Haala Ilaalcha Ortodoksii(ኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ)
Відкрити в Telegram
Waa'ee Mana Kiristaanaa Fi Biyya Keenyaa Haala Ilaalcha Ortodoksiin Hubachuu የቤተክርስቲያናችንና ሀገራዊ ሁኔታዎችን በኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ መረዳት
Показати більшеКраїна не вказанаКатегорія не вказана
273
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1330 день
Архів дописів
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
"የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ" በእውነት ሚዛን
"የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ " ፦ቤተ እምነቶችን የፖለቲካ ማብሳያ ምድጃ ለማድረግ፣
ታላቋን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም በጸረ ኦርቶዶክስ ፖለቲከኞች ዘንድ ታስቦበት የተቋቋመ ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን፣የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት፣የኢትዮጵያ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን፣የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ፣መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን እና የዋቄፈና እምነትን በአባልነት ይዟል።
ይኽ ተቋም ጸረ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሆኑን ፦ የተመሠረተበት ዓላማ ተብለው የቀረቡት ነጥቦችና በመሬት ላይ እየሆነ ያለው የሰማይና የምድር ያክል መራራቁን ማስረጃ እንደ ማሳያ ማቅረብ ይቻላል።
"የተመሠረተበት ዋና ዋና ዓላማዎች ?"
1. የሃይማኖት ነፃነትንና እኩልነትን ማስከበር
ሀ)በሀገሪቱ በሕገ-መንግሥቱ የተደነገገው የሃይማኖት ነፃነትና የእኩልነት መብት በተግባር እንዲከበር መሥራት።
👉 በተግባር ሲመዘን፦ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እንደ ተቋም በ እስልምና የወሀቢያ ዑዝታዞች በጴንጤ ወጠጤዎች ስትሰደብ ነጻነት ሲጊፉ ይኽ ተቋም ከተመሠረተበት ጀምሮ አንዳች ቀን አልተናገረም በመግለጫም አላወገዘም
ለ) በመንግሥትና በሃይማኖት ተቋማት መካከል ያለው ግንኙነት ጤናማ፣ ሕጋዊና አንዱ በሌላው ጣልቃ የማይገባበት (የዓለማዊነት/Secularism መርህን የጠበቀ) እንዲሆን መሟገት።
👉በተግባር ሲመዘን፦ መንግሥት የፓርቲውን አርማ ሃይማኖታዊ አርማ(የፕሮቴስታን) ሲያደርግ፣ ኦርቶዶክስን በጠላትነት ሲፈርጃት፣ለብልጽግና አትመቸም እያለ ሲከሳት፣አ ሲኖዶሷን ከፍፍሎ የራሱን ሰዎች ሲያስቀምጥ፣በመዋቅሮችዋ ውስጥ የደኅንነት አካላትን ሲሰገስግ አንዳች ቀን መንግሥትን አልተወሙም ።
2. የሰላም ባህልን መገንባትና የጋራ እሴቶችን ማሳደግ
ሀ) በኢትዮጵያ ውስጥ ለዘመናት የኖረውን የሃይማኖቶች መቻቻል፣ መከባበርና ተስማምቶ የመኖር (Co-existence) ባህል መጠበቅና ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ።
👉በተግባር ሲመዘን፦ የኦርቶዶክሳውያንን ትዕግሥት የሚፈታተኑ የእምነት ትንኮሳ ሲፈጸም አልተቃወመም እንደውም ከአጥፊዎች ጎን ተሰልፎ ቤተ ክርስቲያንና ልጆችዋን ይከሳል።
ለ) በተለያዩ እምነቶች መካከል ያሉትን የጋራ ማኅበራዊና ሥነ-ምግባራዊ እሴቶች (እንደ በጎነት፣ ታማኝነት፣ ፍቅርና ርኅራኄ) በጋራ ማጎልበት።
👉በተግባር ሲመዘን፦ የኦርቶዶክስ እሴት፣ባህል፣ታሪክ በጠላትነት ሲፈረጅ ተቋሙም ተባባሪ ነው።
3. ግጭቶችን በውይይት መከላከልና መፍታት
ሀ) በሃይማኖት ተቋማት መካከል ወይም በሕዝቦች መካከል አለመግባባቶች ሲፈጠሩ ወደ ግጭት ሳይቀየሩ በቅድመ-መከላከል ሥራዎችና በውይይት (Dialogue) መፍታት።
👉በተግባር ሲመዘን፦ኦርቶዶክሳውያን በኦሮሚያ፣በሱማሌ፣በሐረሪ፣በሲዳማ፣በሥሌጤ፣በአጣዬ ፣በከሚሴ በጽንፈኖች ሲታረዱ፣አቢያተ ክርስቲያናት በእሳት ሲጋዩ አይደርም አይታደግም መግለጫም አያወጣም ቢያወጣም እንኳ መረጃ ያዛባል፣ለመንግሥት ፕሮፓጋንዳ በሚያመች መልኩ ነው የሚያወጣው።
ለ) ግጭቶች በተከሰቱባቸው አካባቢዎች የሃይማኖት አባቶችን ያካተተ የሽምግልና እና የዕርቅ ሥርዓትን በመዘርጋት ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ማድረግ።
👉በተግባር ሲመዘን፦ ለመንግሥት ለሚዲያ ፕሮፓጋንዳ ፣ ኦርቶዶክሱን ለማዘናጋትና የከፋ ጭፍጨፋ እንዲፈጸምበት ይሄዳሉ።ኦሮሚያ ላይ ያለው ኦርቶዶክስ ዘሩ እየጠፋ ያለው በዚህ ተቋም ጭምር ነው። አባላቱ እስከ አርሲ ድረስ ሄደው " ኦርቶዶክስ አልሞተም " ማለታቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው።
4. በአገራዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ መቆም
ሀ) በሀገር ግንባታ፣ በሕዝብ አንድነትና በልማት ሥራዎች ላይ የሃይማኖት ተቋማት የጋራ ድምፅና አቋም እንዲኖራቸው ማድረግ።
👉በተግባር ሲመዘን፦ሀገር ከሚያፈርሱት ሕዝብ ከሚከፋፍሉት ጎን መሰለፍ፣ለሀገር የሚጸልዩትን ለሀገር ዋጋ የሚከፍሉትን ማሳደድ ፣የሀገር ሀብት ሀገርን ከማልማት ይልቅ ለጦርነት ሲውል ለምን ብሎ አልጠየቀም
ለ)እንደ ድህነት፣ ድንቁርና፣ የሥራ አጥነት እና ማኅበራዊ ቀውሶች ያሉ አገራዊ ፈተናዎችን ለመዋጋት ተቋማዊ አቅምን አስተባብሮ መንቀሳቀስ።
👉 በተግባር ሲመዘን፦ 72% በላይ የትዮጵያ ሕዝብ በድህነት ሲሰቃይ፣ የትምህርት ተቋማት የወታደር ካምፕ ሲሆን፣ትውልዱ ሥራ አጥቶ ተስፋ ቆርጦ ከሀገር ተሰዶ የቀይ ባሕር ሲሳይ ሲሆን ፣በሊቢያ በየመን በረሆች የአሞራ ቀለብ ሲሆን አንዳች የመፍትሔ አቅጣጫ አላስቀየጠም
5. የሰብአዊ መብቶችና የአካባቢ ጥበቃን መደገፍ
ሀ) የሰውን ልጅ ክብርና መብት ማስከበር፣ የሴቶችና የሕፃናት ደኅንነት እንዲጠበቅ ማስተማር።
👉 በተግባር ሲመዘን፦የሰው ልጅ ክብር ከቢንቢና ከበረሮ አንሶ ቁልቁል ሲሰቀል፣ኦርቶዶክሳውያን ከተገደሉ በኋላ እሬሳቸው በእሳት ሲቃጠል፣እሬሳቻቸው ለውሾች ሲሰጥ፣ነፍሰጡር ሴቶች ሆዳቸው ተሰንጥቆ ሆዳቸው ሲቀደድ፣ህጻናት የቆንጀራ መለማመጃ ሲሆኑ፣በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ህጻናት በየካምፑ በረሃብ ሲገረፉ አንዳች ቀን ርህራሄ አሳይቶ አያውቅም።
* ከተፈጥሮ ጥበቃና ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚመጡ ችግሮችን ለመከላከል ማኅበረሰቡን በሃይማኖታዊ አስተምህሮ ጭምር ማነቃቃትና ለአካባቢ ጥበቃ ማሰለፍ።
👉በተግባር ሲመዘን፦ ሰው ካለቀ በኋላ የሐዘን መግለጫ ማውጣት
****
አንባቢው ያስተውል
♣️ይኽ ተቋም ሥርዐቱ ኦርቶዶክስን ለመምታት የሚጠቀምበት በትር ነው
♣️ኦርቶዶክስን ወክሎ ተቋሙን የሚመራው "ቄስ?"ታጋይ ታደለ ፍትፍት ለመብላትና እንደ ባቄላ ንፍሮ የሚዘገን ገንዘቧን ለመጠቀም እንጂ በኦርቶዶክሳዊነት የማያምን የሞርሞን(ሞርሞንዝምን) እምነት በኢትዮጵያ ምድር እያስፋፋ ያለ ሰው ነው።ለዚህ ነው ኦርቶዶክስን አምርሮ የሚጠላት።
♣️ኦርቶዶክሳውያን ከዚህ ጸረ ኦርቶዶክስ ተቋም የሚተላለፍ የትኛውንም መልእክት መቀበል የለብንም
♣️የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከዚህ ተቋም ራሷን ማግለል አለባት
♣️ተቋሙ ኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈጸሙ ጭፍፋዎች ሁሉ ተባባሪ መሆኑን ለትውልዱ ማስረዳት የፍትሕ ቀን ሲመጣ ደግሞ በዘር አጥፊነት ሊጠየቅ ይገባል።
https://t.me/Eyo21e
አባቶቹ አጥንታቸውን ከስክሰው ደማቸውን አፍስሰው ነፍሳቸውን ገብረው ያቆዩለትን ሀገር ከላይ ሆኖ መምራት ሲገባው የሩቅ ተመልካች ሆኖ በጅምላ እየተገደልና እየተሰደደ " እግዚአብሔር የተሻለ ፓርቲ ያምጣልን፣እመቤቴ የተሻለ ፓርቲ ታምጣልን .. እያለ ስንፍናንና ፍርሃትን እንደ በመንፈሳዊነት የሚቆጥር የመከነ ትውልድ።
Repost from Haala Ilaalcha Ortodoksii(ኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ)
ይኽችን ቻናል ተባብረን እናሳድጋት።ጥቅሙ ለእኔ ሳይሆን ለቤተ ክርስቲያን ነው። በምትጠቀሙት ሚዲያ ሁሉ ሊንኩን አጋሩት።ቢያንስ 1k እናስገባት።ከሁሉም በላይ ኦሮሚኛ ተናጋሪው ቢገባና በሃይማኖቱ ላይ ምን እየተካሄደ እንደለ ቢረዳ የመከራ ቀኖቻችንን ያሳጥረዋል።
https://t.me/rete14
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
+1
በባለሥስጣናቱና በካድሬዎች ምላስ ላይ፣በድጅታል የሚዲያ ሠራዊት ስልክ ላይ፣በ ኢቲቪ፣በፋና፣በAMN፣በOBN፣በEOTC Tv ፣በአሚኮ...ላይ ያለችቱ "ምናባዊት ኢትዮጵያ"በ10.2% ያደገች ሲሆን በመሬት ላይ ያለችው ኢትዮጵያ ግን 72% የሚሆኑ ሕዝቦችዋ በድህነት የሚሰቃዩ ዳቦ ወርቅ የሆነባቸው ናቸው። ለዚህ ነው መግባባት ያልቻልነው የእኛ እና የእነርሱ ኢትዮጵያ ይለያያሉና።
Repost from ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት
✅በቋንቋ፦ የጠፋውን ትውልድ በቋንቋ መመለስ ለቤተክርስቲያን አሁናዊም ትናንትናዊም ነጋዊም ተልዕኮዋ ነው።
✅በቋንቋ፦የተመረዘውን የትውልድ አእምሮ በቋንቋ መመለስ.................
✅በቋንቋ፦ የተከፋፈለውን ትውልድ በቋንቋ አንድ ማድረግ............
✅በቋንቋ፦ የጥል ግድግዳ የገነባውን ትውልድ የጥሉን ግድግዳ በቋንቋ ማፍረስ........
✅በቋንቋ ፦ ከሃይማኖት ማማ ዝቅ ያለውን ትውልድ በቋንቋ ከፍ ማድረግ......
✅በቋንቋ የደነዘዘውን አእምሮ በቋንቋ መክፈት .......
✅በቋንቋ የተዘጋውን ጆሮ በቋንቋ መክፈት........
✅በቋንቋ የተበሻሸቀውን ትውልድ በቋንቋ ማዋሐድ......
✅በቋንቋ የተቋጠረውን ልቡና በቋንቋ መፍታት.......
✅በቋንቋ የተዘጋችዋን ቤተክርስቲያን በቋንቋ መክፈት....
✅በቋንቋ የሻከረውን ልቡና በቋንቋ ማለስለስ.......
