ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Открыть в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Больше2 938
Подписчики
+1424 часа
+3877 дней
+38530 дней
Архив постов
ውድ አማራዊያን የብልፅግናው ስርዓት እያስቸገረንም ቤሆን አማራ ነፃ እስከሚወጣ መስራታችን አናቆምም የፊስቡክ እና የቴሌግራም ፒጃችን ለሌሎች ሸር እና ጆይን በማድርግ አዲስ አዲስ መረጃዎችን ቀጥታ ከግንባር ታገኙበታላችሁ ይወዳጁን!!
የብልፅግና ጦር አባላት ምሽግ እየለቀቁ ወደ ፋኖ የመቀላቀላቸው ሁኔታ መጨመሩ ተገለጸ
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ አፄ ዘር ያዕቆብ ኮር በፍቃዱ በላይ ክፍለ ጦርን ሁለት የኮማንዶ አባላት የተቀላቀሉ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የአገዛዙ ሃይል በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የክፍለጦሩ አመራሮች እንደገለጹት፣የብልፅግና ሰራዊት የመዋጋት ሞራል በከፍተኛ ደረጃ የወረደ በመሆኑ ጠቅላላ አባላቱ ውጊያን ሳይሆን የመውጫ ቀዳዳን ብቻ በመፈለግ ላይ ይገኛሉ። በተጨማሪም ክፍለ ጦሩን የተቀላቀሉት የመከላከያ አባላት “የብልፅግና አገዛዝ ፍትሃዊ ያልሆነ ጦርነት ሲያካሂድ በመቆየቱ ምክንያት ማሸነፍ አልተቻለም'' በመሆኑም ሰራዊቱም ገብቶታል ብለዋል።
በፍቃዱ በላይ ክፍለ ጦር ከአገዛዙ ብልፅግናጦር ለቀው የሚመጡ የሰራዊት አባላትን በአግባቡና በሞቃት አቀባበል አስተናግዶ እየተቀበለ እንደሚገኝም አስታውቋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
+2
#አሁን_ላይ_ጉዞ_ወደ_ፋኖ_በሚል_መሪ_ቃል_የአገዛዙ_ሰራዊት ለራሱ መጠቀሚያ ለማድረግ እንደ እቃ ከሚጠቀምባቸው መንግስት እየከዱ ህልውናውን ለማስጠበቅ ከሚዋደቀው ፋኖ ጋር እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።
በእምነት ቦታዎች በተለይ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖትና እስልምና ላይ የአነጣጠረ ጥቃት እየፈፀመ ያለው ንፁሐን በል የአውሬው መንግስት አስመሳይ ጭንብሉ ተገፎ እውነተኛ መልኩ ገሀድ ስለወጣ አለኝ የሚላቸው ወንበር ጠባቂ ቅጥረኞች እየከዱት ፋኖን ተቀላቀሉ።
በትናትናው ዕለት ደብረኤልያስ ወረዳ ሩፋኤል መንደር ከመሸገው የአገዛዙ ኃይል #ዋለ_ይሁን የተባለ የአድማ ብተና ቲም መሪ እንዲሁም በዛሬው እለት የ10ኛ ክፍለጦር 1ኛ ሬጅመንት የሻምበሏ ዳታ ሰብሳቢ ሽፈራው አባይነህ፣ ለዚሁ ሬጅመንት ኦፒ የነበረው ፈንታሁን ጋሻውና ፋኖስ አስናቀው የተባሉ የአገዛዙ መጠቀሚያ አባሎች ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ማለትም
👉2 ጥቁር መሳሪያ (ክላሽ)
👉2 .ባለ ሁለት እግር ታጣፊ ክላሽ
👉2 ቦንብ
👉7 ካዝና እና
👉506 የክላሽ ጥይት
