Haala Ilaalcha Ortodoksii(ኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ)
Відкрити в Telegram
Waa'ee Mana Kiristaanaa Fi Biyya Keenyaa Haala Ilaalcha Ortodoksiin Hubachuu የቤተክርስቲያናችንና ሀገራዊ ሁኔታዎችን በኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ መረዳት
Показати більшеКраїна не вказанаКатегорія не вказана
273
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1330 день
Архів дописів
አንዳንድ ሰዎች፦
👉 እነርሱ ሆድ አደር ስለሆኑ እኛም ሆድ አደር እንድንሆንላቸው ይፈልጋሉ
👉እነርሱ ኅሊና ቢሶች ስለሆኑ እኛም ኅሊናቢሶች እንድንሆን ይፈልጋሉ
👉እነርሱ አጎብዳጅ ስለሆኑ እኛም አጎብዳጅ እንድንሆንላቸው ይፈልጋሉ
👉እነርሱ አስመሳዮች ስለሆኑ እኛም አስመሳዮች እንድንሆንላቸው ይፈልጋሉ
👉 እነርሱ አላዋቂዎች ስለሆኑ እኛም አላዋቂዎች እንድንሆንላቸው ይፈልጋሉ
👉እነርሱ ይሁዳ ስለሆኑ እኛም ይሁዳ እንድንሆንላቸው ይፈልጋሉ
👉እነርሱ ለፍትፍት እና ለሙዳየ ምጽዋት እየኖሩ እውነትን ስለሚያሳድዱ እኛም እንደነርሱ እንድንኖር ይፈልጋሉ
👉እነርሱ ጠባቦች ስለሆኑ እኛም ጠባቦት እንድንሆንላቸው ይፈልጋሉ
👉እነርሱ ጎጠኞች ስለሆኑ እኛም ጎጠኞች እንድንሆንላቸው ይፈልጋሉ
👉እነርሱ ሰፈርተኞች ስለሆኑ እኛም ሰፈርተኞች እንድንሆንላቸው ይፈልጋሉ
👉እነርሱ ዘረኞች ስለሆኑ እኛም ዘረኞች እንድንሆንላቸው ይፈልጋሉ
"እስጢፋኖሳዊነት" የማይቀረው መፍትሔ!
በቤተክርስቲያን ጉዳይ ሽምግልና፣ማቻቻል፣ መሸፋፈን፣ መተላለፍ ወዘተ ነገሮችን ሁሉ ትቶ እውነት እውነቷን በአደባባይ መነጋገርና የሚመጣውን ሁሉ መቀበል፣ ከራስ ክብር ይልቅ ቤተክርስቲያንን ማስቀደም፣ የእግዚአብሔርንም የሕዝብንም ዳኝነት ለመቀበል መወሰን ያስፈልጋል ይህ ራሳችንንም ቤተክርስቲያንንም ወደ ልዕልና ይመልሳል።
እስጢፋኖሳዊ ልብ ይኑረን!!
መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ
Repost from ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት
ክርስቲያንነት ነሁላላነት አይደለም።
ክርስቲያንነት አስመሳይነት አይደለም።
ክርስቲያንነት አታላይነት አይደለም።
ክርስቲያንነት ጎብዝነት አይደለም።
ክርስቲያንነት ድቡልቡልነት አይደለም።
ክርስቲያንነት ኅብረታዊ ርቱዕነት ነው።
ክርስቲያንነት የቀና የጸና አስተሳስብ ነው።
ክርስቲያንነት ኵላዊነት ነው።
ክርስቲያንነት የተስፋ ፍጽምና ነው።
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
መንግሥታዊ ፍጅት በአርሲ ምድር
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና ልጆችዋ ላይ የሚደርሰው ጥቃት እንደ ድንገት የተከሰተ ሳይሆን፦ ሥርዐታዊ፣መዋቅራዊና ርዕዮተዓለማዊ ነው፣ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ግብ ያለው ነው፣ከኦርቶዶክስ የጸዳች አዲስ ሀገር የመፍጠር ጉዞ ነው። የጥቃቱ ዓይነት ቢለያይም ዋና ዓለማቸው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ኦርቶዶክሳውያንን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጽዳት ነው።ይኽን እቅዳቸውን ከግብ ለማድረስ በአራቱም አቅጣጫ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የመከራ እሳት የተለኮሰ ቢሆንም በኦሮሚያ ክልል እየሆነ ያለው ግን ይለያል ከሁሉም ደግሞ በአርሲ ምድር።የአርሲ ኦርቶዶክሳውያን የሚታረዱት በመንግሥት መዋቅር እና ከፑንትላንድ እስከ አርሲና ባሌ በተዘረጋው በአልሸባብና በአይአይ ኤስ የአሸባሪ ቡድን ነው። ሰሞኑን በሽርኮ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የተሠሩ ሥርዐታዊ ውንብድናዎችን በመረጃና ማስረጃ አጋልጣለው።
ፎቶ አንድ(1)
ኦቢኤን ከሁለት ቀናት በፊት "ኦርቶዶክሳውያን አልተገደሉም"የሚል የሠራው ዶክሜንተሪ ነው።በዚህ ዶክመንተሪ ላይ ካህናትና ኦርቶዶክሳውያን ሽማግሎች "በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሠራጨው መረጃ ሐሰት ነው" እንዲሉ ተገደዋል።የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ጣሂር አማኖ "በወረዳችን ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ሲነዙ የነበሩና አሁንም እየተነዙ ያለው ወሬዎች ውሸት ናቸው (ኦርቶዶክሱ አልተገደለም) እንዲህ ዓይነት ወሬዎች ኦርቶዶክሱ በወረዳችን ላይ እንዳይኖር ያደርጋል" ሲል የኦርቶዶክሳውያንን ፍጅት ክዷል ዳግም ጥቃት ሊፈጽሙ እንደሚችሉም ዝቷል። አቶ ጣሂር አብደላ አማን( አብደላ ማይክሮ) ከሚባል ባለሥልጣናት ጋር ከመተባበር ለወሀቢያዎቹ ድጋፍ የሚያደርግና ኦርቶዶክሳውያንን በማስጨፍጨፍ እጁ በደም የቆሸሸ ሰው ነው።በዚህ ወረዳ ከ164 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል(ታግተው ደብዛቸው የጠፋ ይኑሩ ይሙቱ ዩማይታወቅ 26 ኦርቶዶክሳውያንን) ሳያካትት።ዛሬ ሥልጣኑንም ሚዲያውንም ባንኩንም ታንኩን ስለ ተቆጣጠሩት እንደፈለጋቸው ይወሻሉ በሞታችን ላይ ይሳለቃሉ ነገ ግን ከርድ አያመልጧትም።ለሙስሊሙ ሕዝብ ጭምር ጥቁር ታሪክ እያስቀመጡ ነው።
ፎቶ ሁለት(2)
