ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Открыть в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Больше2 931
Подписчики
-124 часа
+1487 дней
+38530 дней
Архив постов
+1
።።።..ሰበር ዜና 1ብሬን 15የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እና በርካታ ተተኳሽ ገቢ ተደርጓል።
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር የአባይ ሸለቆ ተርቦች አዳራቸውን ታምር ሰርተዋል።
==========================
.....ሰኔ 27/2018 ዓ.ም
ከመርጡለ ማርያም ከተማ ዙሪያ ተከማችቶ የነበረውን የሚሊሻ ካምፕ ላይ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም በርካታወችን ሙት ፣ ቁስለኛና ምርኮ አድርገውታል። በዚህም ከ20 በላይ የአብይ ወንበር አስጠባቂ ወደ ላይኛው ሲሸኝ ከሞት የተረፈው ከካምፕ ወጥቶ እግሩ ወደመራው ሲበታተን ሁለቱ መማረክ ተችሏል ።
በተደረገው ሰልታዊ ማጥቃት 5 ባንዳ ቆስሎ ሆስፒታል የገባ ሲሆን 01ብሬን እና 15 የነብስ ወከፍ መሳሪያ እና በርካታ ተተኳሽ ጥይት ጋር ገቢ ሆኗል።
ወደማይቀረው ከተሸኙት ሚሊሻወች ውስጥም ፦
◍አስራት ዳምጤ
◍ ልዑል የተንካባው
◍ገብሩ አልማው ምክትል ሻለቃ
◍እንዳለው ጌትነት
◍ አልማው ባየ
◍አዲሱ የእነባው
◍ሹሙ
◍ መርሻ አሞኘ
◍መሰረት ምስጋን
◍ ሀብቴ
◍መሰረት ያለው
◍ገነት ተሜ እና መሰረት ደባልቄ ጥቂቶቹ ናቸው።
👉 አሁንም አልረፈደም የደም ግብር ነጋዴው አብይ አህመድ በሚጠራው የጦርነት ድግስ ውስጥ እየገባችሁ የምትማገዱ የብልፅግና ፍርፋሪ ለቃቃሚወች የአማራ ፋኖ ይቅር ባይ ነውና በይቅርታ ወደ ቤተሰባችሁ ተቀላቀሉ በማለት አሁንምጥሪ እናቀርብላቹሀለን
ነብሰ በላው የአባይ ሸለቆ ተናዳፊ ተርብ ስራ ጀምሯል🔥🔥🔥🔥
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር ይበልጣል ጥሩነህ የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ጊ/መንግስት ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን
አማራ የህልውና አደጋ የተጋረጠበት ህዝብ ብቻ ሳይሆን እየጠፋ ያለ ህዝብ ነው። እኛ ደግሞ የዚህ እየጠፋ ያለ ህዝብ ልጆች ነን ስለዚህ ይህን ህዝብ ማሰልጠን፣ማደራጀት፣ማስታጠቅ እና ማንቃት መብት ሳይሆን አማራዊ ግዴታችን ስለሆነ ይህንን የማይፈልግ /በራሱ መንገድ ባርነትን እና ውርደትን የመረጠን ህዝብ ደግሞ የመጨረሻ እጣፈንታው ምን ሊሆን እንደሚችል እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይከብድም።
ይህን ህዝብ ነፃ ለማውጣት ደግሞ ብቸኛ አማራጩ ከአለት የጠነከረ እንደብረት ምሰሶ ቀጥ ያለ በመጣ በሔደው እማይናወጥ ጠንካራ የሆነ አማራን እሚመጥን በመተማመን ላይ የተመሰረተ ድርጅት መፍጠር የግድ ይላል ይህ ደርጅት የአማራን ህዝብ ከሌሎች ወንድም ህዝቦች እሚያስበልጥ ወይም እሚያሳንስ ሳይሆን የህዝብን ሰላም እና ጥቅም በዘላቂነት ለማረጋገጥ እሚያስችል መሆን ይኖርበታል።
የእኛ አንድነት የማያወላዳ፣የማያሻማ ፣የጥንካሪያችን እና የአሸናፊነታችን ቁልፍ ምስጢር ነው ።
የትግል ስልታችንን እና የትግል መስመራችንን የአማራን ህዝብ ባህልን፣ሀይማኖትን፣ቋንቋን እና ሌሎች ሁነቶችን ያማከለ ሊሆን ይገባል። አንድነታችንን የጠላ ሁሉ የአማራ ህዝብ ታሪካዊ ጠላት እንደሆነ እራሱን በማሳመን ነገ ለሚደርስበት የታሪክ ክስ እና ፍርድ ከወዲሁ መልሱን እያዘጋጀ እንዲጠብቀን ለማሳሰብ እወዳለሁ።
በዚህ የህልውና ትግል ውስጥ የአንዱ መጠንከር ለሌላው አቅምና ጉልበት እንጂ ስጋት አይደለም ።
ፊታውራሪ ባዩ አለባቸው
አፋብን ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ !
በአንድ መድረክ ላይ ከተናገረው የተወሰደ ....
ዓፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በመርሀቤቴ አውራጃ በሬማ ከተማ በፈፀመው ልዩ ኦፕሬሽን ጠላት ሲደመሰስ፥ ጠላት ንፁሀንን ደብድቦ ረሸነ!!
ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ አምደጽዮን ኮር ዓፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በትጥቅ ትግሉ መስመር ወታደራዊ የበላይነትን እያረጋገጠ የሚገኘው የፋኖ ኃይል፣ በመርሀቤቴ አውራጃ በምትገኘው ሬማ ከተማና ዙሪያዋ ላይ ድንቅ የተቀናጀ ወታደራዊ ኦፕሬሽን መፈጸሙን የዓፄ አምደጽዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ።
ትላንት ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚንቀሳቀሰው የዓፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፣ የአገዛዙ ወታደራዊ አቅም መገለጫ ነው በሚባለው 101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ላይ ያነጣጠረ ጠንካራ ጥቃት ሰንዝሯል። ከቀኑ 6:00 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ለተከታታይ ስድስት ሰዓታት በዘለቀውና በፋኖ ከፍተኛ አመራሮች በተመራው በዚህ የአውደ ውጊያ ኦፕሬሽን፣ የፋኖ ሰራዊት ወራሪውን ኃይል ሙሉ በሙሉ ከበባ ውስጥ በማስገባት ስልታዊ የበላይነትን ተቀዳጅቷል።
የክፍለ ጦሩ አናብስቶች በአራዲት ቀበሌ፣ በቆሮ፣ በአፈር ባይኔ ቀበሌ እንዲሁም በከተማዋ ሰሜን አቅጣጫ በጠጠር አምባ መስመር በኩል ወደ መሀል ከተማ በመዝለቅ በፈጸሙት የተቀናጀ ጥቃት፦ ከ 17 በላይ የሚሆኑ የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር (ቀይ ቦኔት ለባሽ) አባላት ሙሉ በሙሉ ተደምስሰዋል። በርካታ ቁጥር ያላቸው የጠላት ኃይሎች መቁሰላቸውንና ከፍተኛ ወታደራዊ፣ ቁሳዊና ሰብአዊ ኪሳራ ማስተናገዳቸውን የግንባ መረጃዎቻችን አረጋግጠዋል።
ይሁን እንጂ በአውደ ውጊያው አይቀሬ ሽንፈት የገጠመውና በፋኖ ክንድ የደነገጠው የአገዛዙ ኃይል፣ የተለመደውን የጦር ወንጀል በንፁሃን ዜጎች ላይ በመፈጸም ፀረ-ሕዝብነቱን አሳይቷል። በመደበኛ ስራው ላይ የነበረውን የአፈር ባይኔ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ሀብታሙ በላይሁን የመከላከያ ዩኒፎርም በማልበስና የሀሰት ድራማ በመስራት በአሰቃቂ ሁኔታ የረሸኑት ሲሆን፣ በሬማ ከተማ መንገዶች፣ ግሮሰሪዎችና የህዝብ መሰብሰቢያዎች የነበሩ ንፁሃን ዜጎች ላይም የፈሪ በትራቸውን በማሳረፍ ከፍተኛ ድብደባ ፈጽመዋል።
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህንን ወታደራዊ ድል በማብሰር፣ በትጥቅ ትግሉ መስመር የሕዝብን ህልውና በተባበረ ክንድ የማስከበሩ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ለሰማዕታት የሚገባው ክብር ሁሉ እንደሚሰጥ በፅኑ አረጋግጧል።
"ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
“ለከበባ የመጣ ጠላት በቆረጣ
ሲቀጠቀጥ ውሏል።”
ዛሬ ሰኔ 26/2018 ዓም ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ የ208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር፣ ደጃች አያሌው ብሩ ክፍለ ጦርን ለመደምሰስ የተንቀሳቀሰው ወራሪ ሠራዊት ቀድመው መንቀሳቀሻ በሩን ደፈጣ ጥለው የጠበቁት የክፍለ ጦሩ ሠራዊት አባላት ክፉኛ ተመትቷል።
