ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Открыть в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Больше2 938
Подписчики
+1424 часа
+3877 дней
+38530 дней
Архив постов
ከውጊያ ጎን ለጎን ህዝባዊ መድረኮች ተጠናክረው ቀጥለዋል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር በተቆጣጠራቸው ቦታዎች ህዝባዊ መድረኮች ተጠናክረው ቀጥለዋል ።
በሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች በኮሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ በክፍለጦሩ ከፍተኛ አመራሮች እና በሲቪል መዋቅሩ ከፍተኛ አመራሮች በጋራ በቀመናጀት 011 ቀበሌ ብርኳኳ፣012 ቀበሌ ቆብ እና 013 ቀበሌ ዘብሎ የህዝብንና የፋኖን ዘላቂ አንድነትና በጋራ ተሳስሮ የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ የነቃ ሳትፎን አካሂደዋል ።
ህዝባዊ መድረኮቹ የህዝቡን የነቃ ተሳትፎ በበላይነት ያሳተፈ ሲሆን በዋናነት የህዝቡን እና የፋኖን ደካማና ጠንካራ ጎን በጥልቀት በመገምገም አሁናዊ የህልውና ትግሉን በጋራ መሻገር እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ህዝባዊ ውይይቶቹ ከ10 ያላነሱ ዋና ዋና አንኳር ነጥቦች ላይ ያተኮረ ሲሆን ለአብነት ያክልም
1' የአማራ ህዝብ የህልውና ትግል መሰረታዊ መነሻዎችና የደረሰበት ደረጃ
2' በህልውና ትግሉ ከህዝብ ምን ይጠበቃል
3' የህዝብ ተግባርና ሃላፊነት
4' የህዝቡና የፋኖ አንድነትና በጋራ አብሮ ከመስራት አኳያ
5' ትግሉን በቅርቡ ለመፈፀም ህዝባዊ ድጋፍ ጋር ተያይዞ በሚል ህዝባዊ መድረኮች ተካሂደዋል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መረጃውን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
ሐምሌ19/11/2018 ዓ'ም
"ሰበር ዜና"!
ከአገዛዙ ጋር ተሰልፈው የነበሩ 8 ሚሊሻዎች ወደ ትግራይ አንዘምትም በማለት ዛሬ በ19/11/2018 ዓ/ም ቴወድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 55ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቀሉ።
- የሚሊሻ ቤተሰቦች
- የፖሊስ ቤተሰቦች
- የአድማ ብተና ቤተሰቦች
- የካድሬ ቤተሰቦች ወደ ትግራይም ይሁን በሌሎች አካባቢዎች ለጦርነት ብሎ ከጠላት ጋር የተሰለፈ ሁኖ በወገን ጥይት ቢሸኝ ፋኖ በሚያስተዳድረው በየትኛውም ቀጠና የመርዶ እለቅሶ እንደማይደረግለት እንድታውቁ።
---ሚሊሻ ፖሊስ አድማ ብተና በማያገባህ አትግባ ና ብለናል---!
