LOGOS
Відкрити в Telegram
🎯የቻናሉ ዓላማ:LOGOS የሚለው ቃል ከGreek የመጣ ሲሆን፦ትርጉሙም ቃል፣ ምክንያት፣ክርስቶስ (የእግዚአብሔር ቃል ዮሐ 1፥1) በዚህ ቃል እውቀታችንን አሳድገን በኑሮ እንድንተገብር ነው
Показати більшеКраїна не вказанаКатегорія не вказана
247
Підписники
Немає даних24 години
+27 днів
+1330 день
Триває завантаження даних...
Схожі канали
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
серпень '26
серпень '26
+19
в 1 каналах
липень '26
+238
в 0 каналах
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 28 серпня | 0 | |||
| 27 серпня | 0 | |||
| 26 серпня | +1 | |||
| 25 серпня | +1 | |||
| 24 серпня | 0 | |||
| 23 серпня | 0 | |||
| 22 серпня | 0 | |||
| 21 серпня | 0 | |||
| 20 серпня | +1 | |||
| 19 серпня | 0 | |||
| 18 серпня | +1 | |||
| 17 серпня | 0 | |||
| 16 серпня | +1 | |||
| 15 серпня | +6 | |||
| 14 серпня | +1 | |||
| 13 серпня | +1 | |||
| 12 серпня | +2 | |||
| 11 серпня | +1 | |||
| 10 серпня | 0 | |||
| 09 серпня | +1 | |||
| 08 серпня | +1 | |||
| 07 серпня | 0 | |||
| 06 серпня | +1 | |||
| 05 серпня | 0 | |||
| 04 серпня | 0 | |||
| 03 серпня | 0 | |||
| 02 серпня | 0 | |||
| 01 серпня | 0 |
Дописи каналу
| 2 | መንፈስ ቅዱስ ልቤን እንደተቆጣጠረዉ በምን አዉቃለሁ ❓
#1,መንፈስ ቅዱስ ልባችንን ከተቆጣጠረዉ፤እዚህ ምድር ላይ ጌታ ኢየሱስን ከምንም ነገር በላይ እንድናከብረው ልባችንን ያነሳሳል።
#2,የእግዚአብሔርን ፈቃድ ፈቅደን እንድናደርግ እና በመከራም እንድንታገስ ያደርገናል።
#3,ለጌታ ኢየሱስ እራሳችንንና መሻታችንን እንድንተዉ ያደርጋል።
ጆን ኮተን
✍️ | 271 |
| 3 | ሕግህ ደስታዬ - Kenesa and Solomon Bula
ሕግህ ደስታዬ ባይሆን ኖሮ
በመከራ ቀን በጠፋው ነበር
ጸጋህ አጽንቶ አቁሞኛልና
