ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 936
订阅者
+1424 小时
+3877 天
+38530 天
帖子存档
የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር ለተከታታይ ቀናት ሲያደርግ የቆየውን ጥልቅ ግምገማ እና የታህድሶ ስልጠና በስኬት በማጠናቀቅ፣ ድርጅታዊና ወታደራዊ አቅሙን የሚያጎለብት ከፍተት የነበራቸው የኮር አመራር ማሟላት በማድረግ ተጠናቋል። እንዲሁም ከዚህ ቀደም የ106ኛ ኮር ተብሎ ይጠራ የነበረው (የደጋው መብረቅ) ኮር ከድርጅታችን አፋብን በወረደው ወታደራዊ የአደረጃጀት መመሪያ መሰረት ከዚህ በኋላ 16ኛ ኮር ተብሎ የሚጠራ ሲሆን የክፍለጦሮች ስያሜም፦ 22ኛ ክፍለጦር ወደ 161ኛ ክፍለጦር፣ 31እኛ ክፍለጦር ወደ 162ኛ ክፍለጦር፣ 34ኛ ክፍለጦር ወደ 163ኛ ክፍለጦር ስያሜ የተሰጣቸው መሆኑን እናበስራለን። ​ይህ አደረጃጀት በየደረጃው ያሉ አርበኞችን አፈፃፀምና ብቃት መሠረት በማድረግ የተከናወነ ሲሆን፣ የኮሩን የወደፊት ድርጅታዊና ወታደራዊ ተልዕኮዎች በተሻለ ቁመና ለማስፈጸም ያለመ ነው። በዚህም የግምገማ፣ ተሃድሶና ስልጠና ፕሮግራም የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ም/ሰብሳቢ አርበኛ ረዳ ዉበቱን(ቀኝ አዝማች)፣ የዕዙ ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ወንድሙ ማሩ(ሚሳኤሉ)፣ የዕዙ ፖለቲካ መምሪያ አርበኛ ሞገስ አባራዉ፣ የዕዙ ጽ/ቤት አርበኛ አለምነው መብራቱ፣ የዕዙ ዘመቻ መምሪያ አርበኛ በለጠ ሸጋዉ እና ሌሎች የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። ​📌 አዲስ የተመደቡ የ16ኛ ኮር አመራሮች ዝርዝር 1)አርበኛ ሀብቴ እባቡ ሰብሳቢ 2)አርበኛ ተመስጌን አለባቸዉ ወታደራዊ አዛዥ 3)አርበኛ ማዕረጉ አስፋዉ ም/ወታደራዊ አዛዥ 4)አርበኛ መ/ር መኩሪያ አጋዥ ፓለቲካመምሪያ 5)አርበኛአስፌ አበጋዥ ዘመቻ መምሪያ 6)አርበኛ ሰለሞን ፀጋየ ም/ዘመቻ መምሪያ 7)አርበኛ አበበ ቢራራ ስምሪት 8)አርበኛ ሙሉቀን አለቤ ፋይናስ መምርያ 9)አርበኛ ፍቅር አራጌ ም/ፋይናስ 10)አርበኛ ናትናኤል ዉዱ ወታደራዊ አስተዳደር 11)አርበኛ ዉበት ደምሴ ም/ወታደራዊ አስተዳደር 12)አርበኛ መሣፍንት ደሴ ሎጀስቲክ መምሪያ 13)አርበኛ ጋሻዉ ም/ሎጀስቲክ መምሪያ 14)አርበኛ እሸቱ አባተ ቃል አቀባይ 15)አርበኛ ሙሉጌታ አሻግሬ ኦርዲናስ 16)አርበኛ መንገሻ ተገኜ የሠዉ ሀይል 17)መረጃ ....................... 18)አርበኛ መቶ አለቃ ሲሳይ ስልጠና መምሪያ 19)አርበኛ ጋሻዉ ቢያርጎ ም/ስልጠና መምሪያ 20)አርበኛ መካሽ ሰጠዪ ህግ ክፍል 21)አርበኛ ሳአለአምላክ አሻግሬ ኦዲተር 22)አርበኛ አወቀ ብዙአየሁ ህዝብ አደረጃጀት 23)አርበኛ ስመኘዉ ሲሳይ የቃኚ መሪ 24)አርበኚት መቅደስ ብርሃን የሴቶች ጉዳይ 25)አርበኛ ዶ/ር መላኩ የሻነዉ የህክምና መምሪያ 26)አርበኛ አለበል ተካልኝ ግዢ ክፍል 27)አርበኛ አታሎ መገናኛ 28)አርበኛ ደንበሩ አስማሜ ኢንዶክትሬኒሽን 29) አርበኛ እንዳለማው ፈጠነ ወታደራዊ አማካሪ በማድረግ አደረጃጀቱ በተሳካ ሁኔታ ተከናዉኗል!! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ! ሐምሌ 25/11/2018 ዓ'ም