በመያዝ የደብረ ኤልያስ ወረዳ ቀስተ ደመና ሻለቃን ተቀላቀሉ ሲል የቀስተ ደመና ሻለቃ ሚዲያ ክፍል ሀላፊ ለንስር አማራ ገልጿል
ሐምሌ 20/2018 ዓ
✨አማራ ማንነትህን እና አንድነትህን ከሰርጎ_ገቦች ጠብቅ✨
ጠንካራ አማራዊ አንድነት ማለት ቅስፈታዊ አሸናፊነት መሆኑን የተረዱ ሰርጎ-ገብ የጥቅም ቡድንተኞች በመጣው አንድነት ምክንያት ከሃቀኞቹ አማሮች እራሳቸውን እየለዩ ይገኛሉ።
አሁን በእውነተኛ የአማራ ልጆች ታላቅ ጥረትና ፅናት እየመጣ ያለውን አማራዊ አንድነትና አንድ የፋኖ ተቋም ዳግም ለማፍረስ የሚራሯሯጡ የውስጥ ቀበኞች እራሳቸውን ፍንትው አርገው እየገለጡ መተዋል።
እነዚህ አረሞች አማራው በታሪኩ እና በእውነተኛው ጥንካሬ ልክ የምስራቅ አፍሪካ ብሎም የአለም ተፅዕኖ ፈጣሪ ሃያልነቱን ዳግም እንዳይጎናፀፍ ከመስራት አልፈው ለዘመናት በጉያው እንደ መዥገር ተለጥፈው የዘር እልቂት እንዲደርስበት በመረጃም በሴራም ጠላቶቹን ሲተባበሩ ኖረዋል አሁንም በዚህ ፀያፍ ምግባራቸው ቀጥለውበታል።
ስለዚህ ለአማራ ህልውና ሲባል ባፋጣኝ ተቆርጠው መጣል አለባቸው። በፊት በአማራው ጉዳዮች ሁሉ ከማንም በፊት ቀድመው ከፊት የሚሰለፉት እነዚህ ፈትፋች ሰርጎ-ገብ የእናት ጡት ነካሾች አሁን አማራ አለመሆናቸውንም በየማህበራዊ ገፆቻቸው እየነገሩን ይገኛሉ።
እነዚህ መርዘኞች አማራነትን ለዘመናት ተጠይፈው ጎጃሜነትን፣ጎንደሬነትን ሸዋዬነትን እና ወሎዬነትን ብቻ የሙጥኝ ያሉ የየሰፈሩ ኩሬ ጉርጦች የአማራ ጥላቻ ምክንያታቸው አማራ አለመሆናቸው ብቻ ሳይሆን ከጎጣችን ወጥተን ወደ እውነተኛ ምንነታችን "አማራ" ከመጣን እንደልባቸው የሚጠመዝዙት የሰፈር የጭቃ ሹም እና የጎጥ ማንነት ስለማይኖረን እንዲሁም እነሱም ተገልጠው ጥለውት ወደ ነበረው ህደጣን ጎሳዎቻቸው ተጠልዘው ሰልሚመለሱ በፍርሃት እየተንቀጠቀጡ ስለሚገኙ ነው።
በጎጠኝነት ብቸኞቹ ተጠቃሚዎች ሰርጎ-ገቦችና የጥቅም ቡድኖች ብቻ ናቸው። አማራ ሃገር መስራች ባለ ሰፊ ስነልቦና እንዲሁም ዘሩን ወዳድ ብሔርተኛ ነው።
የሰፈር ጉርጦች መልካም ማንቋረር😫
💥አማራ አንገቱ አንድ ነው💥 #Dave #Amhara
+7
ሐምሌ 20/2018 ዓ/ም
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ስራ አስፈጻሚ የድርጅትና የኮር ተወካይ አመራሮች በተገኙበት የጋራ አጀንዳዎች ላይ የመጀመርያ ውይይት አድርጓል።
ተቋማችን አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ አዲሱን መዋቅራዊ አደረጃጀት ይፋ ባደረገ ማግስት፣ ከፍተኛ የስራ አስፈጻሚ አካላቱን የኮር ተወካዬች በተገኙበት በይፋ አስተዋውቋል።
በዚህም የስራ ማስጀመሪያ መድረክ ላይ የተቋሙን የወደፊት ስትራቴጂካዊ ግቦች እና አጠቃላይ የስራ አቅጣጫዎች በተመለከተ ጥልቅ ውይይት ተካሂዷል። ይህ አሰራር አዲሱን ውህድ አመራር የተቀመጡ ተቋማዊ ግቦችን በቁርጠኝነት እና በሙሉ ብቃት ለማስፈጸም ያለመ ዝግጁነት በግልጽ ያሳየ ነበር።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
Gashaw Gizat
ብርጋዲየር ጄኔራል ሶፊያን ሸህ መሀመድ የአስገድዶ መድፈርና የዘር ማጥፋት መሐንዲስ!