ከዘጠኛ (9)ቀናት በፊት የምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሚዲያ "ከሽር ካወረዳ ጋዶ ቀጠና ተፈናቅለው ወደ ጎረቤት ወረዳ የሸሹ ምዕመናን የመመለስ ስራ ተጀምሮአል ተፈናቃዮቹን በቀበሌ በመለየት ከሚታና ጋዶ ቀበሌ የተፈናቀሉት ከጋዶ ከተማ በስተ ደቡብ ከሰንጎ ያያ ቀበሌ የተፈናቀሉ ከጋዶ ከተማ በስተ ምስራቅ ቦታ በማዘጋጀት ፕላን እና ካርታ ተሰርቶ ለአንድ አባ ወራ 250 ካሬ ለ200አባወራ የወረዳው ቤተክህነት የወረዳው አስተዳደር የዞን እና የክልል ተወካዮች በተገኙበት የቦታ ርክክብ ተፈጽሞ ለህዝቡ በእጣ ተከፋፎሎ ጌዜያዊ ካርታ ተሰቶአል"በማለት በገጹ ላይ የፖሰተው ነው። እዚህ ጋር ሁለት ነገር ልብ እንበል
1) ዜናው "ምዕመናን" እንጂ ኦርቶዶክሳውያን አይልም።ኦርቶዶክሳውያን አልተገደሉም አልተፈናቀሉም ለማለት ሆን ተብሎ የተሸረበ ሴራ ነው።
2) የእስልምና እምነት ተከታዮች ከሌላ ቦታ ተመልምለው መጥተው ከስደተኞች ኦርቶዶክሳውያን ጋር እንዲቀላቀሉና ፊት ተቀምጠው ፎቶ እንዲነሱ ተደርጓል። እውነታው ግን ከሦስት ቀበሌዎች ማለትም ከሚታና ጋዶ ቀበሌ ፣ከሰንጎ ያያ ቀበሌና ና ከሶዲ ሳዴ ቀበሌ ቤታቸው ፈርሶ ወደ ጎረቤት ወረዳ በ በቆጂ ከተማ የተሰደዱት 100% ኦርቶዶክሳውያን ናቸው። ይኽን ማስረጃ ማቅረብ እችላለሁ።
ሀ) ከሚታና ጋዶ 118 አባወራዎች (667 ኦርቶዶክሳውያን)
ለ) ከሰንጎ ያያ 65 አባወራዎች (ወደ 322ኦርቶዶክሳውያን)
ሐ) ከሶጂ ሳዴ 273 አባወራዎች( ከ1500 በላይ)።
ቤታቸውን ያሰረሱት ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ወሀቢያዎችና ሙሉ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ነው። ልብ በሉ ይኽ ሁሉ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በወረዳው ውስጥ ካሉ 37 ቀበሌዎች በሦስቱ ቀበሌዎች ብቻ ነው ሌሎች የተቀሩ 34 ቀበሌዎችን አያካትትም።ከመስከረም 5/2018ዓ.ም እስከ ጥቅምት 2018ዓ.ም ብቻ የተፈጸመ ነው።በጥቃቱ ምክንያት የተፈናቀለ አንድም ሙስሊም የለም።ከፊት የተቀየጡት ሙስሊሞች ለፕሮፖጋንዳ ተመርጠው የመጡ ናቸው።በዚህ የሴራ ቅንብር ውስጥ የውስጥ የክልል፣የዞንና የወረዳ ባልሥልጣናት ተሳትፈውበታል።ጥቃቱን የሚመራው የመንግሥት መዋቅር ነው የምንለው ለዚህ ነው።
እንባቢው ያስተውል!!!
👉በእዚህ የ ኦርቶዶክሳውያንን ፍጅት የመካድ ሴራ ውስጥ ከፌዴራል እስከ ወረዳ ድረስ ያለው የመንግሥት መዋቅር ተሳታፊ ነው፣የ ኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተሳታፊ ነው፣የኦሮሚያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተሳታፊ ነው፣አባ ገዳዎች ተሳታፊ ናቸው።
👉 በአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚደረገው ፍጅት የሚቆመው ኦርቶዶክሳውያን በኅብረት ቆመው ራሳቸውን መከላከል ሲጀምሩ ብቻ ነው።
https://t.me/Eyo21e
Repost from ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)
እንዴት በፍጥነት በሚያስደነግጥ መልኩ ኦርቶዶክሳዊነት እየተዳከመ ቤተክርስቲያን እየፈራረሰች መኾኑን ሊረዳ የሚችል ሰው በጣም ጥቂት ነው። ለዚኽ ነው ለብዙዎች እየኾነ ያለው ግድ የማይሰጠው። ጠፍራችን ሲበቅል፣ ቁመታችን ሲጨምር፣ ውፍረት ስንጨምር፣ ጠጉር ሲሸብት ሂደቱ አይታይም። ወፍረን፣ ሸብተን ፣ ጥፍራችን አድጎ ነው የምናየው። ውጤቱን ነው የምንገነዘበው።
ቤተክርስትያንም እንዲያ ነው እየኾነች ያለው። ለውጡን የሚያውቁት አድራጊዎቹና ጥቂት ንቁ የተደረገባቸው ብቻ ናቸው።
ቤተክርስቲያን ውስጥ ኹሉም በዝምታ እንደውም በዝማሬ ለሽ ብሎ ያለው ዙሪያው እየኾነ ያለው አያስደነግጠውም። እንደም በሚቆጩና በሚደነግጡ ሰዎች ይበሳጫል። ዝም አትልም ወይ? አርፈኽ አትቀመጥም ወይ ያሉሃል።
ግድ የለም ደንግጡ፣ በምታዩት በምትሰሙት ደንግጡ በፍጥነት ነው እየጠፋን ያለነው። ጥፋቱ የማይስተካከል ይኾናል። ባሕል አስተሳሰብ ትውፊት ሥነ ልቡና ሥነ ምግባር ኹለ ነው እየተለወጠ ያለው።
ንዋይ ካሳሁን
• እፎይ ምን ይጠየቅ…?
