ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Открыть в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Больше2 923
Подписчики
+3224 часа
+3727 дней
+36630 дней
Архив постов
+2
ሰበር የድል ዜና የአፋብን፤ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፤206ኛ ኮር/የ14ኛ ክ/ጦር አካል የሆነችው የእሳት ነበልባሏ የበረኸኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃ ድል ተቀዳጀች!!!
ዛሬ በቀን 21/12/2018ዓ,ም ከሌሊቱ 8:00ስዓት በተጠና ኦፕሬሺን በደብረኤልያስ ወረዳ ልዩቦታው አበሸም በተባለ ት/ቤት መሺጎ በነበረው የአብይ አህመድ ዙፋን አስጠባቂ የአድማብተና የሚሊሻ አባላት ላይ መብረቃዊ! ጥቃት በማድረስ ሙትና ቁስለኛ ማድርግ ተችሏል::
ተችሏል ::
በኦፕሬሺኑ የተገኙ ድሎች:-
👉በእጅ የተማረከ=አንድ ሚሊሻ
👉 ኮሪያ ክላሺ =አንድ
👉ሲሶክላሲ =አንድ
👉በርካታ ተተኳሺ
👉በርካታ ወታደራዊ ሻጣ
👉ለጊዜውበቁጥር ያልታወቀ የድማ ብተና እና ሚሊሻ አባል ሙትናቁስለኛ ማድረግ ተችሏል::
ነሃሴ 21/12/2018አዓ,ም
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳስብ!!አዲስ ተስፋ የአፋብን፤ቴዎድሮ2ኛ ዕዝ/206ኛ ኮር/የ14ኛክ/ጦር ህዝብግንኙነት መምሪያ
+2
የንስሩ አርበኛ የቁርጥ ቀን ልጅ እና የህዝብ ፍቅር! እኔ በታሪክና በውጊያ ሜዳ በርካታ የቆረጡ የአማራ ጀግኖችን አውቃለሁ፤ ለወገናቸው ዋጋ የከፈሉ ህያው ስሞችንም አጠናለሁ።
ነገር ግን ከእነዚህ ሁሉ መካከል እንደ ንስር ከተራራ ተወርውሮ ጠላትን የሚያስበርድ፣ በውጊያ ስልቱ ወደር የሌለው አንድ ልዩ የአማራ ልጅ አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ኢሳይያስ ደመቀ ነው!
ምርጥ አዛዥነትና የጦር ሜዳ ብቃት፦ አርበኛ ኢሳይያስን ልዩ የሚያደርገው በጦር ሜዳ ያለው የብረት ያህል የጠነከረ ጀግንነቱ ብቻ አይደለም። ፈጣን ውሳኔ የመስጠት ብቃቱና የውጊያ ስልቱ ከታችኛው ተራ ሰራዊት እስከ ከፍተኛ አመራሩ ድረስ ሙሉ አክብሮትና ታዛዥነትን አትርፎለታል።
❤️ኢሱ ልብ የሚነካው የህፃናት ስስት፦ ከወታደራዊ ግርማ ሞገሱ ይልቅ ግን ስሜትን የሚያንቀሳቅሰው የእሱና የህዝቡ ግንኙነት ነው! በተለይም የአማራ ህፃናት እሱን ሲያዩ የሚያሳዩት የስስት፣ የኩራት እና የአድናቆት አስተያየት የሰውን ልብ ይነካል፤ ህፃናቱ የሚያዩት እንደ ወታደራዊ አዛዥ ብቻ ሳይሆን፣ ከፊት የሚቆምላቸው ታላቅ ወንድማቸው አድርገው ነው።