ብልፅግና በጎጃም ቀጠና የዘረጋው የዘር ጭፍጨፋ ፕሮጀክት ፈፃሚው ብርጋዲየር ጄኔራል ሶፊያን ሸህ መሀመድ ስም ከወታደራዊ መሪነት ይልቅ፣ የመንግስትን ስልታዊ የዘር ማጥፋት በማስፈጸም ረገድ በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። በአሁኑ ወቅት በጎጃም ቀጠና የ6ኛ ዕዝ የኮር አዛዥ ሆኖ የተመደበው ይህ ግለሰብ፣ በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ግፎችና የክፋት መሐንዲስ ነው።
ጄኔራል ሶፊያን በትግራይ ጦርነት ወቅት ይመራው በነበረው ጦር፣ ጾታዊ ጥቃትንና አስገድዶ መድፈርን እንደ ወታደራዊ ስልት በመጠቀም፣ የህብረተሰቡን ማህበራዊ ትስስርና ሞራል የመስበር ተግባር ላይ ያተኮረ ነበር። ሌላው በጦርነት ውስጥ እየተገበረው ተልዕኮው በሲቪሊያኑ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት፣ ወታደራዊ ግብን መሰረት ያላደረገ፣ የጅምላ ጭፍጨፋ መሪ ነበር። ይህንኑ በትግራይ ሲፈፀምው የነበረ ወንጀል አሁንም በአማራ ህዝብ ላይ እየፈፀመው ይገኛል።
©Birhanu Chalie Demelash
https://www.facebook.com/share/1BMtrRDfpz/
ኮሩ በተቆጣጠራቸው 145 በላይ ቀበሌዎች ከቀይ-መስቀል ጋር በመተባበር የትራኮማ ክትባት መሰጠቱን የ206ኛ ኮር ጤና መምሪያ አስታወቀ።
ሐምሌ 20/ 2018 ዓ.ም
==================================
ከሐምሌ 13-21 2018 ዓ.ም The Carter Center በተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት (NGO) ድጋፍ የሚገኘውን የትራኮማ በሽታ መከላከያ ዚትሮማክስ(Azithromycin) መድሐኒት 206ኛ ኮር ከቀይ መስቀል ጋር በመተባበር በ145 ቀበሌዎች ለሚገኙ ነዋሪዎች ማሰራጨቱን የኮሩ ጤና መምሪያ አስታወቀ።
የአገዛዙ ሰራዊት ለተከታታይ ቀናት በሜካናይዝድ የንፁሐን መንደሮች በሚደበድብበት አሰቸጋሪ ጊዜ በዘመቻ ቤት ለቤት የሚሰጠው የትራኮማ ክትባት ኮሩ በተቆጣጠራቸው ቀጠናዎች ካሉ 20 ጤና ጣቢያዎች እና የጤና ባለሙያዎች ጋር በመተባበር ክትባቱ መሰጠቱ ተገልጿል።
በኮሩ ጤና መምሪያ ስር ያሉ የጤና ባለሙያዎች፣ የጤና ሰራዊት ከጤና ጣቢያ የጤና ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት በተደረገው ዘመቻ ከቤት መውጣት ለማይችሉ የማህበረሰብ ክፍሎች ጭምር ክትባቱን ተደራሻ ማድረጉን መምሪያው አሳውቋል።