"…ሰላም ተወዳጆች ሆይ…
"…በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዛሬ ምሽት 1:00 ሰዓት ላይ የዘመድ ቴቪ በሳምንታዊው "ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር" መርሀ ግብር ላይ ወንድም እፎይን በእንግድነት ጋብዞ ወደ እናንተ ያቀርባል።
"…መርሀ ግብሩን ሚልዮኖች
• በዘመድ ቴቪ በቴሌቭዥን
• በ zemedtv.com ዌብሳይት
• በዘመድ ቴቪ ራምብል
• በዘመድ ቴቪ ትዊተር (×) ሚልዮኖች ይከታተሉታል።
"…ከዚህ በተጨማሪም ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያና የዘመዴ ቲክቶክም በቀጥታ ስርጭቱን ያስተላልፋሉ።
• እርስዎም ማንም ይሁኑ ማን በሃይማኖትዎ እስላም፣ ካቶሊክ፣ ፕሮቴስታንት፣ ኦርቶዶክስ የፈለጉትን ይሁኑ ብቻ ለወንድም እፎይ ቢቀርብልኝ የሚሉት ጥያቄ ካለ ከአሁን ሰዓት ጀምሮ በአዲሱ የእጅ ስልክ ቁጥሬ +4915216158791 ኋትስአፕ ላይ በመጻፍ መጠየቅ ይችላሉ።
• መጠየቅ ያደርጋል ሊቅ ‼
• ስምምነ …?
+4
የኦርቶዶክስን እናጥፋ😭 ዘመቻ በወላይታ ዞን ቦሎሶ-አረካ
#በሰሞኑ እንደታዘብኩት የወላይታ ቦሎሶ ወረዳ ያሉት የኦርቶዶክስ አቢያተ-ክርሰቲያናት ላይ ለይቶ የማጥቃትና የማጥፋት ዘመቻ በወረዳው እና በከተማ መንግስት በቀጥታ በመዋቅር ደረጃ ተወሰኖ እየተሰራ መሆኑ በግልጽ እየታየ ይገኛል።
#ማሳያዎችን እነሆ ፦
1ኛ= የቦሎሶ ሶሬ ወረዳ፦ የጋራ ጎዶ ጫላ አቡነ ተክለሐይማኖት ቤተክርስቲያን በቀጥታ ይፈረስ ውሳኔ!
2ኛ= የመፍትሄ ጥያቄ ለመጠየቅ ወደ ዞን አስ/ር ለመሄድ የጋራ-ጎዶ ማዘጋጃ ከመናሪያና መውጫ እንዳያገኙ መከልከላቸው፤ እና በአረካ ከተማ እንዳያልፉ በፖትሮል መንገድ ዘግተው መከልከላቸው ??
3ኛ= በቅርቡ አቹሪ አቦ ላይ ያለ ሁከት ሁከት በመፍጠር የወረዳው ፖሊስ ካህናትን ከመቅደሱ አውጥቶ እንደ #እባብ ስቀጠቅጡ እና ከ30 በላይ ምዕመናንን ያለ ጠያቂ አስረው ማሰቃየታቸው ??