ትዛዝህን ከቶ አልረሳም
ቃልህ ደስታዬ ባይሆን ኖሮ
በመከራ ቀን በጠፋው ነበር
ጸጋህ አጽንቶ አቁሞኛልና
ትዛዝህን ከቶ አልረሳም
ስርአትህን እሻዋለው ትዛዝህን አስባለሁ
ልቤንም አስፍተህልኛል በመንገድህም እሮጣለሁ
ስርአትህን እሻዋለዉ ቃልህን በልቤ አኖራለሁ
ልቤንም አስፍተህልኛል በመንገድህም እሮጣለሁ
ነፍሴ አንተን አንተን አንተን ብቻ ትሻሀለች|3× |
@remnant_s | 56 |
| 4 | Highi_destaye_ሕግህ_ደስታዬ_Kenessa_and_Solomon_Bula_ኬነሳ_እና_ሰለሞን_.m4a | 48 |
| 5 | #መድሃኒቴ
በህክምናው አለም ዙሪያ ያላችሁ እንደምታውቁት የፋርማኮሎጂ መሠረታዊ መርህ ''Every drug is a poison'' [ሁሉም መድሀኒት መርዛማ ነው] የሚል ነው። ሁሉም መድሀኒት በተባለለት መጠን ና የጊዜ ገደብ ካልተወሰደ ለከፋ ጉዳት ብሎም ለሞት ሊዳርግ ይችላል።
የአለም መድሀኒት የሆነው ክርስቶስ ግን ያለገደብ የተሰጠን ፈውሳችን ነው። ባይገርማችሁ የትኛውም መድሀኒት እንዳትሞቱ ይከላከላል እንጂ ከሞታችሁ በኋላ በቃ አበቃ!! የእኛ መድሀኒት ግን በበደላችን ሙታን ሆነን ሳለን ህይወት ሰጠን። የታመመን የሚፈውስ ብቻ ሳይሆን የሞተን የሚያስነሳ ብርቱ መድሃኒት ኢየሱስ ነው!! ይህ መድሃኒት
👉 የሀጢያት ማስታገሻ ሳይሆን ፈዋሽ ነው
👉 ምንም የጎንዮሽ ጉዳት (side effect) የለውም
👉 ፈውሱ ዘላለማዊ ነው።
👉 ለአለም ሁሉ የቀረበ ነው
👉 አለቀ የማይባል ነው
👉 እጅግ ጉልበታም ነው
* እንዲህ አይነት መድሃኒት በዚህ ምድር ቢሸጥ ምን ያህል ያወጣ ይሆን? ይህ መድሃኒት ግን:
👉 ነፃ ነው
#ኢየሱስ_ምግባችንም_መድሃኒታችንም_ነህ@LOGOSJ1ASHU ነህ | 597 |
| 6 | የመንፈስ ቅዱስ ቋንቋ
መጽሐፍ ቅዱስ ነው።
•••••••
ጆን ካልቪን
•••••••
መንፈስ ቅዱስ እኛን እንድሰራ ከፈለግን መፅሐፍ ቅዱስ እናጥና ። | 574 |
| 7 | #እግዚአብሔርን_መፍራት ፤ #ፍርሃትን_ሁሉ የሚያስወግድ ፍርሃት ነው ። እግዚአብሔር ሆይ አንተን እፈራለሁ ፣ በዚህ ፍርሃት ሁሉንም እደፍራለሁ ።
📌ስራችን ሰዎችን ማስደሰት ሳይሆን የእግዚአብሔርን መልዕክት ማወጅ ነው። የምንኖረው በመጭው የእግዚአብሔር የፍርድ ብርሃን ስለሆነ የዛሬው የሰዎች ፍርድ አያስፈራንም።
እግዚአብሔርን ብቻ እንፈራለን (10፡28)፦ ሰዎች ሊያደርጉ የሚችሉት ነገር ቢኖር ሰውነትን መግደል ብቻ ነው ፤ ይህንንም ቢያደርጉ ፥ የአማኙ ነፍስ ከአብ ጋር ለመሆን ወደ ሰማያዊ ቤቷ ትሄዳለች ። እግዚአብሔር ግን ነፍስንም ስጋንም በገሃነመ-እሳት ሊያጠፋ ይችላል !