መደራጀት ስንጀምር እንደ ሞኝ የቆጠሩን ነበሩ። እንደ እብሪተኛ የተመለከቱንም ነበሩ። መሰልጠን እና መደራጀት ስንጀምር ማንንም ተማምነን አልነበረም። ትላንትን ከዛሬ ጋር ባሰናሰለ ነገንም ባመላከተ ስልታዊ ትንተና ላይ መቆማችን ደፋር እንድንሆን ስላስቻለን እንጅ።
ገና ከፕሪቶሪያ ስድስት ወራት አስቀድሞ በህግ ማስከበር ስም በእንጭጩ የማክሰም ዘመቻ ሲከፍቱብን የአማራ ህዝብ ከጎናችን በመቆሙ እርሾ ሆነን መቀጠል ቻልን።
ያገለገላቸውን የአማራ ልዩ ኃይል በክህደት በትነው ጦርነቱን ሲጀምሩት ትጥቃቸውን ቀምተን ጥርስ አልባ እናደርጋቸዋለን ብለው ነበር። በምላሹ የሆነው ግን የቀድሞ አለቆቻቸው የአባቶቻችንን ቤልጅግ እና ምኒሽር መንጠቃቸው ያሳደረብንን ቁስል አልዘነጋንም እና በገፍ ያመጡትን የቡድን እና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ በገፍ ተቀበልናቸው። የሞተበትን ለመቅበር፣ የቆሰለበትን ለማንሳት ወኔ እንዲኖረው የሚያደርግ ዓላማ አልታጠቀምና ከጦርነት ወደ ጦርነት የሚያዞሩትን "ምስኪን" ሰራዊት በየ ጥጉ አዝረከረክነው።
ሲጀምሩ ቀበቶ እናስፈታለን ያሉ ጦረኞች መሀል ላይ ህዝብ ነው የወጋን ብለው በየደረሱበት ጭፍጨፋ ፈፀሙ። ያጋጠማቸው የበለጠ መዝረክረክ ሆነ። እንደገና ሽፍታ ናቸው አላማ የላቸውም አሉን። የህዝብ ተቋም ጠብቀን፣ ለወጉን ምህረት አድርገን፣ ኃይል ገንብተን፣ ሰራዊት አደራጅተን በራሳቸው ተተኳሽ ተዋግተን አሳዬናቸው። ህዝብ አደራጅተን፣ መልክ እና ደርዝ ያለው ፖለቲካ ሰርተን ራቁታቸውን ስናስቀራቸው አንድ አይሆኑም የተከፋፈሉ ናቸው የሚል ፕሮፖጋንዳ ጀመሩ።
የጠላትን ረጅም እጆች ሰብረን፣ ትግላችንን የጡረታ መውጫ ሊያደርጉ የቋመጡትን ጥግ አስይዘን፣ የፍላጎት ቡድኖችን ቅርብ አዳሪ ህልሞች አክሽፈን፣ የውስጣችንን ግላዊ እና ቡድናዊ ፍላጎቶች ገርተን ግዙፍ ድርጅት መስርተን መጣን።
ከዚህ ጎን ለጎን የአብይ አህመድ አገዛዝ በቀጣናው ህዝብ ላይ ያወጀውን የጥፋት ዘመቻ በልዩ ስልት ብቻችንን መክተን በአፍሪካ ቀንድ አዲስ እና አስተማማኝ ኃይል መሆናችንን አስመሰከርን።
አፋብን አይፀናም ብለው ክፉ የተመኙትን አፍ አስይዘን ማዕበል ሳያናውጠን በመርህ ላይ ቆመን እና ፀንተን አሃዶቻችንን አዋህደን የጠላትን ሁለንተናዊ ርብርብ በመቋቋም ትላልቅ ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ድሎችን ተቀዳጅተናል።
ከረግረጉ መውጣት ያልቻለው ብልፅግና ከኤደን ባህረ ሰላጤ እስከ ቀይ ባህር ያሉ አጀንዳወችን በማንሳት ትኩረት ለማስለወጥ ቢሞክርም አልሆን ሲለው ተባብረው ሊመቱኝ ነው ብሎ የሚጨፈጭፈውን ህዝብ የሙጥኝ እንዲልርገነዋል።
ዓላማችንን ለኢትዮጵያውያን አስረድተን በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የለውጥ ኃይሎች አሰባስበን በአማራ ላይ ይሳቡ የነበሩ ቀስቶችን ወደ አገዛዙ እንዲዞሩ አደረግን። የቅርብ እና የሩቅ ጎረቤት አገሮች ከተለመደው የዲፕሎማሲ አካሄድ ወተው ከህዝብ ትግል ጎን እንዲቆሙ አድርገናል።
በዚህ ምክንያት ሽፍታ ናቸው፣ ዓላማ ቢስ ናቸው፣ ዋሻ ናቸው አይነት ፕሮፖጋንዳወች አፈር ለብሰው ከውጭ ሀይሎች ጋር ተባበሩብኝ ይሉትን እዬዬ ተያይዞታል።
ብልፅግናወች "በምርጫ ድግስም" ሆነ በብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን የማይመክቱት ማዕበል እየመጣባቸው መሆኑን ውቃቤያቸው የነገራቸው ይመስላል። ሁለት ምርጫ አላቸው። ጦርነት አቁሞ ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ መስጠት ወይም የሽንፈትን ፅዋ መጎንጨት!
