BBC Amharic | ቢቢሲ አማርኛ
رفتن به کانال در Telegram
2 077
مشترکین
-524 ساعت
-197 روز
-8730 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
سپتامبر '26
سپتامبر '26
+4
در 0 کانالها
اوت '26
+15
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '26
+7
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '26
+5
در 0 کانالها
Get PRO
مه '26
+2
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+4
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '26
+8
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+4
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+29
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+79
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+447
در 2 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+182
در 1 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+133
در 2 کانالها
Get PRO
اوت '25
+231
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '25
+241
در 2 کانالها
Get PRO
ژوئن '25
+300
در 0 کانالها
Get PRO
مه '25
+780
در 1 کانالها
Get PRO
آوریل '25
+1 874
در 1 کانالها
Get PRO
مارس '250
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '250
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '250
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '240
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '240
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '240
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '240
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '24
+655
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '240
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '240
در 0 کانالها
Get PRO
مه '240
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '240
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '240
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '240
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '240
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '230
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '23
+349
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 11 سپتامبر | 0 | |||
| 10 سپتامبر | 0 | |||
| 09 سپتامبر | 0 | |||
| 08 سپتامبر | +1 | |||
| 07 سپتامبر | 0 | |||
| 06 سپتامبر | +1 | |||
| 05 سپتامبر | 0 | |||
| 04 سپتامبر | +1 | |||
| 03 سپتامبر | +1 | |||
| 02 سپتامبر | 0 | |||
| 01 سپتامبر | 0 |
پستهای کانال
የየመን ሁቲ ታጣቂዎች ወሳኝ የቀይ ባሕር ወደብ የሆነችውን ሞካን መቆጣጠራቸው ተዘገበ
የየመን ሁቲዎች፣ በሳዑዲ የሚደገፉ የመንግሥት ኃይሎችን በመርታት ስትራቴጂያዊ የሆነችውን በቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የምትገኘውን ሞካ የወደብ ከተማን መያዛቸውን ወታደራዊ ምንጮች እና የዐይን እማኞች ገለፁ። በኢራን የሚደገፈው ቡድን ሞካን መያዙን ተከትሎ፣ ከባብ ኤል መንደብ ወሽመጥ ያለው ርቀት 75 ኪሎ ሜትር ብቻ ሆኗል። ይህ ወሽመጥ እስያን እና አውሮፓን የሚያገናኝ እንዲሁም በቀይ ባሕር በኩል ለሚደረጉ የመርከብ ጉዞዎች ቁልፍ የሆነ የንግድ መስመር ነው። ነገር ግን ሁቲዎቹ በዓለም አቀፍ የመርከብ እንቅስቃሴ ላይ ምንም ስጋት እንደማይፈጥሩ ገልጸዋል። ሆኖም ከሳዑዲ አረቢያ የሚመጡ መርከቦችን ዒላማ እንደሚያደርጉ በድጋሚ ዝተዋል። ሳዑዲ አረቢያ የአሜሪካ እና የእስራኤል ጦርነት በባሕረ ሰላጤው የሚገኘው የሆርሙዝ ወሽመጥን በአብዛኛው ከተዘጋ በኋላ የነዳጅ ምርቶቿን ለመላክ በቀይ ባሕር ላይ ጥገኛ ሆናለች።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
| 2 | ከ600 በላይ እስረኞች በይቅርታ ሲለቀቁ 28 ይቅርታ ባለመጠየቃቸው ሳይፈቱ ቀሩ
ከአማራ እና ከኦሮሚያ ክልሎች በከባድ ወንጀሎች ተከስሰው በፌደራል መንግሥቱ በእስር ላይ ይገኙ የነበሩ ከስድስት መቶ በላይ ሰዎች በይቅርታ መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። በተመሳሳይ ክስ ለዓመታት በእስር ላይ የቆዩ ነገር ግን ይቅርታ ለመጠየቅ ፈቃደኛ ያልሆኑ 28 እስረኞች ደግሞ ሳይፈቱ ቀርተዋል። በ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት ዋዜማ ጳጉሜ 52018 ዓ.ም. ከእስር መፈታታቸው የተነገረው በመቶዎች የሚቆጠሩ ታሳሪዎች ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው በይቅርታ፣ ክሳቸው በሂደት ላይ የነበረው ደግሞ እንዲቋረጥ ተደርጎ መሆኑን ኮሚሽኑ አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም ለአዲሱ ዓመት ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ላይ ልዩ ልዩ ወገኖች "በአንድም ሆነ በሌላ ስህተት የታሠሩ ወገኖች በይቅርታ እና በሕግ አግባብ እንዲፈቱ" መጠየቃቸውን እና መንግሥትም ተቀብሎ "በሂደቱ የተስማሙትን ፈትቷል" ብለዋል። ኢሰመኮ እንዳለው የተለቀቁት ሰዎች ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ በሽብር እና በሌሎች ከባድ ወንጀሎች ተከሰው ፍርድ ቤት ውሳኔ የሰጠባቸው እንዲሁም በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው በፍርድ ሂደት ላይ የሚገኙ ነበሩ። ታሳሪዎቹ "ጉዳያቸው በልዩ ሁኔታ እንዲታይ. . . በኮሚሽኑ በኩል ለመንግሥት እንዲቀርብላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ" በማድረግ ኢሰመኮ ታሳሪዎቹ በሕግ ሂደት ይቅርታ እንዲገያኙ ጉዳዩን ለመንግሥት አቅርቦ ምላሽ ማግኘቱን ገልጿል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 28 |