በጦርነት ወቅት ሊፈጠር የሚችለውን የጤና አገልግሎት መስተጓጎል ከግምት በማስገባት ሰፊ ስራዎችን እያከናወነ የሚገኘው የ206ኛ ኮር ማህበረሰቡን የሚያገለግሉ የጤና ባለሙያዎችን በመመደብ፤ በሁሉም ቀበሌዎችና ጎጦች የጤና ሰራዊት በመመልመልና በማሰልጠን እናቶች በጤና ተቋማት እንዲወሉዱ ፈጣን የህብረተሰብ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ ገልጿል።
አገዛዙ የቀይ መስቀል አምቡላንስ አገልግሎት በመከልከሉ እናቶች በቤታቸው ለመውለድ እየተገደዱ እንደሆነ የጠቆመው መምሪያው የጤና ሰራዊት በማደራጀት ችግሩን ለመቅረፍ ሰፊ ስራዎች ተሰርተዋል ብሏል። በጦርነት አውድ ውስጥ ያለውን ህዝባችን ከሚደርስበት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና ባለፈ በጤናው ዘርፍ ጉዳት እንዳያስተናግድ ከቀይ መስቀል ጋር በመተባበር በቅድመ መከላከልና በህክምና አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽነቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የ206ኛ ኮር ጤና መምሪያ አስታውቋል።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
✅ 2ኛ አሊ ሻለቃ👏👏👏
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር 2ኛ አሊ ሻለቃ!
+4
ሰበር ዜና
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የ106ኛ ኮር 31ኛ ሰንጥቅ ክፍለ ጦር ዳውንት ወረዳን ተቆጣጥረዋል!!
ሀምሌ 20/2018 ዓ/ም ዳውንት ወረዳን
ከአገዛዙ ሰራዊት ሙሉ በሙሉ ማፅዳት ተችሏል።
የአገዛዙ ሰራዊ መዋቅሩን አፈራርሶና ተበታትኖ እግሬ አውጭኝ በማለት የፈረጠጠ ሲሆን፡በርካታ የሚኒሻ እና የፖሊስ አባላቶች ተማርከዋል።የወረዳዋ ማህበረሰብ ነፃነቱን በፋኖ ክንድ በማገኘቱ ደስታቸውን እየገለጡ ይገኛሉ። የዘር ተኮር ጨፍጫፍው ስርዓት በጨጎማና ወተዬ ቆላማ ቀበሌዎች ተበታትኖ ደመነፍስ እየፈረጠጠ ይገኛል።የብአዴን ሎሌና ተላላኪ አመራሮችም ከሚፈረጥጠው የጁላ ሰራዊት ጋር አብረው እየፈረጠጡ ነው ሲል የ106ኛ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
ሀምሌ 20/2018 ዓ/ም
+2
የራንቦ ክፍለ ጦር በብልፅግና 103ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ላይ ልዩ ኦፕሬሽን አካሄደ!!