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ወሎ ቤተ አምራ ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር ታላቅ ድል ተጎናፀፈ።
መነሻውን በሰሜን ወሎ ዞን ዴውንት እና ተረፌ ከተማ ያደረገው የአገዛዙ ጨፍጫፊ ቡድን በ101ኛ ኮር አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ የመጣበትን አላማ ሳያሳካ ሙትና ቁስለኛውን አዝረክርኮ ተመልሷል።
የአገዛዙ ታጣቂ ሃይል ወደ ሳንቃ ከተማ በሌሊት ቢንቀሳቀስም በአይቀመሴዎቹ የ101ኛ ኮር ነበልባሎች ተገርፎ ወደመጣበት ተመልሷል።
የአገዛዙ የ61ኛ ክፍለ ጦርን በተለያዩ አቅጣጫዎች ማለትም ከቀይ ዋሻ በመውረድ ቀይ አንባ፣ጃርሳ፣እና ገዶ በሚባሉ ቦታዎች በማሰለፍ ያለ የሌለ አቅሙን በመጠቀም እልህ አስጨራሽ ዉጊያ ቢያደርግም ነብሮቹ ወደ መግደያ ቦታ ስቦ በማስገባት በ101ኛ ኮር አይነኬ ተዋጊዎች የበላይነት ተጠናቋል።
በዚህም ጠላት እራሱ አቅዶበት በመጣው ውጊያ የስነ ልቦና ስብራቱን ታቅፎ ሙትና ቁስለኛውን እያንጠባጠበ ሽንፈቱን ተከናንቦ ያሰበውን ቦታ ሳይዝ ተመልሷል ሲል የ101ኛ ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!
ሀምሌ 19/2018 ዓ.ም
🦅 ሞት አልፎኝ... ዛሬ እዚህ ቆሜአለሁ!
(ከትናንት የእሳት እቶን ወደ ነገው የድል አክሊል) 🚨 ይህንን መልእክት ሳታነብ አልፈህ እንዳትሄድ! ብዙዎቻችን የምንኖረው በትናንትናችን ጥቁር ጥላ ስር ተቀብረን ነው። ያሳለፍነው መከራ፣ የገጠመን ውድቀት፣ ወይም የደረሰብን በደል እንደ ብረት ሰንሰለት የታሰርንበት እስር ቤት ሆኖብናል። በየቀኑ ያንን አሮጌ የታሪክ ትዝታ በልባችን እናጫውታለን... እያሰብን፣ እያለቀስን፣ እና እራሳችንን እያደማን። 😔
ነገር ግን ቆም ብለህ ስማኝ፡ ትናንት የሞተ ቀን ነው! ❌ 🕊️ እኔ የትናንት ተአምር... የዛሬ ህያው ምስክር ነኝ! የዛሬ አራት አመት በዚህች ቀን ➔ ቅዱስ ገብርኤል ከአረመኔው አብይ አህመድ ስርዓት ከመከላከያ እና ከአማራ አድማ መከላከል መረብ ያወጣኝ ቀን ነው! 🙏ሐምሌ 19/2015 ዓ.ም ➔ በደብረ ብርሃን ከተማ (ጠባሴ) ከኦሮምማው ኦነጉ ስርዓት ቃል አቀባይ አንድ ይሁዳ እና በአንድ የአዲስ አበባ የሚኖር የEEIG የኮንስትራክሽን ድርጅት ሰራተኞች እጅ ልወድቅ በተአምር የተረፍኩበት እውነተኛ የህይወት ታሪኬ ነው! 🕊️💥 ይህ ሁሉ የሚያሳየው አንድ ታላቅ እውነት ነው፡ ቁስልህ የመጨረሻህ ማብቂያ ሳይሆን... የታላቅ ድልህ መጀመሪያ ነው! 🏆 👞 አንዱ እግርህ በቁስል... ሌላው በስኬት! በምስሉ ላይ እንደሚታየው፡🦶 አንዱ እግር ➔ በአሮጌና በተቀደደ ጫማ ውስጥ ነው (የትናንት ህመምህና ስቃይህ) 👞 ሌላኛው እግር ➔ በዘመናዊና በስኬት ጫማ ውስጥ ነው (የነገው ታላቅነትህ) አንተም በውስጥህ የትናንት ከባድ ታሪክ ይዘሃል፤ ነገር ግን ያ ያለፈ ህመም ዛሬ ወደፊት የምታደርገውን ታላቅ እርምጃ እንዲያቆመው በፍጹም አትፍቀድለት! 🛑