| 3 | ኮሚሽኑ ትግራይን የሚመለከቱ አጀንዳዎችን የሚያቀርበው ለፌዴራል መንግሥቱ መሆኑን ገለፀ
ከአራት ዓመታት በላይ ወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮችን በማሰባሰብ ከአንድ ወር በላይ ምክክር ያደረገው ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ውጤቱን ለሚመለከታቸው አካላት እንዲሁም ትግራይን የሚመለከቱ አጀንዳዎችን ለፌደራል መንግሥቱ እንደሚያርብ አስታወቀ። በዚህም አራት ሺህ የሚሆኑ ተመካካሪዎች የተሳተፉበትን ኮሚሽኑ የሀገራዊ ምክክር ውጤት የሆነውን የመጨረሻውን ምክረ-ሃሳብ ከመስከረም 10 በፊት ለመንግሥት እንደሚያቀርብ አመልክቷል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ በምክክሩ የቀረቡ ምክረ-ሃሳቦችን ለተግባሪ የፌዴራል መንግሥት አካላት ከመስከረም 10 በፊት ለማቅረብ ምክረ-ሃሳቦቹን እያደራጀ መሆኑን ይፋ አድርጓል። በተጨማሪም በክልሎች እና በከተማ አስተዳደሮች ውስጥ ለሚደረጉ ምክክሮች የሚረዱ አጀንዳዎችን፣ እንዲሁም እነዚህ አካላት ሊፈፅሟቸው የሚገቡ የሕዝብ ጥያቄዎችንም በዚሁ ጊዜ ውስጥ ለማስረከብ እየሠራ መሆኑን ገልጿል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 30 |
| 4 | ከ325 ሺህ ብር በላይ የሚያስወጣው አዲሱ የአይፎን ስልክ ምን ይዟል
አፕል አይፎን ስልኮችን ለገበያ ካቀረበ ከ20 ዓመታት በኋላ በስልኩ ላይ የተደረገውን ትልቁን ለውጥ ይፋ አድርጓል። ረቡዕ ዕለት በኩባንያው ዓመታዊ የምርት ማስተዋወቂያ ዝግጅት ላይ የመጀመሪያውን ታጣፊ የአይፎን ስልክን ማቅረቡን አስታወቋል። እንደ መጽሐፍ በሚታጠፍ ቅርጽ የተዘጋጀው አዲሱ አይፎን "ዱዎ" ተብሎ የተሰየመ ሲሆን፣ እስካሁን ከተመረቱት አይፎኖች ሁሉ በመጠኑ ትልቁ ነው። አዲሱ ስልክ በአሜሪካ ዋጋው ከ1,999 ዶላር ጀምሮ እስከ 3,200 ዶላር (325 ሺህ አስከ 500 ሺህ ብር በላይ) የሚደርስ ሲሆን፣ እስካሁን ለገበያ ከቀረቡ የአይፎን ስልኮች መካከል ከፍተኛ ዋጋ የሚያስወጣ ነው።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 27 |
| 5 | አስመራ፡ በውሃ እጥረት የምትሰቃየው ከተማ
"ትንሿ ሮም" በመባል የምትታወቀው አሥመራ አሁን መልክዓ ምድሯ ተለውጦ፣ ነዋሪዎቿ በከባድ የውሃ እጥረት የሚንገላቱባት ሆናለች። የከተማዋ ጎዳናዎች በቢጫና ሰማያዊ የውሃ ጄሪካኖች እንዲሁም ውሃ በሚያመላልሱ በእጅ የሚገፉ ጋሪዎች ተሞልተው ይስተዋላሉ። ይህ ለወራት የቀጠለ የውሃ ችግር ነው። ሕጻናት ሳቀይር ውሃ ለመፈለግ ሲንገላቱ ይታያል። የዚህን ችግር መንስኤ እና የሚተገበሩ የመፍትሄ አማራጮችን በተመለከተ ቢቢሲ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ ገብረመስቀል እና በለንደን የሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲን ጠይቋል። ሁለቱም አካላት መልስ አልሰጡም። የአመሥራ ከተማ ነዋሪ የሆነው አስመሮም (ስሙ ተቀይሯል) "በዕድሜዬ እንዲህ ያለ ችግር አይቼ አላውቅም" ይላል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 26 |
| 6 | የአማካይ ዘመን ምርጫን ሪፐብሊካኖች ካሸነፉ እያንዳንዱ አዋቂ አሜሪካዊ 5,000 ዶላር እንደሚያገኝ ትራምፕ ተናገሩ
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በኅዳር ወር በሚካሄዱት የአማካይ ዘመን ምርጫዎች ሪፐብሊካኖች ሁለቱንም ምክር ቤቶች ካሸነፉ፣ እያንዳንዱ አዋቂ አሜሪካዊ 5,000 ዶላር እንዲያገኝ እንደሚያደርጉ ተናገሩ። ይህ ዕቅድ ከአንድ ትሪሊዮን ዶላር በላይ የሚያስወጣ መሆኑ ተገልጿል። ትራምፕ አከራካሪ የሆነውን ይህን ቃል የገቡት በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ዘመን አማካይ ላይ የሪፐብሊካን ፓርቲ ለመጀመሪያ ጊዜ ባካሄደው ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው። ዕቅዱ እንዴት እንደሚተገበር እና ገንዘቡ ከየት እንደሚመጣ ግን ምንም ዝርዝር አልሰጡም። ሆኖም ገንዘቡ አሜሪካ ውስጥ ብቻ መዋል እንዳለበት ተናግረዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 28 |
| 7 | ሰሜን ኮሪያ አዲስ ባለ ሁለት ፎቅ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ጣቢያ መገንባቷ ተገለፀ
ሰሜን ኮሪያ ተጨማሪ ባለ ሁለት ፎቅ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ጣቢያ መገንባቷን የዓለም የኒውክሌር መሣሪያዎች ተቆጣጣሪ ተቋም አስታወቀ። ይህንን ድርጊትም "እጅግ አሳሳቢ" ሲል ገልፆታል። አዲሱ ግንባታ የዋናው ኒውክሌር ማዕከል ዮንግብዮን አካል ሲሆን፣ ዩራኒየምን ለማበልጸግ የሚጠቅሙ እስከ 28 ሴንትሪፊዩጅ የሚባሉ የማሽን ስብስቦችን ማስተናገድ እንደሚችል ተነግሯል። ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ ባለፈው ወር መጨረሻ በወጣው ሪፖርት፣ ፒዮንግያንግ በሌላ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ቦታ ላይም አዲስ ማስፋፊያ ሰርታ ወደ ሥራ አስገብታለች። እነዚህ ግኝቶች ሰሜን ኮሪያ በማዕቀብ የተገደበውን የኒውክሌር መሠረተ ልማቷን ቀስ በቀስ እያስፋፋች መሆኗን የሚያመለክቱ ናቸው። ተቆጣጣሪዎቹ ከአውሮፓውያኑ 2009 ጀምሮ ከሰሜን ኮሪያ ከተባረሩ በኋላ በሀገሪቱ ውስጥ የክትትል ሰራተኞች የሌሉት ኤጀንሲው፣ በሳተላይት ምስሎች ላይ በመመስረት ነው ግምገማዎችን የሚያደርገው።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 31 |
| 8 | ስደተኞች ከሞሮኮ ወደ ሴዩታ ከመሻገራቸው በፊት የስፔን የደኅንነት ተቋም መረጃ እንደደረሰው ተገለጸ
በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ከሞሮኮ ወደ ስፔን ግዛት ሴዩታ ከመሻገራቸው በፊት የስፔን የደኅንነት ተቋም መረጃ ደርሶት እንደነበረ አዲስ የመንግሥት ሰነድ ይፋ አደረገ። የስፔን መንግሥት በርካታ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች ከሞሮኮ መሻገራቸውን በተመለከተ ተመጣጣኝ እርምጃ አልወሰደም በሚል እየተወቀሰ ሳለ ነው ሰነዶቹን ያወጣው። በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ስደተኞች የስፔንን ድንበር እንዲሻገሩ ጥሪ የሚያደርጉ ይዘቶች መዘዋወራቸውን በተመለከተ በአውሮፓውያኑ ሐምሌ 29 የስፔን ብሔራዊ ደኅንነት ተቋም ለሞሮኮ እና ሴዩታ ባለሥልጣናት አስታውቋል። በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩት ስደተኞች ሴዩታ የገቡት ሐምሌ 30 ነበር።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 29 |
| 9 | በአሜሪካ ከፍተኛ የተባለውን ከ230 ሚሊዮን ዶላር በላይ ክሪፕቶከረንሲ የሰረቀው ሴንጋፖራዊ ወጣት