✅በቋንቋ የታመመውን ትውልድ በቋንቋ ማከም ለቤተክርስቲያን ትናንትናዊም ዛሬያዊም ነጋዊም ተልኮዋ ነው ዓላማዋም ነው።
✅የቋንቋ ርኩስም ቅዱስም የለውም።
በቋንቋ ምክንያት ርኩስና ቅዱስ ሰው ግን ሊፈጠርበት ይችላል።
✅የቋንቋ ጻድቅም ኃጥዕም የለውም።
ቋንቋን ምክንያት ግን ኃጥዕም ጻድቅም ሊፈጠር ይችላል።
✅ሰይጣናዊም መንፈስ ቅዱሳዊም ቋንቋ የለም።
በቋንቋ ምክንያት ሰይጣናዊና መንፈስ ቅዱሳዊ ሰው ግን ሊፈጠር ይችላል።
✅የቋንቋ ትልቅም ትንሽም የለውም።
ቋንቋን ምክንያት በማድረግ አንዱን ትንሽ አንዱን ትልቅ የሚያደርግ ሰው ግን ይኖራል።
✅የቋንቋ ደግም መጥፎም የለውም።
በቋንቋ ምክንያት ደግና መጥፎ ሰው ግን ሊፈጠር ይችላል።
👉ቋንቋን ለተቀደሰ ነገር መጠቀም ግን ቅዱስነት ነው።
በቋንቋ የምትወረስ መንግሥተሰማያትም የለችም።
👉አሁን ላይ የቤተክርስቲያን ታላቁ ፈተናዋ ቋንቋ ነውና በቋንቋ የመጣባትን ፈተና በቋንቋ ለማስወገድ የተለያየ ቋንቋ የሚችሉ ኦርቶዶክሳውያንን ማስተማር ይገባል።
ይህንንም ችግር ለመፍታት ጉባኤ ቤታችን ምሥራቀ ጸሐይ ከተለያዩ ብሔረ ሰቦች ደቀመዛሙርትን እያመጣ በቋንቋ ያስተምራል።
👉ነገር በነገር ይመለሳል እሾኽ በእሾኽ ይነቀሳል እንዲሉ አበው።
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
እውነት መራራ ናት!!!
ከትናንት ወዲያ "የብልጣብልጦች ቢዝነ በ ቤተ ክርስቲያን"የምትል ጽሑፍ ማጋራቴ"የሚታወስ ነው። ብዙዎች ሲንጫጩ እየተመለከትሁ ነው።
፩ የጽሐፌ ዋና ዓላማ አስተዳደራዊ በደልን ማጋለጥ እንጂ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እንከን አለባት አላልሁም አልወጣኝም ።ሃይማኖቴ እንከን የለባትም ራሷ ክርስቶስ ነውና።
፪ አንዳንዶች ጽሑፉን የጻፈው መናፍቅ ነው ይላሉ።የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳራዊ ሥርዐት ይስተካከል፣ቤተ ክርስቲያን የቁሳውያን አካላውያን ስብስብ መሆን የለባትም ማለት ምንፍቅና ነው እንዴ?
፫ በቁጥር "፬" ላይ ስለ ታቦት መደራረብ ያነሳሁት አሳብ ከአቢያተ ክርስቲያናት መስፋፋት ጋር የሚገናኝ ሳይሆን በአንድ ደብር ላይ ስለሚደራረቡ ጽላቶች ነው።ለምሳሌ በአንድ ደብር እስከ 6 እና 7 ጽላቶች ከዚያም በላይ ይደራረባሉ።የቅዱሳኑ ፍቅር በትክክል ገብቶን ቢሆን እኮ ጥሩ ነው ችግሩ እኛ ብር ማግኛ ምስኪኑን ሕዝብ ማታለያ አደርገነው።
፬ ብዙዎች አባትን አትናገር ይላሉ? የተሳሳተን ሰው ስሕተቱ ካልተነገረ እትዴት ነው የሚስተካከለው? ጳጳሳቱን የማይሳሳቱ አድርጎ ማሰብ ካቶሊካዊነት ነው።ካቶሊካውያን ፖፑ አይሳሳትም ብለው ነው የሚያምኑት።በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ የማይሳሳተው እግዚአብሔ ብቻ ነው። ሰው የእግዚአብሔር ማደሪያ ቢሆንም በራሱ ፍላጎት መጓዝ ሲጀምር ይሳሳታል።
፭ ለምን ወደ አደባባይ ታወጣላችሁ እዚያው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አትወያዩም ወይ? ለምትሉ፦ መዋቅሩን የተቆጣጠሩ ሰዎች ከውስጥ ሆነው ቤተ ክርስቲያንቱን ለማዳከም የተላኩ ፣ ገሚሶቹ በውይይትና በአሳብ ልዕልና የማያምኑ አላዋቂና ደካሞች ስለሆኑ ነው።ስለዚህ ሕዝቡ ቤተክርስቲያኑን ከእነዚህ ግሪሳዎች እንዲጠብቅ መቀስቀስ ግድ ይላል።
፮ ዝም በሉ አትናገሩ ምን አገባችሁ? የሚሉ ጮኸቶች ቁጥራቸው ቀላል አይጀለም፦ በ ቤቱ ጉዳይ የማያገባው አባወራ አለ ወይ? ቤተ ክርስቲያን የጥቂት ሰዎች ብቻ የግል ንብረት አይደለችም በክርስቶስ ክርስቲያን ለተሰኘን ሁሉ የጋ ራ ርስታችን ናት።የካህናትና የምዕመናንን ኅብረት ናት።መጽደቂያችን ናት።አያገባችሁም የምትሉን እናንተ እነ ማን ናችሁ?
፯ እያወራን ያለነው ስለግለሰቦች የግል ኀጢአት አይደለም ሆነ ተብሎ ታስቦበት ቤተ ክርስቲያንቱን ለማዳከም ስለሚደረገው መዋቅራዊ በደል ነው።በግል በምንም ላይ የመፍረድ ሥልጣን የለኝም አልተሰጠኝምም።
መፍትሔው ምንድን ነው?
👉 በጭፍን ከመደገፍና ከመቃወም ወጥተን ማያ መለኪያችን የ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ይሁን።
👉ቤተ ክርስቲያን ፍትፍቷንና ገንዘቦችዋን እንጂ እርስዋን በማይወዷት ሰዎች እጅ ላይ መውቋን ማወቅ መረዳት ላላወቁት ማሳወቅ ላልተረዱት ማስረዳት
👉ገንዘባችንን እንጂ እኛን የማያፈልጉ ምንደኛ እረኞችን አለመከተል አለመታዘዝ ።እውነተኞችን አይመለከትም።
👉 ቤተ ክርስቲያን እያለ አዲስ ቤተ ክርስቲያን ለሚሠሩ ፣የህንጻ ውድድር ላይ ለተጠመዱት አቢያተ ክርስቲያናት ምንም ዓይናት መዋጮ አለመስጠት።በዚያ ፈንታ በገጠር በእናቶች ቀሚስ ለሚቀድሱ፣ጧፍ ለሌላቸው መስጠት፣ጉባኤ ቤቶችን መርዳት፣የተቸገሩ ጎረቤቶቻችንን ማገዝ።ተመርቀው ሥራ ላጡ ወጣቶች ሥራ መፍጠር ወዘተ...።የሚያጸድቀን ይኽ ነው።ዘሪፊዎችን መቀለብ አያጸድቅም።
👉መዋቅሮቻችንን የተቆጣጠሩ በመንደርና በዘመድ የተደራጁ አቅመቢሶችን እና ዘራፊዎችን ጠራርጎ ማስወጣት እውነተኛ ሊቃውንትን ወደ ፊት ማምጣት
https://t.me/Eyo21e
መንግሥታት ሕዝብን ሲጨቁኑ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ሚና ምንድን ነው?