🪞 ትናንት ማሳለፊያ እንጂ መኖሪያ አይደለም! ❌ የትናንት መከራህ ➔ ዛሬ የምትሆነውን ሰው አይወስነውም። ❌ ውድቀትህ ➔ ማብቂያህ አይደለም፤ የታላቅነትህ ትምህርት ቤት እንጂ! ❌ ያለፈው ጊዜ ➔ እንደ መስተዋት ነው፤ 🪞 ተመልክተኸው አልፈህምትሄድ እንጂ ገብተህ የምትኖርበት ቤት አይደለም! 🔥 አሮጌውን ጫማህን አውልቀህ ጣል! ዛሬ የምትወስደው አንዲት ትንሽ እርምጃ፣ ከትናንት የባሰ እንደሚጠቅምህ ሙሉ በሙሉ እመን። 💪 ትናንት የተሰበረው ልብህ፣ ዛሬ ለሚገነባው ታላቅ ስኬትህ ጠንካራ መሰረት ነው! ✨ ያለፈውን ተወው፤ የወደፊቱን በእጅህ ጨብጥ! 🤲 ለትናንት ህመም አትገዛ፣ ለነገው ብርሃን ኑር! ምክንያቱም አንተ የትናንት ታሪክህ ተጠቂ ሳትሆን... የነገው የድል አድራጊው ጀግና ነህ! 🦅🔥
✍️ Dave Amhara ነኝ ከጀግኖቹ ❤ከ7ለ70❤ መንደር (ይህ መልእክት ለአንድ እንኳ ተስፋ ለቆረጠ ሰው እንዲደርስ 🔴 SHARE እና COPY LINK ማድረጉን አትርሱ... እወዳችኋለሁ!) ❤️ ድል ለአማራ ህዝብ!!
የመከላከያ መንገድ መሪ የነበሩ የዞንና የወረዳ ካድሬዎች ተገደሉ/ ተሽከርካሪው ወደመ!
በአፋብን ወለጋ/ቢዛሞ ቀጠና አይሻ ሰይድ ዕዝ ስር የሚገኙ ክፍለ ጦሮች በምስራቅ ወለጋ እና በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞኖች ባካሄዱት ተከታታይ የተቀናጀ የፀረ-ማጥቃት እርምጃ፡ መንገድ መሪ ካድሬዎችን ጨምሮ በርካታ የጠላት ኃይልን በመደምሰስ የጦር መሣሪያዎችንና ወታደሮችን በመማረክ እንዲሁም ስትራቴጂካዊ አካባቢዎችን በመቆጣጠር አንፀባራቂ ድል ተቀዳጁ።
አርበኞቹ ትናንት ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም ከማለዳ ጀምሮ ባካሄዱት የተቀናጀ ኦፕሬሽን፡ የቀድሞው የሃሮ ሊሙ ወረዳ አስተዳዳሪና የአሁኑ የምስራቅ ወለጋ ዞን ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ኃላፊው አቶ ደቻሳ ገነቲን ጨምሮ ሌሎች የብልፅግና መከላከያ ሰራዊቱን መንገድ ሲመሩ የነበሩ ብዛት ያላቸው የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ካድሬዎችን መገደላቸውን ለማረጋገጥ ችሏል።
መንገድ መሪ ካድሬዎቹ የተገደሉት ከአንገር ጉትን ከተማ በ4km ርቀት ገደማ ላይ ልዩ ስሙ ነጩ መንገድ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ ሲሆን፡ ከከተማዋ በቅርብ ርቀት የምትገኝ ወሳኝ ወታደራዊ ስፍራም በአርበኞቹ ቁጥጥር ስር መዋሏ ታውቋል።
በአይሻ ሰይድ ዕዝ ስር የአንገር ጉትን ክፍለ ጦር አርበኞች በዚህ አከባቢ በወሰዱት እርምጃ ከተገደሉ መንገድ መሪ ካድሬዎች በተጨማሪ ተሳፍረውበት የነበረው ወታደራዊ ተሽከርካሪ ሙሉ በሙሉ መውደሙን ነው ጣቢያችን ለማረጋገጥ የቻለው።
በዕዙ ስር የአበጀ ጥበቡ ነበልባል ክፍለ ጦር አርበኞች ከጉትን ከተማ በቅርብ ርቀት መንደር 4 ቀበሌ በመግባት የጠላትን ኃይል ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አካባቢውን ከጠላት ወታደሮች አፅድተው በቁጥጥራቸው ስር አስገብተዋል።