በእርግጥ እግዚአብሔር በክርስቶስ ያመኑትን ከልጆቹ አንድስንኳ አይኮንንም ደግሞም አይፈረድበትም #(ሮሜ 8:1 ዮሐ 5:24)
🗯️ማርቲን ሉተር ይህ እውነት በርቶለት ነው ይህን ግጥም የፃፈው ፦
ቁሳቁስና መሰሎቹ
ይኼም በስባሽ ስጋ ሟቹ
ይለፍ ሁሉም በእውነቱ
በስርዓቱ ። | 729 |
| 8 | 📌‹‹በውነት በነዉር መንገድ አትሂዱ። እግዚአብሔር የማይወደው መንገድ፣ በኋላ የህልና ጸጸት፣ ማታ ስትተኙ ባልጋችሁ ላይ የእግዚአብሔርን ሀሳብና ፈቃድ አደረኩ ብላችሁ በማትሉት ይልቁን፣ መንፈሳችሁ በውስጣችሁ በሚቆዝምበትና በሚያዝንበት የነዉር መንገድ አትሂዱ።
👉🏿የመንግስት ስራ ላይ የተመደበችሁ ሃላፊዎች፣ ደሞዛችሁ ይብቃችሁ፤ ደሞዛችሁ ይብቃችሁ። ትንሽ ሊሆን ይችላል፣ ግን እንደ እግዚአብሔር ሰው፣ እጃችሁን ጭናችሁ ጸልያችሁ፤ እግዚአብሔር ሆይ የማገኘው ይሄ ነው፣ ኑሮው ደግሞ የሚጠይቀኝ ይሄ ነው። እንግዲህ አንተ አድርሰው ብላችሁ ባላችሁ ሂዱ፤ ባላችሁ ኑሩ። ከፈቀደላችሁ ውጪ፣ ስራችሁ ካስገኘላችሁ ጥቅም እና ጥቅማጥቅም ውጪ አትሂዱ።
👉🏿የመንግስትን ሃላፊዎች ደጅ የምትጠኑ ጉዳይ አስፈፃሚዎች፣ የመንግስትን ባለስልጣናት ለማባበል ነገ ጉዳያችሁን በሚፈልጉት መንገድና በአጭር ጊዜ ለማስፈፀም በጎን አትሂዱ፣ አትሂዱ። ህጉ፣ ደንቡ፣ መመሪያው ከሰራላችሁ፣ የሚያጋጥማችሁ ስራ ሃላፊ ወይም ባለስልጣን በቀና መንገድ ጉዳያችሁን ፈጽመዉ ከሸኛችሁ ይሸኛችሁ፣ ካልሆነ ለእግዚአብሔር ስጡት። እግዚአብሔር ወደ ላይ በመውሰድም ያድናል፣ ወደ ጎን በመውሰድም ያድናል፤ እነዚህን የመንግስት ስልጣን ተገን አድርገው ጉዳያችሁን በአግባቡ፣ በመንገዱ በማይፈጽሙ የስራ ሃላፊዎች ላይ እግዚአብሔር የሚመጣበት መንገድ አለ። ስለዚህ የእናንተ ነገር ዛሬ ባይፈጸም፣ ነገ በሌላ ባለስልጣን ይፈጸምላችኋል። ሙስና የሚፈፀመዉ፣ በመስጠትም በመቀበልም ስለሆነ።
👉🏿ነጋዴዎች በሀቅ ነግዱ፤ በሀቅ ስትነግዱ፣ መደብራችሁ ሼልፉ ላይሞላ ይችላል፣ ላይደምቅ፣ ላይሞቅ ይችላል፣ ነግዳችሁ ላይደራ ይችላል፣ ግን በእውነት እግዚአብሔር ይባርካችኋል።» | 66 |
| 9 | ወደ እግዚአብሔር ፊት ስንቀርብ ባለንበት ሁኔታ እንጂ መቅረብ ያለብን የበቃን አስመስለን አይደለም ፤ ምን ማለት ነው ፦
✅ደብሮን ከሆነ ጌታ ሆይ ደብሮኛል ማለት አለብን
✅በእሱ ላይ እምነት ከሌለን በአንተ ላይ እምነት የለኝ በአንተ እንድታመን እርደኝ ማለት አለብን ፤
✅ተስፋ ከቆረጥን ተስፋ ቆርጫለሁ ማለት
✅ሁሉ ነገር ከሰለቸን ሰልችቶኛል ማለት አለብን
✅ባዶነት ከተሰመን ባዶነት ተሰምቶኛል ማለት
✅ፀሎት ከከበደን ፀሎት ከብዶኛል ማለት ....
