ru
Feedback
BBC Amharic | ቢቢሲ አማርኛ

BBC Amharic | ቢቢሲ አማርኛ

Открыть в Telegram

BBC AMHARIC UNOFFICIAL, RSS FEEDS ONLY

Больше
2 073
Подписчики
-124 часа
-217 дней
-8930 дней

Загрузка данных...

Похожие каналы
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
сентябрь '26
сентябрь '26
+4
в 0 каналах
август '26
+15
в 0 каналах
Get PRO
июль '26
+7
в 0 каналах
Get PRO
июнь '26
+5
в 0 каналах
Get PRO
май '26
+2
в 0 каналах
Get PRO
апрель '26
+4
в 0 каналах
Get PRO
март '26
+8
в 0 каналах
Get PRO
февраль '26
+4
в 0 каналах
Get PRO
январь '26
+29
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '25
+79
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+447
в 2 каналах
Get PRO
октябрь '25
+182
в 1 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+133
в 2 каналах
Get PRO
август '25
+231
в 0 каналах
Get PRO
июль '25
+241
в 2 каналах
Get PRO
июнь '25
+300
в 0 каналах
Get PRO
май '25
+780
в 1 каналах
Get PRO
апрель '25
+1 874
в 1 каналах
Get PRO
март '250
в 0 каналах
Get PRO
февраль '250
в 0 каналах
Get PRO
январь '250
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '240
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '240
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '240
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '240
в 0 каналах
Get PRO
август '24
+655
в 0 каналах
Get PRO
июль '240
в 0 каналах
Get PRO
июнь '240
в 0 каналах
Get PRO
май '240
в 0 каналах
Get PRO
апрель '240
в 0 каналах
Get PRO
март '240
в 0 каналах
Get PRO
февраль '240
в 0 каналах
Get PRO
январь '240
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '230
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+349
в 0 каналах
Дата
Привлечение подписчиков
Упоминания
Каналы
13 сентября0
12 сентября0
11 сентября0
10 сентября0
09 сентября0
08 сентября+1
07 сентября0
06 сентября+1
05 сентября0
04 сентября+1
03 сентября+1
02 сентября0
01 сентября0
Посты канала
ለቀድሞ ፍቅረኛው ያበረከታቸውን ስጦታዎች በገንዘብ አስልቶ እንዲመለስለት ክስ ያቀረበው ግለሰብ ጥያቄው ውድቅ ሆነ አንድ ሲንጋፖራዊ ለቀድሞ ፍቅረኛው ለስጦታ እና ለተለያዩ ነገሮች ያወጣውን በመቶ ሺህዎች የሚቆጠር ዶላር ከተለያዩ በኋላ ለማስመለስ ያቀረበው ክስ በፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገበት። ቻንደር አጋርዋል የቀድሞ ፍቅረኛው ፌሊሺያ ሊ አብረው በነበሩ ጊዜ ያወጣውን 468,000 የሲንጋፖር ዶላር ወይም ወደ 370 ሺህ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ለማስመለስ በፍርድ ቤት ክስ መሥርቶ ሲከራከር ቆይቶ ነበር። ነገር ግን ጉዳዩን የተመለከተው የሲንጋፖር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሳሽ ገንዘቡን ለቀድሞ ፍቅረኛው ያወጣው ወዶ ፈቅዶ በመሆኑ እንድትመልስለት ፍቅረኛውን እንደማያስገድድ ወስኗል። የፍርድ ቤቱ ዳኛ ሊ ሴዩ ኪን እንደገለጹት፣ አጋርዋል ከሊ ጋር ፍቅር ከመጀመሩ በፊትም ቢሆን ውድ ስጦታዎችን በተደጋጋሚ ይሰጣት ነበር፣ እናም ገንዘቡ እንድትመልስለት እንደማይጠብቅ ያረጋግጥላት ነበር። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA

2
ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ነጋዴዎችን ጨምሮ በርካቶችን ያሰጋው የኬንያ ፕሬዝዳንት ትዕዛዝ ንዲኬች አሊ በኬንያ መዲና ናይሮቢ የባጃጅ ሹፌር ነው። ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ዋነኛ ችግር የሆነበት የናይሮቢ የትራፊክ መጨናነቅ ነው። መጤ ጠልነት ይገጥመኛል ብሎ ግን አላሰበም። ቡሩንዲያዊው ንዲኬች ኬንያውያን እንግዳ ተቀባይ እንደሆኑ ይናገራል፤ በቀላሉ ጓደኛ ለማድረግም ይመቻሉ ይላል። ባለፈው ሳምንት ግን ሁሉም ነገር ተለወጠ። ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ ከውጭ አገራት ወደ ኬንያ የገቡ ጥቃቅን እና አነስተኛ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ትዕዛዝ ሰጡ። "አሁን ተነስተውብናል" ይላል ንዲኬች። ወደ አገራቸው ለመመለስ የሚያስፈልጋቸውን ሰነድ ከሚጠባበቁ አንዱ ነው። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
14
3
ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ነጋዴዎችን ጨምሮ በርካቶችን ያሰጋው የኬንያ ፕሬዝዳንት ትዕዛዝ ንዲኬች አሊ በኬንያ መዲና ናይሮቢ የባጃጅ ሹፌር ነው። ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ዋነኛ ችግር የሆነበት የናይሮቢ የትራፊክ መጨናነቅ ነው። መጤ ጠልነት ይገጥመኛል ብሎ ግን አላሰበም። ቡሩንዲያዊው ንዲኬች ኬንያውያን እንግዳ ተቀባይ እንደሆኑ ይናገራል፤ በቀላሉ ጓደኛ ለማድረግም ይመቻሉ ይላል። ባለፈው ሳምንት ግን ሁሉም ነገር ተለወጠ። ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ ከውጭ አገራት ወደ ኬንያ የገቡ ጥቃቅን እና አነስተኛ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ትዕዛዝ ሰጡ። "አሁን ተነስተውብናል" ይላል ንዲኬች። ወደ አገራቸው ለመመለስ የሚያስፈልጋቸውን ሰነድ ከሚጠባበቁ አንዱ ነው። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
8
4