አማራ ጠሉ የአብይ ቅጥረኛ ሰራዊት በዛሬው ዕለት በቦዛ ግንባር በሦስት አቅጣጫ፣
በዳባት፣ በጭና፣ በአብጠራ፣ በ13፣ በአንድ አይጠጣሽ አቅጣጫዎች
ከዘጠኝ በላይ ዲሽቃና ሌሎችን ሜካናይዝድ ጦር አቀናጅቶ፣ በርካታ ሠራዊት አሰማርቶ ያቀደው እቅድ በነበልባሎቹ ብርቱ ክንድ ደቅቋል። ውጊያው እስከዚህ ሰዓት እንደቀጠለ ሲሆን በርካታ የአገዛዙ ሠራዊት እንደ ቅጠል ረግፏል።
ውጊያው በበላይ እዝ ከፍተኛ አመራር አርበኛ አራጋው እንዳለ፣ በኮሩ ዋና ዘመቻ መምሪያ
50 አለቃ አሥራት፣ የኮሩ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ ኢንጂኒየር ፃድቅ ዋለልኝ እንዲሁም በክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ አርበኛ ክቡሬ ፊታውራሪነት የተመራ ውጤታማ ተጋድሎ ተከናውኗል። አሁን በዚህ ሰዓት የኮሩ ሌላኛው የክፍለ ጦር አሐድ የሆነው የሰሜን አምባራስ ክፍለ ጦር ሠራዊት ስምሪት ወስዶ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል።
የአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ
208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር
ደጃች አያሌው ብሩ ክፍለ ጦር
የፊስቡክ አካውንታችን ከዚህ በታች ያለውን የፊስቡክ ሊንክ በመንካት ሸር ጆይን በማድርግ ይወዳጁን!!
https://www.facebook.com/share/1JVuJ9cNyB/
+4
201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር 2እጁ እነሴ ወረዳ ህዝባዊ ውይይቶች እንደቀጠሉ ናቸው!!
^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^
~~~
ሰኔ26/2018ዓ.ም
ያለ አንዳች መካሪና ተቆርቋሪ፥ ያለ አንድ ሰው ሃሳብ አበዳሪ ከመከራው ተምሮ፥ ከራሱ መክሮ #አማራ የራሱን አቢዮት ራሱ ፈጠረ።ሲነሳ በደነገጡት ጠላቶቹ ፊት ራሱን በፍጥነት #አደራጅቶ የህልውና ትግሉን ጀመረ።እፍኝ የማትሞላ ተተኳሽ በመቶ ሽዎች ብር እየገዛ፥ ታጣቂም አስታጣቂም ራሱ ሆኖ ወደ ራሱ ግብ መገስገስ ቀጠለ እንዲል መሪው አረበኛ ዘመነ ካሴ አማራ የራሱን መንግስትነት በጊዜዊነት እያሳደገ ይገኛል።
ዛሬ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር 2እጁ እነሴ ወረዳ ገዳም አቦ ቀበሌ ሰፊ ህዝባዊ ውይይት የወረዳው ጊዜአዊ መንግስት አካሒዳል።
የአብይ አህመድን መንግስት ነኝ ድስኩርና የጋሻጃግሬዎችን አሁናዊ የጭንቀት እንቅስቃሴ ያብራራና የህዝብን የኃላ ደጀንነት በፋኖ አደረጃጀት በሚገባ እየተመራ መሆኑን በመድረኩ ተብራርቷል።
በቀጠናው እያንዣበበ ያለውን ህዝብን ትጥቅ አስፈታለው የጠላት እቅድ በየደረጃው ያለው የማህበረሰብ ክፍል በተጠንቀቅ እንደቆመና ለመመከት ዝግጁ እንደሆነ ንግግር ተደርጓል።
በፋኖ መንግስታዊ መዋቅር ጊዜአዊ መንግስቱ የህዝብን ሁለንተናዊ ችግር በመረዳት የፍትህና የሰላም ችግሮችን ቀበሌው ድረስ በመምጣት ትላልቅ አባቶችን በመያዝ እየፈቱ ነው በማለት በአደረጃጀቱ ደስታቸውን የቀበሌው ማህበረሰብ ገልፀዋል!!
እናደራጃለን!
አማራዊ ስነልቦና እንገነባለን!!
አማራነት ያሸንፋል!!
አዲስ ትውልድ!! አዲስ አስተሳሰብ!! አዲስ ተስፋ!!
