ar
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

الذهاب إلى القناة على Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

إظهار المزيد
1 719
المشتركون
-224 ساعات
-77 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
ከጠበቅነው በላይ እስከ አሁን 26 ተወዳዳሪዎች በማግኘታችን እየተወዳደራችሁ ያላችሁትን እና ውድድሩን እየተከታተላችሁ ድምጽ እየሰጣችሁ ያላችሁትን ሁሉ እናመሰግናለን! የቤተሰባችን ቁጥርም 1000ን በመሻገሩ ደስታችን ግዙፍ ነው!!! ይህንንም በማስመልከት ሁለተኛ እና ሶስተኛ ለሚወጡ ግጥሞችም የመጽሐፍት ሽልማት እንደምናበረክት እወቁልን!

አይ ሰው ከስር ከስራቸው እየተከተልን ሲጠሩን ስንመጣ ሲላቸው ሲያባሩን እኔ ነኝ ያለውን እነሱን ሊነካ ነክሰን እየያዝን ጥበቃው ቢሳካ የኖሩ ኖሩና ተምሳሌትን ቢያጡ ግብሩን እየሰሩ ስሙን ለኛ ሰጡ እጅጉንም ሳኩኝ ሆዴን አሻሽቼ ውሻ ብሎ ስድብ ከሰዎች ሰምቼ @sarinamard

"ህይወት....🤔 ጢባ ጢቤ..." ከፍታ ላይ 'ምታወጣ አንዲት ቅጠል ጥላ ትታ! አልያም ደ'ሞ የምትጥል ትንሽ ድልን አስገኝታ!! ወይም ደሞ..የለገመች... ከፍ ላትል ላትረታ ለሞከሯት.. ጠዋት ማታ!!! @ZionismT

መልካም ዜና ለሱ ሀዘኔን ላልካሰኝ ሳላለቅስ የቻልኩት ለ"ምነው?" ሆድባሰኝ ስወጣ ጠንካራ ተደብቆ አልቃሻ (ተብረክርኮም መቆም፤ቢዝልም ትከሻ) ሲፈሩት ይደፍራል ሃዘን እና ውሻ! @Guadyeee

ወዲህም ካየሽ ፈሶ ደም ወዲያም ካየሽ ፈሶ ደም ሌላው ሌላው ቢቀር "እኔን"ንን ለማለት ፤ አፍሽ አይሎገም ።።።።።።።።።።።።።።።፡።።። ✍ሳሙኤል አለሙ @Samuelalemuu

መንታ ፍልስፍና.... የሚንከራተተው ያ'ዳም ዘር በሙሉ: ሲዳፋ ሲቃና ሲዋትት መዋሉ: የመፈጠሩን ቅድ ሊደፍን ነው አሉ። @NikoTheGreat

.......የሞኝ ኑዛዜ...... ፈውስማ አለፈኝ፣ ምክኒያት ደንታን አልፎ ተቅበዝባዥ አረገኝ፣ ከፍርሃት እብደት ተርፎ ሃሳቤ ራስ ስቶ፣ ንግግሬ በዝቶ ይገላምጠኛል፣ እውነቴ ተብቶ . ውብ ብያለሁና፣ ደማቋ ደመራ ጭልም የሆንሽውን፣ የግሃነም ጮራ። -ኖኔም

ትናንት ትዝ እንዳይለኝ- ከራሴ ጋ ማልኩኝ ትናንትን ስረሳ- ለዛሬም አልኖርኩኝ ካላየሁዋት የነገ ፀሐይ ተወዳጀሁ እምነትን ይዤ ለተስፋ ደገስሁ ከዛማ... በተከራየሁት የጊዜ ሰሌዳ እኔ ሆንኩኝና የራሴ አለቃ፣ ቀጠሮን ቀጠርኩኝ ነገ ዛሬ ሲሆን ደሞ ላባርረው አዲስ ቅዠት ልቃዥ፣ የፈረደበትን መልሼ ልቀጥረው @Mtesfaye7

ለመደስኮሩማ ስብከት ለመስበኩ በወርች ሱባኤ ፍቅርን ለማምለኩ መምህር መች ሽቶኝ ለወሬ ሽንገላው እኔው መቼ አነስኩ የቸገረኝ ቢኖር የጠፋኝ ያጠረኝ መፍትሄ ብልሀቱ የአክስቴን ገዳይ ቆስሎ ከተኛበት ደግፎ ማንሳቱ በቆሎ ተዘርቶ ኩርንችት ማፍራቱ @Mahlet_Be