የሰው ሠራሽ አስተውሎት እድገት ፍጥነት በሰው ልጅ ላይ የፈጠረው ስጋት ቁጥጥር እንዲደረግበት ጥያቄ አስነሳ የዓለማችን ሦስት ዋነኛ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ተቋማት መሪዎች ኤአይ በሰው ልጅ ደኅንነት ላይ አደጋ ሊያስከትል ይችላል በሚለው ስጋት ምክንያት ዘርፉ እየተጓዘ ያለበት ፍጥነት መቀነስ አለበት ሲሉ አሳሰቡ። አንትሮፒከል የተባለው የሰው ሠራሽ አስተውሎት ተቋም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዳሪዮ አሞዴይ የቴክኖሎጂው እድገት ፍጥነቱ እየጨመረ ከቀጠለ፣ ከቁጥጥር ውጭ የሚሆኑ የኤአይ ሞዴሎች በይነ መረቡን ሊቆጣጠሩ ይችላሉ ሲሉ አስጠንቅቀዋል። የዓለማችን ቁጥር አንድ ባለሃብት እና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ባለቤት ኢላን መስክ እና የኦፕንኤአይ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳም አልትማም ሰው ሠራሽ አስተውሎት ደቅኖታል በተባለው የስጋት ግምገማ እንደሚስማሙ ተናግረዋል። ከቀናት በፊት ከአንትሮፒክ ሥራውን የለቀቀው ተመራማሪ ጄኮብ ኮክሰን ለቢቢሲ በሰጠው ልዩ ቃለ ምልልስ፣ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (ኤአይ) ልማት ፍጥነት ካልቀነሰ "ሁላችንም በቅርብ ጊዜ ልንጠፋ እንችላለን" የሚል ስጋቱን ከገለጸ በኋላ ጉዳዩ ትኩረት አግኝቷል። አሁን ደግሞ የቀድሞ አለቃው እና የአንትሮፒክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዳሪዮ አሞዴይ፣ ከኤአይ ጋር የተያያዙ አደጋዎች ከባድ በመሆናቸው እና ኩባንያዎችም ሆኑ መንግሥታት እነዚህን አደጋዎች ለመፍታት ጊዜ እንዲያገኙ፣ የኤአይ ሞዴሎች የልማት ፍጥነት "እንዲቆም ወይም እንዲዘገይ" ጥሪ አቅርበዋል። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
11
5
በኢንተርኔት ግንኙነት እናቱን ያጭበረበረውን ናይጄሪያዊ ፍለጋ አህጉራትን ያቋረጠው ስፔናዊ "ውስብስ መንገድ የሚጠቀሙ ሆነው አላገኘኋቸውም። ብልህም አልነበሩም እጅግ ያስገረመኝም እርሱ ነው" ይላል ካርሎስ ባራጋን። ካርሎስ አፍቃሪ ሰው መስሎ እናቱን ያጭበረበረውን ግለሰብ ለማግኘት ወደ ናይጄሪያ ሲጓዝ፣ የተካነ አጭበርባሪ ሰው እንደሚያገኝ ጠብቆ ነበር። በሶሪያ ከሚገኝ አሜሪካዊ ወታደር እንደሆነ የገለጸው ግለሰብ በላካቸው ኢሜይሎች ላይ ያለው የበይነ መረብ (አይፒ) አድራሻ የሚያሳየው ናይጄሪያ ውስጥ እንዳለ ነበር። ካርሎስ ወደ ናይጄሪያ ከሄደ በኋላ ግን ወንጀለኛውን የማጋለጥ ዕቅዱን ትቶታል። ይልቁንም ለአራት ዓመታት ያህል 'ናሁ ቦይስ' ተብለው የሚታወቁትን የናይጄሪያ ወጣት አጭበርባሪዎች ማጥናት ተያያዘ። ከእነዚህ ወጣቶች ውስጥ አብዛኞቹ በትምህርታቸው ያልገፉ፣ ገንዘብ የሌላቸው እና ዕድል ያልተመቻቸላቸው ናቸው። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
9
6
በየመን በሚካሄደው ውጊያ ምክንያት በ24 ሰዓት ውስጥ 1,400 ሰዎች ጂቡቲ ገቡ በየመን ውስጥ እየተስፋፋ ያለውን ውጊያ በመሸሽ በርካታ ሰዎች ቀይ ባሕርን በመሻገር ወደ ጂቡቲ መግባታቸውን የአገሪቱ ኢኮኖሚ እና ፋይናንስ ሚኒስትር አስታወቁ። በየመን መንግሥት ኃይሎች እና በኢራን በሚደገፉት የሁቲ ታጣቂዎች መካከል እየተካሄደ ባለው ውጊያ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 1,400 ያህል ሰዎች ከየመን ወደ ጅቡቲ መሰደዳቸውን ሚኒስትሩ ኢሊያስ ሙሳ ዳዋሌ ገልጸዋል። የሁቲ ታጣቂዎች ባለፉት ቀናት በቀይ ባሕር ዳርቻ ያሉ የየመን ግዛቶችን እየተቆጣጠሩ ባሉበት ወቅት ጦርነቱ በመንግሥት ቁጥጥር ስር ወደሚገኙ አካባቢዎች እየተስፋፋ ነው። የጂቡቲ ኢኮኖሚ እና ፋይናንስ ሚኒስትር ኢሊያስ ሙሳ ዳዋሌ በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ እንደጻፉት፣ ጦርነቱን የሸሹት 1,400 ሰዎች የባብ ኤል መንደብ ወሽመጥን በማቋረጥ ነው ወደ ጂቡቲ የገቡት። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