ነበልባል ክ/ጦር የጨፍጫፊውን አገዛዝ ጥምር ጦር ዕቆድ አከሸፈ! ​ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ​የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ ከሰም 2ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር የአገዛዙን ጥምር ኃይል በንጹሃን ዜጎች ላይ ያቀደውን የጥቃትና የዝርፊያ እንቅስቃሴ አከሸፈ። ​የአገዛዙ ጥምር ሀይል በቀን 24/11/2018 ዓ.ም በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ማለትም ሲቪለን፣ ምነበላ፣ አዳማ ወንዝእና ቱሊ በተባሉ አካባቢዎች ሰፊ እንቅስቃሴ ያደረገ ቢሆንም በነበልባል ክ/ጦር ፈጣን የማጥቃት እነሰቅስቃሴ በማድረግ የአገዛዙን ሀይል ያዋረደ ድል ተቀዳጅተዋል። አገዛዙ በነበረው እልህ አስጨራሽ ውጊያ በአርሶ አደር ቤት እና ንብረት ላይ ያለውን ሁሉ መሳሪያ የተጠቀመ ቢሆንም የአርሶ አደሮች ንብረት እና ህይወት ማጥፋቱን ቀጥሎበታል። የነበልባል ክ/ጦር የሲቪሎችን ህይወት ለመታደግ ሲባል የስልት ለውጥ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። ነበልባል ክፍለ ጦር አባላት ከአገዛዙ ኃይል ጋር ባደረጉት ፍልሚያ የተቃጣውን የጥቃት እቅድ አክሽፈዋል። ​ የጠላት ኃይል አርሶ አደሮችን ለውጊያ መከታነት ለመጠቀም በሞከረበት ወቅት የፋኖ ሰራዊታችን የውጊያ ስልቱን በመቀየር የንጹሃንን ህይወት መታደግ ችሏል። በተለይም በሲቪለንእና ምነበላ ግንባሮች የነበረው ከፍተኛ ውጊያ የጠላትን ሀይል ሙትና ቁስለኛ ማድረጋቸውን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል። ​በተጨማሪም በአዳማ ወንዝ አካባቢ በተደረገ የተቀናጀ ደፈጣ በጥምር ኃይሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ያሳወቁ ሲሆን፤ የአገዛዙ ጨፍጫፊ ኃይል በሰነዘረው የከባድ መሳሪያ ድብደባ በንጹሃን አርሶ አደሮች ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የግንባር መረጃችን አክሎ ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የማንነት ውዥንብርና የእውነት ምላሽ!! ​ለረጅም ጊዜያት በአገራችን ፖለቲካ ውስጥ ትልቅ ግራ መጋባትና ድንግርግር ሲፈጠር አስተውለናል። ይህ ውዥንብር ደግሞ እንዲሁ በዋዛ የተፈጠረ ሳይሆን፣ እኛን ለማሳደድና ለማግለል የታሰበበት ስልት ነበር። ​‘እኛ አማራዊያን ነን፤ አማራ ነን’ ብለን ማንነታችንን ስንናገር፣ ‘አይ እናንተ አማራ ሳትሆኑ ኢትዮጵያዊ ናችሁ’ እያሉ የራሳችንን ማንነት ሊነጥቁን ይሞክራሉ። እሺ ብለን ‘ኢትዮጵያዊ ነን’ ስንላቸው ደግሞ፣ ገጽታቸውን ቀይረው ‘አይ እናንተማ አማራ ናችሁ’ እያሉ የታሪክና የማንነት ድንግርግር ውስጥ በመክተት ሲያሳድዱንና ሲያገለሉን ኖረዋል። ​ይህ የቃላትና የታሪክ ጨዋታ፣ ማንነታችንን የማደናገርና የማን አለብኝነት አካሄድ አሁን አብቅቶለታል። ​አማራነትና ኢትዮጵያዊነት ተቃራኒዎች አይደሉም፤ አንዱ ያለ አንዱ ሙሉ አይሆንም። አማራ መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ፣ እንዲሁም ከታሪክ እስከ ዛሬ ኢትዮጵያዊነትን ደም አድርጎ መኖርና አገርን ማስቀደም እንዴት እንደሆነ አሁን በግልጽ፣ በጽናትና በተግባር እናሳያቸዋለን! ከደባይ ጮቄ የተራራ ጫፎች የጀግንነትና የፅናት አሻራ የተላበሱ የቴዎድሮስ አናብስት ፋኖዎች! ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ፣ 206ኛ ኮር፣ 24ኛ ክፍለ ጦር ደባይ ጮቄ #Dave #Amhara ከጎጃም ሰማይ ስር!!