4ኛ=የአረካ ከተማ፦ በቁጥር ከ80 በላይ አባወራ ኦርቶዶክሳዊያን ከአምልኮተ እግዚአብሔር ተልይቶ ላልተወሰነ ጊዜ እንድቆዩ ትዕዛዝ መስጠቱ እና ከ2006 ዓም በፍት #በስጦታ ባገኙት ይዞታቸው ላይ የሰሩትን መቃኞ መቅደስን በማፍረስ በአረካ ፖሊስ ጣቢያው ላይ ማኖራቸው እና ለመጠየቅ የሄዱትን ካህናትን እና ምዕመናንን ጭምር አስሮ ማንገላታታቸው የዘመቻው አካል ነው።
#እሺ የት እንሂድ ?? የማይታወቅ የተሰወረ ነገር የለም
አስታውስ ‼️ኦርቶዶክስንክስን ንቆ ሌላውን አንጥልጥሎ የሚኖር ሰላም የሚገነባ ሀገር የለም‼️ተዋህዶን እያሳደድክ በስልጣን ለመቆየት ማሰብ የድኩማን ሀሳብ ነው።
#Nuna Awude Gakkanawu Yedettutee
#የወረዳው እና የከተማው መንግስት ሆይ እስከ መቼ ድረስ ታሳድደናለህ ??
ከ ወለተ ሳራ ገጽ
👆ኦርቶዶክስ በአራቱም አቅጣጫ እንዲህ ይጨፈጨፋል።ግን መቼ ይሆን የምንነቃው?መቼ ይሆን የሚገባን?ይልቁኑ ኦሮሚኛው ተናጋሪው ኦርቶዶክስ።
" ከዚህ ቀደም ብዙ ተፈትነን ነበር። የአሁኑ ሆኖ የማያውቅ አሰቃቂ ነው " - ነዋሪ
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረጃርሶ ወረዳ ታጣቂዎች ሰሞኑን በፈጸሙት አዲስ ጥቃት አባት እና ልጅን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ሲገደሉ የስድስት ቀበሌ ቤቶች መቃጠላቸውን፣ በርካታ ከብቶች መዘረፋቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
አንድ ነዋሪ በሰጡን ቃል፣ "በወረዳው ሸንኮራ ቀበሌ በሸኔ ታጣቂዎች ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ/ም አራት ሰዎች ሲገደሉ፣ አንዲት እናት ቆስላ በህክም ትገኛለች። 100 ኩንታል እህል ወድሟል። 150 የቀንድ ከብት ተዘርፏል። 150 የንብ ቀፎ ተቃጥሏል" ብለዋል።
"ሰዎች ታፍነው ተወስደዋል። በቁጥር አልታወቁም። አንድ፣ አንድ ሚሊዮን ብር ከፍለው የተለቀቁም አሉ። በዚህ ሳምንት ብቻ ከስድስት ቀበሌ በላይ ንብረት ወድሟል፣ ከብት ተዘርፏል" ሲሉም ተናግረዋል።
"ይሄ ነገር የተጀመረው ከአምስት አመት በፊት ነው። ቀበሌው ላይ ከአምስት አመት በፊት 17 ሰዎች ገድለው፣ ዘርፈው፣ ቤት አቃጥለዋል። በየጊዜው እየመጡ ሁለት፣ ሦስት ሰዎች እየገደሉ፣ እያፈናቀሉ ሙሉ ቀበሌውን አፈናቅለውታል" ነው ያሉት።
"ሸኔዎች ናቸው እንደዚህ የሚያደርጉት" የሚሉት ነዋሪው፣ "ከ15 ቀበሌዎች በላይ አፈናቅለው ገድለው ጨርሰዋል። ሁሉም ተፈናቅሎ ነው ያለው። የወረዳውም የዞኑም አካላት ያውቁታል" በማለትም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
"ይህንን ለማስቆም ህብረተሰቡ ተደራጅቶ ራሱን እንዲከላከል ተጠይቋል። ግን መፍትሄ አልሰጡም" ሲሉ የጉዳዩን አሳሳቢነት ገልጸው፣ የሚመለከተው አካል ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
ሌላኛው መረጃ አቀባይ፣ "ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ/ም በተፈጸመው ጥቃት አራት ሰዎች ተገድለዋል፤ ሁለቱ አባት እና ልጅ ናቸው። አንዲት ሴት ተመትታለች። ሦስት ህፃናት የያዙ ሰዎች ከነልጆቻቸው ተወስደው በኋላ ገንዘብ ተከፍሎ ተለቀዋል" ሲሉ ነግረውናል።