✨ የነገዋ የወታደራዊና የኢትዮጵያ ታላቅ ጀነራል አርበኛ ኢሳይያስ ደመቀ! ሰናይ ሌሊት ይሁንላችሁ ወዳጆቼ! #Dave #Amhara
በምስራቅ ወለጋ ጊዳ ወረዳ አንዶዴ ድቾ ቀበሌ በቢዛሞ ፋኖ ሽንፈት የተከናነበው የገዳ ኮማንዶ ለእምነታቸው የመነኑ ቀሳውስት፣ ቆሞስና ሴቶችን በግፍ ረሽኗል።
በአንዶዴ ድቾ ስላሴ ቤተክርስቲያን ኪዳን በማድረስ ላይ የሚገኙት በግፍ ከተረሸኑት መካከል ቆሞስ አባ ታደሠ መኮንን ይገኙበታል።
ቆሞስ አባ ታደሠ መኮንን በጊዳ ወረዳ ሀገረ ስብከት አንዶዴ ስላሴ ለአካባቢው ማህበረሰብ በመልካም አስተምሮና እኔ የስላሴ ባሪያ ነኝ በማለት፤ ለስላሴ ግልጋሎት ኪዳን ከሚቋረጥ በክብር መስዋት እመርጣለሁ አንጂ ስጋየን ለሚገል አህዛብ እምነቴን አጸናለሁ በማለት በቆረቆሩትና ስላሴ ቤተክርስቲያን ውስጥ በጨካኞች ተገለዋል።
ወንድማለም መንፈሳዊ አባቴ ነፍስዎን በአጸደ ገነት ያሳርፍልን በረከትዎ ይደርብን።
በሰዴ ወረዳ የቆሎ ተማሪወች እና ህዝቡ ላይ በምሽት ቤት በማስከፈት ዝርፊያ እና ጥቃት ተፈፀመባቸው።
========================
.........ነሐሴ20/2018 ዓ.ም
የከሰረዉ እና በውድቀት ጎዳና ላይ ያለው የብልፅግና ስርዓት አማራ ጠልነቱን በይፋ በድሮን እና በከባድ መሳሪያ መከራዉን እያበዛ የሚችለዉን ሁሉ እያደረገ ይገኛል።
የፋኖን በትር መቆቋም ያቃተዉ ሆድ አደሩ እራሱን ጠልቶ ለአብይ የሚያሽቃብጠዉ የብልፅግና ሚሊሻ እና የፖሊስ አመራር ሰዴ ከተማ ዉስጥ ሌሊት እየተቀሳቀሰ በጨለማ ጭብል በመልበስ ከንፁሀን ማህበረሰብ ቤት እያስከፈተ መዝረፉን ቀጥሏል ።
ማለትም ነሐሴ18/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 2:00 ሰዓት ላይ ዉዱ ከሚባል ባለሱቅ በቀዳዳ ብር የወሰዱ ሲሆን አንድ የቆሎ ተማሪ 1.ኤልያስ አለህኝ የተባለ ደግሞ ቤት ክፈት ብለዉ ሊዘርፉት ሲሞክሩ አልከፍትም ሲላቸዉ በጥይት መተዉታል እና ሌላም በርካታ ነጋዴወች በዚህ መልኩ ገንዘብ እየተዘረፉ ስለሆነ እና ወጣትም ሊያፍሱ ስለሆነ የሰዴ ወረዳ ማህበረሰቦች ከእንዲህ አይነት ሌባ እና ቀማኛ ስርዓት እራሳቹህን እንድጠብቁ ስንል የጥንቃቄ መልክታችን እናሳዉቃለን።
የ201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የሰዴ ወረዳ ጊ/መንግስት አስተዳደር ሚዲያ እና ህ/ግንኙነት ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም
ድል ለአማራ ፋኖ ክብር በጀግንነት ለተሰዉ ሰማእታት
አዲስ ትዉልድ፣ አዲስ ተስፋ አዲስ፣ አስተሳሰብ
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለትና ቡልጋ አውረጃ የአፋብን የትግል አቅጣጫዎችና መዋቅራዊ አሰራሮች ላይ ያተኮረ በርካታ ህዝባዊ መድረክና ስልጠና ሲካሄድ መቆዬቱ ተገለፀ !!