የአማራን ሕዝብ ጠላትና ወዳጁን ከአባይ ማዶ ተሻግረው ሊያስተምሩት ሲዳዱ እናያለን። ማነው የበላይ ልጅ ጎጃምን? ማነው የቴዎድሮስ ልጅ ጎንደርን? ማነው የሚኒልክ ልጅ ሸዋን? ማነው የአሳምነው ልጅ ወ
የአማራን ሕዝብ ጠላትና ወዳጁን ከአባይ ማዶ ተሻግረው ሊያስተምሩት ሲዳዱ እናያለን። ማነው የበላይ ልጅ ጎጃምን? ማነው የቴዎድሮስ ልጅ ጎንደርን? ማነው የሚኒልክ ልጅ ሸዋን? ማነው የአሳምነው ልጅ ወሎን? ስለ አማራ ሊያስተምር የሚችለው? #ፊሽኩዋ ተነፍታለች አለቀ ሆነ ተከናወነ ከታች ያለውን የቴሌግራም አካውንት ሸርና ጆይኝ በማድረግ ይወዳጁን!!

ስቦ ማስከዳቱ ቀጥሏል #_4ሚሊሻ እና 2 ፓራ ኮማንዶ አባለት ፋኖን ተቀላቅለዋል። ~~~~ ....ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም ከደ/ወርቅ እና ግንደወይን ከተማ 2 ፓራ ኮማንዶ እና 4 ሚሊሻዎች በድምሩ 6 የጠላት ኃይል ኮብልለው ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን ተቀላቅለዋል። 1.የፀዳው ምኒልክ....ፓራ ኮማንዶ 2.ንዋይ ቢተው......ፓራ ኮማንዶ 3.ጀንበሩ ይዘንጋው .....ሚሊሻ 4.አስማረ ባየ.........ሚሊሻ 5.በተግባር ተምትም.........ሚሊሻ 6.ጌቴ ዮሐንስ..........ሚሊሻ ሲሆኑ በ74ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አሁንም ጊዜው አልረፈደም እራሳቹትን አድኑ!! አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የጠላት ኃይል ወደ ይፋት አውራጃ--ቀወት  ለዘረፋ ያደረገው እንቅስቃሴ በፋኖ ከበባ ውስጥ ሲገኝ በጥቂት ሰዓታት ውጊያ ብዙ ሙትና ቁስለኛ ማስተናገዱ ተገለፀ!!         ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም የጠላት ሀይል ከባሽ ተነስተው ወደ ይፋት አቅጣጫ በሦስት መስመር የመውረር ሙከራ ያደረገ ሲሆን፦ ➛ከባሽ በንፋስ አምባ በኩል ወደ ዘከሬ ተራራ፣ ➛ከባሽ ቀጥታ ወደ ቀወት መስመር፣ ➛ከባሽ ወደ ቆሎማያ አቅጣጫ በሦስቱም አቅጣጫዎች የተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ወደፊት ለመግፋትም ሆነ ወደኋላ ለመመለስ በማይችልበት ደረጃ በአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ደጃዝማች ተሰማ እርገጤ እና አስቻለው ደሴ ክፋለጦር ከበባ ውስጥ ይገኛል። ተጨማሪ ኃይል (ከሸዋሮቢት፣ ከሞላሌ እና ከመሐል ሜዳ)  ቢጠይቅም፣ በወገን ሀይል ከበባ ውስጥ የሚገኘትን ደፈጣዎችና ከበባዎች ለማለፋ የተቸገረው ሀይል የደገፈውና የመጣለት ኃይል እደሌለ ተረጋግጧል። የባሽ ከተማ ሙሉ በሙሉ በደጃዝማች ተሰማ እርገጤ በክፍለ ጦሩ ቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን፤ በዚህ ውጊያ ላይ የባሽ ክላስተር እና የተሬ ክላስተር አባት አርበኞች ጦር ከፍተኛ ታሪክ እየሠሩ ይገኛሉ ሁለት የጠላት ኃይልን እስከወዲያኛው እዳሰናበቱ ተረጋግጧል። በሌላ እቅጣጫ ከመዘዞ አቅጣጫ የተቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ከመዘዞ ተነስቶ በአያበር ቀበሌ በኩል ወደ መንግስት ለመሸጋገር ሲንቀሳቀስ  በአካባቢው በሚገኘው አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር ቅጽበታዊ እርምጃ ተወስዶበት ከበባ ውስጥ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት መሶቢት በተባለ ቦታ ተራራ ላይ ተሰቅሎ የሚገኝ ሲሆን፣ ተጨማሪ ደጋፊ ኃይል ቢጠይቅም የሚደርስለት በማጣቱ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ይገኛል። በተያያዘ ዜና ከአጣዬና አላላ ተነስቶ በሁለት አቅጣጫ ማለትም የአጣየው በከሰያት ወደ ደረትማ እዲሁም የአላላው በብርቂቶ ወደ ደረትማ  የተንቀሳቀሰውን ዘራፊ ጥምር ቡድን ጀግናው 7/ለ70 ክፍለጦር እዳመጣጡ እያሳደዱት ሲሆን መሸሽ ያልቻለው በየጉረኖው ተደፍቶ ቀርቷል። በዚሕም ጠላት የሞቱትን ትቶ የቆሰሉት ወደ አጣዬ ወስዶ በማሳከም ላይ ይገኛል። ክብር ለትግሉ ሠማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

+1
በታሪክ ማህደር ውስጥ እንደወርቅ ደምቆ የተጻፈ ህያው እውነት አለ፦ የአማራ ልጅ ፋኖ ወይ አይጀምርም፤ ከጀመረ ደግሞ ዓላማውን ከግብ ሳይያደርስና ሳይጨርስ በፍፁም እጁን አይሰጥም! ​ለአማራ ልጅ ፋኖ መሸነፍን ተፈጥሮ በፍፁም አትፈቅድለትም። ይልቁንም የመከራ እሳት ባበጠረው ቁጥር ይበልጥ የሚጠነክር፣ የፍትህና የነጻነት ምልክት ነው። ለዚህም ማረጋገጫው ከደባይ ጮቄ የተራራ ጫፎች የተነሱት፣ የጀግንነትና የፅናት አሻራን የታጠቁት የዳግማዊ ቴዎድሮስ ተወርዋሪ አናብስት ፋኖዎች ናቸው! ​የአባቶች ውርስና የነጻነት መንፈስ የተላበሱት ​በአፋብን በጎጃም ጠቅላይ ግዛት በጮቂ ተራራማ ጫፎች ላይ የሚነፍሰው የጠዋት ንፋስ ተራ ንፋስ አይደለም፤ የቀደሙ አባቶችን የነጻነት ወግ፣ የልዑልነት ክብርና የማይጠፋውን የታሪክ እሳት አዝሎ የሚያደርስ ህያው የመልእክት ነፋስ ነው! ይህ ንፋስ የነፃነትን ጥሪ ያበስራል፤ የህዝብን አደራና የሀገርን ክብር ያስታውሳል። ​የጦር አውድማው ውሎና ድል በእጃቸው ሁሌም የሆነው ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ፣ 206ኛ ኮር በባለፈው ባደረገው ተከታታይና የተቀናጀ ተጋድሎ ታላላቅ ወታደራዊ ድሎችን አስመዝግቧል። ​የፋኖ ኃይሎች በላቀ ወታደራዊ ስትራቴጂና በጥበብ በተመራ የማጥቃት እርምጃ፦ ​አረመኔያዊ የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ ኃይል ላይ በአማራ ህዝብ ላይ ሲበርፉ ሴት በመድፈር ድርጊቶችን ሲፈጽም የነበረውን በተዘጋጀለት ወጥመድ ውስጥ በመሳብና በማስገባት፤ ​ከቦታ ቦታ አሳዶ በመምታትና ከፍተኛ ውድመትና ምታት እንዲቀበል በማድረግ ተጠቃሽና አርአያነት ያለው ድል አስመዝግበዋል። ​"የአማራ ፋኖ የነጻነት ጉዞ አይገታም፤ ታሪክ የሰጠውን አደራ ሳይጨርስም በፍፁም ወደኋላ አይልም! Dave Amhara