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሣምነው ዕዝ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው የራንቦ ክፍለ ጦር በጠላት ኃይል ላይ በአይነቱ ለየት ያለ እና የተሳካ ኦፕሬሽን ማካሄዱን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ።
የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ከግንባር ባደረሰን መረጃ፤ ኦፕሬሽኑ የተፈፀመው ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት እስከ ጧት 2:00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ በተካሄደ ጠንካራ ውጊያ ነው። ይህ ኦፕሬሽን በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ስር በሚገኙት አርማኒያ ክላስተር፥ አርማኒያ፣ ማፉድ፣ ገደባ፣ ማፉድ የውሃ ታንከር እና ማፉድ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አካባቢዎች ላይ የተደረገ ኦፕሬሽን መሆኑን ገልጿል።
በነዚህ ስፍራዎች ላይ ሰፍሮ በነበረው የብልፅግና 103ኛ የኮማንዶ ክፍለ ጦር ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱን የጠቀሰው ኮሩ፤ የራንቦ ክፍለ ጦር ባደረገው ስልታዊ ውጊያ የጠላትን ምሽግ ማስለቀቁን፣ የጠላት ኃይልን መደምሰሱን እንዲሁም ሙትና ቁስለኛ በማድረግ መብረቃዊ ጥቃት መፈጸሙን ሲያሳውቅ በወገን ሀይል በኩል ያለምንም ጉዳት የተሳካ ኦፕሬሽ መስራቱን ገልጿል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት"
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሣምነው የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰበር ዜና‼️
በጀግናው የአማራ ፋኖ ሰራዊታችን ቅንጅት በከፍተኛ ከበባ ውስጥ የገባው የአገዛዙ መከላከያ ሰራዊት አሁን ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ላይ የቤተ-አማራዋ ደገር ከተማን ለቆ ወደ ከላላ ከተማ ሲፈረጥጥ፣ በሬማ ከተማ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ውስጥ የከተመው የብልፅግናው 101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ መግባቱን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር የአፄ ዳዊት ክፍል ጦር ም/የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ አርበኛ ዲ/ን ያሬድ ታመነ ከስፍራው መረጃውን ለኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አድርሷል።
ድል ለጀግናው የአማራ ፋኖ❗️
ድል ለአማራ ህዝብ‼️
ሐምሌ 19/2018 ዓ.ም
🙏Congratulations❗️
የአፋብን የቴዎድሮስ ዕዝ የአመራር ሪፎርም ተጠናቀቀ!
👉
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የቴዎድሮስ ዕዝ የአመራር ሪፎርም መጠናቀቅን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የቴዎድሮስ ዕዝ ላለፉት ወራት የአመራር ሪፎርም ለመስራት ከፍተኛ ስራ ሲሰራ የቆየ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ሂደት ዕዙ መዋቅራዊ አንድነቱ ተጠብቆ ጤናማ ሽግግር እንዲያደርግ ሂደቱን በጥንቃቄ እና በትዕግሥት መምራት አስፈላጊ በመሆኑ በሚፈለገው መልኩ በፍጥነት ሳይጠናቀቅ ቆይቷል።
የአደረጃጀት ፈተና ከድርጅት ዕድገት ጋር ተያይዞ በየጊዜው የሚፈጠር ቢሆንም ከውጭ ወደ ውስጥ የሚሰነዘሩ ከፋፋይ ጥቃቶችን እየመከቱ ተፈጥሯዊውን ውስጣዊ ትግል ለመዋቅራዊ ዕድገት በሚጠቅም መልኩ ለማዋል በጥበብ የተመራ ትግል ተደርጓል።
ድርጅታዊ መስመርን ለማስጠበቅ የተሄደበት ውስጠ ድርጅታዊ አሰራር ተገቢ እና ትክክል መሆኑ የዕዙን መዋቅራዊ አንድነት አስጠብቆ ለላቀ ግዳጅ የሚያበቃ ውጤት ላይ እንዲደረስ አስችሏል።
ይህ የዕዝ አመራር ሪፎርም በተለያዬ ደረጃ ውስጥ ያለፈ እና የመዋቅሩ ተዋረዳዊ ተሳትፎ የነበረበት ነው። የዕዙ ስራ አስፈጻሚ የሪፎርም ስራ አፈጻጸም ሂሩት ላይ የዕዙ ተወካይ በሆኑ የፖሊት ቢሮ አባላት አማካኝነት የኮር እና የክፍለ ጦር አመራሮች ጋር ውይይት ተደርጓል። ቀጥሎም ምክትል መምሪያ ሀላፊዎች እና ሌሎች የክፍል ሀላፊዎችን አወያየቷል። በመጨረሻም በነዚህ መድረኮች የተገኘውን ግብአት በመውሰድ የዕዙ ስራ አስፈጻሚ የሪፎርም ኮሚቴ እንዲዋቀር ወስኖ የአወቃቀር ሂደቱ የሚመራበትን መመሪያ አዘጋጅቶ ወደ ስራ ገብቷል።
በዚህ መሠረት ከክፍለጦሮች፣ ከኮር እና ከምክትል መምሪያ ሀላፊዎች የተውጣጣ ኮሚቴ በማዋቀር የሪፎርም ኮሚቴው ተመሰርቷል። የዕዝ ስራ አስፈፃሚው በሰጠው መመሪያ እና ስልጣን መሠረት የሪፎርም ኮሚቴው የዕዙን የአመራር ሪፎርም ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ስራውን ጨርሶ ፕሮፖዛሉን ለዕዙ ስራ አስፈጻሚ አቅርቧል። ስራ አስፈጻሚው የቀረበለት ፕሮፖዛል መነሻ አድርጎ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ የኮሚቴው ፕሮፖዛል ላይ መጠነኛ ማሻሻያ አድርጎ የዕዙን የአመራር ሪፎርም የመጨረሻ ዝርዝር አጽድቋል።
በዚህም መሠረት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ የአፋብን መተዳደሪያ ደንብ አንቀፅ 60 ስር በተቀመጠው መዋቅር መሰረት ከዚህ በታች በተዘረዘረው መልኩ ተደራጅቷል።
1) ሰብሳቢ:- አርበኛ ተፈሪ ካሳሁን
2) ም/ሰብሳቢ:- አርበኛ ጎበዜ ጌታቸው
3) ወታደራዊ አዛዥ:- ሻለቃ የኔአለም ዘለቀ
3.1) ምክትል ወታደራዊ አዛዥ:- መቶ አለቃ እሱባለው ዋለ
4)ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ ግሩም ምሳሌ
4.1) ምክትል:- አርበኛ አማረ ካሴ
5) ፅህፈት ቤት ኃላፊ:- አርበኛ ናትናኤል ስናማው
5.1)ምክትል:- አርበኛ ብዙነህ እምቢያለ
6) አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ እስቲበል አለሙ
6.1) ምክትል:- አርበኛ ደመላሽ አንድነው
7) የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ ወግደረስ ጤናው
7.1)ምክትል:- አርበኛ ታደሰ አስማረ
8)ጥናትና ስትራቴጂ ጉዳዮች መምሪያ:- አርበኛ ዳሞት አለኸኝ
8.1)ምክትል:- አርበኛ መንግስቱ አማረ
9)ፋይናንስ እና ግዥ አስተዳደር:- አርበኛ ይትባረክ አንዳርጌ
9.1)ምክትል:- አርበኛ ያሬድ በቀለ
10)የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ:- አርበኛ ዘመን ተሻለ
10.1)ምክትል:- አርበኛ በለጠ ልየው
11) ሴቶች ጉዳይ መምሪያ- ፋኒት አትጠገብ አጥናፉ
11.1)ምክትል:- ፋኒት ክብራለም አያልነህ
12) ማሕበራዊ ጉዳይ መምሪያ:- አርበኛ ላይችሉህ ገበየሁ
12.1) ምክትል:- አርበኛ በላይነህ አለምነህ
13) የሰው ሃብት -ዳኛው ሽባባው
13.1) ምክትል:- አርበኛ በረከት አጥናፉ
14)ት/ት እና ስልጠና መምሪያ:- አርበኛ ክንፈመላክ ካሳ
14.1)ምክትል:- አርበኛ ዘውዳለም አዱኛ
15) መካናይዝድ ጦር መምሪያ:- ኮሎኔል አደመ ልጃለም
15.1) ምክትል:- መቶ አለቃ ሳሙኤል አታላይ
16)ህግ እና ስነስርዓት መምሪያ:- አርበኛ ዘማርያም እስከዚያ
16.1) ምክትል:- አርበኛ ቻላቸው ታፈረ
17) ሀብት አፈላላጊ መምሪያ- አርበኛ ሀይለሚካኤል ባዬህ
17.1) ምክትል:- አርበኛ ደሴ ጌታሁን
18) እቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ:- አርበኛ የሻነው መለሰ
18.1) ምክትል:- አርበኛ አታላይ ሞሴ
19) ዘመቻ መምሪያ-አምሳ አለቃ ታደሰ ልንገሬ
19.1) ምክትል:- መቶ አለቃ አጃናው ጥላሁን
20) ሎጀስቲክ መምሪያ:- አርበኛ ይርሳው ደምስ
20.1) ምክትል:- መቶ አለቃ አስረስ ምህረቴ
21) ወ/አስተዳደር መምሪያ- መቶ አለቃ ያሬድ ጫኔ
21.1) ምክትል:- 50 አለቃ ይበልጣል መልካሙ
22)ወ/ስልጠና መምሪያ:- ሻምበል ጌትነት ንጉሴ
22.1) ምክትል:- አምሳ አለቃ ዘላለም ደሴ
23) ልዩ ዘመቻ መምሪያ- መቶ አለቃ ማርቆስ አሞኜ
23.1)/ምክትል:- ሻለቃ በላይ ብዙ አየሁ
24) መረጃ - ----------
24.1) ምክትል-- --------
25)ኢንዶክትርኔሽን መምሪያ:- መቶ አለቃ ጊዮን ጀንበሬ
25.1) ምክትል- መቶ አለቃ ገረመው አጋዠ
26) ወታደራዊ እቅድ እና ስትራቴጅ:- ሃምሳ አለቃ ስማቼው ቢሻው
26.1) ምክትል:- መቶ አለቃ ለዓለም ጌታሁን
27) ወታደራዊ መረጃ------
27.1) ምክትል- -------
28) ጤና መምሪያ:- ዶክተር እንዳላማው ጤናው
28.1) ምክትል-- ዶክተር ደመቀ አያሌው
ምንጭ፦ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
በምስራቅ ጎጃም ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ከፍተኛ የፖሊስ አመራሮች ትግሉን ተቀላቅለዋል።
ሐምሌ 19/2018 ዓ.ም
==================================
በምስራቅ ጎጃም ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ለትግራይ ጦርነት አንዋጋም ያሉ ሁለት የፖሊስ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ አራት (4) ፖሊስና ሦስት (3) ሚኒሻዎች ትግሉን ተቀላቅለዋል።
1.ኢንስፔክተር አሸናፊ ከፋለ
2.ኢንስፔክተር ያብባል አዝመራው
3.ሳጅን በላቸው ዳምጤ
4.ሳጅን ሁናቸው ቢሆነኝ
5. ሳጅን ደጉ ቢታው
6. ሚኒሻ ጋሻው ዳሩ
7. ሚኒሻ ገበያው አረጋ
8. ሚኒሻ ጥላው ላቀ
በትግራይ እና በአብይ አህመድ ሰራዊት በኩል ግልፅ የጦርነት እንቅስቃሴን መጀመሩን ተከትሎ የሚኒሻና ፖሊስ አባላት ለግዳጅ እየተዘጋጁ ሲሆን ወደ ትግራይ ጦርነት አንዘምትም ያሉ የአገዛዙ አገልጋዬች እየታሰሩም ይገኛሉ። በዚህ መሰረት
1. ዋና ሳጅን አሸናፊ ሙሉ
2. ሚኒሻ ደስታ ገደፋው በግንደወይን ከተማ መታሰራቸው ታውቋል።