የሲንጋፖር ዜጋ የሆነ ወጣት በአሜሪካ ካጋጠመ ከፍተኛ ከሆኑት የክሪፕቶከረንሲ ስርቆቶች መካከል አንዱን በመምራት የቀረበበትን ክስ ተቀብሎ ለፍርድ ቤት ጥፋተኛ መሆኑን አመነ። የ22 ዓመቱ ማሎን ላም ከጓደኞቹ ጋር በመተባበር 245 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ቢትኮይን በመስረቅ እና የተሰረቀውን በሕጋዊ መንገድ እንደተገኘ ለማስመሰል መሞከሩን አምኗል። የአሜሪካ ፍትሕ ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ላም እና ተባባሪዎቹ የተሰረቀውን ገንዘብ በመጠቀም በአንድ ምሽት እስከ 500 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በምሽት መዝናኛ ክለቦች ወጪ ያደርጉ ነበር። በተጨማሪም ዋጋቸው ከ100 ሺህ እስከ 3.8 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ውድ የቅንጦት መኪኖችንም ገዝተው ነበር። ላም ጥፋተኝነቱን ማመኑን ተከትሎ እስከ 20 ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት ሊፈረድበት ይችላል። ጉዳዩን የተመለከቱት ዳኛ ኮሊን ኮላር-ኮቴሊ የቅጣት ውሳኔ ለማሳለፍ ቀን አልቆረጡም።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 28 |
| 10 | የአሜሪካ እና የኢራን ጦርነት እንዴት ሊቆም ይችላል የሦስት ተንታኞች ዕይታ
የአሜሪካ እና የኢራንን ጦርነት ለማስቆም ተጨባጭ የሆነ ስምምነት ላይ ይደረሳል የሚለው ተስፋ ደብዝዞ ይታያል፤ ሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች ጥቃቶችን በመፈጸም እና የማይለሳለሱ አቋሞችን በማንጸባረቅ ላይ ናቸው። እነዚህ ጥቃቶች የተከሰቱት አሜሪካ ወደ አዲስ ምዕራፍ እየገባች መሆኗን ከገለጸች ከቀናት በኋላ ነው፤ በኢራን እና ከኢራን ጋር የንግድ ግንኙነት ያላቸው አገራት ላይ ያነጣጠረ ሰፊ የኢኮኖሚ ማዕቀብ ይፋ አድርጋለች። የአሜሪካ ዓላማ ኢራንን ወደ ድርድር ማምጣት እና በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የምትፈጽማቸውን ጥቃቶች እንድታቆም ማስገደድ ነበር። ይህ ለዓለም ንግድ በጣም ወሳኝ የሆነው የመርከብ መተላለፊያ መስመር፣ አሜሪካ እና እስራኤል ግጭቱን ባለፈው የካቲት ወር ከጀመሩ ወዲህ በተግባር ተዘግቶ ቆይቷል። ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር የፈረሙት እና በ60 ቀናት ውስጥ ወደ ቋሚ የተኩስ አቁም እና የሰላም ስምምነት ሊያመራ የነበረው የመግባቢያ ሰነድ ጊዜው አልፏል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 28 |
| 11 | ኤርትራ ግለሰቦች እና ተቋማት በሚይዙት የጥሬ ገንዘብ መጠን ላይ ገደብ ጣለች
የኤርትራ ግለሰቦች እና የንግድ ተቋማት ከባንክ ሥርዓት ውጭ ለተወሰነ ጊዜ መያዝ የሚችሉትን የጥሬ ገንዘብ መጠን የሚገድብ አዲስ መመሪያ ማውጣቷን የአገሪቱ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ። ረቡዕ ጳጉሜ 42018 ዓ.ም. በአገሪቱ መንግሥታዊ የሕግ ጋዜጣ ላይ ታትሞ ይፋ በተደረገው መመሪያ ማንኛውም ዓይነት የኤርትራ ገንዘብ፣ ናቅፋ ዝውውር በባንኮች እና በገንዘብ ተቋማት ብቻ መሆን እንዳለበት አዝዟል። በአዲሱ መመሪያ መሠረት ግለሰቦች ከ25 ሺህ ናቅፋ በላይ የሚሆን ጥሬ ገንዘብ ከ15 ቀናት በላይ በእጃቸው ማቆየት አይችሉም። እንዲሁም በተለያዩ ሦስት ደረጃዎች የተመደቡ የንግድ ተቋማትም በ50 ሺህ፣ በ100 ሺህ እና በ150 ሺህ ናቅፋ መጠን የተገደበ ጥሬ ገንዘብ ለሁለት ሳምንታት ብቻ መያዝ እንዲችሉ ተፈቅዷል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 41 |
| 12 | ሜታ የሕጻናት ወሲባዊ ብዝበዛ ይዘት ያላቸው ማስታወቂያዎች ማስተላለፍ መቀጠሉን አዲስ ሪፖርት አጋለጠ