11
7
ከመስከረም 1 ጥቃት ከዓመታት በፊት ሲአይኤ 'ስለ ሚፈነዱ አውሮፕላኖች' ማስጠንቀቂያ ደርሶት እንደነበር ተገለጸ የመስከረም 1 ጥቃት ከመፈጸሙ ከሦስት ዓመታት በፊት የአሜሪካ የደኅንነት ተቋም ባለሥልጣናት "አል-ቃኢዳ ተቀጣጣይ አውሮፕላን ወደ ከተማዋ ሊያበርር የሚችልበት ዕድል እንዳለ" መወያየታቸውን አዲስ ሰነድ አሳየ። ከዚህ ቀደም ምሥጢራዊ የነበረው ሰነድ አሁን ለሕዝብ ይፋ የሆነው ከሽብር ጥቃቱ 25ኛ ዓመት መታሰቢያ ጋር በተያያዘ ነው። የአሜሪካ የደኅንነት ተቋም (ሲአይኤ) 71 ገጽ ፕሬዝዳንታዊ ሰነዶችን ይፋ አድርጓል። እነዚህም ከአውሮፓውያኑ 1998 ጀምሮ ጥቃቱ ከደረሰበት ቀን በኋላ እስካለው ጊዜ የተሰበሰቡ ናቸው። በአውሮፓውያኑ መስከረም 122001 የተመዘገበ አንድ ሰነድ እንደሚያሳየው በአክራሪ ቡድኖች ዘንድ ጥቃት የመጸም ሴራ መኖሩ "በስፋት የሚታወቅ" ነበር። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
25
8
የኖርዌይ ልዕልት በወንድማቸው የአገሪቱ ንጉሥ ቀብር ላይ ከተገኙ ከሁለት ቀናት በኋላ አረፉ የኖርዌይ ልዕልት አስትሪድ የአገሪቱ ንጉሥ በሆኑት በወንድማቸው ንጉሥ ሃራልድ አምስተኛ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ከተሳተፉ ከሁለት ቀናት በኋላ መሞታቸውን የኖርዌይ ንጉሣዊ ቤተ መንግሥት አስታወቀ። ልዕልቲቱ በ94 ዓመት ዕድሜያቸው ያረፉት ታናሽ ወንድማቸው ንጉሥ ሃራልድ አምስተኛ ካረፉ ከሳምንት እንዲሁም ቀብራቸው ከተፈጸመ ከሁለት ቀናት በኋላ ነው። አዲሱ የኖርዌይ ንጉሥ ሃኮን ስምንተኛ የልዕልቱቱን ኅልፈት ተከትሎ "ልዕልት አስትሪድ በረጅም ዘመናቸው ሁሉ ንጉሣዊ ቤተሰቡን በቀናነት እና በታማኝነት ወክለዋል" ብለዋል። ንጉሥ ሃራልድ ባለፈው ነሐሴ ወር በ89 ዓመታቸው ከ35 ዓመታት በላይ በንግሥና ከቆዩ በኋላ ነበር ያረፉት። ልዕልቲቱ በመጨራሻ ለሕዝብ የታዩት በወንድማቸው የቀብር ሥነ ሥርዓት ወቅት ነበር። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
27
9
ለፍቅር ግንኙነት የተዋወቋቸውን ሰዎች በሚሊዮኖች ያጭበረበሩ ናይጄሪያውያን ለአሜሪካ ተላልፈው ተሰጡ የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ በአሜሪካ ያሉ ሴቶችን በኢንተርኔት አማካይነት ቀርቦ የፍቅር ግንኙነት በመጀመር የማጭበርበር ወንጀሎችን በመፈጸም የሚፈለጉ ስድስት ናይጄሪያውያንን ለኤፍቢአይ አሳልፎ ሰጠ። የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት እንዳሉት፣ ናይጄሪያውያኑ በአሜሪካ ውስጥ ከ100 በላይ ሴቶችን በማጭበርበር ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ በመዝረፍ ይከሰሳሉ። ለአሜሪካ ተላልፈው የተሰጡት ግለሰቦች በ2021 ታስረው ነበር፤ እንዲሁም "ብላክ አክስ" የተባለ ከሰዎች ዝውውር፣ ከበይነ መረብ ማጭበርበር እና ከግድያ ጋር የተያያዘ የናይጄሪያ የማፍያ ዓይነት የወንጀል ቡድን አባላት እንደሆኑ ይታመናል። ገንዘባቸውን ከተጭበረበሩት መካከል ጡረተኞች እና ነጋዴዎች እንዳሉበት ተገልጿል። እነዚህ ሰዎች "ገንዘባቸውን ለመውሰድ የተራቀቁ የኢንተርኔት ግንኙነቶችን በመጠቀም ዒላማ ተደርገው ነበር" ሲል የደቡብ አፍሪካ ልዩ የፖሊስ ኃይል ገልጿል። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
29
10
ሳዑዲ አረቢያ በተፈጸመባት የድሮን ጥቃት ወሳኝ የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧዋን ዘጋች ሳዑዲ አረቢያ በተፈጸመባት የድሮን ጥቃት ወሳኝ የሆነው የዘይት ማስተለላፊያ ቧንቧዋ ከተመታ በኋላ እንዲዘጋ አድርጋለች፤ ይህም በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው ግጭት እየሰፋ መሄዱን ያሳያል እየተባለ ነው። ይህ ጥቃት ከኢራን ድንበር አጠገብ ከሚገኝ ግዛቷ እንደተፈጸመ ኢራን አረጋግጣ፣ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ወታደራዊ አዛዥ ከኃላፊነት ተነስቶ ምርመራ እንደተጀመረ አስታውቃለች። 1,200 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይህ የነዳጅ ማስተለላፊያ ቧንቧ፣ በዓለም ትልቋ ድፍድፍ ነዳጅ ላኪ የሆነችው ሳዑዲ አረቢያ፣ የሆርሙዝ ወሽመጥ ከተዘጋ በኋላ ምርቷን ለገበያ ለማቅረብ አማራጭ ሆኗት ነበር። ይህ ክስተት፣ በኢራን የሚደገፉት የየመን ሁቲ አማጺያን ወሳኝ ድል በማግኘት የቀይ ባሕር ዳርቻዎችን በተቆጣጠሩበት ወቅት የተከሰተ ሲሆን፣ የአሜሪካ እና ኢራን ጦርነት ወደ ሰባተኛ ወሩ በገባበት በአሁኑ ጊዜ በዓለም የነዳጅ ዝውውርን አስተጓጉሏል። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
25
11
በምዕራብ ወለጋ ስለተቃጠሉት ነዳጅ ጫኝ ተሽከርካሪዎች ቢቢሲ በሳተላይት ምሥሎች ያደረገው ማጣራት ምን ያሳያል በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን፣ ጊምቢ ከተማ አቅራቢያ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት ከዘጠኝ ያላነሱ ነዳጅ ጫኝ ከባድ ተሽከርካሪዎች ሙሉ በሙሉ እና በከፊል መቃጠላቸውን ቢቢሲ ከምንጮች እና ከሳተላይት ምሥል አረጋገጠ። ታጣቂዎች ባለፈው እሑድ ጳጉሜ 12018 ዓ.ም. በደፈጣ እንደፈፀሙት በተገለፀው በዚህ ጥቃት፣ ከስምነት ያላነሱ ሾፌሮች ታግተው መወሰዳቸውን የኢትዯጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኅበር ገልጿል። ቢቢሲ የተመለከታቸው ተንቀሳቃሽ ምሥሎች በርካታ የተቃጠሉ ተሽከርካሪዎችን የሚያሳዩ ሲሆን ከሳተላይት መረጃዎች ጋር በማናበብ በሠራው ትንታኔ በእርግጥም ጥቃቱ በዚያ አካባባቢ በተጠቀሰው ቀን ስለመፈጸሙ አመላካች መረጃዎችን አግኝቷል። የተቃጠሉ ነዳጅ ጫኝ ከባድ ተሽከርካሪዎችን የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምሥሎች (ቪዲዮዎች) በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት ተዘዋውረዋል። ተሽከርካሪዎቹ ነዳጅ ጭነው ከጊምቢ በነጆ አድርገው ወደ አሶሳ በማቅናት ላይ እንደነበሩ የአካባቢው ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
27
12
የዓለምን ገጽታ የቀየረው የመስከረም 1 ጥቃት 25ኛ ዓመት እና የስለላው ዘርፍ ያጋጠመው ውድቅት ለብዙ አስርተ ዓመታት የተለያዩ መሪዎች እንደተናገሩት፣ የማንኛውም መንግሥት የመጀመሪያ ግዴታ ሕዝቡን መጠበቅ ነው። በአውሮፓውያኑ 2001 መስከረም 11 ቀን ግን አሜሪካ ይህንን ግዴታ ለመወጣት ሳትችል ቀርታለች። የስለላ መረጃዎች ቢኖሩም፣ የተለያዩ ፍንጮችን በጊዜው አገናኝቶ ተግባራዊ እርምጃ የወሰደ አልነበረም። በኋላ "911" ተብለው የታወቁት በአሜሪካ ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶች እና ለእነሱ የተሰጠው ምላሽ፣ በዚህ ክፍለ ዘመን የመጀመሪያዎቹን ሁለት አስርተ ዓመታት የውጭ ጉዳይ፣ የደኅንነት እና የስለላ ፖሊሲዎችን በእጅጉ የቀረጹ ክስተቶች ሆነዋል። በ2001 መስከረም 11፣ አጥፍቶ ለመጥፋት የተዘጋጁ የአልቃኢዳ አብራሪዎች የተጠለፏቸው አውሮፕላኖችን ዓለም ንግድ ማዕከል ሰማይ ጠቀስ ሕንጻዎች ጋር በማጋጨት ጥቃቱን ከጀመሩ በኋላ በዚያ ቀን 2,977 ሰዎች ተገድለዋል። እነዚህ ጥቃቶች ከየትም ተነስተው የመጡ አልነበሩም። የአሜሪካ ማዕከላዊ የስለላ ድርጅት (ሲአይኤ) ከ2001 በፊት ለብዙ ዓመታት ስለ አልቃኢዳ እና በስደት ስለሚኖረው ሳዑዲያዊ መሪው ኦሳማ ቢን ላደን መረጃ ነበረው። እንዲያውም እሱን ለመያዝ ተመድቦ የሚሠራ ልዩ ቡድን ነበረው። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
46
13
በዲሞክራቲክ ኮንጎ ትምህርት ቤት ውስጥ በተከሰተ የእሳት አደጋ ከ20 በላይ ልጆች ሞቱ በምሥራቃዊው የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በአማጺያን ቁጥጥር ሥር ባለችው ቡካቩ ከተማ ውስጥ ሁለት ትምህርት ቤቶች ላይ የእሳት አደጋ ከተነሳ በኋላ ከእሳቱ ለማምለጥ በተፈጠረ መረጋገጥ ቢያንስ 24 ተማሪዎች መሞታቸውን ባለሥልጣናት ገለጹ። በተከሰተው የእሳት አደጋ ምክንያት ከተማሪ ልጆች በተጨማሪ አዋቂዎችም ሕይወታቸውን ማጣታቸው የተመዘገበ ሲሆን የሟቾች ቁጥርም ሊጨምር እንደሚችልም ስጋት አለ። ከአደጋው የተረፉ ሰዎች በአቅራቢያ ወደ ሚገኙ ሆስፒታሎች ተወስደዋል፤ ከቦታው የተቀረጹ ምሥሎችም ጉዳት የደረሰባቸው ልጆች እየተሰቃዩ በሆስፒታል ወለል ላይ ተኝተው ያሳያሉ። በእሳቱ ምክንያት 300 ያህል ቤቶችም ወድመዋል፤ የእሳቱ መንስኤ ግን እስካሁን አልታወቀም። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
43
14
የየመን ሁቲ ታጣቂዎች ወሳኝ የቀይ ባሕር ወደብ የሆነችውን ሞካን መቆጣጠራቸው ተዘገበ የየመን ሁቲዎች፣ በሳዑዲ የሚደገፉ የመንግሥት ኃይሎችን በመርታት ስትራቴጂያዊ የሆነችውን በቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የምትገኘውን ሞካ የወደብ ከተማን መያዛቸውን ወታደራዊ ምንጮች እና የዐይን እማኞች ገለፁ። በኢራን የሚደገፈው ቡድን ሞካን መያዙን ተከትሎ፣ ከባብ ኤል መንደብ ወሽመጥ ያለው ርቀት 75 ኪሎ ሜትር ብቻ ሆኗል። ይህ ወሽመጥ እስያን እና አውሮፓን የሚያገናኝ እንዲሁም በቀይ ባሕር በኩል ለሚደረጉ የመርከብ ጉዞዎች ቁልፍ የሆነ የንግድ መስመር ነው። ነገር ግን ሁቲዎቹ በዓለም አቀፍ የመርከብ እንቅስቃሴ ላይ ምንም ስጋት እንደማይፈጥሩ ገልጸዋል። ሆኖም ከሳዑዲ አረቢያ የሚመጡ መርከቦችን ዒላማ እንደሚያደርጉ በድጋሚ ዝተዋል። ሳዑዲ አረቢያ የአሜሪካ እና የእስራኤል ጦርነት በባሕረ ሰላጤው የሚገኘው የሆርሙዝ ወሽመጥን በአብዛኛው ከተዘጋ በኋላ የነዳጅ ምርቶቿን ለመላክ በቀይ ባሕር ላይ ጥገኛ ሆናለች። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
42
15
ከ600 በላይ እስረኞች በይቅርታ ሲለቀቁ 28 ይቅርታ ባለመጠየቃቸው ሳይፈቱ ቀሩ ከአማራ እና ከኦሮሚያ ክልሎች በከባድ ወንጀሎች ተከስሰው በፌደራል መንግሥቱ በእስር ላይ ይገኙ የነበሩ ከስድስት መቶ በላይ ሰዎች በይቅርታ መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። በተመሳሳይ ክስ ለዓመታት በእስር ላይ የቆዩ ነገር ግን ይቅርታ ለመጠየቅ ፈቃደኛ ያልሆኑ 28 እስረኞች ደግሞ ሳይፈቱ ቀርተዋል። በ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት ዋዜማ ጳጉሜ 52018 ዓ.ም. ከእስር መፈታታቸው የተነገረው በመቶዎች የሚቆጠሩ ታሳሪዎች ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው በይቅርታ፣ ክሳቸው በሂደት ላይ የነበረው ደግሞ እንዲቋረጥ ተደርጎ መሆኑን ኮሚሽኑ አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም ለአዲሱ ዓመት ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ላይ ልዩ ልዩ ወገኖች "በአንድም ሆነ በሌላ ስህተት የታሠሩ ወገኖች በይቅርታ እና በሕግ አግባብ እንዲፈቱ" መጠየቃቸውን እና መንግሥትም ተቀብሎ "በሂደቱ የተስማሙትን ፈትቷል" ብለዋል። ኢሰመኮ እንዳለው የተለቀቁት ሰዎች ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ በሽብር እና በሌሎች ከባድ ወንጀሎች ተከሰው ፍርድ ቤት ውሳኔ የሰጠባቸው እንዲሁም በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው በፍርድ ሂደት ላይ የሚገኙ ነበሩ። ታሳሪዎቹ "ጉዳያቸው በልዩ ሁኔታ እንዲታይ. . . በኮሚሽኑ በኩል ለመንግሥት እንዲቀርብላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ" በማድረግ ኢሰመኮ ታሳሪዎቹ በሕግ ሂደት ይቅርታ እንዲገያኙ ጉዳዩን ለመንግሥት አቅርቦ ምላሽ ማግኘቱን ገልጿል። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
41
16
ኮሚሽኑ ትግራይን የሚመለከቱ አጀንዳዎችን የሚያቀርበው ለፌዴራል መንግሥቱ መሆኑን ገለፀ ከአራት ዓመታት በላይ ወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮችን በማሰባሰብ ከአንድ ወር በላይ ምክክር ያደረገው ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ውጤቱን ለሚመለከታቸው አካላት እንዲሁም ትግራይን የሚመለከቱ አጀንዳዎችን ለፌደራል መንግሥቱ እንደሚያርብ አስታወቀ። በዚህም አራት ሺህ የሚሆኑ ተመካካሪዎች የተሳተፉበትን ኮሚሽኑ የሀገራዊ ምክክር ውጤት የሆነውን የመጨረሻውን ምክረ-ሃሳብ ከመስከረም 10 በፊት ለመንግሥት እንደሚያቀርብ አመልክቷል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ በምክክሩ የቀረቡ ምክረ-ሃሳቦችን ለተግባሪ የፌዴራል መንግሥት አካላት ከመስከረም 10 በፊት ለማቅረብ ምክረ-ሃሳቦቹን እያደራጀ መሆኑን ይፋ አድርጓል። በተጨማሪም በክልሎች እና በከተማ አስተዳደሮች ውስጥ ለሚደረጉ ምክክሮች የሚረዱ አጀንዳዎችን፣ እንዲሁም እነዚህ አካላት ሊፈፅሟቸው የሚገቡ የሕዝብ ጥያቄዎችንም በዚሁ ጊዜ ውስጥ ለማስረከብ እየሠራ መሆኑን ገልጿል። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
39
17
ከ325 ሺህ ብር በላይ የሚያስወጣው አዲሱ የአይፎን ስልክ ምን ይዟል አፕል አይፎን ስልኮችን ለገበያ ካቀረበ ከ20 ዓመታት በኋላ በስልኩ ላይ የተደረገውን ትልቁን ለውጥ ይፋ አድርጓል። ረቡዕ ዕለት በኩባንያው ዓመታዊ የምርት ማስተዋወቂያ ዝግጅት ላይ የመጀመሪያውን ታጣፊ የአይፎን ስልክን ማቅረቡን አስታወቋል። እንደ መጽሐፍ በሚታጠፍ ቅርጽ የተዘጋጀው አዲሱ አይፎን "ዱዎ" ተብሎ የተሰየመ ሲሆን፣ እስካሁን ከተመረቱት አይፎኖች ሁሉ በመጠኑ ትልቁ ነው። አዲሱ ስልክ በአሜሪካ ዋጋው ከ1,999 ዶላር ጀምሮ እስከ 3,200 ዶላር (325 ሺህ አስከ 500 ሺህ ብር በላይ) የሚደርስ ሲሆን፣ እስካሁን ለገበያ ከቀረቡ የአይፎን ስልኮች መካከል ከፍተኛ ዋጋ የሚያስወጣ ነው። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
35
18
አስመራ፡ በውሃ እጥረት የምትሰቃየው ከተማ "ትንሿ ሮም" በመባል የምትታወቀው አሥመራ አሁን መልክዓ ምድሯ ተለውጦ፣ ነዋሪዎቿ በከባድ የውሃ እጥረት የሚንገላቱባት ሆናለች። የከተማዋ ጎዳናዎች በቢጫና ሰማያዊ የውሃ ጄሪካኖች እንዲሁም ውሃ በሚያመላልሱ በእጅ የሚገፉ ጋሪዎች ተሞልተው ይስተዋላሉ። ይህ ለወራት የቀጠለ የውሃ ችግር ነው። ሕጻናት ሳቀይር ውሃ ለመፈለግ ሲንገላቱ ይታያል። የዚህን ችግር መንስኤ እና የሚተገበሩ የመፍትሄ አማራጮችን በተመለከተ ቢቢሲ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ ገብረመስቀል እና በለንደን የሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲን ጠይቋል። ሁለቱም አካላት መልስ አልሰጡም። የአመሥራ ከተማ ነዋሪ የሆነው አስመሮም (ስሙ ተቀይሯል) "በዕድሜዬ እንዲህ ያለ ችግር አይቼ አላውቅም" ይላል። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
39
19
የአማካይ ዘመን ምርጫን ሪፐብሊካኖች ካሸነፉ እያንዳንዱ አዋቂ አሜሪካዊ 5,000 ዶላር እንደሚያገኝ ትራምፕ ተናገሩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በኅዳር ወር በሚካሄዱት የአማካይ ዘመን ምርጫዎች ሪፐብሊካኖች ሁለቱንም ምክር ቤቶች ካሸነፉ፣ እያንዳንዱ አዋቂ አሜሪካዊ 5,000 ዶላር እንዲያገኝ እንደሚያደርጉ ተናገሩ። ይህ ዕቅድ ከአንድ ትሪሊዮን ዶላር በላይ የሚያስወጣ መሆኑ ተገልጿል። ትራምፕ አከራካሪ የሆነውን ይህን ቃል የገቡት በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ዘመን አማካይ ላይ የሪፐብሊካን ፓርቲ ለመጀመሪያ ጊዜ ባካሄደው ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው። ዕቅዱ እንዴት እንደሚተገበር እና ገንዘቡ ከየት እንደሚመጣ ግን ምንም ዝርዝር አልሰጡም። ሆኖም ገንዘቡ አሜሪካ ውስጥ ብቻ መዋል እንዳለበት ተናግረዋል። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
37
20
ሰሜን ኮሪያ አዲስ ባለ ሁለት ፎቅ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ጣቢያ መገንባቷ ተገለፀ ሰሜን ኮሪያ ተጨማሪ ባለ ሁለት ፎቅ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ጣቢያ መገንባቷን የዓለም የኒውክሌር መሣሪያዎች ተቆጣጣሪ ተቋም አስታወቀ። ይህንን ድርጊትም "እጅግ አሳሳቢ" ሲል ገልፆታል። አዲሱ ግንባታ የዋናው ኒውክሌር ማዕከል ዮንግብዮን አካል ሲሆን፣ ዩራኒየምን ለማበልጸግ የሚጠቅሙ እስከ 28 ሴንትሪፊዩጅ የሚባሉ የማሽን ስብስቦችን ማስተናገድ እንደሚችል ተነግሯል። ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ ባለፈው ወር መጨረሻ በወጣው ሪፖርት፣ ፒዮንግያንግ በሌላ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ቦታ ላይም አዲስ ማስፋፊያ ሰርታ ወደ ሥራ አስገብታለች። እነዚህ ግኝቶች ሰሜን ኮሪያ በማዕቀብ የተገደበውን የኒውክሌር መሠረተ ልማቷን ቀስ በቀስ እያስፋፋች መሆኗን የሚያመለክቱ ናቸው። ተቆጣጣሪዎቹ ከአውሮፓውያኑ 2009 ጀምሮ ከሰሜን ኮሪያ ከተባረሩ በኋላ በሀገሪቱ ውስጥ የክትትል ሰራተኞች የሌሉት ኤጀንሲው፣ በሳተላይት ምስሎች ላይ በመመስረት ነው ግምገማዎችን የሚያደርገው። ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
34