3. ለተገፉት መጠጊያና ከለላ መሆን
መንግሥታት ሕዝብን በሚያሳድዱበት ጊዜ፣ የአባቶች ሚና ቤተ ክርስቲያንንና ገዳማትን የፍትሕ ሉዓላዊ ቦታዎች ማድረግ ነው። ተበድሎ የመጣን ሰው ለመንግሥት አሳልፎ አለመስጠት የቤተ ክርስቲያን ጥንታዊ ሥርዓት ነው።
የቅዱሳን አርአያ
አባ አትናቴዎስ፦ መናፍቃን ነገሥታት ኦርቶዶክሳውያንን በሰይፍና በስደት በሚያሰቃዩበት ዘመን፣ ቅዱስ አትናቴዎስ ሕዝቡንና እምነቱን ለመጠበቅ ሲል አምስት ጊዜ ከሃገሩ ተሰዷል። ነገር ግን በስደት ላይ ሆኖ እንኳ ለተጨቆኑት ምዕመናን በመንፈስ አባት ሆኖ ያበረታታቸው ነበር።
የኢትዮጵያ አባቶች አርአያ (የደብረ ሊባኖስ አባቶች)፦ በፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ዘመን፣ የደብረ ሊባኖስ ገዳም አባቶችና መነኮሳት ለአርበኞች (ለነፃነት ለሚዋጉት የሃገር ልጆች) መጠጊያ፣ ስንቅና መድኃኒት በመሆን ከለላ ሆነዋል። በዚህም ምክንያት ጨካኙ ግራዚያኒ ከ400 በላይ መነኮሳትንና ድቁና ያላቸውን ተማሪዎች በአንድ ቀን አስጨፍጭፏል። አባቶቹ ግን ለሕዝብና ለሃገር ነፃነት ሲሉ ሕይወታቸውን አሳልፈው ሰጡ።
4. ለሕዝብ ነፃነት ሰማዕት መሆን
ጭቆናው አይሎ፣ የመንግሥት ኃይል ፍጹም ጨካኝ በሚሆንበት ጊዜ የአባቶች የመጨረሻው ሚና ለሕዝባቸው ፍቅርና ነፃነት ሲሉ ራሳቸውን ለሞት አሳልፎ መስጠት (ሰማዕት መሆን) ነው።
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ሰማዕት)፦ በ1928 ዓ.ም የፋሺስት መሪዎች የኢትዮጵያን ሕዝብ በጭስና በጋዝ እየጨረሱ፣ መሪዎችን በግፍ እየገደሉ በነገሡበት ዘመን፣ አቡነ ጴጥሮስ ለጠላት ሊንበረከኩ አልቻሉም። ይልቁኑ ለሕዝቡ የነፃነት አባት በመሆን "የኢትዮጵያ ሕዝብ ለፋሺስት እንዳይገዛ አውግዣለሁ፤ ምድሪቱም ጠላትን እንዳትቀበል የተረገመች ትሁን" በማለት በአደባባይ በጥይት ተደብድበው ሰማዕትነትን ተቀብለዋል። የእሳቸው መስዋዕትነት ለሕዝቡ የነፃነት ትግል ትልቅ የብርታት ምንጭ ሆኗል።
ማጠቃለያ
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ አስተምህሮ፣ የአባቶች ክህነትና ሥልጣን የተሰጠው "ሕዝብን ለመጠበቅ" እንጂ "ከጨቋኝ መንግሥታት ጋር ለመሻረክ" አይደለም። ስለዚህ መንግሥታት ሕዝብን ሲጨቁኑ የእውነተኛ አባቶች ሚና፦
1. የጭቆናው ተባባሪ ወይም ዝምተኛ አለመሆን፣
2. ከሕዝቡ ጎን መቆም፣ ማልቀስና መጸለይ፣
3. ስለ እውነትና ፍትሕ ሲሉ የነገሥታትን ሰይፍና ግዞት ሳይፈሩ መጋፈጥ ነው።
https://t.me/rete14
ይኽችን ቻናል ተባብረን እናሳድጋት።ጥቅሙ ለእኔ ሳይሆን ለቤተ ክርስቲያን ነው። በምትጠቀሙት ሚዲያ ሁሉ ሊንኩን አጋሩት።ቢያንስ 1k እናስገባት።ከሁሉም በላይ ኦሮሚኛ ተናጋሪው ቢገባና በሃይማኖቱ ላይ ምን እየተካሄደ እንደለ ቢረዳ የመከራ ቀኖቻችንን ያሳጥረዋል።
https://t.me/rete14
መንግሥታት ሕዝብን ሲጨቁኑ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ሚና ምንድን ነው?
2. ግፈኛ መሪዎችን ፊት ለፊት መገሰጽና ማውገዝ
አባቶች የሕዝብ እረኞች በመሆናቸው፣ መንግሥት ሥልጣኑን ተጠቅሞ ሕዝብን ሲጨቁን "ይህ የምታደርገው ግፍ ነው" ብለው የመገሰጽና የሕዝብን መብት የማስከበር መንፈሳዊ ግዴታ አለባቸው።
የቅዱሳን አርአያ፦
ቅዱስ አምብሮስ (የሚላን ሊቀ ጳጳስ)
ቅዱስ አምብሮስ መጀመሪያ የሮም መንግሥት ከፍተኛ አስተዳዳሪ (ገዢ) የነበረና በኋላም ሕዝቡ በነፃ ምርጫ ጳጳስ አድርጎ የሾመው ታላቅ አባት ነው። "መንግሥት በቤተ ክርስቲያን ጉዳይና በምዕመናን ሕሊና ላይ ሥልጣን የለውም" የሚለውን መርህ ያስመሰከረ መሪ ነው።
ንግሥት ዩስቲና (Justina) የአርዮስ ወገን ስለነበረች፣ በቁጥጥሯ ሥር የነበረውን ወታደር ልካ የሚላን ካቴድራል ቤተ ክርስቲያንን በኃይል ልትቀማው ስትሞክር፣ አምብሮስ ከምዕመናን ጋር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በማደርና መዝሙር በመዘመር ወታደሮቹን መክቷል። "የቄሣር የሆነውን ለቄሣር የእግዚአብሔርን ግን ለእግዚአብሔር ስጡ፤ ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ናትና ለቄሣር አትሰጥም" በማለት የንግሥቲቱን ኃይል አሳፍሯል።
ታላቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ በሰሎንቄ ከተማ አመጽ ተነሳ ብሎ 7,000 የሚጠጋ ሕዝብ በጅምላ እንዲጨፈጨፍ ባዘዘ ጊዜ፣ አምብሮስ እጅግ አዘነ። ንጉሡ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሊጸልይ ሲመጣ አምብሮስ በደጃፉ ላይ ቆሞ አገደው። "ንጉሥ ሆይ! እጆችህ በንጹሐን ደም ተበክለዋል፤ እንደ ዳዊት በደልህን አምነህ ንስሐ ሳትገባ ወደ ቅዱሱ መሠዊያ አትቀርብም" አለው። ኃያሉ ንጉሥም በጳጳሱ ፊት ተንበርክኮ፣ አልቅሶና ንስሐ ገብቶ ነው ቅዱስ ቁርባን የተቀበለው።
ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ (የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ)
ቅዱስ አትናቴዎስ "የሃይማኖት ዓምድ" በመባል ይታወቃል። የሮም ነገሥታት አርዮሳውያንን በመደገፍ ኦርቶዶክሳውያንን በግፍ ሲያሳድዱና ሲጨቁኑ፣ እርሱ ግን ለሕዝቡና ለእውነት ብቻ የቆመ እረኛ ነበር።
