለተስፋ ደገስሁ
ከዛማ... በተከራየሁት የጊዜ ሰሌዳ
እኔ ሆንኩኝና የራሴ አለቃ፣ ቀጠሮን ቀጠርኩኝ
ነገ ዛሬ ሲሆን ደሞ ላባርረው
አዲስ ቅዠት ልቃዥ፣ የፈረደበትን መልሼ ልቀጥረው
@Mtesfaye7
ለመደስኮሩማ ስብከት ለመስበኩ
በወርች ሱባኤ ፍቅርን ለማምለኩ
መምህር መች ሽቶኝ ለወሬ ሽንገላው እኔው መቼ አነስኩ
የቸገረኝ ቢኖር የጠፋኝ ያጠረኝ መፍትሄ ብልሀቱ
የአክስቴን ገዳይ ቆስሎ ከተኛበት ደግፎ ማንሳቱ
በቆሎ ተዘርቶ ኩርንችት ማፍራቱ
@Mahlet_Be
የእሽቅድድም ህይወት
ግራን አስቀድሞ ቀኝን ለማስቀረት
አንድ አካልን ጥሎ በአንዱ መንኳተት
ሙሉነቱን ጥሎ በግማሽ እየለፋ
በግማሽ አካሉ ሰውን እየገፋ
ቀኙን ማዶ ጥሎ ግራውን እየሣበ
በአንድ አካሉ ማራቶን ያሰበ
@blessedloner
ከትርምስ መሀል ከኖረ ፀጥታ
በክፉ ቀን መሀል ከበዛ ዝምታ
ያንን ነዉ መተርጎም አንድም ለአንድምታ።
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
በትዝታ ወልዴ እንደተፃፈ
@Tizita21
ቤት የለኝም
ያም ሰፈር የነሱ ይሄም የእነንትና
የትጋ ቤቴን ልስራ ከማን ልጠጋና
ዘር አልቆጥር ነገር የፈጣሪ ልጅ ነኝ
እንግዲ እኔ አልሰራም ቤቴን ራሱ ይስጠኝ🙏
ያሬድ.የ
@Yjaredy
......የዘመኔ ምስል.......
ጉልበት ሳይዝል፤ ልብ ደከመ
ስጋ አብቦ ፤ ነፍስ ቆዘመ
በምጥ መሀል፤ ባለች ፈገግታ
ስንቱ ታለለ ፤ ህይወት ተረት'ታ. ..!!
(ነብዩ.ብ)
መሪ ቃል
ባይሆን እሮጣለሁ፥
በዘመን ሜዳ ላይ፥ በሰው የመሆን መም፤
ባይሆን አሸንፌ፥
አውለበልባለሁ፥ የልቤን ባንዲራ፥ የ'ኔነቴን ቀለም።
ካልሆነ ግን...
ለመሮጥ የሚሆን፥ ቢያንሰኝ እንኳ አቅም፤
ሯጩን ላለመጥለፍ፥ መሙ ላይ አልወድቅም።
ኑ !ወደ ነፃነት እንንጎድ
እፍ እያልን
በጭስ እንባ ሳናባክን
ኑ !ለነገ እንንደድ
ኑ።
(ኤደን ሙሉነህ)
@Oritethe
፠ሰመመን፠
ሲቃ በሚንጠው በጠቆረ ሰማይ
በዋይታ እርይታ በስቃይ ላይ ስቃይ
በትዝታ ጭሰት ጭስ በሌለው ንዳድ
በብቸኝነት ውስጥ በባይተዋር ጉድጓድ
በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ፋቅርን ተሸክሜ
በቀቢፀ ተስፋ ላይቀለኝ ደክሜ
አለሁ!!
አለሁ እንዳለሁኝ ሞቼም አገግሜ፡፡
✍️መሊኩ [ MAJNUN ]
@Bufal
ሠው ምንድን ነው
ታስበው ዘንድ ብሎ መዝሙር እንደፃፈው
ትመረምረው ዘንድ ብሎ እንደቀጠለው
እኔም ልጠይቅህ የሠማይ ፈጣሪ
የብርሃናት አባት የምድርም ቀማሪ፤
እድል ፈንታው ፈቅዶ ሞትን የሸለምከው
ይሄ ያንተ አምሣል፤ ጌታ ''ሠው'' ምንድን ነው?
26/11/13
ገጣሚ : ዳዊት:ጥዑማይ
@faberfortunae
!?!
እርምጃችን ሁሉ ታንፆ በስጋት
መራቅ ለመጠጋት
ባዶ ተስፍ መጋት
ጀንበርን መናፈቅ እየሸሹ ንጋት
ምን ይሉት ነው ደግሞ?
ለመድረስ መጓጓት እርምጃን አቁሞ
✍️ቶፊቅ መሀመድ ( #አዲብ )
@Tufaw_muhe
.................ፀ*ፀ*ቴ*
አዎን ፀፀቴ ነህ ንስሀ ያስገባኸኝ
ካምላኬ አጣልተህ ካምላኬ ያስታረከኝ
ጥፋቴን አልወቅሰው መርቶኛል ወደ
እውነት
ተመርጫለሁኝ ለትልቁ ደስታ በትንሹ
ክፋት
@Mekdiyemariyam
የይሁዳ ከንፈር
ስለ አንተና እኔ
ትንቢት ባይፃፍም ነብይ ባይናገር
ልትሄድ መምጣትህን ልቤ ነግሮኝ ነበር
አንተ ይሁዳ ሆነህ
እኔ ሆኜ አምላክ
ባላንጣህ ባይገዛኝ በ"ዲናር" ባትሸጠኝ
በመጨረሻ እራት በመሳም ሸኘኸኝ...
በምህረት
ሐምሌ /2013ዓ .ም
@mihretengida
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