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር 2እጁ እነሴ ወረዳ ሚዲያ ክፍል
የቴክኖሎጂ የበላይነት በአማራ ፋኖ ፊት ያለውን አቅም አልባነት የታየበት ክስተት
የአንድ ስርዓት የመጨረሻው የመውደቂያ ምልክት የሚጀምረው የሚተማመንባቸው ተቋማዊና ወታደራዊ መዋቅሮች ትርጉም ማጣት ሲጀምሩ ነው። ዛሬ በሜጫ ሰማይ ስር የታየው የብልፅግና የመጨረሻው ዘመናዊ ምሽግ የሆነው ድሮን ቴክኖሎጅ በደቂቃዎች ውስጥ መከስከስ የወታደራዊ ቁስ መውደም ብቻ ሳይሆን፣ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የቴክኖሎጂ የበላይነት በአማራ ፋኖ ፊት ያለውን አቅም አልባነት ያሳየበት የታሪክ ምዕራፍ ነው።
የብልፅግናው ወንበዴ ስርዓት በህዝቡ ዘንድ ፖለቲካዊ ቅቡልነት ስላጣ በሰራዊቱ ውስጥ መከፋፈል መፈጠሩና በሞራል ዝቅጠት ሲታመስ፣ የመጨረሻ መሸሸጊያውን በድሮንና በከባድ መሳሪያዎች ላይ አድርጎ ይገኛል። ይሁን እንጂ፣ ዛሬ በሜጫ የታየው ክስተት የብልፅግና ስርዓት ዛሬ ላይ አለኝ የሚለውን የድሮን ቴክኖሎጂ እንኳን ወጥቶ መግባት የማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል። ይህ የእብድ ስብስብ የሆነው ብልፅግና የጉዞ አቅጣጫው ጠፍቶበት እየፈራረሰ ያለ ስርዓት ነው።
የአማራ ፋኖ ዛሬ የተለመደው የሽምቅ ተዋጊ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም ጥልቅ ማህበራዊ መሰረት ያለውና የህዝብን የህልውና ጥያቄ የተሸከመ ኃይል ነው። የዛሬው የሜጫው ክስተት ፋኖ በመሬት ላይ ያለውን ቁጥጥር ወደ አየር ክልል የበላይነት ማሳጣት እያሸጋገረው መሆኑን ነው። አሁን አሁን በዘመናዊ ጦርነት ውስጥ ድል የሚገኘው በድሮን ብዛት ሳይሆን በዓላማ ፅናት መሆኑን ነው። ፋኖ በህዝብ ደጀንነትና በፍትሃዊ ዓላማ የታጠቀ በመሆኑ፣ የብልፅግናን የቴክኖሎጂ የበላይነት ወደ ስነ-ልቦናዊ ሽንፈት እየቀየረው ይገኛል። የድሮኑ መከስከስ የብልፅግናን የመጨረሻ ምሽግ ሰባብሮታል።
በሜጫ ሰማይ ስር የተከሰከሰው ድሮን እንዲሁ የብረት ስባሪ ብቻ አይደለም፤ የአንድ ጨቋኝና አቅጣጫውን የሳተ ስርዓት ውድቀት መቃብር ላይ የሚጻፍ መታሰቢያ ነው። ፋኖ በታሪክ ፊት እውነትንና ፍትህን አንግቦ እያደረገ ያለው ጉዞ፣ ወደ ታላቅ ድል እያመራ መሆኑን ይህ ክስተት ያረጋግጣል። ታሪክ ይህንን ጊዜ የጥቁር ህዝብ የነጻነት ተምሳሌት የሆነችው ሀገር፣ በልጆቿ መስዋዕትነት ዳግም የተወለደችበት ወቅት ብለው እንደሚዘግቡት ጥርጥር የለውም።
ታሪክ በድል አድራጊዎች ብዕር ይፃፋል!
ቀን 26/10/2018 ዓ.ም
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወቅታዊ መግለጫ
“የአማራን ሕዝብ በሴራና በክህደት የማንበርከክ ዕቅድ በቆራጥነት ይመከታል!”
ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በተለይም ለተከበርከው የአማራ ሕዝብ ገዥው ሥርዓት የአማራን ሕዝብ የህልውና ትግል ለማደናቀፍ በሃይልም ሆነ በውስጥ ሴራ ለማዳከም ሌት ከቀን እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የስርዓቱን አጠቃላይ የክረምት ስልታዊ ዕቅድና የወታደራዊ ቅኝት እንቅስቃሴን በጥብቅ በመከታተል፣ መረጃዎችን አደራጅቶ ለፀጥታ መዋቅሩና ለሕዝቡ የሚከተለውን ወቅታዊ መግለጫና ጥሪ ያቀርባል።
1. ለፀጥታ ኃይሉ (ሚሊሻ፣ ፖሊስና ሰላም አስከባሪ) የቀረበ አጣዳፊ የህልውና ጥሪ
ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ የአማራ ክልል ፀጥታ ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ ደጀኔ ልመንህ የሰ/ሸዋ ዞን እና ደ/ብርሀን ሜትሮ
ፖሊታን ከተማ የብልፅግና ካድሬን አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቶ ያስተላለፈው ውሳኔ ከሰሜን ሸዋ ከየወረዳ የሚውጣጣ 370 ከደ/ብርሀን 150 በድምሩ=520 ፖሊስ፣ከሰሜን ሸዋ ከየወረዳ የሚውጣጣ 1700 እና ከደ/ብርሀን 800 በድምሩ =2500 ሚኒሻ በአጠቃላይ ከ3000 በላይ ሚኒሻና ፖሊስ ከነ ሙሉ ትጥቁ ተመልምሏል ። ይህ ፕሮግራም በአማራ ክልል በሁሉም ዞኖች የሚደረግ ሲሆን የምስራቅ አማራው ቡርቃ፣ የጎንደር ፣የጎጃም በሚል በሰዎስት ማእከል ሰልጥኖ ካጠናቀቀ በኋላ ከመከላከያ ጋር ተፈውዞ በራሱ ማህበረሰብ ላይ ሊዘምት መዘጋጀቱን ከውስጥ የመረጃ ምንጫችን አረጋግጠናል ።
መልእክታችን ወንድሞቻችን የሆናችሁ የሚሊሻ፣ የፖሊስና የሰላም አስከባሪ አባላት! በእናንተ ላይ የተጣለባችሁ “ወደ ስልጠና ማዕከላት ገብቶ የመሰልጠን” አስገዳጅ ትዕዛዝ፣ ዓላማው እናንተን ለማብቃት ሳይሆን በገዛ ወገኖቻችሁ ላይ እንድትዘምቱና ለወንድማማች የዘር ፍጅት እርስ በእርስ እንድትጨራረሱ የተደገሰላችሁ የሞት ወጥመድ መሆኑን ከወዲሁ እንድትገነዘቡት እንፈልጋለን። ሥርዓቱ የራሱን ዕድሜ ለማራዘም እናንተን እንደ ጭዳ ከፊት አሰልፎ በገዛ እናትና አባቶቻችሁ፣ በገዛ ወንድሞቻችሁ ላይ ሊያዘምታችሁ ቆርጦ ተነስቷል።
ስለሆነም፣ ለዚህ እኩይና የክህደት ተግባር ፍጹም ተባባሪ እንዳትሆኑ፤ ይህንን የጥፋት መዋቅርና የስርዓቱን ሰንሰለት በመበጠስ ከወዲሁ በመውጣት ወደ ወገን ዘመዳችሁ፣ የአብራካችሁ ክፋይ ወደሆነው የፋኖ ኃይልና ወደ ሕዝባችሁ እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናቀርባለን። ሕዝባችሁና የህዝብ ልጅ የሆነው ፋኖ ሁልጊዜም እቅፋቸውን ከፍተው ሊቀበሏችሁ ዝግጁ ናቸው።
2. በሴራና በገንዘብ የህልዉና ታጋዩን የመከፋፈል ሙከራን በተመለከተ
የጠላት ቀጣይ ዕቅድ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በመመደብ፣ በፋኖ የድርጅት፣ የኮር አመራሮችና በታችኛው መዋቅር ውስጥ ሰርገው የሚገቡ ሰላዮችን በመመልመል፣ በመካከላችን ጥርጣሬንና መከፋፈልን መፍጠር እንደሆነ በግልጽ አውቀነዋል።
መልእክታችን፦ የአሳምነው ዕዝ አመራሮችና የፋኖ አባላት ከመቼውም ጊዜ በላይ የተሳሰሩና የአማራን ሕዝብ ጥያቄ በፅናት የሚያስከብሩ እንጂ በገንዘብ የማይደለሉ መሆናቸውን እናረጋግጣለን። በውስጣችን ሰርጎ ገቦችን ለመለየትና የጠላትን የውስጥ ሴራ ለማክሸፍ የደህንነት መዋቅራችን በንቃት እየሰራ ይገኛል።