በእግዚአብሔር ፊት ያልሆነውን ሆነን እንድንቀርብ እግዚአብሔር አይፈለግም ፤ የሆነውን ሁሉ እሱ ስለሚያውቅ መደበቅ አያስፈልግም ፤ በእግዚአብሔር ለመታከም የሆነውን ሁሉ ሳንደብቅ ለእሱ መንገር አለብን ። ጭንቅ ውስጥ ከሆንን እንደ ዳዊት ግልፅ እንሁን
📖“ ...ጭንቅ ውስጥ ነኝና ፈጥነህ መልስልኝ።”(መዝሙር 69:17) | 910 |
| 10 | የLOGOS ቤተሰቦች ... ከዚህ Channel እየተጠቀማችሁ ከሆነ ሌሎችም እንድጠቀሙ 🔗Linkun share አድርጉ
https://t.me/LOGOSJ1ASHU
ከቻላችሁ ለ 5 ጓደኞቻችሁ 🙏 | 90 |
| 11 | “ሰው ራሱን ዝቅ አድርጎ የራሱን #አቅመ-ቢስነት እስካልተረዳ ድረስ፣ ለእግዚአብሔር #ጸጋ #ቦታ አይኖረውም።"
💭 ጆን ካልቪን
◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦
ሰው በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ይሆን ዘንድ፣ከሴትስ የተወለደ ንጹሕ ይሆን ዘንድ ይችላልን?📖(ኢዮብ 25:4)
በኢየሱስ ክርስቶስ በሆነው ቤዛነት እንዲያው በጸጋው ጸድቀዋል፤
📖(ሮሜ 3:24)
ብቃታችን ከእግዚአብሔር ነው እንጂ፣ በራሳችን ብቃት ከእኛ ነው የምንለው አንዳች ነገር የለንም።📖(2 ቆሮንቶስ 3:5) | 900 |
| 12 | “ሰው ራሱን ዝቅ አድርጎ የራሱን #አቅመ-ቢስነት እስካልተረዳ ድረስ፣ ለእግዚአብሔር #ጸጋ #ቦታ አይኖረውም።"
💭 ጆን ካልቪን
◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦
ሰው በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ይሆን ዘንድ፣ከሴትስ የተወለደ ንጹሕ ይሆን ዘንድ ይችላልን?📖(ኢዮብ 25:4)
በኢየሱስ ክርስቶስ በሆነው ቤዛነት እንዲያው በጸጋው ጸድቀዋል፤
📖(ሮሜ 3:24)
ብቃታችን ከእግዚአብሔር ነው እንጂ፣ በራሳችን ብቃት ከእኛ ነው የምንለው አንዳች ነገር የለንም።📖(2 ቆሮንቶስ 3:5) | 1 |
| 13 | 📔 ሰይጣን በእግዚአብሔር ላይ ያለንን እምነት ማጥፋት ይፈልጋል። እግዚአብሔር ደግሞ በራሳችን ላይ ያለንን እምነት ማጥፋት ይፈልጋል።
እግዚአብሔር አብ በሰጠን በልጁ #እንድንተማመን አጥብቆ ይፈልጋል ደግሞም(ዮሐ 6፡40) ፤ በቅዱስ ቃሉ ውስጥ ያለውን #ሀብት እንድናውቅ ይፈልጋል ።
📔#በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ
ያለው #ሐብት #ክርስቶስ ነው(ዮሐ 5፡39) ። የእውነተኛ አምልኮ ምንጭም ይሄን እውቀት ማወቅ ነው
📔የአምልኮ መነሻ ምንጭ፥ስሜት አይደለም፤ስነመለኮት ነው።
(ጆን ኪምቤል፤ሲንክሌር ፈርጉሰን፤ኢሬኔየስ)
✍️ወንድም አሻግሬ | 934 |
| 14 | #ቅድስና ወደ ኢየሱስ ያመጣን መንገድ
አይደለም፤
#ኢየሱስ ነው ወደ ቅድስና ያመጣን።
•••••••••••••••
ቻርልስ ስፐርጀን
•••••••••••••••
#ኢየሱስ ትላንት ያገኘንህ የማትወሰድ ፅድቃችን ነህ ፤
#ኢየሱስ ዛሬን ያቆምከን የማትነቃነቅ ዓለታችን ነህ ፤
#ኢየሱስ የማትጨልምብን የሚትመጣ ተስፋችን ነህ ።
🔒ዋሴ አንተ ነህ ለዘላለም አልጠፋም ፤
በማይፋቅ ቀለም በደምህ ተፅፏል ስሜ በሕይወት መዝገብ ፤ ማነው የሚደመስሰኝ !