በተመሣሣይ፡ በአይሻ ሰይድ ዕዝ ስር የታፈረ አለሙ ሳተናው ክፍለ ጦር አርበኞች በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤ ደንጎሮ ወረዳ ባካሄዱት ልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ስትራቴጂካዊቷ ቱሉጋና ከተማን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥራቸው ስር ማስገባታቸውን የወለጋ ቢዛሞ ቀጠና ዘጋቢ ለማረጋገጥ ችሏል።
ለቀናት በዘለቀው በዚህ የመከላከልና የመልሶ ማጥቃት አውደ ውጊያ 31 ክላሽንኮቭ መሣሪያዎች በአርበኞቹ ቁጥጥር ስር ሲውል፡አንድ በሲቪል ሲንቀሳቀስ የነበረ የደህንነት አባልን ጨምሮ 5 የገዳ ኮማንዶ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እጅ ከፈንጅ ተማርከዋል።
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ የአመራር ምደባ አድርጓል። የቀድሞወቹ ሁለት እዝ አመራሮች በጋራ በአካል በመገናኘት ባካሄዱት ጉባኤ የተዋሃደው የጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ አመራር በሚከተለው መልኩ የኃላፊነት ምደባ ተደርጓል።
የሰብሳቢውን ቦታ አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ እና አርበኛ ባዬ ቀናው ለ3 ወራት ያክል በጥምር የሚመሩት ይሆናል፡፡
1ኛ/ ከሁለቱ አርበኞች በተጨማሪ የተመደቡ የስራ አስፈፃሚ አባላት:-
ተቀ/ምክ/ሰብሳቢ…………………አርበኛ ሰለሞን አጣናው
ም/ሰብሳቢ ለፖለቲካ ጉዳዮች………አርበኛ ኪሩቤል ጎቤ
ወታደራዊ አዛዥ…………………….አርበኛ ደረጀ በላይ
ምክ/ወታደራዊ አዛዥ………………አርበኛ አሻምበል አምሳሉ ማዘንጊያ
ምክ/ወታራዊ አዛዥ ለአስተዳደር ጉዳዮች....አርበኛ ሸጋ ጌታቸው
ወታራዊ አማካሪ…………………………ኮ/ል አበራ አዛናው
ፖለቲካ መምሪያ…………………..……አርበኛ አንተነህ ድረስ
ዘመቻ መምሪያ……………………….አርበኛ ተሾመ አበባው
ጽ/ቤት ኃላፊ……………………….አርበኛ በየነ አለማው
አደረጃጀት ጉዳይ …..……………..አርበኛ አበበ መልኬ
ፋይናንስና ግዥ መምሪያ……….አርበኛ ሐብታሙ ሙላው
ሎጅስቲክ መምሪያ…………….………አርበኛ በላዬ ዘለቀ
ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ………….…አርበኛ ጋሻው ግዛት
ሕዝብ አስተዳደር መምሪያ………….አርበኛ ንጉሴ አዱኛ
ልዩ ዘመቻ መምሪያ..……………….አርበኛ አስፋው ሰርፀ
ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ…….……አርበኛ ጌታሰው በሬ
ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጂ መምሪያ…..አርበኛ ተመስገን አብርሃም