ንጉሥ ቆስጠንጥዮስ(Constantius) አርዮስን ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲቀበለውና የኦርቶዶክስን እምነት እንዲለውጥ በኃይልና በዛቻ በጠየቀው ጊዜ፣ አትናቴዎስ ፍጹም እምቢ አለ። ንጉሡ "ዓለም ሁሉ ከአንተ ጋር ተጣልቷል" ሲለው፣ አትናቴዎስ "እንግዲያውስ አትናቴዎስ ከዓለም ጋር ይጋፈጣል" (Athanasius contra mundum) በማለት የነገሥታትን ምድራዊ ኃይል ንቆታል።
እምነቱንና ምዕመናንን ከነገሥታት ጭቆና ለመጠበቅ ሲል ለ45 ዓመታት ያህል በጳጳስና ሥልጣኑ ላይ በነበረበት ዘመን አምስት ጊዜ ከሃገሩ ተሰዷል። በስደት ምድረ በዳ ሆኖ እንኳ ለሕዝቡ ማጽናኛና ትምህርት ይጽፍ ነበር። ንጉሥ ዩሊያኖስ ሊገድለው በጦር በፈለገው ጊዜ "ይህችማ የምታለፍ አጭር ደመና ናት" በማለት የጨቋኝ መንግሥታትን ዕድሜ አጭርነት በተግባር አሳይቷል።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ(የቁስጥንጥንያ ሊቀጳጳስ)
በቤተ መንግሥቱ አካባቢ የነበረውን የቅንጦት ሕይወት፣ ፍትሕ ማጓደልና የድሆችን መበዝበዝ በግልጽ ይወቅስ ነበር።በተለይም ንግሥት አውዶክሲያን በኃይልና በግፍ የደሆችን መሬትና ንብረት (የአንዲት መበለት የወይን ቦታ ጨምሮ) እየቀማች ለራሷ ማድረጓን እና በቅድስት ሶፊያ (Hagia Sophia) ካቴድራል አቅራቢያ የራሷን የብር ሐውልት አቁማ ሐውልቱ በተመረቀበት ወቅት የሚደረገው ጭፈራ፣ ጩኸትና አረማዊ ሥነ-ሥርዓት በቤተክርስቲያኑ ውስጥ የሚደረገውን ቅዳሴና ጸሎት በመረበሹ "ሄሮድያዳ በድጋሚ አበደች፣ በድጋሚ ታወከች፣ በድጋሚ ጨፈረች፣ የዮሐንስንም ራስ በወጭት ልትወስድ በድጋሚ ፈለገች..." በማለት አውዶክስያን በቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዘመን ከነበረችው ከሄሮድያዳ ጋር በማመሳሰል ተቃወማት።
ከእነዚህ አባቶች ሕይወት የምንረዳው፦
. ክህነት ለስልጣን አለማጎብደድ፦ ነገሥታት በምድራዊ ሰይፋቸውና በሠራዊታቸው ቢመኩም፣ አባቶች ግን በእግዚአብሔር እውነትና በሕዝብ እረኝነት ስላመኑ አልፈሩም።
2. የመንግሥትና የቤተ ክርስቲያን ወሰን፦ መንግሥት ፍትሕን ሲያጓድልና ሰብአዊ መብትን ሲረግጥ ቤተ ክርስቲያን ዝም ማለት እንደሌላት በተግባር አሳይተዋል።
3. የሕዝብ አባትነት፦ ለምዕመናን ነፃነትና ክብር ሲሉ ስደትን፣ ሞትንና እስራትን በደስታ ተቀብለዋል።
https://t.me/rete14
Yeroo kanatti gochi kun weerartuu alaa waliin kan wal-qabate yoo ta'eyyuu, abbootiin taabotaa fi fannoo qabatanii imala waraanaa dhaabsisuuf yaalii taasisan ifatti agarsiisaniiru.
Taatee:Waraanni Faashistii Xaaliyaanii gara giddu-gala Itoophiyaatti deemaa yeroo turetti, Finfinnee fi naannoo isheetti luboonni fi monoksoonni taabota Qulqulleettii Maariyaamii fi kan adbaaroota biroo qabatanii, fannoo harkaatti qabatanii diina dura dhaabbachuu fi dhumatii uummataa dhaabsisuuf gara fuulduraatti bahan.
👉Cichoommina Abbootii: Diinni alaa akka mootota biyya keessaa taabotaa fi fannoof kabaja kan hin qabne yoo ta'eyyuu, abbootiin garuu gaachana uummataa ta'uuf taabota isaanii qabatanii hamma dallaa dhukaasaatti deemuun mirga namoomaa fi bilisummaa eeguuf dhaabbataniiru.
Abbootiin uummataaf abukaatoo (falmituu) dhaabbachuun isaanii Mana Kiristaanaa Ortodoksii Tawaahidoo keessatti gaggeessitoonni amantii utubaa nagayaa fi dhokata uummataa ta’uu isaanii agarsiisaniiru. Abbootiin kana kan taasisan:
👉Aangoo mootichaa mormuuf osoo hin taane, mootichi seefii isaa osoo hin luqqisin dura namummaa fi murtii waaqayyo akka isa yaadachiisuufi.
👉Eegduu uummataa ta’uu isaanii gochaan agarsiisuufi—eegaan hoolonni isaa osoo hin qalamne dura lubbuu isaa dabarsee kenna waan ta'eef.
Abbootiin Ammaa jirahoo???
Itti fufa.,
https://t.me/rete14
Yeroo Mootummoonni Uummata Cunqursan Gaheen Abbootii Amantaa Mana Kiristaanaa Maali?
Gaheen Abbootii Mana Kiristaanaa Ortodoksii Tawaahidoo (Hangafoonni phaaphaasotaa, lubootaa fi monoksitootaa) yeroo uummatni sabaaba cunqursaa fi jal’ina mootummootaatiin miidhamu Gaheen Isaan taphatan, kallattiin amala Tiksummaa Kiristos irraa kan madde dha. Tikseen dhugaan immoo "lubbuu isaa hoolota isaatiif dabarsee kenna" (Yoh. 10:11).