ሜታ ሰው ሠራሽ አስተውሎት በመጠቀም በመቶዎች የሚቆጠሩ የሕጻናት ወሲባዊ ብዝበዛ ይዘት ያላቸው ማስታወቂያዎችን ማስተላለፉን አዲስ የወጣ ሪፖርት አጋለጠ። ክፍያ የተፈጸመባቸው ማስታወቂያዎቹ ባለፉት 10 ወራት መለቀቃቸውን መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገ የመብት ተሟጋች ቡድን ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል። እነዚህ ማስታወቂያዎች በሕንድ በስፋት ወጥተዋል። ከሁለት ወራት በፊት ሜታ የሕጻናት ወሲባዊ ብዝበዛ ይዘት ያላቸውን ማስታወቂያዎች ከኢንስታግራም እንዲያጠፋ ከሕንድ መንግሥት ማሳሰቢያ ተሰጥቶት ነበር።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 39 |
| 13 | የሱዳን የጤና ሥርዓት የውድቀት አፋፍ ላይ መድረሱን አንድ የሕክምና በጎ አድራጎት ድርጅት ገለፀ
ዓለም አቀፍ ድጋፍ በመቀነሱ ምክንያት በመላው ሱዳን በርካታ የጤና ተቋማት እየተዘጉ መሆናቸውን እና ቀድሞውንም የተዳከመው የሱዳን የጤና ሥርዓት የውድቀት አፋፍ ላይ እየተጠጋ እንደሆነ ሜዲሲን ሳን ፍሮንቲየርስ (ኤንኤስኤፍ) አስጠነቀቀ። የሕክምና በጎ አድራጎት ድርጅቱ እንዳለው፣ የሱዳን ከፍተኛ እርዳታ ለጋሽ የነበረችው አሜሪካ የውጭ እርዳታ የሚያቀርበውን ኤጀንሲ ዩኤስኤአይዲን ባለፈው ዓመት ከዘጋች በኋላ፣ በርካታ ድርጅቶች ተለዋጭ የገንዘብ እርዳታ ምንጭ ማግኘት አልቻሉም። በኒው ዮርክ የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ የተሰበሰቡ የዓለም መሪዎች ፈጣን እርምጃ እንዲወስዱ ኤንኤስኤፍ ጥሪ አቅርቧል። በሱዳን ጦር እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች መካከል በሚያዝያ ወር 2015 ዓ. ም. የተጀመረው ጦርነት፣ ዓለም ላይ ካሉት እጅግ አስከፊ ሰብአዊ ቀውሶች አንዱ እንዲፈጠር አድርጓል። በአሁኑ ጊዜ በሱዳን ከ33 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የሕክምና እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 31 |
| 14 | ኦፕንኤአይ 90 ዓመት ላስቆጠረ ከባድ የሒሳብ ጥያቄ በ88 ሰዓታት ውስጥ መልስ ማግኘቱን አስታወቀ
ኦፕንኤአይ 90 ዓመት ላስቆጠረ ከባድ የሒሳብ ጥያቄ በሰዓታት ውስጥ ምላሽ ማግኘቱን አስታወቀ። የሰው ሠራሽ አስተውሎት ሞዴል እና በሺህዎች የሚቆጠሩ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቦቶችን በመጠቀም ለሒሳብ ጥያቄው በ88 ሰዓታት ውስጥ መልስ ማግኘት ተችሏል። ቻትጂፒቲን የሠራው ኦፕንኤአይ ትናንት ማክሰኞ እንዳስታወቀው 10,000 የኤአይ ቦቶች በመጠቀም የሒሳብ ችግሩ ተፈትቷል። የሒሳብ ጥያቄው 'ናቪየር-ስትሮክስ ኢኩዌዥንስ' የተባለው የሒሳብ ቀመር ክፍል ሲሆን፤ ለ90 ዓመታት ያህል ስሌቱ ሳይረጋገጥ ቆይቷል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 28 |
| 15 | የአሜሪካ እና ካናዳ የንግድ ጦርነት ሲቀጥል፣ አሜሪካ በርካታ የካናዳ ምርቶች እንዳይገቡ አገደች
አሜሪካ የአልኮል መጠጦችን፣ የወተት ተዋጽኦ እና ሞተር ሳይክሎችን ጨምሮ በርካታ የካናዳ ምርቶች እንዳይገቡ እግድ ጣለች። እርምጃው የተወሰደው ካናዳ በአሜሪካ ምርቶች ላይ የጣለቻቸው አፀፋዊ ቀረጦች ተግባራዊ መሆናቸውን ተከትሎ ነው። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ማክሰኞ ዕለት በፈረሟቸው ተከታታይ ፕሬዝደንታዊ ትዕዛዞች፣ ካናዳ በአሜሪካ ላይ "አድልዎ እያደረገች ነው" ብለዋል። በካናዳ ምርቶች ላይ የጣሉት እገዳ ከመስከረም 19 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆንም ገልፀዋል። ከትራምፕ እርምጃ አስቀድመው በተመሳሳይ ቀን የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ካርኒ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልእክት፣ አገራቸው ከፍተኛ የንግድ አጋሯ ከሆነችው ከአሜሪካ በመራቅ አዲስ አጋሮችን ለመፈለግ በምታደርገው ሽግግር "ዋጋ በማስከፈል" የሚፈፀም ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 25 |
| 16 | ህወሓት ኦሉሴጎን ኦባሳንጆን "ገለልተኛ አይደሉም" ማለቱ አንድምታው ምንድን ነው
ህወሓት የፕሪቶሪያ ስምምነት አሸማጋይ የሆኑት የአፍሪካ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ "የገለልተኛ አደራዳሪነት መርኅ አልታየባቸውም" ሲል ከስሷል። የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦባሳንጆ ለቀረበባቸው ክስ በጽሕፈት ቤታቸው በኩል በሰጡት ምላሽ፤ በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ባለሥልጣናት መካከል የነበረው ግንኙነት ተቋርጦ የፕሪቶሪያን ስምምነት የሚጥሱ ሙከራዎች እንዲሁም "ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ጠብ ጫሪ" ሁኔታዎች በመታየታቸው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንደጀመሩ አስታውቀዋል። የትግራይ ጦርነት በፕሪቶሪያ ስምምነት ከተገታ በኋላ የስምምነቱ ተፈጻሚነት ላይ ሁለቱም ወገኖች ጥያቄ እያነሱ ሲሆን፤ ለተፈጠሩ ክፍተቶች አንዳቸው ሌላቸውን ሲወቅሱም ይደመጣል። በስምምነቱ መሠረት መፈጸም የነበረባቸው በርካታ ጉዳዮች ተግባራዊ አለመሆናቸውን ሁለቱም ወገኖች ሲያነሱ ቆይተዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 30 |
| 17 | በዋስ ከተለቀቁ "ፅምዶን ሊቀላቀሉ ይችላሉ" በሚል ፖሊስ ይግባኝ በማቅረቡ የኢሕአፓ ፖለቲከኞች እና ጠበቃ አበራ ሳይፈቱ ቀሩ
ባለፈው ሳምንት ፍርድ ቤት ከእስር በዋስ እንዲለቀቁ የወሰነላቸው ፖለቲከኞች እና የሕግ ባለሙያ ፖሊስ ይግባኝ በማቅረቡ ምክንያት ሳይፈቱ መቅረታቸውን ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ። ተጠርጣሪዎቹ በዋስ የሚፈቱ ከሆነ "ከፅምዶ ቡድን ጋር ተቀላቅለው ሊሰወሩ ይችላሉ" በማለት የስር ፍርድ ቤትን የዋስትና ውሳኔ በመቃወም ፖሊስ ይግባኝ ጠይቋል። "በሽብር ወንጀል" የተጠረጠሩት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ፖለቲከኞች አቶ አበበ አካሉ እና አቶ ይሳቅ ወልዳይ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ፣ እያንዳንዳቸው በ50 ሺህ ብር ዋስ እንዲፈቱ የፌዴራሉ ፍርድ ቤት ባለፈው ሳምንት ዓርብ ነሐሴ 292018 ዓ.ም ነበር የወሰነው። የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦች ትላንት ሰኞ ጳጉሜ 2 የዋስትናውን ገንዘብ ቢያስይዙም፣ ፖሊስ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ በማለቱ አለመፈታታቸውን ጠበቃቸው አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የፌዴራል ፖሊስ ለጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ባቀረበው የይግባኝ አቤቱታው፣ ሦስቱ ተጠርጣሪዎች "ጫካ ከሚገኘው ፅምዶ ቡድን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው" ሲል አመልክቷል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 40 |