ምክ/ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ……..……አርበኛ ስጦታው ዳኛው/ባሻ
ሜካናይዝድ ጦር መምሪያ………..አርበኛ ሲሳይ አሸብር
ቴክኖሎጅና ምህንድስና መምሪያ……አርበኛ ያለው አዱኛ
ጥናትና ስትራቴጂ መምሪያ………..አርበኛ ዘመነ እረኛው
ትምህርትና ስልጠና መምሪያ……….አርበኛ ዘላለም በላይነው
ሕግና ስነ-ምግባር ጉዳይ መምሪያ……አርበኛ ማሩ ቢተው
ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ………..አርበኛ ብዙአየሁ ወንድምነው
ሴቶችና ወጣቶች መምሪያ………..አርበኝት አስምሪው መሳፍንት ተስፉ
ሰው ሃብት አስተዳር መምሪያ….……አርበኛ አዳነ ፀጋ
ሃብት አፈላላጊ መምሪያ….…………..አርበኛ ማሩ በሪሁን
ኢንዶክትሪኔሸን መምሪያ…..………አርበኛ ተመስገን ውባንተ
የውስጥ ኦዲት መምሪያ……………..አርበኛ ግዛቸው አሌ
ጤና መምሪያ……………………………አርበኛ አታለለ ሰጠኝ
እቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ……አርበኛ ታደሰ ወርቁ
ቁጥጥርና ኦዲት ኮሚቴ ሰብሳቢ…………አርበኛ ባንቲደር እውነቱ
ሕግና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ሰብሳቢ…………አርበኛ ወልደአረጋይ ሸርብ
ወታራዊ ፍርድ ቤት ሰብሳቢ……………..አርበኛ ታርቆ ከበደ
2ኛ) ምክትል የስራ አስፈጻሚ መምሪያዎች
ምክ/ፖለቲካ መምሪያ………………..…አርበኛ ዳኛው አጣናው
ምክ/ጽ/ቤት………………………..አርበኛ መ/አ ገዳም ካሳ
ምክ/አደረጃጀት ጉዳይ…………………...አርበኛ ብርሃኑ ነጋ
ምክ/ፋይናንስና ግዥ መምሪያ…………..አርበኛ ስጦታው መልኬ
ምክ/ሎጅስቲክ መምሪያ…………………አርበኛ ደፋሩ አቤ
ምክ/ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ…………አርበኛ ማንደፍሮ ተሰማ
ምክ/ ሕዝብ አስተዳደር መምሪያ……….አርበኛ ዋሴ ታደሰ
ምክ/ልዩ ዘመቻ መምሪያ..………………...አርበኛ ሙሉዬ ደሴ
ምክ/ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ…………ሻምበል መሳፍንት ተስፉ
ምክ/ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጂ………...አርበኛ እያቸው ብርሃኑ
ምክ/ሜካናይዝድ ጦር መምሪያ…….…….አርበኛ ንጋት አየለ
ምክ/ቴክኖሎጅና ምህንድስና መምሪያ…….አርበኛ አለሜ ባዬ
ምክ/ጥናትና ስትራቴጂ መምሪያ………...አርበኛ ፋሲል ሙሏለም
ምክ/ትምህርትና ስልጠና መምሪያ………..አርበኛ አብዩ ማሩ
ምክ/ሕግና ስነ-ምግባር መምሪያ………..…አርበኛ ደመቀ አለሙ
ምክ/ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ…………..አርበኛ ደምሰው ድረስ
ምክ/ሴቶችና ወጣቶች መምሪያ……………….አርበኝት ገነት ፀጋው
ምክ/ሰው ሃብት አስተዳደር መምሪያ………አርበኛ ወዳጅ አስፋው
ምክ/ሃብት አፈላላጊ መምሪያ ….…………..አርበኛ አስማማው ዋለልኝ
ምክ/ኢንዶክትሪኔሸን መምሪያ ….…………አርበኛ አዲሱ መሰለ
ምክ/የውስጥ ኦዲት መምሪያ………………..አርበኛ መ/አ ቢራራ
