ru
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Открыть в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Больше
2 938
Подписчики
+1424 часа
+3877 дней
+38530 дней
Архив постов
እረፍት የለሹ ክፍለ ጦር ዛሬም በድልና በልዩ ዝግጅት ተገልጿል።         ሀምሌ 25/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር: የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ሃይል ተመስርቶ በመላዉ የአማራ ክልል ጦርነት በታወጀበት 3ኛ አመት የድል ቀን፣ የብልፅግና ስርዓት ለመጨረሻ ተወግዶ የአማራ ህዝብ ህልዉና የሚረጋገጥበት፣ ለመላዉ ኢትዮጵያዉያን ሰላም፣ ፍትህና ነፃነት የሚያሰፍን ስርዓተ መንግስት ለመመስረት የመጨረሻዋ ፉሽካ በሁለት ሰሜናዊ ግንባር በተነፋበት ዛሬ ሀምሌ 25/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር ከሻለቃ ሶስት ጋር ልዩ የተሃድሶ ዝግጅት አድርጓል። ጀብደኛዉ 44ኛ ክፍለ ጦር ወታደራዊ ዝግጅቱን በጎን እያካሔደ በሌላ በኩል ደግሞ ፋኖን ለመምታት ደፈጣ የያዙ ሁለት የጠላት ሀይልን ቲሊሊ ከተማ አቅራቢያ በመማረክ ድል ተጎናፅፏል። አይነኬ መሆኑን እያስመሰከረ የቀጠለዉ የቀጠናዉ ልዕለ ሀያል ክፍለ ጦር ቀጣይ ለየት ያሉ ጀብዱዎችን ለመስራት በብልፅግና ትኩስ መቃብር ላይ ቁሞ በልዩ ድምቀት የሻለቃ ሶስት ተሃድሶ ፕሮግራምን አካሂዷል። ድርጅታችን አፋብን ያለሰለሰ አለማቀፋዊና ቀጠናዊ ግንኙነቶች በትኩረት እያካሄደ፤ ስነ መንግስትንነት በክብር ለመረከብ ሌት ቀን እየሰራ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ባለበት በዚህ ልዩ ሰሃት ነበልባሉ ክፍለ ጦርም በልዩ የስነልቦና እና ወታደራዊ ዝግጁነት ማረጋገጡን ቀጥሏል። አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት፡

በላስታ ወረዳ ከገለሶት(07) ቀበሌ እና ከእርፋ (08) ቀበሌ ማህበረሰብ ጋር የአማራን የህልውና ትግል አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ ህዝባዊ ውይይት ተካሄደ! ​በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን የህልውና ትግል ይበልጥ ለማጠናከር እና የትግሉን ህዝባዊ መሰረት ይበልጥ ለማስፋት ያለመ ሰፊ ህዝባዊ ውይይት በላስታ ወረዳ ከገለሶት(07)ቀበሌ  ማህበረሰብ ጋር ተካሂዷል። ​በዚህ ወሳኝ የንቅናቄና የውይይት መድረክ ላይ የትግሉ ከፍተኛ ወታደራዊ እና የሲቪል አመራሮች የተገኙ ሲሆን፤ ​በዚህም አርበኛ አሰፋ መለሰ — የምኒልክ ዕዝ አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ ፣አርበኛ ኢንጅነር አራጋዉ ያለዉ — የምኒልክ ዕዝ እቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ኃላፊ ፣የ303ኛ አሳምነዉ ኮር ከፍተኛ አመራሮች ፣የ19ኛ (እሽት) ክፍለ ጦር አመራሮች፣ እንዲሁም የላስታ ወረዳ ጊዚያዊ አስተዳደር ሲቪል መዋቅር አመራሮች ተሳትፈዋል። ​በመድረኩ ላይ በተደረገው ውይይት፤ የአማራን ህዝብ ህልውናና ክብር ለማስጠበቅ በሚደረገው ትግል ውስጥ ማህበረሰቡ ለሰራዊቱ እያደረገ ያለውን ደጀንነትና ያልተቋረጠ ድጋፍ ይበልጥ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሰፊው ተመክሮበታል። ወታደራዊና የሲቪል አመራሮቹ በበኩላቸው፤ ሰራዊቱ ከህዝቡ ጋር ያለውን የማይበጠስ ትስስር በማጠናከር የትግሉን የመጨረሻ ግብ ለማሳካት በከፍተኛ ሞራል ቆርጦ መነሳቱን አብራርተዋል። ​በውይይቱ የተሳተፉት የገለሶት ማህበረሰብ አባላት በበኩላቸው፤ "ትግሉ የሁላችንም የህልውና ትግል ነው" በማለት፣ ከሰራዊቱ ጎን በፅናት በመቆም ስንቅ ከማቅረብና ሎጂስቲክስ ከመደገፍ ጀምሮ ለትግሉ  የሚያደርጉትን ሁለንተናዊ አስተዋፅኦ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል። ​ይህ አይነቱ ህዝባዊ መድረክ በትጥቅ ትግሉ፣ በጊዜያዊ አስተዳደሩ እና በማህበረሰቡ መካከል ያለውን መግባባት ከማሳደጉም ባሻገር፤ የህዝቡን አንድነት በማፅናት ለትግሉ ስኬት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተጠቁሟል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!     ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!          ሐምሌ:- 26/ 2018 ዓ/ም

#አሳዛኝ_ዜና ❗❗ በንፁሃን ዜጎች እና በዕድሜ ጠገብ አባት እናቶች ላይ የሚደርስ ማንኛውም ዓይነት እንግልት መከራ ስቃይ እና የህይወት ህልፈት እጅግ የሚያዝን ልብ የሚሰብር ነው። ሰላማዊ ሁነው በዕ
#አሳዛኝ_ዜና ❗❗ በንፁሃን ዜጎች እና በዕድሜ ጠገብ አባት እናቶች ላይ የሚደርስ ማንኛውም ዓይነት እንግልት መከራ ስቃይ እና የህይወት ህልፈት እጅግ የሚያዝን ልብ የሚሰብር ነው። ሰላማዊ ሁነው በዕድሜ የገፉ ታላላቅ ሰዎች ላይ የሚፈፀም ጥቃትና ግፍ በማንኛውም አካል ቢፈፀም ሰብዓዊነትን የሚፃረርና ተቀባይነት የሌለው ነው። ​እንደነዚህ ያሉ አሳዛኝ ዜናዎችን መስማት እና ምስሎችን ማየት ምን ያህል ልብ እንደሚነካ እንደሚያሳዝን ይታወቃል ።ተወልደው ባደጉበት ሀገር በራሳቸው ቅየ ተደብድበው የሚገደሉ ወጣቶች ብዙ ናቸው ከቀን ወደ ቀን እየባሰ የመጣው ይህ ስርዓት ወጣቱን እና እድሚያቸው የገፉትን ከማንምና ከምንም ነገር ነፃ ሁነው በሰላም የሚኖሩትን አማሮች በግፍ እየደበደበና እየረሸነ መጣሉን ቀጥሎበታል። በጎንቻ ሲሶ እነሴ ጠጅ ባህር ቀበሌ ውስጥ የሚኖሩ እኒህ የ65 ዓመት እድሜ የሆኑት አባት በአማራነታቸው ብቻ በአገዛዙ ቅጥረኛ በጭካኔ በጥይት ተደብድበው ህይዎታቸው አልፏል። ነፍስ ይማር 😢

አርበኛ ዘመነ ካሴ እና የአፋር ኡጉጉሞ አመራር ተወያዩ! ​"እንዲያ ምን ይሻላል ጎጃም ሲሉት ጎንደር ገብቶ አስቸገራቸው… መቀሌ ነው ቢሉት መተከል ጉምዝ ከች ብሎ አገኙት… ኤርትራ ነህ ሲሉት ሸዋ ተ
+1