"ከዚህ ቀደም ብዙ ተፈትነን ነበር። የአሁኑ ሆኖ የማያውቅ አሰቃቂ ነው። ከ100 በላይ ከብቶች ተወስደዋል። በቀበሌው የነበሩ ቤቶች ሲቃጠሉ ጭሱ እየጎነነ በሰማይ ተገናኘ። ከ40 እስከ 50 የሚሆኑ ቤቶች ተቃጥለዋል። ህዝቡ ተፈናቅሎ ወደ ጎሀፂዮን ገብቷል" ነው ያሉት።
የእነዚህኑ ነዋሪዎችን ሀሳብ የተጋሩት ሌላናኛው መረጃ አቀባይ፣ "ቤቶች ተቃጥለዋል። ቀበሌው ውስጥ አንድ የቀረ ሳር ቤት የለም። ከ40 በላይ ቤቶች ተቃጥለዋል" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በሸንኮራ ቀበሌ ሚያዚያ 27 ሁለት ሰዎች፣ ሚያዝያ 30 ቀን 2014 ዓ/ም አራት ሲገደሉ፣ ሰሞኑን ብቻ በወረዳው በስድስት ቀበሌዎች ቤቶች መቃጠላቸውን የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ ህዝቡ ተፈናቅሎ ችግር ላይ በመውደቁ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ደረሰ ለተባለው ጥቃትና የተፈናቃዮች የመፍትሄ ጥያቄ የአካቢውን ባለስልጣናት ምላሽ ለማካተት ያደረገው ጥረት ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ ጥረቱ ይቀጥላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
siyaasa mootummaa bilxiginnaa kana irratti ortoodoksii maal argate?
👉 amanta ortoodoksii kan amarati jechuun ummata beekumsa hin qabne gara amanta biroo dhibuu
👉 ajjeechaa sababa amanta isaanif arsiiitti,harargeetti, jimmatti, sumaaleetti
👉 qabeenya mana amantaa kana akka lafa qonna,
lafa magaala samuu
👉garee ummuun amantoota walitti naquu fi wal jibbisiisuu
👉 namoota ciccimoo ortoodoksii hidhuufi biyya baasuu
👉warroonni amanta biroo akka ortoodoksii jibbani irratti hojechu
marree ortoodoksii mootummaa kana irraa maal argate?
@ChristianNetwork
ኦሮሚኛ ተናጋሪ ወንድሞችና እህቶች ጓደኞቻችሁን ወደዚህች ቻናል ጋብዟቸውና ሕዝቡን እናንቃው ።ቋንቋውን የሚችል ከሌለ ወደ ኦሮሚኛ በመተርጎሞ ጊዜየን ማቃጠል አልፈልግም።
https://t.me/rete14
በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚደረገው፦
👉 የጅምላ ግድያ
👉 የጅምላ ማፈናቃል
👉 የስም ማጥፋት
👉ማኅበራዊ መገለል
👉 ከሥልጣንና ከሥራ መገለል
👉ማደህየት
👉 ቤተ መፍረስ
👉እስር
👉 ከሀገር ማባረር፦
፩ ከተራ ወንጅል ያለፈ ነው
፪ ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ግብ ያነገበ ነው
፫ መንግሥታዊ መዋቅር ሽፋን የሚሰጠው ነው
፬ በማንነት ላይ ያነጣጠረ፦የዘር ማጥራት(Ethnic Cleansing)ተብሎ በዓለም ዓቀፍ ህግ የተፈረጀው የጥፋት ዓይነት ነው።
https://t.me/rete14
+1
የቤተ ክህነት ሰዎች የሰው ፓርቲ አድማቂ ከሚሆኑ የራሳቸውን ፓርቲ ቢመሠስርቱ ይሻላቸዋል ባይ ነኝ😜