ምክ/ወታደራዊ መረጃና መገናኛ መምሪያ……አርበኛ ሚናስ አለማየሁ
ምክ/ጤና መምሪያ…………………………..አርበኛ ምዕራፍ ሙጨ
ምክ/እቅድ ዝግጅና ግምገማ መምሪያ……….አርበኛ መ/አ ኃይለየሱስ ታደሰ
3ኛ) ሌሎች የስራ ክፍል ኃላፊዎች፡-
የሕዝብ ሰላምና ደህንነት ከፍል…………አርበኛ መለሰ ተሾመ
ምርኮኛ አስተዳደር ከፍል …………….አርበኛ አለማየሁ ሰማ
ወታደራዊ ቃል አቀባይ………………..አርበኛ ቢኒያም አለምነህ
ቀጠናዊ ትብብር……………………...አርበኛ ዘመኑ ታደሰ
ሰማዕታት ቤተሰብ ድጋፍ ክፍል………..አርበኛ አማኑኤል ተፈራ
ስንቅ አቅርቦት ክፍል…………………..አርበኛ ክንዱ ግርማ
ሒሳብ ሹም…………………………….አርበኛ አያናው አዱኛ
መሰረተ-ልማትና ኢኮኖሚ ክፍል……..አርበኛ አበበ አመኑ
ኦርዲናንስ……………………………..አርበኛ ዳንኤል አስረስ
ፐርሶኔል …………………………….አርበኛ ዮናስ አያልቅበት
ግዥ ክፍል ………………………….አርበኝት ትዕግስት ተረፈ
ገንዘብ ያዥ……………….…………..አርበኛ መላክ ተስፋ
ሕዝብ አገልግሎት ………………….አርበኛ አለባቸው ጌጡ
ኪነ-ጥበብና መዝናኛ ክፍል…………..አርበኛ አስተውል አምሳሉ
ታሪክና ማሕደር ክፍል ……………..አርበኛ አንዷለም አሰፋ
አባት አርበኞች ማደራጃ ክፍል………አርበኛ ጌትነት ስመኝ
ማሕበራዊ ፍርድ ሸንጎ………………..አርበኛ ማናለ ገላጋይ
ፕሮጀክት ቀረፃና አስተዳደር …………አርበኛ ባንቲ ጌትነት
አፋብን ወሎ ቤተ-አምራ የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጋራ በመሆን በአገዛዙ ሰራዊት ላይ የበላይነትን በመዉሰድ ድልን ተጎናጽፈዋል !
የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር 22ኛ ክፍለ ጦር እና የ303ኛ አሳምነዉ ኮር 81ኛ ክፍለ ጦር ጥምረት በመፍጠር በጠላት ላይ በወሰዱት የማጥቃት እርምጃ የአገዛዙን ሰራዊት በርካታ ሙትና ቁስለኛ
ያደረጉት ሲሆን ከሞት የተረፉትን ቁስለኛ ሰራዊታቸውን ወደ ጋሸና እና ገረገራ በመኪና ጭነው እግሬ አውጭኝ በማለት ፈርጥጠዋል።
በዚህ አውደ ውጊያ ፍፁም የፋኖዎች የሀይል የበላይነት የተረጋገጠበት ሲሆን የአገዛዙ ሰራዊት ቅስም የተሰበረበት ትዕይንት ሆኗል!!
የአማራን ህዝብ እንደ ህዝብ ከምድረ ገፅ ለማጥፋት የገባው የአገዛዙ ሰራዊት የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች ክንድ እያከሸፉት የሚገኙት ግስላዎች የዘወትር የማንነት ሀላፊነታቸውን ተወጥተዋል። በጠላት ሰራዊት ላይ የጥምር በትራቸውን በማሳረፍና የሚታወቁት 22ኛ ክፍለጦርና 81ኛ ክፍለጦር በቀጠናቸው የአበሳውን ድርሻ ተጎናፅፈው ሲል የ106ኛ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ መረጃውን አድርሷል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሀምሌ 18/2018 ዓ/ም
+3
ማህበረሰቡ ከፋኖ ጋር በመቀናጀት ሌቦች እና ዘራፊወች ላይ እርምጃ ተወስዷል!!