እኔ ነኝ ወይስ ልዩ ፍጥረት ! #ሉራ(ከቶ)
✍️ወንድም አሻግሬ | 840 |
| 15 | ይቅር ለተባለ ኃጢአተኛ ሲዖል የለም።
እግዚአብሔር እንደ አባት ያቅፈዋል እንጂ እንደ ፈራጅ አይኮንነውም።
•••••••••••••••
ቻርልስ ስፐርጀን
•••••••••••••••
...ስለዚህ በክርስቶስ ኢየሱስ ያሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም፤ (ሮሜ 8:1)
✍️ወንድም አሻግሬ | 652 |
| 16 | ይቅር ለተባለ ኃጢአተኛ ሲዖል የለም።
እግዚአብሔር እንደ አባት ያቅፈዋል እንጂ እንደ ፈራጅ አይኮንነውም።
•••••••••••••••
ቻርልስ ስፐርጀን
•••••••••••••••
...ስለዚህ በክርስቶስ ኢየሱስ ያሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም፤ (ሮሜ 8:1)
✍️ወንድም አሻግሬ | 1 |
| 17 | መንግሥተ ሰማያትን
መንግሥተ ሰማያት ያደረገው
#የኢየሱስ መገኘት ነው።
••••••••••••••••••
እግዚአብሔር በእምነት ሲገልጥልን፥
የሌለንና የሚያስፈልገን ሁሉ
#በክርስቶስ #ኢየሱስ እንዳለ እናስተውላለን።
◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦◦
ጆን ካልቪን | 969 |
| 18 | የኢየሱስ አምላክነት(መለኮትነት)
...የመጨረሻ ክፍል
ለትምህርቱ የመጨረሻ ክፍል ነው ፤ ስለ ኢየሱስ ግን ጀምርን እንጂ ከቶ አንጨርስም ።
ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ የመሆኑ አስፈላጊነት
ሀ.የሚያምኑበትን ሁሉ ፍርዳቸውን ሊሸከም እና ሊያስወግድ የሚችል ፍፁም አምላክ የሆነ ማንነት ።
ለ.ደህንነት ከእግዚአብሔር ብቻ ነው (ዮሐ 2:10)
ሐ.ፍፁም አምላክ እና ፍፁም ሰው የሆነ ማንነት ብቻ ነው በሰው እና በእግዚአብሔር መካከል መካከለኛ መሆን የሚችለው (1ጢሞ 2:5)
በመሆኑም ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ባይሆን ኖር ደህንነትም ፤ ክርስትናም ፈፅሞ አይኖሩም ነበር።
“ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ የለውም ” 1ዮሐ 2:23 | 706 |
| 19 | የኢየሱስ መለኮታዊ ባህርያት (Divine Essences)
➧መለኮታዊ ባህርያት ማለት መለኮት ብቻ ሊኖረው የሚችለው የትኛውም ፍጥረት የማያኖረው የአምላክ መታወቂያና መገለጫ ባህርያቶቹ ናቸው ።
ሀ.ሁሉን ማድረግ ይችላል
(Omnipotent )
➣ማዕብል በቃሉ አዟል (ማቴ 8:26-27)
➣ዳቦና አሳ አበርክቷል (ማቴ 14:19)
➣ውኃ ወደ ወይን ጠጅ ቀይሯል (ዮሐ 2:1-11)
ለ.ሁሉን አዋቂ (Omniscience )
➣የሰዎችን ሀሳብ ...(ማቴ 2:8) የይሁዳን (ዮሐ 6:64)
(ዮሐ 2:25, 16:30)
ሐ.በሁሉ ቦታ ይገኛል(Omnipresence)
➣(ማቴ 18:20,28:20)
መ.ዘለዓለማዊ ነው
(ዮሐ 8:58, ራዕ 22:13)
ሠ.ሉዓላዊ ስልጣን አለው (Sovereignty)
➣ኃጢአትን ይቅር ማለት (ማር 2:5-7) እኔ ብሎ ያወራል “I am” ማለት ይችላል (5:22,28, 32, 34, 39, 44)
ረ.አምልኮን ይቀበላል
➣ከመላእክት (ዕብ 1:6 ራዕ 5:6-19)
➣ከሰው (ዮሐ 9:38)
➣ጉልበት ሁሉ(2:9-11)
➣ኢየሱስ ክርስቶስ የመለኮት ሙላት ሁሉ የተገለጠበት ነው ። (ቆላ 1:19, 2:9) | 595 |
| 20 | ስቃ በምትገድል ዓለም ፣ ቆስለህ የፈወስከን የእግዚአብሔር ልጅ ሆይ ተመስገን !
... ከሰማያዊው ጥሪ ተካፋዮች የሆናችሁ ቅዱሳን ወንድሞች ሆይ፥ የሃይማኖታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህናት #ኢየሱስ_ክርስቶስን_ተመልከቱ ” (ዕብ 3:1)
ኢየሱስ ብዛልን
እለት እለት እንብላህ ጣፍጥልን
የአብ ትኩረት የሆንከውን እንመልከትህ
በቤተክርስቲያን ስንኖር ከቶ የማታከስረን ኢየሱስ
✍️ወንድም አሻግሬ | 500 |