| 18 | የተካረረው የአሜሪካ እና የካናዳ የንግድ እና የታሪፍ ጦርነት
የአሜሪካንን እርምጃ ተከትሎ ካናዳ በበርካታ የአሜሪካ ምርቶች ላይ የጣለችው የአጸፋ ታሪፍ ከዛሬ ማክሰኞ ጀምሮ ሥራ ላይ መዋል ጀመረ። ይህ ካናዳ በአሜሪካ ላይ የጣለቸው የአጸፋ ታሪፍ ወደ 28 ቢሊዮን የካናዳ ዶላር (20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር) የሚጠጉ ከአሜሪካ ወደ ካናዳ የሚገቡ ምርቶችን ይመለከታል። ይህም ከብረት እስከ የቤት እቃዎች፣ ጥጥ እና የተለያዩ አልባሳትን የሚያካትት ሲሆን፣ የታሪፉ መጠን እስከ 50 በመቶ ይደርሳል። የአሜሪካ እና የካናዳ ባለሥልጣናት አዲስ ስምምነት ለመፈራረም ፍላጎት እንዳላቸው ቢገልጹም፣ በነሐሴ መጨረሻ የተቋረጡትን ውይይቶች ለመቀጠል የሚደረግ ምንም እርምጃ አልታየም።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 37 |
| 19 | ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ በህወሓት መሪዎች ለቀረበባቸው ቅሬታ ምላሽ ሰጡ
የትግራይ ጦርነትን ያበቃው የፕሪቶሪያ ስምምነት አሸማጋይ የሆኑት የአፍሪካ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ መሪዎች ገለልተኛ አይደሉም በሚል ለቀረበባቸው ክስ ምላሽ ሰጡ። የትግራይ ክልል አስተዳደርን ተቆጣጥረው ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ፍጥጫ ውስጥ የገቡት የህወሓት መሪዎች እሁድ ዕለት ባወጡት መግለጫ የቀድሞውን የናይጄሪያ መሪ ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ የገለልተኛ አደራዳሪነት መርኅ አልታየባቸውም በማለት ወቅሷል። በፌደራል መንግሥቱ እና በህወሓት መሪዎች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት እየተባባሰ በነበረበት ጊዜ ኦባሳንጆ ባለፈው ነሐሴ አጋማሽ በድንገት ወደ መቀለ ሄደው ከክልሉ ባለሥልጣናት ጋር ንግግር አድርገው እንደነበር ይታወሳል። ይህንንም በማስመለክት የትግራይ ባለሥልጣናት ባወጡት መግለጫ ላይ "በቅርቡ... በኦሉሴጉን ኦባሳንጆ በኩል የማደራደሩ ሂደት እንደገና ሊጀመር መሆኑን የሚያመለክት የይምሰል ድራማዎች ለመፍጠር የተደረገ ጥረት ታይቷል" በማለት እንቅስቃሴው "በራሳቸው ተነሳሽነት ወይስ በብልፅግና ትዕዛዝ ነው የሚል ከባድ ጥያቄን እያስነሳ ይገኛል" ብሏል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 37 |
| 20 | "ልጆቻችንን ትምህርት ቤት መላክ ያስፈራናል"- ፍልስጤማውያን ወላጆች
ፍልስጤማውያን ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ተመልሰዋል። አል-ሙግሀይር የወንዶች ትምህርት ቤት ዳይሬክተር በጠዋት ተማሪዎችን ለመቀበል ተገኝቷል። በይዞታ ሥር ባለው ዌስት ባንክ የሚገኘው ትምህርት ቤቱ በቅርቡ የብረት አጥር ተሠርቶለታል። በወይራ ዘይት ዛፍ መካከል ብረቱ ይታያል። ባሳም አል አሲፍ "ፈርተናል። ተማሪዎችና ወላጆችም ፈርተዋል" ይላል። በያዝነው ዓመት በአል-ሙግሀይር ሦስት ተማሪዎችን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ተገድለዋል። ሰፋሪዎች ፍልስጤማውያን ላይ የሚፈጽሙት ጥቃት እየተባባሰ መጥቷል። ከተገደሉት አንዱ የ14 ዓመቱ አውስ አል-ናሳን ነው። ከትምህርት ቤቱ ውጭ ከሰፋሪ በተተኮሰ በጥይት ተገድሏል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 37 |