የእሽቅድድም ህይወት ግራን አስቀድሞ ቀኝን ለማስቀረት አንድ አካልን ጥሎ በአንዱ መንኳተት ሙሉነቱን ጥሎ በግማሽ እየለፋ በግማሽ አካሉ ሰውን እየገፋ ቀኙን ማዶ ጥሎ ግራውን እየሣበ በአንድ አካሉ ማራቶን ያሰበ @blessedloner

ከትርምስ መሀል ከኖረ ፀጥታ በክፉ ቀን መሀል ከበዛ ዝምታ ያንን ነዉ መተርጎም አንድም ለአንድምታ። ❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤ በትዝታ ወልዴ እንደተፃፈ @Tizita21

ቤት የለኝም ያም ሰፈር የነሱ ይሄም የእነንትና የትጋ ቤቴን ልስራ ከማን ልጠጋና ዘር አልቆጥር ነገር የፈጣሪ ልጅ ነኝ እንግዲ እኔ አልሰራም ቤቴን ራሱ ይስጠኝ🙏 ያሬድ.የ @Yjaredy

......የዘመኔ ምስል....... ጉልበት ሳይዝል፤ ልብ ደከመ ስጋ አብቦ ፤ ነፍስ ቆዘመ በምጥ መሀል፤ ባለች ፈገግታ ስንቱ ታለለ ፤ ህይወት ተረት'ታ. ..!! (ነብዩ.ብ)

መሪ ቃል ባይሆን እሮጣለሁ፥ በዘመን ሜዳ ላይ፥ በሰው የመሆን መም፤ ባይሆን አሸንፌ፥ አውለበልባለሁ፥ የልቤን ባንዲራ፥ የ'ኔነቴን ቀለም። ካልሆነ ግን... ለመሮጥ የሚሆን፥ ቢያንሰኝ እንኳ አቅም፤ ሯጩን ላለመጥለፍ፥ መሙ ላይ አልወድቅም።

ኑ !ወደ ነፃነት እንንጎድ እፍ እያልን በጭስ እንባ ሳናባክን ኑ !ለነገ እንንደድ ኑ። (ኤደን ሙሉነህ) @Oritethe

፠ሰመመን፠ ሲቃ በሚንጠው በጠቆረ ሰማይ በዋይታ እርይታ በስቃይ ላይ ስቃይ በትዝታ ጭሰት ጭስ በሌለው ንዳድ በብቸኝነት ውስጥ በባይተዋር ጉድጓድ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ፋቅርን ተሸክሜ በቀቢፀ ተስፋ ላይቀለኝ ደክሜ አለሁ!! አለሁ እንዳለሁኝ ሞቼም አገግሜ፡፡ ✍️መሊኩ [ MAJNUN ] @Bufal

ሠው ምንድን ነው ታስበው ዘንድ ብሎ መዝሙር እንደፃፈው ትመረምረው ዘንድ ብሎ እንደቀጠለው እኔም ልጠይቅህ የሠማይ ፈጣሪ የብርሃናት አባት የምድርም ቀማሪ፤ እድል ፈንታው ፈቅዶ ሞትን የሸለምከው ይሄ ያንተ አምሣል፤ ጌታ ''ሠው'' ምንድን ነው? 26/11/13 ገጣሚ : ዳዊት:ጥዑማይ @faberfortunae

!?! እርምጃችን ሁሉ ታንፆ በስጋት መራቅ ለመጠጋት ባዶ ተስፍ መጋት ጀንበርን መናፈቅ እየሸሹ ንጋት ምን ይሉት ነው ደግሞ? ለመድረስ መጓጓት እርምጃን አቁሞ ✍️ቶፊቅ መሀመድ ( #አዲብ ) @Tufaw_muhe

.................ፀ*ፀ*ቴ* አዎን ፀፀቴ ነህ ንስሀ ያስገባኸኝ ካምላኬ አጣልተህ ካምላኬ ያስታረከኝ ጥፋቴን አልወቅሰው መርቶኛል ወደ እውነት ተመርጫለሁኝ ለትልቁ ደስታ በትንሹ ክፋት @Mekdiyemariyam

የይሁዳ ከንፈር ስለ አንተና እኔ ትንቢት ባይፃፍም ነብይ ባይናገር ልትሄድ መምጣትህን ልቤ ነግሮኝ ነበር አንተ ይሁዳ ሆነህ እኔ ሆኜ አምላክ ባላንጣህ ባይገዛኝ በ"ዲናር" ባትሸጠኝ በመጨረሻ እራት በመሳም ሸኘኸኝ... በምህረት ሐምሌ /2013ዓ .ም @mihretengida