በሐሰት ወሬ የማይበገር፣ በእውነት አርማ የተገነባ የነጻነት ትግል!! ​የአቢይ አህመድ ጨቋኝ ስርዓት የአማራን ልጆች ትግል ለመከፋፈል፣ ወንድምን ከወንድም ለማጣላትና የህዝቡን የጋራ ክንድ ለማዳከም ሁልጊዜ መጀመሪያ የሚመዝዘው ያረጀ “ፋኖ ሙስሊም ጠል ነው” የሚል የክህደት ካርድ ነበር። ​ነገር ግን የነጻነት ታጋዮቹ በቃላት ሳይሆን በተግባር፣ በወሬ ሳይሆን በደም የተሳሰረ እውነተኛ ወንድማማችነታቸውን አስመስክረዋል! እኛ የምንታገለው በሃይማኖትና በብሄር ልዩነት ሳይሆን በእኩልነት፣ በፍትህና በእውነተኛ አንድነት ላይ ስለሆነ እውነታውን ለዓለም አሳይተናል! ​ለዚህ ህያውና የማይንወደወድ ማረጋገጫ የሚሆነው ​ከአማራ ልጅ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ ከሰባት ለሰባ ክፍል ጦር ከታሪካዊቷ የኤፋት ምድር የተገኘው ብርቅዬውና ደፋሩ የአማራ ልጅ አርበኛ ሰይድ ደምስ (የኤፋት ኮከብ) የዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር የፋይናንስ ኃላፊ ሆኖ በከፍተኛ ኃላፊነትና በጀግንነት ተመድቦ የሚሰራው አርበኛችን ተጠቃሽ ነው። ​ይህ ታሪካዊ የማይበገር አንድነት፦ የፋኖ ትግል የሃይማኖት ልዩነት ሳይበግረው ሁሉንም የአማራ ልጅ በእኩልነት የሚያቅፍ የፍትህ አርማ መሆኑን! የጠላት ሽንፈት የገዢው ስርዓት ለዓመታት ሲያሰራጨው የነበረው የመከፋፈል ሴራ በታጋዮቹ ጽናትና እውነት አየር ላይ ቀርቶ መክሸፉን! እውነተኛ አርበኝነት አርበኛ ሰይድ ደምስ በቆራጥነቱና በታማኝነቱ ጠላት የአማራ ልጆችን ለማጣላት የሚጠቀምበትን ‘ፋኖ ሙስሊም ጠል ነው’ የሚል የሐሰት ካርድ እኛ ራሳችን በታሪክና በተግባር አክሽፈነዋል! ፋኖ የእውነት፣ የፍትህና የጋራ ድል ጋሻ ነው!” ​ ድል ለተጨቆኑ ህዝቦች! እውነቱ ይሸንፋል! ​👇 የጠላትን ሴራ ለማጋለጥና የእውነቱን ድል ለማብሰራት ይህንን መረጃ ለሁሉም ሼር (Share) ያድርጉ! 👇 #Dave #Amhara

ኅቡኡ አባት እና የአማራ ልጅ በነፃነት የመኖር የመጨረሻው ምዕራፍ!! ​የአማራ ልጅ ፋኖ በትግል ጎዳናው ላይ በሚያደርጋቸው እልህ አሥጨራሽ እንቅስቃሴዎች ውስጥ እጅግ ብዙ አጋጣሚዎችንና ገጠመኞችን ያስተናግዳል። ከተራሮች ግርጌ እስከ ሸለቆቹ ጥግ ድረስ በየመንደሩ የሚኖሩ ጀግኖችና ባለታሪኮች ታሪካቸውን ደብቀው ይኖራሉ። ​በአንድ አጋጣሚ፣ ከተገለለችና ትንሽ ከሆነች የገጠር መንደር ውስጥ ከሚኖሩ አንድ አረጋዊ አባት ጋር ተገናኘን። የእነዚህ አባት እውቀትና ጥበብ ከመንደሯ ወሰን ያለፈ፣ ከእድሜያቸውም በላይ የሆነ እጅግ ማያልቅ ጥልቅ አእምሮ ነበር። አባታችን ስለ ታሪካችን ጥልቀትና ስለ ሕዝባችን ማንነት ሲተርኩ መንፈስን ያንቀጠቅጣሉ። ​ድምፃቸውን ከፍ አድርገው በቁጭት እንዲህ አሉ፦ ​ ስርዓቱ እኮ የሚጠላንና የሚያሳድደን በምክንያት ነው! የድሮ አባቶቻችንን ውበትና ግርማ ሞገስ ጠብቀን እንዳንኖር፣ ታሪካዊ ጀግንነታቸውንና ያቆዩልንን ቅርስ እንዳንጠብቅ በየመንገዱ እንቅፋት የሚደቅኑብን የማንነታችን ጥንካሬ ስለሚያስፈራቸው ነው። ​በእውነትም፣ ዛሬ የአማራ ልጅ ፋኖ የአባቶቹን ታሪክ፣ ክብርና ወግ ጠብቆ የአማራን ሕዝብ አንገቱን ቀና የሚያደርግበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ይህ ትግል የህልውና ብቻ ሳይሆን የክብርና የታሪክ መመለስ ምዕራፍ ነው። ​ከእድሜያቸው በላይ በሆነው እውቀታቸው የመንገዳችን ብርሃን ለሆኑት ለእነዚህ አባታችን ምስጋናችን ወሰን የለውም። አባታችን ክበሩልን! አምላክ እድሜና ጤና ይስጥልን! Dave Amhara

አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነዉ ኮር  በአገዛዙ ወታደር ላይ የማያዳግም እርምጃ በመዉሰድ ድልን ተቀዳጁ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አፋብን ወሎ ቤተ -አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል የሆነው 14ኛ (ጀኔራል ሃይሉ ከበደ) ክፍለ ጦር በዋግህምራ ዞን ጋዝጊብላ ወረዳ  09 ቀበሌ ላልኪው የ አፓርታይዱ አብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ  ወታደር ላይ በተሰላና በታቀደ የተጠናከረ ሽምቅ ውጊያ እና ተስቦ በመግባት ከተኛበት ምሽግ ላይ የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅተዋል። የሽምቅ ውጊው ሐምሌ 23ለ24  ሃሙስ ለአርብ  ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት እስከ ንጋት 11:00 ሰዓት የተጠናከረ ሲሆን ልዩ ቦታው ገበያው ሰፈር ወይም በተለምዶ ጊወርጊስ ትኩ ተብሎ ከሚጠራው ተራራ ላይ መሽጎ የነበረውን የጥላት ሃይል በሽምቅ ከማጥቃት ሙሉ በሙሉ ምሽጉን በማስለቀቅ በአገዛዙ ላይ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰውበታል ። በተጠናከረው የሽምቅ ውጊያ ከ17በላይ የጥላት ሃይል ሲደመሰስ 4 ምርኮኛ፣9ጥቁር ክላሽ ፣1500 የብሬን ተተኳሽ፣725 የክላሽ ተተኴሽ ፣2 ኤፍዋን የእጅ ቦንብ ፣አንድ የወገብና አንድ የደረት ትጥቅ ተማርኳል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ! ሐምሌ 24/11/2018 ዓ'ም

አሳዛኝ ዜና የአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት በፈረስ ቤት ከተማ ተቃጠለ። ሐምሌ/ 24/2018 ዓ.ም የአማራ ህዝብን በመጨፍጨፍ፣ ሀብትና ንብረቱን ማውደም የዘወትር መገለጫው የሆነውና ተስፋ የቆረጠው የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት፣ የአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ወላጆችን መኖሪያ ቤት በፈረስ ቤት ከተማ ማቃጠሉ ታውቋል። በራሱ ህዝብ ላይ ታንክ፣መድፍና አየር ኃይል አሰማርቶ ንፁሃንን የሚጨፈጭፈው፣ የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ፣ መሀመድ ተሰማ ለምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ እድሚያለም ለሚባል ቅጥረኛ ግለሰብ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መኖሪያ ቤቱ መቃጠሉን ከመረጃ ምንጮቻችን ለማወቅ ተችሏል። በቃጠሎው የደጋ ዳሞት ወረዳ፣ የአገዛዙ ቅጥረኛ ካድሬዎችና የሚሊሻ አባላት እንደተሳተፉ የዓይን እማኞች ገልጸዋል። በቤቱ ውስጥ ይገኙ የነበሩ ቁሳቁሶችን ጨምሮ ሌሎች ጠቃሚ ንብረቶች በእሳቱ መውደማቸው ታውቋል። በፈረስ ቤት ከተማ፣ ቀበሌ 02 ይገኝ የነበረው ይህ መኖሪያ ቤት፣ የአርበኛው ወላጆች ኑሯቸውን