Adeemsa seenaa keessatti, yeroo mootummoonni uummata cunqursan Gaheen abbootii amantii maal ta’uu akka qabu seenaa qulqullootaan kan mirkanaa’an hojiiwwan gurguddoo afur ilaaluu ni dandeenya:
1. Bulchitoota Duratti Abukaatoo (Falmituu) Uummataa Ta’uu
Gaheen guddaan abbootii mana kiristaanaa Inni guddaanvmootummaa fi uummata cunqursame gidduu dhaabbachuun, dheekamsa bulchitootaa qabbaneessuu fi uummataaf dhiifamaa fi bilisummaa kadhachuu dha. Kana yeroo taasisan kabaja mootummaaf osoo hin taane, eegumsa uummata hiyyeessaa yaadaniiti.
Qulqulloota Fakkeenya ta'an:
Qusxinxiniyaa (Antsookiyaa) keessatti uummatni sabaaba gibirri itti ulfaataateef fincila kaasuun fakkii (siidaa) Mootii Tewodosiyos yeroo cabsetti, mootichi magaalattii guutuu seefidhaan fixuuf dhaadate. Yeroo sanatti hangafni Phaaphaasii maanguddoo kan turan Abbaa Filaaviyaan dhumaatii uummataa dhaabuuf jecha, qorraa fi cabbii keessa deemanii mooticha duratti dhiyaatan. Mooticha dhiifamaa fi murtoo Waaqayyoon amansiisanii magaalattii fi uummata dhumatii jumlaa irraa oolchaniiru.
Abbootii Itoophiyaa፦
Seenaa biyya keenya keessatti mootonni fincilaan ykn gibirri kaffaluu dhiisuun uummata irratti duuluuf yeroo ka'an, phaaphaasonni fi abbootiin gadaamotaa Taabota baasanii, fannoo qabatanii daandii irratti ciisuun "Uummata keenya ajjeesuu dura nu ajjeesaa" jechuun humna waraana moototaa dhaabsisaa turan.
Mootichi hammamiyyuu gara-jabeessa yoo ta'e, kabaja Taabotaa fi Fannoo irra ejjetee darbuun kuffatii mooraalii fi hafuuraawaa waan ta'uuf, loltoonni imala isaanii dhaabuuf ni dirqamu turan. Gochaawwan seenaa kana keessaa fakkeenyonni gurguddoon muraasni kanneen armaan gadiiti:
Abbootii Debra Libaanos:-
Jaarraa 13ffaa fi 14ffaa keessa abbootiin gadaamotaa turan (keessattuu monoksitoonni Gadaama Debra Libaanos) walitti bu’iinsa moototaa fi uummata gidduutti uumamuuf gahee araaraa guddaa taphachaa turan.
Taatee: Mootonni fincilaan ykn gibira kaffaluu dhiisuun uummata waraanuuf waraana isaanii ajajanii yeroo ka'an, abbootiin fannoo fi taabota isaanii qabatanii waraana dura dhaabbatu turan. Mootichaa fi loltootaan "Uummata kana waraanuun Dura isin nuyii fi taabota kana irra ejjettanii darbuu qabdu" jechuun daandii irratti gombifamanii ciisu turan.
👉 Bu’aa Isaa: Waraanni taabotaa fi fannoo arguun meeshaa waraana isaa lafa buusa turan. Kanaanis sabaaba kanaan mootonni waraana dhiisanii uummata waliin marii fi araaraan akka dubbatan dirqamaa turan.
Fakkeenya Araara Seenaa Bara Atsee Bakaafaa (Jaarraa 18ffaa)
Bara mootummaa Gondar, keessattuu bara Astee Bakaafaa (Bara 1713–1723 A.L.H) mootichaa fi uummata gidduutti wal-dhabdeen jabaan ka'ee ture. Mootichi finciltoota adabuuf waraana guddaa ajajee duuluuf ka'e.
👉 gahee Abbootii: Luboonni uummatni jumlaan akka hin dhumatne sodaachuun, taabota baatanii, fakkii qulqullootaa fi fannoo meetii qabatanii bakka mootichi fi waraanni isaa bira darban duratti bahan.
Hojii Isaanii: Luboonni fi abbootiin daandii irratti gombifamanii booyichaa fi kadhannaan "Mootii keenya! Uummata kana kan waraantu yoo ta'e, dura nuyi fi Taabota Waaqayyoo balleessuu qabda" jedhaniin.
Bu’aa Isaa: Atsee Bakaafaa kabaja taabotaa fi kadhannaa abbootii arguun ajaja waraana isaa haqee jira. Waraanaan dhiigni qulqulloota baay’ee dhangala’uuf ture aarsaa abbootii fi kofoo taabotaatiin ooleera.
Weerara Faashistii Xaaliyaanii fi Dhugaa-ba’umsa Hayyoota (Bara 1928 A.L.H)