አርበኛ ዘመነ ካሴ እና የአፋር ኡጉጉሞ አመራር ተወያዩ! ​"እንዲያ ምን ይሻላል ጎጃም ሲሉት ጎንደር ገብቶ አስቸገራቸው… መቀሌ ነው ቢሉት መተከል ጉምዝ ከች ብሎ አገኙት… ኤርትራ ነህ ሲሉት ሸዋ ተገኘባቸው… ጎንደር ነው ቢሉት አፋር ተገኘባቸው… እንዲያ ምን ይሻላል እሳት እርመጥ ሆኖ አስቸገራቸው የአብዮቱ ፎርሙላ አርበኛ ዘመነ ካሴ! ​ትግል የቦታወሰን የለውም፤ የዓላማ እንጂ! ዛሬ ታሪክ ሌላ ምዕራፍ እየጻፈች ነው፤ ድንበርና አጥርን ያፈረሰ፣ የህዝቦችን እውነተኛ ወንድማማችነት ያበሰረ አዲስ መንገድ እየተጠረገ ይገኛል። ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሰብሳቢ አርበኛ ዘመነ ካሴ ከአፋር ኡጉጉሞ ሰብሳቢ ጋር ባደረጉት ታሪካዊ ውይይት፣ ሀገራዊና ቀጠናዊ የፖለቲካ አሰላለፉን ሙሉ በሙሉ የሚቀይር አዲስ የጋራ መሰረት ጥለዋል! ​ይህ ውይይት የፖለቲካ ንግግር ብቻ አይደለም፤ የህዝቦች የእጅ ለእጅ ተያይዞ የመቆም ጽኑ ማረጋገጫ ነው! እሳት አርመጥ የሆነው የለውጥ እሳቤ ዛሬ ከአፋር በረሃ እስከ ጎጃም፣ ጎንደር፣ ሸዋ እና ወሎ ድረስ የአንድነትና የነጻነትን ጥሪ እያስተጋባ ይገኛል። ​የለውጡ አቅጣጫ ግልጽ ነው የተበታተነ ትግል የለም፤ የጋራ አላማ እና የጋራ ድል እንጂ! Dave Amhara

እኛ አማራዎች ነን! ​ለሰው ልጅ ያለን ፍቅር የጠለቀ፣ ሰብእናችን ወሰን የሌለው፣ እጃችን ለደግነትና ለእንግዳ ተቀባይነት ሁልጊዜ የተዘረጋ ነው! ይህ ፍቅራችን የዘመናት እሴታችን፣ የማንነታችን መሠረት ነው፤ ለምን ቢሉ... አማራ ሆነን መፈጠራችን ራሱ የፍቅር፣ የጽናትና የክብራችን ታላቅ ምስክር ስለሆነ! ​​የታሪክ ድርሳናት አንድ በአንድ ይገለበጡ፤ ብራናዎችና የገድል መጻሕፍት በጥቅስና በስም ይነበቡ! ትናንት ሀገርን በደም አጥንታቸው ያቆሙ አባቶቻችን የጀግንነት ምዕራፍ ዛሬም በደም ስራችን ውስጥ እንደ ወንዝ የሚፈስ። ከነባሩ የታሪክ ስር የበቀልን፣ የሀገር ምሰሶና ማገዶ ሆነን የኖርን ጠንካራ ህዝቦች ነን። ​ ​እኛ የጀግናው አሳምነው የማይበገር ፅናትና ቁርጠኛ መንፈስ የተላበስን፣ በታላቅነቱና በጥበቡ የዐፄ ሚኒሊክ አጥንት የተገነባን የማይናወጥ ማህበረሰብ የትናንቱ የነፃነትና የጀግንነት ታሪካችን ዛሬም በነፃነት ትግላችን ውስጥ ህያው ሆኖ የሚነድ ባልምጡቅ አዕምሮ ያደለን ፍጡር ጭምር እንጅ!! ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ድርጅታችን ከጽኑ መከራና ግፍ ነፃ የሚወጣበት፣ የታሪካችን የመጨረሻው የነፃነትና የክብር ነፀብራቅ የሆነ በጊዜ ሂደት የምንጠፋ ሳንሆን ታሪክ የወለደን፣ ታሪክን ከትናንት ወደ ዛሬ፣ ከዛሬ ደግሞ ወደ ነገ አሻግረን ለወደፊቱ ትውልድ እንድናስረክብ ተፈጥሮ ራሷ በልዩ ጸጋ ያደለችን ፍጡራን ነን! ፅናታችን አይበገሬ፣ ጉዟችንም ወደ ሙሉ ነፃነትና ክብር ነው! የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ አስተዳደር መምሪያ አርበኛ ኤፍሬም ባዬ ታናሽ ወንድምህ #Dave #Amhara

አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የቀድሞው 106ኛ ኮር የአሁኑ 16ኛ ኮር የተሳካ ኦፕሬሽን በፋሽስቱ ሰራዊት ላይ ወስዷል!! የቀድሞዋ 34ኛ ክፍለጦር በአድሱ አደረጃጀት 163ኛ ክፍለጦር በ2ኛ ሻለቃ በጋዞ ምድር የጠላትን ሰራዊት ዶግ አመድ ተደርጓል!! ትናንት ሀምሌ 24/2018 ዓ/ም 2ኛ ሻለቃ ጋዞ እስታይሽ ዋሮ ተብሎ በሚጠራ ቀበሌ፡ሲቀሳቀስ በነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ቅስፈታዊ ጥቃት በመክፈት በርካታ የጠላት ወታደራዊና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰዉበታል። ማህበረሰቦች 08 የመከላከያ ሰራዊቶች መሳሪያ ደርበው ወደ መጡበት ቀጠና ሲመለሱ አይተናል ያሉ ሲሆን፤ከዚህ ዜና ጋር ተያይዞ ሶስት የተደመሰሱና አስከሬናቸውን ሳያነሳ ጥሎ የፈረጠጠ ሲሆን፤04 ከባድ ቁስለኛ ተደርገዋል። ✔️ቁስለኞቹን በስትሬቸር ተሸክሞ ወደ ጉሬው ተመልሷል!! መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል ሲል የ16ኛ ኮር ቃል አቀባይ መረጃውን አድርሶናል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሀምሌ 25/2018 ዓ/ም

አፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ‼ፋኖን ለመያዝ ደፈጣ የጣሉ የብልፅግና ወንበር ጠባቂ ሰራዊት አባላት በአፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር ቲሊሊ ከተማ አቅራቢያ በቁጥጥር ስር ውለዋል። #Dave
+1
አፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ‼ፋኖን ለመያዝ ደፈጣ የጣሉ የብልፅግና ወንበር ጠባቂ ሰራዊት አባላት በአፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር ቲሊሊ ከተማ አቅራቢያ በቁጥጥር ስር ውለዋል። #Dave #Amhara

የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር ለተከታታይ ቀናት ሲያደርግ የቆየውን ጥልቅ ግምገማ እና የታህድሶ ስልጠና በስኬት በማጠናቀቅ፣ ድርጅታዊና ወታደራዊ አቅሙን የሚያጎለብት ከፍተት የነበራቸው የኮር አመራር ማሟላት በማድረግ ተጠናቋል። እንዲሁም ከዚህ ቀደም የ106ኛ ኮር ተብሎ ይጠራ የነበረው (የደጋው መብረቅ) ኮር ከድርጅታችን አፋብን በወረደው ወታደራዊ የአደረጃጀት መመሪያ መሰረት ከዚህ በኋላ 16ኛ ኮር ተብሎ የሚጠራ ሲሆን የክፍለጦሮች ስያሜም፦ 22ኛ ክፍለጦር ወደ 161ኛ ክፍለጦር፣ 31እኛ ክፍለጦር ወደ 162ኛ ክፍለጦር፣ 34ኛ ክፍለጦር ወደ 163ኛ ክፍለጦር ስያሜ የተሰጣቸው መሆኑን እናበስራለን። ​ይህ አደረጃጀት በየደረጃው ያሉ አርበኞችን አፈፃፀምና ብቃት መሠረት በማድረግ የተከናወነ ሲሆን፣ የኮሩን የወደፊት ድርጅታዊና ወታደራዊ ተልዕኮዎች በተሻለ ቁመና ለማስፈጸም ያለመ ነው። በዚህም የግምገማ፣ ተሃድሶና ስልጠና ፕሮግራም የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ም/ሰብሳቢ አርበኛ ረዳ ዉበቱን(ቀኝ አዝማች)፣ የዕዙ ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ወንድሙ ማሩ(ሚሳኤሉ)፣ የዕዙ ፖለቲካ መምሪያ አርበኛ ሞገስ አባራዉ፣ የዕዙ ጽ/ቤት አርበኛ አለምነው መብራቱ፣ የዕዙ ዘመቻ መምሪያ አርበኛ በለጠ ሸጋዉ እና ሌሎች የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። ​📌 አዲስ የተመደቡ የ16ኛ ኮር አመራሮች ዝርዝር 1)አርበኛ ሀብቴ እባቡ ሰብሳቢ 2)አርበኛ ተመስጌን አለባቸዉ ወታደራዊ አዛዥ 3)አርበኛ ማዕረጉ አስፋዉ ም/ወታደራዊ አዛዥ 4)አርበኛ መ/ር መኩሪያ አጋዥ ፓለቲካመምሪያ 5)አርበኛአስፌ አበጋዥ ዘመቻ መምሪያ 6)አርበኛ ሰለሞን ፀጋየ ም/ዘመቻ መምሪያ 7)አርበኛ አበበ ቢራራ ስምሪት 8)አርበኛ ሙሉቀን አለቤ ፋይናስ መምርያ 9)አርበኛ ፍቅር አራጌ ም/ፋይናስ 10)አርበኛ ናትናኤል ዉዱ ወታደራዊ አስተዳደር 11)አርበኛ ዉበት ደምሴ ም/ወታደራዊ አስተዳደር 12)አርበኛ መሣፍንት ደሴ ሎጀስቲክ መምሪያ 13)አርበኛ ጋሻዉ ም/ሎጀስቲክ መምሪያ 14)አርበኛ እሸቱ አባተ ቃል አቀባይ 15)አርበኛ ሙሉጌታ አሻግሬ ኦርዲናስ 16)አርበኛ መንገሻ ተገኜ የሠዉ ሀይል 17)መረጃ ....................... 18)አርበኛ መቶ አለቃ ሲሳይ ስልጠና መምሪያ 19)አርበኛ ጋሻዉ ቢያርጎ ም/ስልጠና መምሪያ 20)አርበኛ መካሽ ሰጠዪ ህግ ክፍል 21)አርበኛ ሳአለአምላክ አሻግሬ ኦዲተር 22)አርበኛ አወቀ ብዙአየሁ ህዝብ አደረጃጀት 23)አርበኛ ስመኘዉ ሲሳይ የቃኚ መሪ 24)አርበኚት መቅደስ ብርሃን የሴቶች ጉዳይ 25)አርበኛ ዶ/ር መላኩ የሻነዉ የህክምና መምሪያ 26)አርበኛ አለበል ተካልኝ ግዢ ክፍል 27)አርበኛ አታሎ መገናኛ 28)አርበኛ ደንበሩ አስማሜ ኢንዶክትሬኒሽን 29) አርበኛ እንዳለማው ፈጠነ ወታደራዊ አማካሪ በማድረግ አደረጃጀቱ በተሳካ ሁኔታ ተከናዉኗል!! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ! ሐምሌ 25/11/2018 ዓ'ም

ነበልባል ክ/ጦር የጨፍጫፊውን አገዛዝ ጥምር ጦር ዕቆድ አከሸፈ! ​ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ​የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ ከሰም 2ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር የአገዛዙን ጥምር ኃይል በንጹሃን ዜጎች ላይ ያቀደውን የጥቃትና የዝርፊያ እንቅስቃሴ አከሸፈ። ​የአገዛዙ ጥምር ሀይል በቀን 24/11/2018 ዓ.ም በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ማለትም ሲቪለን፣ ምነበላ፣ አዳማ ወንዝእና ቱሊ በተባሉ አካባቢዎች ሰፊ እንቅስቃሴ ያደረገ ቢሆንም በነበልባል ክ/ጦር ፈጣን የማጥቃት እነሰቅስቃሴ በማድረግ የአገዛዙን ሀይል ያዋረደ ድል ተቀዳጅተዋል። አገዛዙ በነበረው እልህ አስጨራሽ ውጊያ በአርሶ አደር ቤት እና ንብረት ላይ ያለውን ሁሉ መሳሪያ የተጠቀመ ቢሆንም የአርሶ አደሮች ንብረት እና ህይወት ማጥፋቱን ቀጥሎበታል። የነበልባል ክ/ጦር የሲቪሎችን ህይወት ለመታደግ ሲባል የስልት ለውጥ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። ነበልባል ክፍለ ጦር አባላት ከአገዛዙ ኃይል ጋር ባደረጉት ፍልሚያ የተቃጣውን የጥቃት እቅድ አክሽፈዋል። ​ የጠላት ኃይል አርሶ አደሮችን ለውጊያ መከታነት ለመጠቀም በሞከረበት ወቅት የፋኖ ሰራዊታችን የውጊያ ስልቱን በመቀየር የንጹሃንን ህይወት መታደግ ችሏል። በተለይም በሲቪለንእና ምነበላ ግንባሮች የነበረው ከፍተኛ ውጊያ የጠላትን ሀይል ሙትና ቁስለኛ ማድረጋቸውን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል። ​በተጨማሪም በአዳማ ወንዝ አካባቢ በተደረገ የተቀናጀ ደፈጣ በጥምር ኃይሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ያሳወቁ ሲሆን፤ የአገዛዙ ጨፍጫፊ ኃይል በሰነዘረው የከባድ መሳሪያ ድብደባ በንጹሃን አርሶ አደሮች ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የግንባር መረጃችን አክሎ ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የማንነት ውዥንብርና የእውነት ምላሽ!! ​ለረጅም ጊዜያት በአገራችን ፖለቲካ ውስጥ ትልቅ ግራ መጋባትና ድንግርግር ሲፈጠር አስተውለናል። ይህ ውዥንብር ደግሞ እንዲሁ በዋዛ የተፈጠረ ሳይሆን፣ እኛን ለማሳደድና ለማግለል የታሰበበት ስልት ነበር። ​‘እኛ አማራዊያን ነን፤ አማራ ነን’ ብለን ማንነታችንን ስንናገር፣ ‘አይ እናንተ አማራ ሳትሆኑ ኢትዮጵያዊ ናችሁ’ እያሉ የራሳችንን ማንነት ሊነጥቁን ይሞክራሉ። እሺ ብለን ‘ኢትዮጵያዊ ነን’ ስንላቸው ደግሞ፣ ገጽታቸውን ቀይረው ‘አይ እናንተማ አማራ ናችሁ’ እያሉ የታሪክና የማንነት ድንግርግር ውስጥ በመክተት ሲያሳድዱንና ሲያገለሉን ኖረዋል። ​ይህ የቃላትና የታሪክ ጨዋታ፣ ማንነታችንን የማደናገርና የማን አለብኝነት አካሄድ አሁን አብቅቶለታል። ​አማራነትና ኢትዮጵያዊነት ተቃራኒዎች አይደሉም፤ አንዱ ያለ አንዱ ሙሉ አይሆንም። አማራ መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ፣ እንዲሁም ከታሪክ እስከ ዛሬ ኢትዮጵያዊነትን ደም አድርጎ መኖርና አገርን ማስቀደም እንዴት እንደሆነ አሁን በግልጽ፣ በጽናትና በተግባር እናሳያቸዋለን! ከደባይ ጮቄ የተራራ ጫፎች የጀግንነትና የፅናት አሻራ የተላበሱ የቴዎድሮስ አናብስት ፋኖዎች! ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ፣ 206ኛ ኮር፣ 24ኛ ክፍለ ጦር ደባይ ጮቄ #Dave #Amhara ከጎጃም ሰማይ ስር!!

የአማራን ሕዝብ ጠላትና ወዳጁን ከአባይ ማዶ ተሻግረው ሊያስተምሩት ሲዳዱ እናያለን። ማነው የበላይ ልጅ ጎጃምን? ማነው የቴዎድሮስ ልጅ ጎንደርን? ማነው የሚኒልክ ልጅ ሸዋን? ማነው የአሳምነው ልጅ ወ
የአማራን ሕዝብ ጠላትና ወዳጁን ከአባይ ማዶ ተሻግረው ሊያስተምሩት ሲዳዱ እናያለን። ማነው የበላይ ልጅ ጎጃምን? ማነው የቴዎድሮስ ልጅ ጎንደርን? ማነው የሚኒልክ ልጅ ሸዋን? ማነው የአሳምነው ልጅ ወሎን? ስለ አማራ ሊያስተምር የሚችለው? #ፊሽኩዋ ተነፍታለች አለቀ ሆነ ተከናወነ ከታች ያለውን የቴሌግራም አካውንት ሸርና ጆይኝ በማድረግ ይወዳጁን!!

ስቦ ማስከዳቱ ቀጥሏል #_4ሚሊሻ እና 2 ፓራ ኮማንዶ አባለት ፋኖን ተቀላቅለዋል። ~~~~ ....ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም ከደ/ወርቅ እና ግንደወይን ከተማ 2 ፓራ ኮማንዶ እና 4 ሚሊሻዎች በድምሩ 6 የጠላት ኃይል ኮብልለው ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን ተቀላቅለዋል። 1.የፀዳው ምኒልክ....ፓራ ኮማንዶ 2.ንዋይ ቢተው......ፓራ ኮማንዶ 3.ጀንበሩ ይዘንጋው .....ሚሊሻ 4.አስማረ ባየ.........ሚሊሻ 5.በተግባር ተምትም.........ሚሊሻ 6.ጌቴ ዮሐንስ..........ሚሊሻ ሲሆኑ በ74ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አሁንም ጊዜው አልረፈደም እራሳቹትን አድኑ!! አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የጠላት ኃይል ወደ ይፋት አውራጃ--ቀወት  ለዘረፋ ያደረገው እንቅስቃሴ በፋኖ ከበባ ውስጥ ሲገኝ በጥቂት ሰዓታት ውጊያ ብዙ ሙትና ቁስለኛ ማስተናገዱ ተገለፀ!!         ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም የጠላት ሀይል ከባሽ ተነስተው ወደ ይፋት አቅጣጫ በሦስት መስመር የመውረር ሙከራ ያደረገ ሲሆን፦ ➛ከባሽ በንፋስ አምባ በኩል ወደ ዘከሬ ተራራ፣ ➛ከባሽ ቀጥታ ወደ ቀወት መስመር፣ ➛ከባሽ ወደ ቆሎማያ አቅጣጫ በሦስቱም አቅጣጫዎች የተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ወደፊት ለመግፋትም ሆነ ወደኋላ ለመመለስ በማይችልበት ደረጃ በአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ደጃዝማች ተሰማ እርገጤ እና አስቻለው ደሴ ክፋለጦር ከበባ ውስጥ ይገኛል። ተጨማሪ ኃይል (ከሸዋሮቢት፣ ከሞላሌ እና ከመሐል ሜዳ)  ቢጠይቅም፣ በወገን ሀይል ከበባ ውስጥ የሚገኘትን ደፈጣዎችና ከበባዎች ለማለፋ የተቸገረው ሀይል የደገፈውና የመጣለት ኃይል እደሌለ ተረጋግጧል። የባሽ ከተማ ሙሉ በሙሉ በደጃዝማች ተሰማ እርገጤ በክፍለ ጦሩ ቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን፤ በዚህ ውጊያ ላይ የባሽ ክላስተር እና የተሬ ክላስተር አባት አርበኞች ጦር ከፍተኛ ታሪክ እየሠሩ ይገኛሉ ሁለት የጠላት ኃይልን እስከወዲያኛው እዳሰናበቱ ተረጋግጧል። በሌላ እቅጣጫ ከመዘዞ አቅጣጫ የተቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ከመዘዞ ተነስቶ በአያበር ቀበሌ በኩል ወደ መንግስት ለመሸጋገር ሲንቀሳቀስ  በአካባቢው በሚገኘው አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር ቅጽበታዊ እርምጃ ተወስዶበት ከበባ ውስጥ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት መሶቢት በተባለ ቦታ ተራራ ላይ ተሰቅሎ የሚገኝ ሲሆን፣ ተጨማሪ ደጋፊ ኃይል ቢጠይቅም የሚደርስለት በማጣቱ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ይገኛል። በተያያዘ ዜና ከአጣዬና አላላ ተነስቶ በሁለት አቅጣጫ ማለትም የአጣየው በከሰያት ወደ ደረትማ እዲሁም የአላላው በብርቂቶ ወደ ደረትማ  የተንቀሳቀሰውን ዘራፊ ጥምር ቡድን ጀግናው 7/ለ70 ክፍለጦር እዳመጣጡ እያሳደዱት ሲሆን መሸሽ ያልቻለው በየጉረኖው ተደፍቶ ቀርቷል። በዚሕም ጠላት የሞቱትን ትቶ የቆሰሉት ወደ አጣዬ ወስዶ በማሳከም ላይ ይገኛል። ክብር ለትግሉ ሠማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!