መስርተው፣ማኀበራዊ ህይዎታቸውን ይመሩበት እንደነበረ ተገልጿል። ላለፉት 3 አመታት በተለያዩ የአማራ ቀጠናዎች ከፋኖ ጋራ ፊት ለፊት ተዋግቶ ማሸንፍ ያልቻለው አገዛዙ፣ የበቀል ዱላውን የሚያሳርፈው ንጹሃን ዜጎችን በመገድልና ሀብት ንብረታቸውን በማውደም እንደሆነ ይታወቃል። በአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ወላጆች ቤት የደረሰው ቃጠሎ የዚህ አንድ አካል ነው። ከውጊያ ቀጠና ውጭ የሚገኙ የሰላማዊ ዜጎችን ሀብትና ንብረት ማውደም፣ በዓለም አቀፉ የጄኔቫ የጦር ስምምነት( Geneva War Convention) መሰረት በጦር ወንጀልነት ሊያስጠይቅ የሚችል መሆኑንን በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የህግ ባለሙያዎች ገልጸዋል። ቃጠሎውን አስመልክቶ፣ ፈረስ ቤት ከተማን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች በስልክና በአካል ያነጋገርናቸው ሰላማዊ ዘጌጎች ድርጊቱን በጥብቅ አውግዘውታል። አንድ አገር እመራለሁ ከሚል አካል ፍፁም የማይጠበቅ "ወራዳ ተግባር" ሲሉ ኮንነው፣ አገዛዙ ምን ያህል የመንግስትነት ቁመናው እንዳጣና ተስፋ እንደቆረጠ ማሳያ ነው ሲሉ ጨምረው ገልጸዋል። አገዛዙ በጎንደር፣ በወሎ፣ በሸዋና በጎጃም ላለፉት 3 ዓመታት የተለያዩ የፋኖ ቤተሰቦችን ሀብት ንብረት ሲያወድሙ እንደቆዩ ይታወቃል። ምስል- የአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ወላጆች መኖሪያ ቤት ከመቃጠሉ ጥቂት ቀደም ብሎ። ምስሉ የደረሰን ከመረጃ ምንጮቻችን ሲሆን ጣራውን፣ በሩንና መስኮቱን በመነቃቀል ለቃጠሎ ካዘጋጁት በኋላ ነው። የተቀረው ምስል- አርበኛ ዝናቡ ልንገረው ከወላጅ አባቱና ከወንድሞቹ ጋራ ።

ማንኛውም ግዳጅ ለመፈፀም ዝግጁ መሆናቸውን የ24ኛ ክ/ጦር ደባይ ጮቄ ሻለቃ አስታወቀ። ሐምሌ23/2018 ዓ.ም ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ለአለፉት ሦስት አመታት በተደረገው ህዝባዊ ተጋድሎ አኩሪ ድል በማስመዝገብ ደማቅ ታሪክ የጻፈው የጮቄው ማማ ደባይ ጮቄ ሻለቃ የሦስት አመት የድል ግስጋሴውን በዛሬው ዕለት በደማቅ ሁኔታ አክብሯል። በደብረ ማርቆስ፣ቁይ፣ ሉማሜ፣ ደብረወርቅ ፣ቢቸና፣ ውሃበር፣ ሰዴ፣ መካነሰላም ፣የቦቅላ በተደረጉ ጠንካራ ውጊያዎች ተሳታፊ በመሆን ጀብድ የፈፀመው የ206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ደባይ ጮቄ ሻለቃ የአለፉ ድሎችን በማስጠበቅ የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ቴዎድሮስ ዕዝ በመልሶ ማደረጃት አዲስ አመራር ማዋቀሩ እንዳስደሰታቸው የተናገሩት የሻለቃ አመራሮችና የሰራዊት አባለት ህግና ስነ-ስርዓትን በማስቀደም ከድርጅታቸው ጎን እንደሚሰለፉ ገልጸዋል የአፋብን አመራሮች፣ የኮርና የክ/ጦር አመራሮች በተገኙበት የሦስት አመት የድል በዓል በድምቀት የተከበረ ሲሆን የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ መርሃግብሩ ተጠናቋል። አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት