ru
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Открыть в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Больше
2 923
Подписчики
+3224 часа
+3727 дней
+36630 дней
Архив постов
የደቡብ ወሎ ዞን የደህንነት ኃላፊ መቶ አለቃ ቢኒያም ምኒልክ 1ኛ ዕዝን በይፋ ተቀላቀሉ! ​የደቡብ ወሎ ዞን የደህንነት ኃላፊ መቶ አለቃ ቢኒያም ከአገዛዙ በመለየት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄን (አ
+1
የደቡብ ወሎ ዞን የደህንነት ኃላፊ መቶ አለቃ ቢኒያም ምኒልክ 1ኛ ዕዝን በይፋ ተቀላቀሉ! ​የደቡብ ወሎ ዞን የደህንነት ኃላፊ መቶ አለቃ ቢኒያም ከአገዛዙ በመለየት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄን (አፋብን) ምኒልክ 1እኛ ዕዝ  በይፋ  በዛሬዉ ዕለት ማለትም በቀን 19/12/2018 ዓ.ም ተቀላቅለዋል። ኃላፊው የምኒልክ 1ኛ ዕዝ፣ 15ኛ ኮር፣ 155ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀለ ሲሆን  ውሳኔውን የወሰዱትም "ገዢው የብልፅግና ስርዓት በዞኑና በሕዝቡ ላይ እየፈጸመ ነው ያሉትን ሴራና አበሳ በመቃወም እንደሆነ አስታውቀዋል"። በተለይም የደሴ፣ ኮምቦልቻና ሐርቡ አካባቢዎችን ጨምሮ የዞኑ ቁልፍ ቦታዎችና አጠቃላይ የሕዝብ ጥቅም የወረዳዉ የብልፅግናዉ ቡድን ለሌላ አካል አሳልፈው ለመስጠት የተሄደበትን መንገድ አጋልጠዋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!    ነሐሴ19/ 2018 ዓ/ም

#አሳዛኝዜና ወጣቶችን አስገድዶ ለጦርነት ለመማገድ አፈሳውን ስራዬ ብሎ የተያያዘው ፀረ -አማራ አገዛዝ ብልፅግና ወጣት #ዮሃንስቻለው ለማላምንበት ትግል አልሰለፍም ስላለ በቀን 18/12/2018 ዓ.ም
+1
#አሳዛኝዜና ወጣቶችን አስገድዶ ለጦርነት ለመማገድ አፈሳውን ስራዬ ብሎ የተያያዘው ፀረ -አማራ አገዛዝ ብልፅግና ወጣት #ዮሃንስቻለው ለማላምንበት ትግል አልሰለፍም ስላለ በቀን 18/12/2018 ዓ.ም በደ/ብርሃን ከተማ ምሀል አደባባይ ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገሏ*ል። የወጣቶች ሕይወት የሀገር ተስፋና የወደፊት ብርሃን ነው። ​ዜጎችን ጨ*ፍ*ጭፎ ፣ በተለይም የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ወጣቶችን በሕይወት የመኖር መብት ነጥቆ የፀና አንባ ገነን አገዛዝ የለም።በወጣቶች ላይ የሚፈጸሙ ማናቸውም ዓይነት ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶችና የኃይል እርምጃዎች እና አፈሳዎች የአገዛዙን የሞራል ዝቅጠትና ሽንፈት ማሳያዎች ናቸው ። ​በወጣት ዮሐንስ ቻለው ሕልፈተ ህይወት ከልብ እናዝናለን።

ከአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ግዙፉ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር ተለይተው የነበሩ አሀዶች ወደ ነበሩበት ተቋማቸው ተመልሰዋል። ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የአፋብን ምክትል ሰብሳቢ ለወታደራዊ ጉዳዮች ኃላፊ ጀኔራል ሀብቴ ወልዴ፣ የዕዙ ሰብሳቢ አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ፣ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ አርበኛ ሰለሞን አጣናው፣ የዕዙ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ጀኔራል ተሾመ አበባው፣ የዕዙ ሎጅስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በላይ ዘለቀ፣ የፋይናንስ ኃላፊ አርበኛ ሀታሙ ሙላው እና ሌሎች የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም አርበኛ ጌታዬ እሱባለውን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ሙሉ ተሳትፈዋል። አንድነትን ማስቀጠልና እና ወንድማማችነትን ማጽናት ላይ ትኩረት ያደረገው ይህ ውይይት የጎንደርን አንድነት የተበሰረበትን እልክ አስጨራሽ የአመራርነት ሂደት እና ፀረ አንድነት ግለሰቦች የፈጠሩትን መደናገር ፣ የህዝባችንን ጽኑ አንድነት ፈላጊነትና የትግል አበርክቶ ከድርጅቱ እና ከዕዙ ከፍተኛ አመራሮቹ ሰፊ ግልጽ ማብራሪያ የተሰጥቶበት መግባባት ላይ ተደርሷል። የጎንደርን እና የህዝባችንን አሸናፊነት የማይሹ አካላት የራሳቸውን የግል ፍላጎት ለማርካት ሲሉ ከዕዙ ፣ ከክፍለ ጦሩ ለመነጠል እና ጥርጣሬዎችን ለመዝራት ያደረጓቸውን ተደጋጋሚ ሙከራዎች በመድረኩ በጥልቀት የገመገመ ሲሆን፣ ችግሮችን በአንድ የጋራ ማዕቀፍ ውስጥ በመፍታት ተቋማዊ አንድነትን ማረጋገጥ የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑን አስረድተዋል። በመሆኑም ከዚህ ቀደም ሲስተዋሉ የነበሩ ውስጣዊ ውጥረቶችንና ቅራኔዎችን በመተው የጋራ ወንድማማችነትን እና ተቋማዊ አንድነትን በላቀ ደረጃ ለማጠናከር ወደ ነበሩበት ክፍለ ጦራቸው ተመልሰው ተቋማቸውን ማጠናከርና ማጽናት እንዳለባቸው ገልጸዋል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉት አባላትም ከዚህ በፊት የነበሩ የሃሳብ ልዩነቶችንና ጥያቄዎችን በግልጽ መድረኩ ላይ ያቀረቡ ሲሆን፣ በድርጅቱ ፣በዕዙ እና በክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች በኩል አወንታዊና ግልጽነት የተሞላበት ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል ። በመጨረሻም አንድነት የምርጫ ጉዳይ አደለም ግዴታ እንጂ ያሉት አባላቱ፣ አንድነት የትግላችን ቋሚ ምሰሶ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ዕዙና ክፍለ ጦራችን በሚሰጠን ማንኛውም ግዳጅ ላይ በቁርጠኝነት በመሳተፍ የህዝባችን የህልውና ትግል ወደ ተሟላ ድል ለማድረስ ዝግጁ ነን ሲሉ ገልጸዋል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

አሳዛኝ የወለጋ አማራ የንፁኋን ስቃይ‼️       (የዘር ማጥፋት ዘመቻ )    ነሐሴ18/2018ዓም በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ወለጋ እና በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞኖች ተጠናክሮ የቀጠለው የአማራን ተወላጅ የዘር ማጥፋት ዘመቻ ያለ ማቋረጥ ለ7ዓመት በተከታታይ ሲገሉ እና ሲፈናቅሉ መቆየታቸው ይታወቃል። በዘንድሮው አመት በተለይም አድማሱን አስፋፍቶ የቀጠለው የንጽኋን ግዲያ ፣የንብረት ዘረፋ እና የቤት ቃጠሎ በሁለቱ ዞኖች የአገዛዙ ሰራዊት መከላከያ እና የክልሉ ጥምር ጦር አገዛዙ በጫካ ያሰማራው ሸኔ ያ ፍላጎታቸው አልሳካ ሲል ወደ ጉያው ያስገባው  ጥሬ ስጋ ሲቀልበው የነበረው የስም ቅያሬ ያደረገለት ገዳ ኮማዶ ፣አድማ ብተና ፣ልዩሃይል፣ጋቸናሲርና ፣ኤርፔሎላ፣ሚኒሻ እና ቄሮ የሚፈጽሙት እኩይ ተግባራቸውን በጋሀድ እየተገበሩት ይገኛሉ ።በተለይም ሰሞኑን በምስራቅ ወለጋ ዞን በጊዳ አያና ወረዳ  ያለማቋረጥ ለሁለት ሳምንት አፀያፊ ስራዎችን በመፈፀም ፈንደቃን እና አዶዴ ዴቾን በማቃጠል እድሁም የሃይማኖት ተቋም ቤተክርስቲያንን ጨምሮ በማውደም ከወለጋ ምድር ላይ አማራን እናጠፋለን በሚል እብሪተኝነት የአገዛዙ ሰራዊት እና የክልሉ ጥምር ሃይል ሲያካሂዱ የነበረውን ነገር በተደጋጋሚ ስንገልፅ ነበር ። ይህ በእድህ እዳለ ነሐሴ13ቀን 2018ዓም በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ አንዶዴ ከተማን ሙሉ በሙሉ በማውደምና ቤተክርስትያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በመግባት በማስቀደስ እና በቅዳሴ ላየ ያሉ ካህናቶች እድሁም ከእናት አስክሬን ጎን የአራት አመት ህፃን በህይወት እደተገኘ እድሁም የሀይማኖት አባቶችን ካህናት ፣አይነ ሰውራንንና መለኮሳትን በግፍ ተረሽነው ለማየት ችለናል።በአሰቃቂ ሁኔታ በግፍ ከተረሸኑት በጥቂቱ የስም ዝርዝራቸውም፦ ➾የአዶዴ ስላሴ ቤተክርስቲያን        ዋና አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ           ታደሰ ➾ቄስ አድስ አየለ        እድሁም አስክሬናቸው ያልተገኙ ካህናትና መነኮሳት በርካታ እንዳለ ሁኖ፤ ትናት ደግሞ ከጠዋቱ 3:00ሰዓት ጀምሮ ይህ የክልሉ ገዳይ ጥምር ጦር እድሁም መከላከያ ማዕከላዊ ዕዝ 101ኛ ኮር 33ኛ ክፍለጦር ከፊት እደኬላ በማስቀመጥ ይህ የክልሉ ጥምር ሀይል መደር ሶስት፣መደር 22 ሙሉ በሙሉ ሲያቃጥሉ እና ተጨማሪ "በጭበጭ" የሚባል ሰፈርን የሃይማኖት ተቋም የጊዮርጊስ ቤተክርስትያንን ጨምሮ አቃጥለዋል። በነዚህ መደሮችም በርካታ ንጹኋንን በጂምላ የአማራ ተወላጆችን ከመኗሪያ ቤታቸው አፈናቅሏል ፣ንጹሐን ደካሞች እና ህጻናት በግፍ እረሽነዋል ፣የቤት ንብረታቸውን እና የቀንድ ከብቶችን ከ450 በላይ በግፍ ተዘርፈዋል ።አሁን በዚህ ስዓት የተገደሉት ንጹሃን 67 ደርሰዋል የተቃጠለው የማህበረሰቡ ቤት በሺዎች እደተቆጠሩ ምንጮች ያሳያሉ ።ይህ የብልጽግና ስርዓት የፋኖን ብርቱ ክንድ መቋቋም ሲያአቅተው ባልተያዙ ቀጠናዎች ይሀንን መጥፎ ተግባሩን ሲፈጽም ውሏል ። የህዝቡ ስቃይ ከቤቱ ያስወጣው የአንሻ ሰይድ 4ኛ ዕዝ  አንገር ጉተን ክፍለ ጦር ትናንት ጧት ደፈጣ በመጣል ኬላ ዘርግቶ ለክልሉ ጥምር ጦር ሽፋን ሲሰጥ የነበረው መከላከያ ሲያዘርፍ ፣ ቤቶችን ሲቃጠሉ ፣የቀድ ከብቶች ሲያዘርፍ፣ንፁኋንን በግፍ ሲያስረሺን ከዋለ ቦኋላ  እቅስቃሴዎችን ሲያደርግ ድቾ ተራራ ለይ በደፈጣ  እንደለመደው ታሪክን በክንዳቸው ጽፈዋል።        ግፍ የወለደን:ግፈኞችን የምቀጣ የአንሻ ሰይድ ወድሞች ነን!!! አፋብን አንሻ ሰይድ 4ኛ እዝ       ህ/ግንኙነት መምሪያ

ቀን 19/12/2018ዓ.ም ከአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ የመውሊድ በዓልን አስመልክቶ የተላለፈ የእንኳን አደረሳችሁ መግለጫ እንኳን ለ1501ኛው የመውሊድ (የነቢዩ ሙሐመድ የልደት) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፣ለሕዝባቸው ክብር፣ ፍትሕና ሰላም ሲሉ ለሚታገሉት ለአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ መሪዎችና አባላት እንዲሁም ለተከበረው ሙስሊም ማህበረሰባችን በሙሉ እንኳን ለታላቁ ነብይ ነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የመውሊድ በዓል የሰላም፣ የርኅራኄ፣ የፍቅርና የሕብረት ታላቅ ተስፋ የሚታደስበት ወቅት ነው። ነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ለዓለም ያስተማሩት የመቻቻል፣ የታማኝነት፣ የወንድማማችነት እና ለበደለኞች አለመበርከክ እሴቶች ለሁላችንም ትልቅ የሞራልና የጽናት ምንጭ ናቸው። ታላቁ ነቢይ ያስተማሩት የእውነትና የፍትሕ መንገድ ለሕዝባችን አንድነት፣ ለሰራዊታችን ጥንካሬና ብርታት ለጋራ ዓላማችን መሳካት ትልቅ ብርሃን ነው። የኢትዮጵያን ህዝብ አንድነት፣የአማራን ሕዝብ ሕልውና፣ ታሪካዊ ክብርንና ፍትሕን ለማስከበር እየተካሄደ ያለው መራራ ትግል በላቀ ድልና በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ  ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። ለሕዝባቸው ህልውናና ደህንነት ሲሉ በየግንባሩ ለሚታገሉት የሰራዊታችን አባላት በሙሉ የሚደረገው የፍትሕና የእውነት ጉዞ በሕዝባችን ደጋፊነትና ጥበቃ ታጅቦ የሕዝባችንን የተነጠቀ መብት፣ ደህንነትና ታሪካዊ ክብር የማስከበር ጉዞ ወደ ኋላ በማይመለስ ጽናት ወደ ፊት ይገሰግሳል። በየመንገዱ የሚገጥሙ ፈተናዎችን ሁሉ በመሻገር ለተበደሉት ፍትሕን፣ ለተፈናቀሉት ወገኖቻችን ደግሞ ዘላቂ መረጋጋትና እፎይታን የሚያመጣ ድል ይረጋገጣል። እስከ አሁን የተከፈለውን ግዙፍ መስዋዕትነት ወደ ተጨባጭ ድል ለመቀየር ሕዝባችን በጋራ ዓላማና አንድነት ሊቆም ይገባል። ‎ ‎ በዓሉ የፍቅር፣ የደስታ፣ የጽናትና የድል ይሁንላችሁ! ‎ድል ለሕዝባችን! ፍትሕና ሰላም ለሀገራችን! መልካም የመውሊድ በዓል!! የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ /አፋብን/ ነሃሴ19/12/2018 ዓ.ም

ከ ሶስት ክ/ጦሮች በላይ የተሳተፍበትን ወረራ በመመከት አንፀባራቂ ድል ተጎናጽፎ ጀብድ ለሰራው የ64ኛ ክ/ጦር ሰራዊት የጅግንነት እውቅና ተሰጠ። ~~~~ የጄኔራል ሶፊያ በክሪን ትዛዝ የተቀበለው ኮሎኔል ፀጋየ በእነማይ ወረዳ ዲማ ጊዮረጊስ፣ ደብረፅሞና፣ ለምጨንና አካባቢ ለመግባት በተንቀሳቀሰው የኮሎኔል ፀጋየ ሰራዊት በ64ኛ ክ/ጦር በተወሰደበት አጻፋዊ እርምጃ ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገደ ሲሆን ከጎጃም የተለያዩ ቦታዎች፣ ደብረወርቅና ቢቸና ያሰማራቸው የሚኒሻና የፖሊስ አባላት ጨምሮ በርካታ የጠላት ሰራዊት መደምሰሱ ተገልጿል። የ64 ክ/ጦር ወታደራዊ አመራሮች ከሰራዊቱ ጋር የነበራቸውን የግዳጅ አፈፃፀም የገመገሙ ሲሆን በዲማ ግንባር በነበረው እልህ አስጨራሽ ፍልሚያ የጠላትን እግረኛ ሰራዊት ወደ ምሽግ በመሳብ በማጥቃት ስልት ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል። የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀን መንፈስ በመለባስ ታሪክ በሚዘክረው ምድር የተፋለመው አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በዲማ ከተማ ከጥዋቱ 1:30 እስከ 12:00 ሰዓት ባደርገው ተጋሃድሎ የጠላት ኮሎኔሮች ሳይቀር በዲማ  ከተማ የነበረው ፋኖ ጠንካራ መሆኑንና ተጨማሪ ኃይል በተደጋጋሚ በመጠየቅ ድጋፍ ሰጭ ሜካናይዝድ ኃይል በማስገባት ያደረገውን ጥቃት በተገቢው ሁኔታ መመከት መቻሉም ተጠቁሟል። ኮሎኔል ፀጋየ 8 ግዜ ምሽግ ለመስበር ያደረገው ማጥቃት ሙከራ ጀግኖች የበላይ ዘለቀ ልጆች ከምሽጋቸው ንቅንቅ ሳይሉ በረካታ የጠላት ሰራዊት በመደምሰስና ክላሽ እንኮቨ መሳሪያ መማረካቸውን የጠላት ሰራዊት ስነልቦና እንዲሞት አድረገዋል ተብሏል። ይህም ድል ሊመጣ የቻለው የክ/ጦሩ ወታደራዊ አመራሮች በመናበብ ሰራዊቱን መምራታቸውና ሰራዊቱም የተሰጠውን ትዛዝ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በመፈፀም ጓዳዊ መተሳሰቡም የተገለፀበት መሆኑን በማውሳት ለጀግናው የ64ኛ ክ/ጦር ሰራዊት የጀግንነት እውቅና ተሰጧል። ሰራዊቱን በማስተባበር ውጊያን በበላይነት በመምራት ከፍተኛ ድል ላስመዘገቡ የክ/ጦር፣ የሻለቃ፣ የክ/ጦሩ አባላትና በየደረጃው ላሉ አመራሮች እውቅናና ምስጋና በመስጠት መርሃግብሩ ተጠናቋል። በመጨረሻም ሰራዊቱ በዲማና አካባቢው የነበረውን የውጊያ ቆይታቸውን ከገመገሙ በሆላ ሰራዊቱ ለቀጣይ ግዳጅ ዝግጁ መሆናቸውን አሳውቀዋል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ ተስፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ!               ነሀሴ 19/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ

አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በአሜሪካ በፓርኪንግ ስራ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ትልቅ ተፅዕኖ የነበራቸው፣ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት እና የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉ መሪ ነበሩ። በከፍተኛ የስልጣን ማዕረግ ላይ በነበሩበት ወቅት የህዝብን ሀብት አለመመዝበራቸው እና ዛሬ በባህር ማዶ በሚደረግ ማንኛውም ህጋዊ ስራ ተሰማርተው በላባቸው ለመኖር አለመሸማቀቃቸው የሚያስደንቅ እና ትልቅ አስተምህሮ ያለው ጉዳይ ነው። በሀገራችን የፖለቲካ ባህል ውስጥ ስልጣን ላይ የሚወጡ ሰዎች ህዝብን ከመጥቀም ይልቅ ለራሳቸውና ለቤተሰቦቻቸው ሀብት ሲያካብቱ ማየት የተለመደ በሆነበት ሁኔታ፣ በንጹህ እጅ ወጥቶ በቅንነትና በክብር በራስ ላብ መኖር የስነ-ምግባር አርአያነትን ያሳያል። ስራ ምንም ይሁን ምን በህጋዊና በሃቅ መንገድ የሚገኝ ገቢ ሁልጊዜም ኩራት እንጂ ውርደት አይደለም። የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት፣ በኋላም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን በስደት ሀገር አሜሪካ ውስጥ በተራ የመኪና ማቆሚያ (Parking) ስራ ላይ ተሰማርተው አየኋቸው። በመጀመሪያ ደረጃ ውስጤ አዘነ፤ ነገር ግን የሀገራችንን ፖለቲካዊና ማህበራዊ እውነታ ጠለቅ ብዬ ስቃኝ አግራሞቴና አክብሮቴ በዛ። በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ስልጣን ላይ የወጣ ሰው የህዝብና የሀገር ሀብት ዘርፎ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በውጭ ሀገር ባንክ አካብቶ፣ በቅንጡ ህይወት ሲኖር ማየት የተለመደ ሆኖ ነበር። አቶ ገዱ ግን በከፍተኛ የስልጣን ማዕረግ ላይ በነበሩበት ወቅት በሙስና ሳይጨማለቁ፣ የህዝብን አደራ ጠብቀው መውጣታቸውን ዛሬ የሚያደርጉት ጥረት ህያው ምስክር ነው። በሁለተኛ ደረጃ፣ ከከፍተኛ የመንግሥት ሃላፊነት ወርዶ ማንኛውንም ህጋዊ ስራ ለመስራት አለመሸማቀቅ፣ ስነ-ልቦናዊ ጥንካሬ እና የሞራል የበላይነትን ይጠይቃል። በላብ አድርቆና ጥሮ ግሮ መብላት እንጂ የሰረቁትን መብላት ነው የሚያፍረው። ስራ አይናቅም፤ በሃቅ የሚኖር ህይወት ደግሞ ሁልጊዜም ዘላለማዊ ክብር አለው። ከዚህ አጋጣሚ የምንማረው ትልቅ ትምህርት አለ፦ ስልጣን ጊዜያዊ ነው፦ ዛሬ የተቀመጥንበት ወንበር ነገ የለም፤ ዋናው ነገር በንጽህና ማገልገል ነው። ሃቅ አይወድቅም፦ በሙስና ያልተበከለ እጅ በማንኛውም የህይወት አጋጣሚ ቀና ብሎ ይሄዳል። ስራን አለመናቅ እና በራስ ላብ መኖር የትኛውም ቦታ የሰው ልጅ ትልቅነት መለኪያ ነው። ለአቶ ገዱ አንዳርጋቸው ላሳዩት የሞራል ብቃት፣ የህሊና ንጽህና እና የስራ አክብሮት ትልቅ ምስጋና እና አክብሮት አለኝ! #ገዱአንዳርጋቸው #የስራክብር #ኢትዮጵያ #ፖለቲካ #ህሊና

በአማራ ህዝብ ላይ በአገዛዙ የሚፈፀሙ ግፎች ሲበረክቱ፣ ሕዝባዊ እቢተኝነት ተጠናክሮ ቀጥለዋል!!        ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መንዝና ግሼ አውራጃ፣ ላሎ ወረዳ ወገሬ ከተማ የአገዛዙ ኃይሎች በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚያደርሱት ግፍና እንግልት ተጠናክሮ መቀጠሉን የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ዓፄ አምደጽዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ። ቁጥራቸው ከ52 በላይ የሚሆኑ ንጹሃን ወገኖች "የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ" በሚል ምክንያት ተጠርጥረው ከሳምንት በላይ በእስር ቤት ውስጥ በግፍ እየተሰቃዩ መሆኑን የታጋች ቤተሰቦች ገልፀዋል። ሕዝብን እርስ በርስ በማጋጨት የስልጣን ዕድሜውን ለማራዘም የሚጋጋጠው ይህ አገዛዝ፣ በሰፈረባቸው ከተሞች ሁሉ የጠራቸው ሕዝባዊ ስብሰባዎች በሕዝቡ በኩል ከባድ ተቃውሞና ምላሽ እያስተናገደ ሲገኝ  በስብሰባው ላይ የተገኙት አካላት፣ "እጠብቃችኋለን እያላችሁ ራሳችሁ ዘረፋ፣ ደፈራ፣ ድብደባና ከአቅም በላይ የሆነ ግብር ጭማሪ ፈጸማችሁብን" ሲሉ ፊታቸውን ላዞሩበት አገዛዝ እውነቱን መናገራቸውና (ማጋለጣቸው) በዬከተማው ቀጥሏል።  ነዋሪዎቹ ባቀረቡት ቅሬታና ተቃውሞ ምክንያት፣ የአገዛዙ ሰራዊት አጀንዳውን በመቀየር በሕዝቡ ላይ ጥቃትና ማስፈራራት እንደቀጠለበት መሆኑም ተገልጿል። የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን አክሎ እንደገለጸው፣ በእስር ላይ የሚገኙት እነዚህ ንጹሃን ወገኖች "እናንተ የጥይት ማብረጃ ትሆናላችሁ" በሚል ዛቻና ማስፈራራት እየደረሰባቸው መሆኑኑ ተረጋግጧል። ይህ በንጹሃን ላይ የሚፈጸመው ሰብአዊ ጥሰትና የእስር እንግልት  የትጥቅ ትግሉን ቁርጠኝነት የሚያጠናክር መሆኑን እየገለፅን ህልውናችንና መብታችንን የማስከበር ሂደቱ በተባበረ ክንድ ይረጋገጣል ሲል ኮሩ በላከው መረጃ አረጋግጧል ።  ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ከገዳም አቦ እና ከአፀደ ብርሃን ቀበሌዎች ማህበረሰብ ጋር ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተካሄደ ነሐሴ 18/2018 ዓም በአፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የሁለት እጁ እነሴ ወረዳ የሲቪል አስተዳደር ከገዳም አቦ እና ከአፀደ ብርሃን ቀበሌዎች ማህበረሰብ ጋር ባደረገው ህዝባዊ መድረክ አገራዊ፣ አካባቢያዊና ትግሉን የተመለከቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል። በዚሁ ህዝባዊ የምክክር መድረክ ላይ የየዘርፉ አመራሮች የተገኙ ሲሆን፦ አርበኛ ኃይመረ እሱባለው — የ54ኛ ክፍለ ጦር የሲቪል አስተዳደር ሰብሳቢ አርበኛ ዮናስ ፈንታሁን — የሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አርበኛ ይታያል አገሬ — የወረዳው ፍትህ ኃላፊ አርበኛ መንግስቱ ጥጋቤ — የወረዳው የፀጥታ ጉዳዮች ኃላፊ አርበኛ ገደፋዮ አገኝ — የወረዳው ሚዲያ ክፍል ኃላፊ አርበኛ አበበ ባዩ — የወረዳው ማህበራዊ ጉዳዮች ኃላፊ አርበኛ አራጋው አያሌው — የወረዳው ኦዲትና ቁጥጥር ኃላፊ በመገኘት ከመድረኩ የተነሱ ሀሳቦችንና ጥያቄዎችን አስተናግደዋል። በመድረኩ ከተነሱት ዋና ዋና የውይይት ነጥቦች መካከል የፋኖ የትግል አጀማመርና ወቅታዊ ቁመና፦ የፋኖ ህዝባዊ ትግል ከተጀመረበት ታሪካዊ መነሻ አንስቶ አሁን ላይ ደርሶበት እስከሚገኘው የጽናትና የጥንካሬ ደረጃ ድረስ ለአካባቢው ማህበረሰብ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል። የታጋዩና የህዝቡ ትስስር፦ ታጋዩ ሰራዊት ከህዝብ የወጣና ለህዝብ መብትና ደህንነት የሚታገል በመሆኑ፣ በህዝቡና በታጋዩ መካከል ያለው ወንድማማችነትና ቅንጅት ይበልጥ ሊጠናከር እንደሚገባ ተስመረበታል። መልካም አስተዳደርና የፍትህ አሰጣጥ በማህበረሰቡ ውስጥ ገለልተኛ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት በመስጠት ረገድ የተዘረጉ አሰራሮች የቀረቡ ሲሆን፣ የህዝቡን እንግልት የሚቀንሱ የመልካም አስተዳደር ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተብራርቷል። የአፋብን የወደፊት አቅጣጫ፦ ወታደራዊና ሲቪል አደረጃጀቱን በማስተሳሰር የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት ዘላቂ ማድረግ፣ የህዝብ አስተዳደር መዋቅሩን ማጠናከር እና የትግሉን አላማዎች ስኬታማ ማድረግ የወደፊት አቅጣጫዎች መሆናቸው ተመላክቷል። የወል መሬት እና የመኖ መሬት ወረራ (የጋራ ሀብት) አጠቃቀም የወል መሬቶችና የመና ሀብቶች ጥበቃን፣ የፍትሃዊ አጠቃቀም ስርዓትን እንዲሁም ህገ-ወጥ አሰራሮችን ከመከላከል አንጻር ከህዝቡ ጋር አዎንታዊ ውይይት ተደርጎባቸዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ከገዳም አቦ እና ከአፀደ ብርሃን ቀበሌዎች ነዋሪዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን፣ በአመራሮቹ በኩል ሰፊና አጥጋቢ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በተሰጣቸው ምላሽና ማብራሪያ መደሰታቸውን ገልጸው፣ ለተዘረጋው የፍትህ፣ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ስራ ሙሉ ድጋፋቸውን እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። ነሐሴ 18/2018 ዓም የሁለት እጁ እነሴ ወረዳ የጊዜያዊ መንግስት ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል

የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ለአቶ እስክንድር ነጋ

በፖሊት ቢሮው ማስጠንቀቂያ ከተሰጠው በኋላ ነው ዛሬ በግልጽ ወጥቶ ኦሕዴድን መቀላቀሉን የገለጸው።
በፖሊት ቢሮው ማስጠንቀቂያ ከተሰጠው በኋላ ነው ዛሬ በግልጽ ወጥቶ ኦሕዴድን መቀላቀሉን የገለጸው።