ቀን 20/12/2018 ዓ.ም
◊◊◊◊◊◊◊◊◊◊◊◊◊◊◊◊◊
በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ በግፍት ክላስተር ስር በሚገኙት ቀበሌዎች ለወራት ማደራጀት ፣ማሰልጠንና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሰፊ ህዝባዊ የምክክር መድረክ ሲካሄድ መቆዬቱ ተገለፀ።
በዚህ ታላቅ ህዝባዊ የምክክር መድረክና ስልጠና በአካባቢው ያሉ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሁነቶች በጥልቀት የገመገመ ሲሆን፣ የህዝቡን ተሳትፎ የሚያሳድጉ ሀሳቦች ተነስተው ሰፊ ሀሳብ ተሰጥቶባቸው ወደ ተግባር ተገብቷል።
ይህ ህዝባዊ የውይይትና የአደረጃጀት የመዘርጋትና የሀሳብ ማጥራት ውይይት ነገ ለሚካሄደው ሁሉን አቀፍ ህዝባዊ ትግል ጠንካራ መሠረት የጣለ ሲሆን፣ ህዝቡ በንቃት በመሳተፍ አማራዊ የፖለቲካ ቀጣይነት ውሳኔዎች ላይ ቀጥተኛ ድርሻ እንዲኖረው መንገድ የሚከፍት ነው ተብሏል።በመሆኑም የተጀመሩ የአሰራርና የመዋቅር ስራዎች በቀጣይነት ውጤታማ እንዲሆኑ የሚረዱ አሰራሮችና የሃላፊነት ድልድሎች ላይ ውይይት በማድረግ በክላስተርና በቀበሌ ደረጃ መሪዎች ተመርጠው ወቅቱን እና ሀላፊነታቸውን የሚመጥኑ ስልጠና መስጠት ተችሏል።
በስልጠናው ላይ ድርጅታችን አፋብን የሚያወርዳቸውን የትግል አቅጣጫዎች በመተግበር የትግሉን ውጤታማነት ማፋጠን እንደሚገባ የክላስተርና የቀበሌው የውይይት ተሳታፊ የማህበረሰብ ክፍልና አመራሮች በአፅንኦት ገልፀዋል። በተለይም አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ትኩረቱን በትግሉ ላይ ብቻ እንዲያደርግ የጋራ ግንዛቤ የተያዘ ሲሆን፣ ህዝቡም በተዘረጋው ግልጽ መዋቅርና በሰለጠኑ መሪዎች አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ስር ሙሉ ፍላጎቱንና መብቱን የሚያረጋግጥበት አሰራር መዘርጋቱ ተመልክቷል።
በውይይቱ ወቅት የሸዋ ህዝብ በህልውናውናውና በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የማይደራደር መሆኑና ለፍትህና እኩልነት የሚደረገውን ትግል አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል። በተጨማሪም በወታደራዊና በአስተዳደራዊ መዋቅሮች ውስጥ ያሉ ክፍተቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻሉ መምጣታቸውና ሰራዊቱም ህዝባዊነቱን በአሰራር ማረጋገጡ ተብራርቷል።
በመጨረሻም ከዕዝ፣ ከኮርና ከክፍለጦር የተውጣጡ አመራሮች እያደረጉ ላለው የማብቃት ስራ ምስጋና የቀረበ ሲሆን፣ ህዝቡም ታሪካዊ ድርሻውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ የቀረበበት አቅጣጫ ተቀምጧል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
+2
በራያ ቆቦ ግንባር 3 የመከላከያ ሰራዊት አባላት አንድ እስናይፐር እና አንድ ክላሽን ኮፍ መሳሪያ በመያዝ ወደ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ የ102ኛን ኮር ቃኝ ተቀላቀሉ።
ዛሬ ነሀሴ 20/2018ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ 3 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከላይ በተጠቀሰው መሰረት 1 የቡድን መሳሪያ እና 1ክላሽን ኮፍ መሳሪያ በመያዝ 102ኛ ኮር ተቀላቀሉ።
ከጠላት የኮበለሉት የመከላከያ ሰራዊት አባላት 250 የክላሽ ጥይት ተተኳሽ እና 200 የስናይፐር ጥይት ተተኳሽ እንድሁም 4 ኤፍ ዋን ቦንብ በመያዝ ተቀላቅለዋል።