መንግሥታት ሕዝብን ሲጨቁኑ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ሚና ምንድን ነው?
የኦርቶዶሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች (ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናትና መነኮሳት) ሕዝብ በመንግሥታት ግፍና ጭቆና በሚደርስበት ጊዜ የሚጫወቱት ሚና በቀጥታ ከክርስቶስ እረኝነት ባህሪ የተቀዳ ነው። እውነተኛ እረኛ ደግሞ "ስለ በጎቹ ነፍሱን አሳልፎ ይሰጣል" (ዮሐ. 10:11)።
በታሪክ ሂደት ውስጥ መንግሥታት ሕዝብን ሲጨቁኑ የአባቶች ሚና ምን መሆን እንዳለበት በቅዱሳን ሕይወት የተረጋገጡትን አራት ዋና ዋና ተግባራት ማየት እንችላለን፦
1. በገዢዎች ፊት የሕዝብ ጠበቃ መሆን
የቤተ ክርስቲያን አባቶች ዋነኛ ሚና በመንግሥትና በተጨቆነው ሕዝብ መካከል በመቆም፣ የገዢዎችን ቁጣ ማብረድና ለሕዝቡ ምሕረትንና ነፃነትን መለመን ነው። ይህንን ሲያደርጉ የንጉሡን ክብር ሳይሆን የምስኪኑን ሕዝብ እረኝነት አስበው ነው።
የቅዱሳን አርአያ ፦ በቁስጥንጥንያ (አንጾኪያ) ሕዝቡ በከበደው ግብር ምክንያት አምፆ የንጉሡን የቴዎዶስዮስን ሐውልት በሰበረ ጊዜ፣ ንጉሡ ከተማዋን በሙሉ በሰይፍ ሊያስመታት ዛተ። በወቅቱ የነበሩት አረጋዊው ሊቀ ጳጳስ አባ ፍላቪያን የሕዝቡን እልቅት ለማስቆም በብርድና በበረዶ ተጉዘው ንጉሡ ፊት ቀረቡ። ንጉሡን በምሕረትና በእግዚአብሔር ፍርድ አሳምነው ከተማዋንና ሕዝቡን ከጅምላ ጭፍጨፋ አድነዋል።
የኢትዮጵያ አባቶች አርአያ፦ በሃገራችን ታሪክ ነገሥታት በአመጽ ወይም ግብር ባለመክፈል በሕዝብ ላይ ሊዘምቱ ሲሉ፣ ሊቃነ ጳጳሳቱና የገዳማት አባቶች ታቦት አውጥተው፣ መስቀል ይዘው በመንገድ ላይ በመተኛት "ሕዝባችንን ከምትገድሉ እኛን ግደሉ" በማለት የነገሥታትን የጦር ኃይል ያስቆሙ ነበር።
ንጉሡ ምንም ያህል ጨካኝ ቢሆን፣ የታቦትንና የመስቀልን ክብር ረግጦ ማለፍ የሞራልና የመንፈሳዊ ውድቀት ስለሚሆን የጦር ሠራዊቱ ጉዞውን ለማቆም ይገደድ ነበር። ከእነዚህ ታሪካዊ ክስተቶች መካከል ጥቂቶቹ ዋና ዋና ምሳሌዎች የሚከተሉት ናቸው፦
የደብረ ሊባኖስ አባቶች ምሳሌ፦
በ13ኛው እና 14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩት የገዳማት አባቶች (በተለይም የደብረ ሊባኖስ ገዳም መነኮሳት) በነገሥታትና በሕዝብ መካከል ለሚፈጠሩ ግጭቶች ትልቁን የዕርቅ ሚና ይጫወቱ ነበር።
ክስተቱ፦ ነገሥታቱ በአመጽ ወይም ግብር ባለመክፈል በሕዝብ ላይ ለመዝመት ሠራዊታቸውን ይዘው ሲነሱ፣ አባቶች መስቀላቸውንና ታቦታቸውን ይዘው በሠራዊቱ ፊት ይቆሙ ነበር። ንጉሡንና ወታደሮቹን "ይህንን ሕዝብ ለመውጋት እኛንና ታቦቱን ረግጣችሁ ማለፍ አለባችሁ" በማለት በመንገድ ላይ ይተኙ ነበር።
👉 ውጤቱ፦ ሠራዊቱ ታቦትና መስቀል አይቶ መሳርያውን ይጥል ነበር። በዚህም ምክንያት ነገሥታቱ ጦርነቱን ትተው ከሕዝቡ ጋር በውይይትና በሽምግልና እንዲታረቁ ይገደዱ ነበር።
በዓፄ በካፋ ዘመን የነበረው የታሪካዊ ዕርቅ ምሳሌ (18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን)
በጎንደር ዘመነ መንግሥት፣ በተለይም በዓፄ በካፋ ዘመን (1713–1723 ዓ.ም) በንጉሡና በሕዝቡ መካከል ከባድ አለመግባባቶችና አመጾች ተነስተው ነበር። ንጉሡ አመጸኞችን ለመቅጣት ከፍተኛ ሠራዊት አዝዞ ለመዝመት ተነሳ።
👉የአባቶች ሚና፦ የጎንደር አድባራት ካህናት ሕዝቡ በጅምላ እንዳያልቅ በመስጋት፣ ታቦታትን ተሸክመው፣ የቅዱሳን ሥዕላትንና የብር መስቀሎችን ይዘው ንጉሡና ሠራዊቱ በሚያልፉበት አደባባይ ፊት ለፊት ወጡ።
ድርጊቱ፦ ካህናቱና አባቶቹ በመንገዱ ላይ ተደፍተው በማልቀስና በመጸለይ "ንጉሥ ሆይ! ይህንን ሕዝብ የምትወጋ ከሆነ መጀመሪያ እኛንና የእግዚአብሔርን ታቦት ማጥፋት አለብህ" አሉት።
ውጤቱ፦ ዓፄ በካፋ የታቦቱን ክብርና የአባቶቹን ጸሎት አይቶ የጦር ትዕዛዙን ሰረዘ። በጦርነት ሊፈስ የነበረው የብዙ ንጹሐን ደም በአባቶች መስዋዕትነትና በታቦቱ ከለላነት ተረፈ።
. የፋሺስት ኢጣሊያ ወረራና የሊቃውንቱ ምሥክርነት (1928 ዓ.ም)
ምንም እንኳ ይህ ክስተት ከውጭ ወራሪ ጋር የተያያዘ ቢሆንም፣ አባቶች ታቦትና መስቀል ይዘው የሠራዊት ጉዞን ለማስቆም ያደረጉትን ጥረት በግልጽ ያሳያል።
👉ክስተቱ፦ የፋሺስት ኢጣሊያ ጦር ወደ መሀል ኢትዮጵያ በግፍ እየገሰገሰ በነበረበት ጊዜ፣ በአዲስ አበባና በአካባቢዋ የነበሩ ካህናትና መነኮሳት የቅድስት ማርያምንና የሌሎችንም አድባራት ታቦታት ይዘው፣ መስቀል ጨብጠው ጠላትን ለመጋፈጥና የሕዝብን እልቅት ለማስቆም ወደ ፊት ወጥተዋል።
👉የአባቶች ጽናት፦ ምንም እንኳ የውጭው ጠላት እንደ አገር ውስጥ ነገሥታት ለታቦቱና ለመስቀሉ ክብር ባይኖረውም፣ አባቶች ግን የሕዝብ ጋሻ ለመሆን ታቦታቸውን ይዘው እስከ መተኮሻው አጥር ድረስ በመሄድ ሰብአዊ መብትንና ነፃነትን ለመጠበቅ ቆመዋል።
አባቶች ለሕዝብ ጥብቅና መቆማቸው ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሃይማኖት መሪዎች የሰላም ምሰሶዎችና የሕዝብ ከለላ መሆናቸውን ያሳያል። አባቶች ይህንን የሚያደርጉት፦
👉የንጉሡን ሥልጣን ለመፈታተን ሳይሆን፣ ንጉሡ ሰይፉን ከመምዘዙ በፊት ሰብአዊነትና መለኮታዊ ፍርድ ትዝ እንዲለው ለማድረግ ነው።
👉 የሕዝብ እረኛ መሆናቸውን በተግባር ለማሳየት ነው—እረኛ በጎቹ ከመታረዳቸው በፊት ራሱን አሳልፎ ይሰጣልና።
የአሁኖቹ አባቶችስ ???
ይቀጥላል
https://t.me/rete14
ከዚህ ምን እንረዳለን?
👉በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የወሀቢያ(wahhabisim)ና የኢኽዋን(Muslim Brotherhood) የጥምረት እንቅስቃሴ መኖሩን
👉የ Pan Arabization እንቅስቃሴ በሀገራችን እየተደረገ መሆኑን
👉 እነዚህ የጥፋት ኀይሎች በጀት የሚያገኙት ከሳዑዲ ዓረቢያ መሆኑን
👉 የዘር ፖለቲካው ለእነዚህ ሰዎች መጠናከር በር እንደከፈተላቸው
👉ቀጣዩ ዘመን ለክርስቲያኖችን ና ለለነባር ሙስሊሞች ከባድ የመከራ ጊዜ መሆኑን
መፍትሔው ምንድን ነው?
👉 እየሆነ ያለውን በትክክል ማወቅናመረዳት ያወቅነውን የተረዳነውን ወደ ተግባር መቀየር
👉ቢቻል ክርስቲያኑና ነባር ሙስሊሙ በጋራ ሆኖ እነዚህን አጥፊዎች ቢከላከል
https://t.me/rete14
በዚህ ዘመን ቅድስናችንን ከሚያጎድሉብን እንቅፋቶች መካከል አንዱ የፎቶአችን ጣኦትነት ነው። በምንሄድበት ቤተ ክርስቲያን ሁሉ ፎቶ ለመነሳት መቸኮልና ሚዲያ ላይ መለጠፍ።ከተራ ምዕመን እስከ ጳጳስ። ከዚያን የከንቱ ዉዳሴ ኮሜንት ይዘንብልናል። እስኪ ዝም ብላችሁ ታዘቡ እየሆነ ያለውን።
12) Kadhannaa Miidiyaa (የሚዲያ ልመና)
TikTookii fi Yuutuibii irratti "Mana kiristaanaa ni gargaarra, mana kiristaanaa ni ijaarra"* jechuun kiisii uummataa onsuu.
13) Lallabaa TikTok (የቲክቶክ ሰባኪ)
Obboleewwan keenya dubartoota biyya Arabaa jiran miskinawwan sana Gowwomsuun qarshii irraa sassabuuf kan hojjetamudha. (Barsiisotaafi obboloota dhugaa hin dabalatu).
14) Baazaarii (ባዛር)
Maqaa eebbaatiin kiisii uummataa gubuu onsuu.
15) Imala Qopheessuu (ጉዞ ማዘጋጀት)
16) Waldaalee Baay'isuu (ማኅበራትን መፈልፈል)
17) Xabala (ጸበል)
Xabala fayyinaaf itti fayyamuun hafee , iddoo uummatni itti walitti qabamuufi madda qarshiin itti sassaabamuu ta'eera
Bizinasii Abshaalootaa mana Kiristaanaa Keessatti
1) Phaphasummaa (ጵጵስና)
Mindaa ji'aa qarshii kuma 50 hanga kuma 70 ni argamsiisa. Kana malees, yeroo bakkaa bakkatti socho'an durgoo (oolee-bulee) guddaatu kafalama. Sanduqni buusiis (ሙዳየ ምጽዋት) n jira, maaddii sooressaa eebbisuun, akkasumas gara Ameerikaafi Awurooppaa yeroo deeman doolaara baayyee sassabu , Tabota daldaluufi qarshii kiisii jedhamee waggatti hanga kumni 300 ni kennamaaf.
2) Monoksummaa Magaalaa (የከተሜ ምንኩስና)
Iddoon jireenya monoksootaa gadaamiidha isaan garuu magaalaa keessa naanna'u. Monoksummaa kan barbaadan qulqullummaaf odoo hin taane, buddeena ittiin nyaachuufi. Isaan akkasii walitti qabanii gara gadaamitti deebisuun barbaachisaadha.
3) Bulchiinsummaa (አስተዳዳሪነት)
Namni tokko gara bulchiinsummaatti yoo dhufe, waggaa tokko ykn lama booda konkolaataa ammayyaafi viilaa (mana jireenyaa ammayyaa) ijaarata. Firoottan isaa hundas mana kiristaanaa keessatti walitti qaba. (Kun sobaa?)
4) Tabota Baay'isanii Walirra Tuuluu (በአንድ አጥቢያ ብዙ ታቦታትን መደራረብ)
Naannoo qulqullummaa tokko keessatti tabota baay'isuun, ayyaana ji'aafi kan waggaa sababa godhachuun kiisii uummataa Onsuu (qarshii irraa fudhatu); itti dabalees faayidaa dhuunfaaf oolchu.
5) Ijaarsa Gamoo (የሕንጻ ግንባታ)
Mana kiristaanaa ijaaramee jiru osoo qabanii, isa biraa jalqabuu; achiinis dafee akka hin xumuramne gochuu. Gamoon sun dafee yoo xumurame ummata irraa qarshii walitti qabuu waan hin mijanneef, ijaaricha harkisuun(tursiisuun) tooftaa isaanii isa jalqabaati. Naannoo keessanitti kun hin jiruuree?
6) yaa'iiwwan Baay'isuu (ጉባኤያትን ማብዛት)
Kaayyoon guba'ee(yaa'ii) inni guddaan wangeela barsiisuu dha.haa ta'u malee, namoota kabaa uffatanii kan dandeettii kadhachuu qaban kireessanii fiduun, uummata jaanjeessuun iyyisiisu. Maqaa qulqullootaa waamaa, "mee araarsummaa ebaluutti kan amantan harka keessan ol kaasaa, harki keessan akka eebbifamuuf walitti rukutaa" jedhanii, achiinis "Gara kiisii fi boorsaa keessaniitti galchaa, waan jiru baasaa kennaa! Har'a manni keessan guutuu ta'a" jechuun uummata hiyyeessa jireenyi itti ulfaate kana kiisii isaa duwwaatti hanbisu.
7) Lallabummaa (ሰባኪነት)
Kunis qarshii baay'ee argamsiisa. Lallabaan tokko Addis Ababaa Irraa ka'ee gara Gondar ykn Hawaasaa deemuuf qarshii kuma100 hanga kuma 200 gaafachuu danda'a. Kun yoo guutameef malee hin socho'u.
8) Faarfattumaa (ዘማሪነት)
Keessattuu maqaan Haadha Keenya karaa ittiin Buddeena nyaatan ta'eera. "Gaara ba'e, gadi bu'e, laga ce'e, baddaa darbe..." kan jedhan, faarfannaa sirbatti dhiyaatan Yuutuubii irratti gadhiisuun daawwattoota kuma 200 argatu. Kanaan daldalaa faarfannaa milkaa'aa ta'u.
9) Cuuphtota (አጥማቂነት)
Hojiin cuuphuu tajaajila luboota hundaatii malee kennaa namoota murasaaf qofa kenname miti. haa ta'u malee "Kennaa cuuphuu qabna" jechuun uummata hiyyeessa oofu, kiisii isaas duwwatti hanbisu. Namoonni kun uummata saamuun dinagdeedhaan badhaadhaniiru; naannoo Ameerikaallee lafa bal'aa bitanii mana kiristaanaa dhuunfaa ijaarratanii phaaphaasota qarshiin Ofjalatt hamma oolchuutti gahaniiru.
10) Abbaa Gaabbiii Magaalaa Ta'uu (የከተሜ ንስሐ አባት መሆን)
Ijoollee gaabbii (የንስሐ ልጆች) irraa qarshii walitti qabanii, waggoota muraasa booda abbaa konkolaataa ta'u mana ijaarratu. Kun "gaabbii qarshiidhaan bituu" jedhama. (Luboota dhugaa isaan hin ilaallatu).
11) Dabtaraa Ta'uu /Margetaa/ (ደብተራነት/መርጌትነት)
Dabtaraa ta'uun bultoo beekumsaati. Garuu warri kashalaboonni maqaa kanaan fayyadamanii "Mastefaqirii (kan jaalala fidu) ni hojjanna, qarshii akka argattan ni goona..." jechuun miliyonoota gowwoomsu. Amma ammoo namoonni adda addaa Telegram irratti "margeetaa Ebaluu" jedhanii ummata hataa jiru.