3. የአመራሮችን እንቅስቃሴ ለይቶ የማጥቃት ስልትን በተመለከተ
ጠላት የፋኖ አመራሮች የሚያድሩበትንና የሚንቀሳቀሱበትን ቦታዎች በመለየት፣ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍሎም ቢሆን ከበባ በማድረግ የመግደልና በቅርብ ሰዎቻቸው የማስመታት ጥቁር ዕቅድ ቀርጿል።
መልእክታችን፦ ለሁሉም የዕዛችን አመራሮችና ታችኛው መዋቅር ጥብቅ የወታደራዊና የደህንነት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መመሪያ አስተላልፈናል። የአንድ አመራር መውደቅ ትግሉን እንደማያቆመው ጠላት ሊያውቀው ይገባል። ይልቁንም ይህ ዓይነቱ የጭካኔ ዕቅድ ይበልጥ እንድንጠነክርና እንድንደራጅ ያደርገናል።
4. በስርዓቱ መዋቅር ውስጥ ያሉ ደጋፊዎቻችንን የማጽዳት ዘመቻ:-ስርዓቱ በመዋቅሩ፣ በፖለቲካ አመራሩና በባለሀብቱ ውስጥ ለፋኖ መረጃና ሎጂስቲክስ የሚያቀርቡትን የውስጥ አርበኞች የማሰርና የማጥፋት ዘመቻ ለመጀመር አቅዷል።
መልእክታችን፦ ከጎናችን ለቆማችሁና መረጃ ለምታቀብሉን የቁርጥ ቀን የአማራ ልጆች በሙሉ፦ ጠላት ሊያደርግ የሚችለውን አፈና በመገመት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንድታደርጉና የደህንነት አሠራራችሁን እንድትቀይሩእናሳስባለን።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ
ሰኔ 2018 ዓ.ም
ቀን 26/10/2018 ዓ.ም
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወቅታዊ መግለጫ
“የአማራን ሕዝብ በሴራና በክህደት የማንበርከክ ዕቅድ በቆራጥነት ይመከታል!”
ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በተለይም ለተከበርከው የአማራ ሕዝብ ገዥው ሥርዓት የአማራን ሕዝብ የህልውና ትግል ለማደናቀፍ በሃይልም ሆነ በውስጥ ሴራ ለማዳከም ሌት ከቀን እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የስርዓቱን አጠቃላይ የክረምት ስልታዊ ዕቅድና የወታደራዊ ቅኝት እንቅስቃሴን በጥብቅ በመከታተል፣ መረጃዎችን አደራጅቶ ለፀጥታ መዋቅሩና ለሕዝቡ የሚከተለውን ወቅታዊ መግለጫና ጥሪ ያቀርባል።
1. ለፀጥታ ኃይሉ (ሚሊሻ፣ ፖሊስና ሰላም አስከባሪ) የቀረበ አጣዳፊ የህልውና ጥሪ
ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ የአማራ ክልል ፀጥታ ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ ደጀኔ ልመንህ የሰ/ሸዋ ዞን እና ደ/ብርሀን ሜትሮ
ፖሊታን ከተማ የብልፅግና ካድሬን አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቶ ያስተላለፈው ውሳኔ ከሰሜን ሸዋ ከየወረዳ የሚውጣጣ 370 ከደ/ብርሀን 150 በድምሩ=520 ፖሊስ፣ከሰሜን ሸዋ ከየወረዳ የሚውጣጣ 1700 እና ከደ/ብርሀን 800 በድምሩ =2500 ሚኒሻ በአጠቃላይ ከ3000 በላይ ሚኒሻና ፖሊስ ከነ ሙሉ ትጥቁ ተመልምሏል ። ይህ ፕሮግራም በአማራ ክልል በሁሉም ዞኖች የሚደረግ ሲሆን የምስራቅ አማራው ቡርቃ፣ የጎንደር ፣የጎጃም በሚል በሰዎስት ማእከል ሰልጥኖ ካጠናቀቀ በኋላ ከመከላከያ ጋር ተፈውዞ በራሱ ማህበረሰብ ላይ ሊዘምት መዘጋጀቱን ከውስጥ የመረጃ ምንጫችን አረጋግጠናል ።
መልእክታችን ወንድሞቻችን የሆናችሁ የሚሊሻ፣ የፖሊስና የሰላም አስከባሪ አባላት! በእናንተ ላይ የተጣለባችሁ “ወደ ስልጠና ማዕከላት ገብቶ የመሰልጠን” አስገዳጅ ትዕዛዝ፣ ዓላማው እናንተን ለማብቃት ሳይሆን በገዛ ወገኖቻችሁ ላይ እንድትዘምቱና ለወንድማማች የዘር ፍጅት እርስ በእርስ እንድትጨራረሱ የተደገሰላችሁ የሞት ወጥመድ መሆኑን ከወዲሁ እንድትገነዘቡት እንፈልጋለን። ሥርዓቱ የራሱን ዕድሜ ለማራዘም እናንተን እንደ ጭዳ ከፊት አሰልፎ በገዛ እናትና አባቶቻችሁ፣ በገዛ ወንድሞቻችሁ ላይ ሊያዘምታችሁ ቆርጦ ተነስቷል።
ስለሆነም፣ ለዚህ እኩይና የክህደት ተግባር ፍጹም ተባባሪ እንዳትሆኑ፤ ይህንን የጥፋት መዋቅርና የስርዓቱን ሰንሰለት በመበጠስ ከወዲሁ በመውጣት ወደ ወገን ዘመዳችሁ፣ የአብራካችሁ ክፋይ ወደሆነው የፋኖ ኃይልና ወደ ሕዝባችሁ እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናቀርባለን። ሕዝባችሁና የህዝብ ልጅ የሆነው ፋኖ ሁልጊዜም እቅፋቸውን ከፍተው ሊቀበሏችሁ ዝግጁ ናቸው።
2. በሴራና በገንዘብ የህልዉና ታጋዩን የመከፋፈል ሙከራን በተመለከተ
የጠላት ቀጣይ ዕቅድ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በመመደብ፣ በፋኖ የድርጅት፣ የኮር አመራሮችና በታችኛው መዋቅር ውስጥ ሰርገው የሚገቡ ሰላዮችን በመመልመል፣ በመካከላችን ጥርጣሬንና መከፋፈልን መፍጠር እንደሆነ በግልጽ አውቀነዋል።
መልእክታችን፦ የአሳምነው ዕዝ አመራሮችና የፋኖ አባላት ከመቼውም ጊዜ በላይ የተሳሰሩና የአማራን ሕዝብ ጥያቄ በፅናት የሚያስከብሩ እንጂ በገንዘብ የማይደለሉ መሆናቸውን እናረጋግጣለን። በውስጣችን ሰርጎ ገቦችን ለመለየትና የጠላትን የውስጥ ሴራ ለማክሸፍ የደህንነት መዋቅራችን በንቃት እየሰራ ይገኛል።
3. የአመራሮችን እንቅስቃሴ ለይቶ የማጥቃት ስልትን በተመለከተ
ጠላት የፋኖ አመራሮች የሚያድሩበትንና የሚንቀሳቀሱበትን ቦታዎች በመለየት፣ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍሎም ቢሆን ከበባ በማድረግ የመግደልና በቅርብ ሰዎቻቸው የማስመታት ጥቁር ዕቅድ ቀርጿል።
መልእክታችን፦ ለሁሉም የዕዛችን አመራሮችና ታችኛው መዋቅር ጥብቅ የወታደራዊና የደህንነት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መመሪያ አስተላልፈናል። የአንድ አመራር መውደቅ ትግሉን እንደማያቆመው ጠላት ሊያውቀው ይገባል። ይልቁንም ይህ ዓይነቱ የጭካኔ ዕቅድ ይበልጥ እንድንጠነክርና እንድንደራጅ ያደርገናል።
4. በስርዓቱ መዋቅር ውስጥ ያሉ ደጋፊዎቻችንን የማጽዳት ዘመቻ:-ስርዓቱ በመዋቅሩ፣ በፖለቲካ አመራሩና በባለሀብቱ ውስጥ ለፋኖ መረጃና ሎጂስቲክስ የሚያቀርቡትን የውስጥ አርበኞች የማሰርና የማጥፋት ዘመቻ ለመጀመር አቅዷል።
መልእክታችን፦ ከጎናችን ለቆማችሁና መረጃ ለምታቀብሉን የቁርጥ ቀን የአማራ ልጆች በሙሉ፦ ጠላት ሊያደርግ የሚችለውን አፈና በመገመት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንድታደርጉና የደህንነት አሠራራችሁን እንድትቀይሩእናሳስባለን።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ
ሰኔ 2018 ዓ.ም
በአንፆኪያ ገምዛ የፋኖን ወቅታዊ ቁመናና የትግሉን ገፊ ምክንያቶች የገመገመ ታላቅ የህዝብ መድረክ ተካሄደ!!
ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም።
በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ፣ አንፆኪያ ገምዛ ክላስተር፣ በአሰለሌ ቀለበት ወንበር ቀበሌ የፋኖን ወቅታዊ የትግል ቁመና እና የወቅታዊ የጠላትን አቋም የገመገመ ታላቅ የህዝብ ስብሰባ ተካሂዷል። "በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር የፋኖ ወቅታዊ ቁመና እና የትግሉ ገፊ ምክንያቶች" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ የአካባቢው ማህበረሰብ በነቂስ ወጥቶ ተሳትፏል።
በመድረኩ ላይ የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፣ የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር እና የአስቴ ጉማ ተራራ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የቀጠናው ህዝባዊ አስተዳደር ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
በዕለቱ በተካሄደው ሰፊ ውይይት የትግሉ መነሻ የሆኑ መሰረታዊ ገፊ ምክንያቶች በዝርዝር ቀርበዋል። የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወታደራዊ ቃል አቀባይ ፋኖ መምህር መንግስቱ፤ አገዛዙ በአንፆኪያ ገምዛ ቀጠና ላይ አቅዶና አስልቶ ያደረሰውን ዘርፈ-ብዙ ጥፋት በማንሳት ለማህበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥቷል።
የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ በበኩሉ፣ የፋኖን ወታደራዊ ግስጋሴና በየግንባሩ የተመዘገቡ ድሎችን አብራርቷል። በተለይም "በዘመቻ አንሻ ሰይድ" አማካኝነት በአካባቢው ሊከናወን የታሰበውን ምርጫ ሙሉ በሙሉ ማስተጓጎል መቻሉ የትግሉ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጾ፤ በአንጻሩ የጠላት ጦር መዋቅር እየፈረሰና ኃይሉ በየግንባሩ እየተበተነ መምጣቱን አስታውቋል።
ይህ ህዝባዊ መድረክ የትግሉን ቀጣይ አቅጣጫዎች ከማስቀመጥ ባለፈ፣ ማህበረሰቡ ለነፃነት ትግሉ እያደረገ ያለውን አስተዋፅኦ ያበረታታበት ነበር። አርበኛ አበበ ሙላቱ በቁርጠኝነታቸው ለሌሎች አርአያ የሆኑ ግለሰቦችን መርጦ ልዩ የዕውቅና ሽልማት አበርክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም በትግሉ ነፃ የወጡ አካባቢዎችን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅና የህዝብ አገልግሎትን ለማስቀጠል የሚያስችል አዲስ የቀበሌ መዋቅርና የአስተዳደር አመራሮች ሹመት በይፋ ተከናውኗል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ አርበኛ አበበ ሙላቱ ባደረገው ንግግር፣ የፋኖ የትግል ጉዞ በታላቅ ድል እንደሚጠናቀቅ በልበ-ሙሉነት ገልጿል።
"የአንድነታችን ውጤት ወደፊት በስራ እና በተግባር የምናየው ይሆናል" በማለት የህዝብና የፋኖ የጋራ ክንድ ያለውን የጎላ ሚና ያብራራው አርበኛው፤ ለአሰለሌ ቀለበት ወንበር ቀበሌ ህዝብም "ጠንካራ ናችሁ በርቱ" በማለት የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን አቅርቧል።
ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!!
ድል ለአፋብን!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!
ስር-ነቀል ለውጥ በተባበረ ክንዳችን!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም።
አየር ወለድ ኮማንዶ የነበረው ወጣት ዛሬ ደግሞ በፋኖነት ታሪክ እየሰራ ነው::
ገና ትግሉ ሲጠነሰስ እሱ በፒካፕ ተሳፍሮ ሲጓዝ ጠላት ሊያፍነው መንገድ ላይ ደፍጦ ጠብቆ ተኩስ ሲከፍትበት ከመኪናይቱ ላይ እንደ ወፍ በመብረር ዘሎ በመከረባበት ጠላት መሀል ገብቶ በታትኗቸው ሀገር ጉድ አስብሏል::
የተለያዩ አውደ ውጊያዎች ላይ ተሳትፏል:: ጥይት አሁን ድረስ ሰውነቱ ውስጥ አለ:: ትግሉ ሲያልቅ እታከማለሁ ብሎ ጥርሱም ነክሶ እየታገለ እና እያታገለ ነው::
በርካታ ወጣቶችን አሰልጥኗል::
አሰልጣኝ የማይመረቅ ሰልጣኝ ነው እንድሉ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል የሰለጠነ የሰው ሀይል በማፍራቱ ሂደት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው::
እየነገርኳችሁ ያለሁት ስለ መካነሰላሙ ጀግና ኮማንዶ ጀንበሩ ጌታቸው ነው::
አየር ወለድ በራሪ ነብር የሚል ፅሁፍ ልብሱ ላይ ይታያል:: በራሪ ነብር መሆኑን እኛም እንመሰክራለን::
ጀንቤ በርታ ወንድምሰው:)