የተቀላቀሉት የደቡብ ዕዝ 202ኛ ኮር 21ኛ ክፍለጦር 1ኛ ሻለቃ 1ኛ ሻምበል ቲም መሪ እና እስናይፐር ተኳሽ ደሳለ መልካሙ እና እሱ ያውቃል ታደሰ እንድሁም 1 ጓዳቸውን በጀሌ /ያለመሳሪያ/ በመያዝ ህዝባችንን አንወጋም በብለው ወደ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 102ኛ ኮር በመምጣታቸው በኮር አመራሮቹ የጀግና አቀባበል ተደርጓላቸዋል ሲል የ 102ኛ ኮር ቃል አቀባይ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አሳምነው 5ኛ ዕዝ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር የናሁሰናይ ሻለቃ የክፍለ ጦሩ ወታደራዊ ኢንዶክትሪኔሽን ዋሲሁን በየነ ጥልቅና አቅጣጫ ጠቋሚ ከግዳጅ መለስ ከአናብስቶች ጋር!! #Dave #Amhara
+8
ህዝባዊ መድረኮች በሁለት እጅ እነሴ ወረዳ ጎድር ሜዳ ቀበሌ ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች ውይይት ተካሂዷል።
=========================
..ነሐሴ20//2018 ዓ.ም
ለአማራ ህዝብ ሲሉ በዚህ ትግል መስዋት የሆኑትን ጎዶችን በማሰብ በሀይማኖት አባቶች በፀሎት የተከፈተ ሲሆን የአፋብን ቴወድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር በ2እጁ እነሴ ወረዳ ጎድር ሜዳ ቀበሌ ነሐሴ19/2018 ዓ.ም ከህዝብ ጋር የጋራ ውይይት ተደርጓል።
➺ በፍትህ አሰጣጥ ና የመልካም አስ/ር
➺በፀጥታ ዙሪያ ያሉ ችግሮችን በመለየት
➺የሐብት አሰባሰብን በተመለከተ
➺የወል መሬት አጠቃቀም በተመለከተ
➺የአፋብን ትግል ከየት ወደየት አሁን የደረሰበት ሁኔታ እና ህዝባዊ አስተዳደርን ጨምሮ በመገምገመ የወደፊት የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ለተነሱ አጭር ማብራሪያ በኮሩ እና በጊዜያዊ መንግስት አመራሮች የማስረዳት ስራ ተሰርቷል።
እንደራጃለን ! እንመክራለን እንፈፅማለን!!
አዲስ ትውለድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣
አዲስ ተስፋ!!
አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ጉና ክፍለ ጦር ገብረ መስቀል ብርጌድ ጣይቱ ሻለቃ ለተከታታይ አምስት ቀን በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አደረሰ!
20/2018 ዓ.ም
የአገዛዙ ኃይል ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ላይ ከደብረታቦር ከተማ ተነስቶ ወደ ማህደረ ማርያም ከተማ አቅጣጫ በመንቀሳቀስ ላይ እያለ ጣይቱ ሻለቃ ልዩ ስሙ ወርቄ በተባለ ቦታ ላይ ደፈጣ በመጣል መብረቃዊ ማጥቃት በመፈጸም አኩሪ ጀብድ ፈፅመዋል።
በአውደ ውጊያው የጨፍጫፊው እና አምባገነኑን ሰራዊት ሻንበል መሪ ጨምሮ 11 የሚሆኑት አባላቱ የተደመስሱ ሲሆን አስከሬኑን ማሳት ተስኖት እያዝረከረከ ከፍተኛ ከባድና ቀላል ቁስለኛውን ተሸክሞ መኮብለል ችሏል።
በመሆኑም በሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ጉና ክፍለ ጦር ገብረ መስቀል ብርጌድ፣ መቅደላ ብርጌድ እንዲሁም ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ተደጋጋሜ ከባድ የሆነ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሽንፈት የደረሰበት የጠላት ኃይል፣ የበቀል ብትሩን እንደለመደው ምንም አይነት መሳሪያ ባልታጠቁ ንፁሐኖች ላይ የዘር ህልቂት እገፈፀመ ይገኛል።
ስለሆነም ከፍተኛ ምት ሲያርፍበት በንጹሐን ላይ የበቀል እርጃ መውሰድ የዘወትር ግብሩ ያደረገው ጠላት ዛሬም ፀረ- አማራነቱን በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ አሳይቷል።
1. ማተቤ ጥላሁን
2. አዱኛ ፍሰሀ
3. ደርሶ ካሰሁን ከወረቄ አካባቢ ወደ ደብረታቦር ከተማ በጠዋት ገብያ ሲሄዱ የነበሩትን ሶስት አርሶ አደር ገበሬዎችን ለፋኖ መረጃ ሰጥታቸዋል በማለት በግፍ የተገደሉ ሲሆን ሌሎች ሁለት አርሶ አደሮች ደግሞ የማይተርፉ መሆኑን ከህክምና ባለሙያዎች ማርጋጋጥ ተችሏል ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ነው ።
ክብር እና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በደፈጣ ጥቃት ወታደራዊ ኪሳራ ማድረሱንና የተዘረፉ ንብረቶችን ማስመለሱን አስታወቀ!!
ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፣ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ ሚዳ ሬማ ወረዳ ልዩ ቦታው «ጨለሚት» በተባለ ቦታ በፈጸመው የደፈጣ ጥቃት በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ወታደራዊ ኪሳራ ማድረሱን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ገለጸ።
እንደ ኮሩ የግንባር መረጃ ገለጻ፣ ጥቃቱ የተፈጸመው ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ላይ ከወረዳው ዋና ከተማ መራኛ 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሲሆን፣ የአገዛዙ ሰራዊት በአዲስ ስምሪት ( ግዳጅ) ወደ አካባቢው በጭነት መኪኖች የተጫነ አዲስ ሰራዊት በማስገባት ላይ ሳለ በተዘጋጀለት የደፈጣ ጥቃት ገብቶ መመታቱን ተረጋግጧል።
በሌላ በኩል፣ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ደራ ወረዳ በኮሉና ዲሚንዳቆ ቀበሌዎች በአገዛዙ ከተሰማራው የሸኔ ዘራፊ ኃይል ከህብረተሰቡ የተዘረፉ በርካታ የቤት እንስሳትን ማስመለስ ተችሏል። ይህ የማስመለስ እርምጃ የተካሄደው የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፡ ከአሳምነው 5ኛ ዕዝ ካራ ምሽግ ብርጌድ አርበኞች ጦር ጋር በመቀናጀት ባደረጉት ተጋድሎና ውጊያ መሆኑ ታውቋል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ የትውልድ ቦታ በጎጃም ቢቸና ለምጨንና በታሪካዊ ቦታ ታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ ገዳምን ለማውደምና ለመዝረፍ ትዛዝ የሰጠው ጄኔራል ሶፊያ በክሪን ወረራ እንዲፈፀም ትዛዝ ቢያስተላልፍም የጄኔራሉን ትዛዝ በመቀበል ወደ ዲማ ከተማ ያቀነው ኮሎኔር ፀጋየ የተሰጠው ትዛዝ ስኬታማ ሳያደርግ በ64ኛ ክ/ጦር ከፍተኛ ኪሳራ ደረሶበታል።
መቀመጫቸውን በታሪካዊ ቦታ ታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ አድርገው የነበሩት የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ ልጆች ከአባታቸው የወረሱትን የትግል ስልት በመጠቀም ዲማ ከተማንና አካባቢውን ለወራሪ ላለማስደፈር በኮሎኔር ፀጋየ እየተመራ ወረራ ለመፈፀም የመጣው የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ጋር ከፍተኛ ተጋሃድሎ በማድርግ የዲማ ከተማ የውስጥ ለውጥ መንገዶች የጠላት አስከሬን ከምረው በመጣል የአባ ኮስትር በላይ ዘለቀ ልጆች መሆናቸውን አስመስክረዋል።
የ64ኛ ክ/ጦር አመራርና አባላት ጀግኖች ወንድሞቻችን መስዋትነት የከፈሉበትን የትጥቅ ትግል ዓላማ ዳር ለማድረስ እውነትን በመያዝ ከሶስት በላይ ክ/ጦሮችንና የሜካናይዝድ ጦር፣ መድፍ፣ BM፣ ዙ23፣ ሞርተር፣ ከ9 በላይ ድሽቃና ከጎጃም የተለያዩ ቦታዎች በርካታ የእግረኛ ሰራዊት በመያዝ ዲማ ከተማ ከአይበገሬዎች ጋር ከፍተኛ ውጊያ ቢያደርግም ጀግኖች 8 ግዜ ማጥቃት የመጠውን የጠላት ሀይል በመረፍረፍ ከ18 በላይ ክላሽ እንኮቭ መሳሪያ ከጠላት አስከሬን አንስተው ታሪካዊ አሻራቸውን አሳርፍው ደስታቸውን እንዲህ እየገለፁ ይገኛሉ።
"እነሱም ይሉናል ተኩሰን አንስትም
እኛም እንላለን ቃታ አናስከፍትም
መተው አየናቸው የጁላን ጥርቅም
አጎንብሶ ዋለ አስከሬን ሲለቅም
የአርበኞች ልጅ ሆነን ታሪክን አንሰጥም"
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ነሀሴ19/2018 ዓ.ም
በገምዛ ማጀቴ ክላስተር"ገምዛ አርበኞች ክፍለ ጦር" በይፋ ተመሠረተ!!