➳➳➳➳💧💧💧💧➳➳➳➳
አፋብን ጎ/ጠ/ግዛት በላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር እትጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር በዛሬው እለተ ማለትም በ18/11/18 ዓ.ም ከአጊሳ; ሰለማያ; ቋሊሳ እንዲሁም ከቋሊሳ; አጊሳ ;ሰለማያ ማህበረሰቡ ለገበያ እንዲሁም ለተለያዩ ግንኙነቶች እንቅስቃሴ ለማድረግ የተቸገረበት ሁኔታ ነበር።
ዛሬም ያን የተለመደ ጸረ ህዝብ ተግባራቸውን ለመፈጸም ገበያ የሚሄደውን ማህበረሰባችን ለመዝረፍ "ቅብቲያ" የተባለ ቦታ ላይ ዝርፊያ ሲፈጽሙ ማህበረሰቡ ከእትጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር አሀድ ፋኖ ጋር በቅንጂት በዘራፊወች ላይ እርምጃ ወስዷል!!
የአካባቢው ማህበረሰብም ለፋኖ ምስጋና አቅርቧል:: እንደዚህ አይነት ተግባራት ከዚህ በኃላም ከህዝባችን ጋር በመሆን በቀጣይነት ሌባ እና ዘራፊ ላይ ተፈጻሚ እንደሚሆኑ እናሳስባለን!!
ድል ለአማራ ፋኖ
አፋብን ጎጠግበላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር
ሞት አይፈሬው፣ ለአባቶቹ ቃልና ለሃገሩ ክብር ታማኝ የሆነው የአማራ ትውልድ፣ የህዝቡን የዘመናት ታሪክ፣ ማንነትና የህልውና አደጋ በጽናት ተሸክሞ ይነሳል። ይህ ትውልድ በግፍ የሚፈሰውን የንጹሐን ወገኖቹን ደም፣ የህፃናትንና የእናቶችን እንባ ተመልክቶ እጁን አጣጥፎ የሚቀመጥ አይደለም። የህዝቡን ህልውና፣ ክብርና ቀጣይነት ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ ሲል በወገኑ ላይ የተደቀነውን የታጠቀና ያልታጠቀ ጠላት በዓይነ ቁራኛ ይከታተላል።
ክንዱን አጠንክሮ፣ ልቡን በታላቅ ወኔና ወንድሜነት ሞልቶ፣ ከምንም በላይ ለህዝቡ ነፃነት ሲል የሞትን አስፈሪነት አቃሎ ይመለከተዋል። ሞት ለእርሱ ፍርሃት ወይም ሽንፈት ሳይሆን፣ ለፍትሕና ለእውነት የሚከፈል የጀግንነት ዋጋ ነው። በመሆኑም ከጠላት ጋር በሚደረገው ማናቸውም ፍልሚያ ወደ ኋላ አያይስብም፤ በጀግንነትና በሙሉ ወኔ ፊት ለፊት ቆሞ፣ የተደቀነበትን እሳትና መከራ በደረቱ እየመከተ፣ ጠላትን በጽናትና በኃይል ይፋለማል።
ድል በግፍ ለሚጨፈጨፈው ለአማራ ህዝብ✊🏽
ድል ለአማራ ፋኖ✊🏽 #Dave #Amhara ከደጋ ዳሞት ሰማይ ሰር!!
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አርበኛ ፋኖ ዳዊት ቀፀላ ከፍተኛ አመራር የአፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ናደው ክፍለ ጦር ለወራት ያሰለጠናቸውን አዲስ ምልምል የፋኖ ኮማንዶ ሰልጣኞችን ያስተላለፈው መልክት ። መልካም የስራ እና የድል ዘመን እንመኛለን!! ወጣቱ የሸዋ ትውልድ!!