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
በታሪካዊቷ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ገምዛ ማጀቴ ክላስተር ውስጥ የወታደራዊ አቅም አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ።
በገምዛ ማጀቴ አካባቢ የሚንቀሳቀሰው የአርበኞች ጦር ወታደራዊና ድርጅታዊ አቅሙን በላቀ ደረጃ በማሳደግ ታላቅ ክፍለ ጦር መሠረተ። "ልጆቼ ይዝሩልኝ፤ እኔ አርመዋለሁ" የሚለው ጀግናውና ቁርጠኛው የማጀቴ ህዝብ ወታደራዊ መንፈሱን በማደስ ሕልውናውንና ነፃነቱን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን አቅም በመሰብሰብ"ገምዛ ክፍለ ጦርን" መሠረቱ ታውቋል።
ቀደም ሲል በአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ፣ ዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር፣ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ሥር ታቅፎ በጀግንነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ብርጌዶች፣ አሁን ባካሄደው አጠቃላይ የመዋቅር ማሻሻያና ማጠናከሪያ ራሱን ወደ ሙሉ ክፍለ ጦር ደረጃ ማሳደጉ ተገልጿል።
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ አመራሮች ባስቀመጡት የቀጠናና የአውራጃ ትስስር አደረጃጀት መመሪያ መሠረት፣ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ስምሪት ወስደው ህዝቡን በንቃት በማደራጀት ላይ የሚገኙት የስምሪት አካላት አደረጃጀቱን በዘመናዊ የወታደራዊ ሳይንስ አካሄድ እየገነቡና እያዘመኑ መሆናቸውም ተረጋግጧል።
እስከ አሁን በነበረው መዋቅር መሠረት አራቱ ብርጌዶች ማለትም፦
1.➢ከነዓን ብርጌድ
2.➢ውባንተ አባተ ብርጌድ
3.➢ምኒልክ ብርጌድ
4.➢ ማጀቴ ብርጌድ
በአዲሱ የመልሶ ማደራጀት መርሃ-ግብር አራቱም ብርጌዶች ጥንካሬአቸውን፣ ወታደራዊ አቅማቸውንና ቁሳቁሳቸውን በማስተባበር በአንድ ወታደራዊ እዝ ሥር ተሰባስበው "ገምዛ አርበኞች ክፍለ ጦር" በሚል አዲስ መጠሪያ ተዋቅረዋል።
ይህ አዲሱ አርበኞች ክፍለ ጦር ለውጊያ ዝግጁ የሆነ ጠንካራ ተወርዋሪ ጦር እና ደጀን ጦር በማለት አደረጃጀቱን አቀናጅቶ፣ ብቁ ወታደራዊ አመራሮችን ሲሰይም፣ አዲሱ ክፍለ ጦር በገምዛ ማጀቴ ክላስተር ሥር የሚመራና ይሆናል።
ይህ ታላቅ የምስረታ መርሃ-ግብር የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች፣ የክላስተሩ አስተዳዳሪዎች እንዲሁም የዓፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር መሪዎች በተገኙበት በታላቅ ስነ-ስርዓት ተከናወኗል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት አመራሮችና ታጋዮች የተከናወነው የወታደራዊ መዋቅር ማሻሻያ ለቀጠናው ሰላምና ለህዝቡ ደህንነት ከመቸውም በላይ አኩሪ እደሚሆን ታምኖበታል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ህዝባዊ ውይይት አደረገ!
ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም
አርበኛ ዳንኤል አስረስ የአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አርበኛ መምህር ንጉሴ አዱኛ ፣ የኮሩ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ወርቁ ሙሉን ጨምሮ ሌሎች የኮር አመራሮች በተገኙበት በጥራሂና ህዝባዊ ውይይት አድርጓል።
በህዝባዊ መድረኩ የአደረጃጀት አንድነትን፣ ቀጣናው ላይ ስላሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ፣ የፍትህ አሰጣጥ ሂደትን እና የመሬት አስተዳደር አፈጻጸም ላይ እየተፈጠሩ ስላሉ ችግሮች ላይ ጥልቅ ውይይት ተደርጎባቸዋል ።
ስለሆነም ህግና ስርዓትን ማስከበር የዘላቂ ሰላም ማስጠበቂያ መሆኑን ያሰመሩበት ተሳታፊዎቹ፣ ፍትህ ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በእኩልነት መዳረስ እንዳለበት አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል። በቀበሌው የሚታዩ የሲቪል መዋቅር ክፍተቶችን እንዲሁም የመሬት አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች በአስቸኳይ በማረም፣ የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ማስከበር እንደሚገባ እና ይህን ጨፍጫፊ ስርዓት በአንድነት ማስወገድ ስለሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ የጋራ ተግባቦት ተደርሶባቸዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የኮሩ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ነው።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ !
