BBC Amharic | ቢቢሲ አማርኛ
الذهاب إلى القناة على Telegram
2 074
المشتركون
-524 ساعات
-197 أيام
-8730 أيام
جاري تحميل البيانات...
القنوات المماثلة
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
سبتمبر '26
سبتمبر '26
+4
في 0 قنوات
أغسطس '26
+15
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '26
+7
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '26
+5
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '26
+2
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+4
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+8
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+4
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+29
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+79
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+447
في 2 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+182
في 1 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+133
في 2 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+231
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+241
في 2 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+300
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+780
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+1 874
في 1 قنوات
Get PRO
مارس '250
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '250
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '250
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '240
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '240
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '240
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '240
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+655
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '240
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '240
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '240
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '240
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '240
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '240
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '240
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '230
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+349
في 0 قنوات
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 12 سبتمبر | 0 | |||
| 11 سبتمبر | 0 | |||
| 10 سبتمبر | 0 | |||
| 09 سبتمبر | 0 | |||
| 08 سبتمبر | +1 | |||
| 07 سبتمبر | 0 | |||
| 06 سبتمبر | +1 | |||
| 05 سبتمبر | 0 | |||
| 04 سبتمبر | +1 | |||
| 03 سبتمبر | +1 | |||
| 02 سبتمبر | 0 | |||
| 01 سبتمبر | 0 |
منشورات القناة
ከመስከረም 1 ጥቃት ከዓመታት በፊት ሲአይኤ 'ስለ ሚፈነዱ አውሮፕላኖች' ማስጠንቀቂያ ደርሶት እንደነበር ተገለጸ
የመስከረም 1 ጥቃት ከመፈጸሙ ከሦስት ዓመታት በፊት የአሜሪካ የደኅንነት ተቋም ባለሥልጣናት "አል-ቃኢዳ ተቀጣጣይ አውሮፕላን ወደ ከተማዋ ሊያበርር የሚችልበት ዕድል እንዳለ" መወያየታቸውን አዲስ ሰነድ አሳየ። ከዚህ ቀደም ምሥጢራዊ የነበረው ሰነድ አሁን ለሕዝብ ይፋ የሆነው ከሽብር ጥቃቱ 25ኛ ዓመት መታሰቢያ ጋር በተያያዘ ነው። የአሜሪካ የደኅንነት ተቋም (ሲአይኤ) 71 ገጽ ፕሬዝዳንታዊ ሰነዶችን ይፋ አድርጓል። እነዚህም ከአውሮፓውያኑ 1998 ጀምሮ ጥቃቱ ከደረሰበት ቀን በኋላ እስካለው ጊዜ የተሰበሰቡ ናቸው። በአውሮፓውያኑ መስከረም 122001 የተመዘገበ አንድ ሰነድ እንደሚያሳየው በአክራሪ ቡድኖች ዘንድ ጥቃት የመጸም ሴራ መኖሩ "በስፋት የሚታወቅ" ነበር።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA
| 2 | የኖርዌይ ልዕልት በወንድማቸው የአገሪቱ ንጉሥ ቀብር ላይ ከተገኙ ከሁለት ቀናት በኋላ አረፉ
የኖርዌይ ልዕልት አስትሪድ የአገሪቱ ንጉሥ በሆኑት በወንድማቸው ንጉሥ ሃራልድ አምስተኛ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ከተሳተፉ ከሁለት ቀናት በኋላ መሞታቸውን የኖርዌይ ንጉሣዊ ቤተ መንግሥት አስታወቀ። ልዕልቲቱ በ94 ዓመት ዕድሜያቸው ያረፉት ታናሽ ወንድማቸው ንጉሥ ሃራልድ አምስተኛ ካረፉ ከሳምንት እንዲሁም ቀብራቸው ከተፈጸመ ከሁለት ቀናት በኋላ ነው። አዲሱ የኖርዌይ ንጉሥ ሃኮን ስምንተኛ የልዕልቱቱን ኅልፈት ተከትሎ "ልዕልት አስትሪድ በረጅም ዘመናቸው ሁሉ ንጉሣዊ ቤተሰቡን በቀናነት እና በታማኝነት ወክለዋል" ብለዋል። ንጉሥ ሃራልድ ባለፈው ነሐሴ ወር በ89 ዓመታቸው ከ35 ዓመታት በላይ በንግሥና ከቆዩ በኋላ ነበር ያረፉት። ልዕልቲቱ በመጨራሻ ለሕዝብ የታዩት በወንድማቸው የቀብር ሥነ ሥርዓት ወቅት ነበር።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 13 |
| 3 | ለፍቅር ግንኙነት የተዋወቋቸውን ሰዎች በሚሊዮኖች ያጭበረበሩ ናይጄሪያውያን ለአሜሪካ ተላልፈው ተሰጡ
የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ በአሜሪካ ያሉ ሴቶችን በኢንተርኔት አማካይነት ቀርቦ የፍቅር ግንኙነት በመጀመር የማጭበርበር ወንጀሎችን በመፈጸም የሚፈለጉ ስድስት ናይጄሪያውያንን ለኤፍቢአይ አሳልፎ ሰጠ። የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት እንዳሉት፣ ናይጄሪያውያኑ በአሜሪካ ውስጥ ከ100 በላይ ሴቶችን በማጭበርበር ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ በመዝረፍ ይከሰሳሉ። ለአሜሪካ ተላልፈው የተሰጡት ግለሰቦች በ2021 ታስረው ነበር፤ እንዲሁም "ብላክ አክስ" የተባለ ከሰዎች ዝውውር፣ ከበይነ መረብ ማጭበርበር እና ከግድያ ጋር የተያያዘ የናይጄሪያ የማፍያ ዓይነት የወንጀል ቡድን አባላት እንደሆኑ ይታመናል። ገንዘባቸውን ከተጭበረበሩት መካከል ጡረተኞች እና ነጋዴዎች እንዳሉበት ተገልጿል። እነዚህ ሰዎች "ገንዘባቸውን ለመውሰድ የተራቀቁ የኢንተርኔት ግንኙነቶችን በመጠቀም ዒላማ ተደርገው ነበር" ሲል የደቡብ አፍሪካ ልዩ የፖሊስ ኃይል ገልጿል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 13 |
| 4 | ሳዑዲ አረቢያ በተፈጸመባት የድሮን ጥቃት ወሳኝ የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧዋን ዘጋች
ሳዑዲ አረቢያ በተፈጸመባት የድሮን ጥቃት ወሳኝ የሆነው የዘይት ማስተለላፊያ ቧንቧዋ ከተመታ በኋላ እንዲዘጋ አድርጋለች፤ ይህም በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው ግጭት እየሰፋ መሄዱን ያሳያል እየተባለ ነው። ይህ ጥቃት ከኢራን ድንበር አጠገብ ከሚገኝ ግዛቷ እንደተፈጸመ ኢራን አረጋግጣ፣ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ወታደራዊ አዛዥ ከኃላፊነት ተነስቶ ምርመራ እንደተጀመረ አስታውቃለች። 1,200 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይህ የነዳጅ ማስተለላፊያ ቧንቧ፣ በዓለም ትልቋ ድፍድፍ ነዳጅ ላኪ የሆነችው ሳዑዲ አረቢያ፣ የሆርሙዝ ወሽመጥ ከተዘጋ በኋላ ምርቷን ለገበያ ለማቅረብ አማራጭ ሆኗት ነበር። ይህ ክስተት፣ በኢራን የሚደገፉት የየመን ሁቲ አማጺያን ወሳኝ ድል በማግኘት የቀይ ባሕር ዳርቻዎችን በተቆጣጠሩበት ወቅት የተከሰተ ሲሆን፣ የአሜሪካ እና ኢራን ጦርነት ወደ ሰባተኛ ወሩ በገባበት በአሁኑ ጊዜ በዓለም የነዳጅ ዝውውርን አስተጓጉሏል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 15 |
| 5 | በምዕራብ ወለጋ ስለተቃጠሉት ነዳጅ ጫኝ ተሽከርካሪዎች ቢቢሲ በሳተላይት ምሥሎች ያደረገው ማጣራት ምን ያሳያል
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን፣ ጊምቢ ከተማ አቅራቢያ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት ከዘጠኝ ያላነሱ ነዳጅ ጫኝ ከባድ ተሽከርካሪዎች ሙሉ በሙሉ እና በከፊል መቃጠላቸውን ቢቢሲ ከምንጮች እና ከሳተላይት ምሥል አረጋገጠ። ታጣቂዎች ባለፈው እሑድ ጳጉሜ 12018 ዓ.ም. በደፈጣ እንደፈፀሙት በተገለፀው በዚህ ጥቃት፣ ከስምነት ያላነሱ ሾፌሮች ታግተው መወሰዳቸውን የኢትዯጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኅበር ገልጿል። ቢቢሲ የተመለከታቸው ተንቀሳቃሽ ምሥሎች በርካታ የተቃጠሉ ተሽከርካሪዎችን የሚያሳዩ ሲሆን ከሳተላይት መረጃዎች ጋር በማናበብ በሠራው ትንታኔ በእርግጥም ጥቃቱ በዚያ አካባባቢ በተጠቀሰው ቀን ስለመፈጸሙ አመላካች መረጃዎችን አግኝቷል። የተቃጠሉ ነዳጅ ጫኝ ከባድ ተሽከርካሪዎችን የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምሥሎች (ቪዲዮዎች) በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት ተዘዋውረዋል። ተሽከርካሪዎቹ ነዳጅ ጭነው ከጊምቢ በነጆ አድርገው ወደ አሶሳ በማቅናት ላይ እንደነበሩ የአካባቢው ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 18 |
| 6 | የዓለምን ገጽታ የቀየረው የመስከረም 1 ጥቃት 25ኛ ዓመት እና የስለላው ዘርፍ ያጋጠመው ውድቅት
ለብዙ አስርተ ዓመታት የተለያዩ መሪዎች እንደተናገሩት፣ የማንኛውም መንግሥት የመጀመሪያ ግዴታ ሕዝቡን መጠበቅ ነው። በአውሮፓውያኑ 2001 መስከረም 11 ቀን ግን አሜሪካ ይህንን ግዴታ ለመወጣት ሳትችል ቀርታለች። የስለላ መረጃዎች ቢኖሩም፣ የተለያዩ ፍንጮችን በጊዜው አገናኝቶ ተግባራዊ እርምጃ የወሰደ አልነበረም። በኋላ "911" ተብለው የታወቁት በአሜሪካ ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶች እና ለእነሱ የተሰጠው ምላሽ፣ በዚህ ክፍለ ዘመን የመጀመሪያዎቹን ሁለት አስርተ ዓመታት የውጭ ጉዳይ፣ የደኅንነት እና የስለላ ፖሊሲዎችን በእጅጉ የቀረጹ ክስተቶች ሆነዋል። በ2001 መስከረም 11፣ አጥፍቶ ለመጥፋት የተዘጋጁ የአልቃኢዳ አብራሪዎች የተጠለፏቸው አውሮፕላኖችን ዓለም ንግድ ማዕከል ሰማይ ጠቀስ ሕንጻዎች ጋር በማጋጨት ጥቃቱን ከጀመሩ በኋላ በዚያ ቀን 2,977 ሰዎች ተገድለዋል። እነዚህ ጥቃቶች ከየትም ተነስተው የመጡ አልነበሩም። የአሜሪካ ማዕከላዊ የስለላ ድርጅት (ሲአይኤ) ከ2001 በፊት ለብዙ ዓመታት ስለ አልቃኢዳ እና በስደት ስለሚኖረው ሳዑዲያዊ መሪው ኦሳማ ቢን ላደን መረጃ ነበረው። እንዲያውም እሱን ለመያዝ ተመድቦ የሚሠራ ልዩ ቡድን ነበረው።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 38 |
| 7 | በዲሞክራቲክ ኮንጎ ትምህርት ቤት ውስጥ በተከሰተ የእሳት አደጋ ከ20 በላይ ልጆች ሞቱ
በምሥራቃዊው የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በአማጺያን ቁጥጥር ሥር ባለችው ቡካቩ ከተማ ውስጥ ሁለት ትምህርት ቤቶች ላይ የእሳት አደጋ ከተነሳ በኋላ ከእሳቱ ለማምለጥ በተፈጠረ መረጋገጥ ቢያንስ 24 ተማሪዎች መሞታቸውን ባለሥልጣናት ገለጹ። በተከሰተው የእሳት አደጋ ምክንያት ከተማሪ ልጆች በተጨማሪ አዋቂዎችም ሕይወታቸውን ማጣታቸው የተመዘገበ ሲሆን የሟቾች ቁጥርም ሊጨምር እንደሚችልም ስጋት አለ። ከአደጋው የተረፉ ሰዎች በአቅራቢያ ወደ ሚገኙ ሆስፒታሎች ተወስደዋል፤ ከቦታው የተቀረጹ ምሥሎችም ጉዳት የደረሰባቸው ልጆች እየተሰቃዩ በሆስፒታል ወለል ላይ ተኝተው ያሳያሉ። በእሳቱ ምክንያት 300 ያህል ቤቶችም ወድመዋል፤ የእሳቱ መንስኤ ግን እስካሁን አልታወቀም።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 37 |
| 8 | የየመን ሁቲ ታጣቂዎች ወሳኝ የቀይ ባሕር ወደብ የሆነችውን ሞካን መቆጣጠራቸው ተዘገበ
የየመን ሁቲዎች፣ በሳዑዲ የሚደገፉ የመንግሥት ኃይሎችን በመርታት ስትራቴጂያዊ የሆነችውን በቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የምትገኘውን ሞካ የወደብ ከተማን መያዛቸውን ወታደራዊ ምንጮች እና የዐይን እማኞች ገለፁ። በኢራን የሚደገፈው ቡድን ሞካን መያዙን ተከትሎ፣ ከባብ ኤል መንደብ ወሽመጥ ያለው ርቀት 75 ኪሎ ሜትር ብቻ ሆኗል። ይህ ወሽመጥ እስያን እና አውሮፓን የሚያገናኝ እንዲሁም በቀይ ባሕር በኩል ለሚደረጉ የመርከብ ጉዞዎች ቁልፍ የሆነ የንግድ መስመር ነው። ነገር ግን ሁቲዎቹ በዓለም አቀፍ የመርከብ እንቅስቃሴ ላይ ምንም ስጋት እንደማይፈጥሩ ገልጸዋል። ሆኖም ከሳዑዲ አረቢያ የሚመጡ መርከቦችን ዒላማ እንደሚያደርጉ በድጋሚ ዝተዋል። ሳዑዲ አረቢያ የአሜሪካ እና የእስራኤል ጦርነት በባሕረ ሰላጤው የሚገኘው የሆርሙዝ ወሽመጥን በአብዛኛው ከተዘጋ በኋላ የነዳጅ ምርቶቿን ለመላክ በቀይ ባሕር ላይ ጥገኛ ሆናለች።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 37 |
| 9 | ከ600 በላይ እስረኞች በይቅርታ ሲለቀቁ 28 ይቅርታ ባለመጠየቃቸው ሳይፈቱ ቀሩ
ከአማራ እና ከኦሮሚያ ክልሎች በከባድ ወንጀሎች ተከስሰው በፌደራል መንግሥቱ በእስር ላይ ይገኙ የነበሩ ከስድስት መቶ በላይ ሰዎች በይቅርታ መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። በተመሳሳይ ክስ ለዓመታት በእስር ላይ የቆዩ ነገር ግን ይቅርታ ለመጠየቅ ፈቃደኛ ያልሆኑ 28 እስረኞች ደግሞ ሳይፈቱ ቀርተዋል። በ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት ዋዜማ ጳጉሜ 52018 ዓ.ም. ከእስር መፈታታቸው የተነገረው በመቶዎች የሚቆጠሩ ታሳሪዎች ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው በይቅርታ፣ ክሳቸው በሂደት ላይ የነበረው ደግሞ እንዲቋረጥ ተደርጎ መሆኑን ኮሚሽኑ አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም ለአዲሱ ዓመት ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ላይ ልዩ ልዩ ወገኖች "በአንድም ሆነ በሌላ ስህተት የታሠሩ ወገኖች በይቅርታ እና በሕግ አግባብ እንዲፈቱ" መጠየቃቸውን እና መንግሥትም ተቀብሎ "በሂደቱ የተስማሙትን ፈትቷል" ብለዋል። ኢሰመኮ እንዳለው የተለቀቁት ሰዎች ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ በሽብር እና በሌሎች ከባድ ወንጀሎች ተከሰው ፍርድ ቤት ውሳኔ የሰጠባቸው እንዲሁም በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው በፍርድ ሂደት ላይ የሚገኙ ነበሩ። ታሳሪዎቹ "ጉዳያቸው በልዩ ሁኔታ እንዲታይ. . . በኮሚሽኑ በኩል ለመንግሥት እንዲቀርብላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ" በማድረግ ኢሰመኮ ታሳሪዎቹ በሕግ ሂደት ይቅርታ እንዲገያኙ ጉዳዩን ለመንግሥት አቅርቦ ምላሽ ማግኘቱን ገልጿል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 37 |
| 10 | ኮሚሽኑ ትግራይን የሚመለከቱ አጀንዳዎችን የሚያቀርበው ለፌዴራል መንግሥቱ መሆኑን ገለፀ
ከአራት ዓመታት በላይ ወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮችን በማሰባሰብ ከአንድ ወር በላይ ምክክር ያደረገው ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ውጤቱን ለሚመለከታቸው አካላት እንዲሁም ትግራይን የሚመለከቱ አጀንዳዎችን ለፌደራል መንግሥቱ እንደሚያርብ አስታወቀ። በዚህም አራት ሺህ የሚሆኑ ተመካካሪዎች የተሳተፉበትን ኮሚሽኑ የሀገራዊ ምክክር ውጤት የሆነውን የመጨረሻውን ምክረ-ሃሳብ ከመስከረም 10 በፊት ለመንግሥት እንደሚያቀርብ አመልክቷል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ በምክክሩ የቀረቡ ምክረ-ሃሳቦችን ለተግባሪ የፌዴራል መንግሥት አካላት ከመስከረም 10 በፊት ለማቅረብ ምክረ-ሃሳቦቹን እያደራጀ መሆኑን ይፋ አድርጓል። በተጨማሪም በክልሎች እና በከተማ አስተዳደሮች ውስጥ ለሚደረጉ ምክክሮች የሚረዱ አጀንዳዎችን፣ እንዲሁም እነዚህ አካላት ሊፈፅሟቸው የሚገቡ የሕዝብ ጥያቄዎችንም በዚሁ ጊዜ ውስጥ ለማስረከብ እየሠራ መሆኑን ገልጿል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 37 |
| 11 | ከ325 ሺህ ብር በላይ የሚያስወጣው አዲሱ የአይፎን ስልክ ምን ይዟል
አፕል አይፎን ስልኮችን ለገበያ ካቀረበ ከ20 ዓመታት በኋላ በስልኩ ላይ የተደረገውን ትልቁን ለውጥ ይፋ አድርጓል። ረቡዕ ዕለት በኩባንያው ዓመታዊ የምርት ማስተዋወቂያ ዝግጅት ላይ የመጀመሪያውን ታጣፊ የአይፎን ስልክን ማቅረቡን አስታወቋል። እንደ መጽሐፍ በሚታጠፍ ቅርጽ የተዘጋጀው አዲሱ አይፎን "ዱዎ" ተብሎ የተሰየመ ሲሆን፣ እስካሁን ከተመረቱት አይፎኖች ሁሉ በመጠኑ ትልቁ ነው። አዲሱ ስልክ በአሜሪካ ዋጋው ከ1,999 ዶላር ጀምሮ እስከ 3,200 ዶላር (325 ሺህ አስከ 500 ሺህ ብር በላይ) የሚደርስ ሲሆን፣ እስካሁን ለገበያ ከቀረቡ የአይፎን ስልኮች መካከል ከፍተኛ ዋጋ የሚያስወጣ ነው።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 32 |
| 12 | አስመራ፡ በውሃ እጥረት የምትሰቃየው ከተማ
"ትንሿ ሮም" በመባል የምትታወቀው አሥመራ አሁን መልክዓ ምድሯ ተለውጦ፣ ነዋሪዎቿ በከባድ የውሃ እጥረት የሚንገላቱባት ሆናለች። የከተማዋ ጎዳናዎች በቢጫና ሰማያዊ የውሃ ጄሪካኖች እንዲሁም ውሃ በሚያመላልሱ በእጅ የሚገፉ ጋሪዎች ተሞልተው ይስተዋላሉ። ይህ ለወራት የቀጠለ የውሃ ችግር ነው። ሕጻናት ሳቀይር ውሃ ለመፈለግ ሲንገላቱ ይታያል። የዚህን ችግር መንስኤ እና የሚተገበሩ የመፍትሄ አማራጮችን በተመለከተ ቢቢሲ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ ገብረመስቀል እና በለንደን የሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲን ጠይቋል። ሁለቱም አካላት መልስ አልሰጡም። የአመሥራ ከተማ ነዋሪ የሆነው አስመሮም (ስሙ ተቀይሯል) "በዕድሜዬ እንዲህ ያለ ችግር አይቼ አላውቅም" ይላል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 32 |
| 13 | የአማካይ ዘመን ምርጫን ሪፐብሊካኖች ካሸነፉ እያንዳንዱ አዋቂ አሜሪካዊ 5,000 ዶላር እንደሚያገኝ ትራምፕ ተናገሩ
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በኅዳር ወር በሚካሄዱት የአማካይ ዘመን ምርጫዎች ሪፐብሊካኖች ሁለቱንም ምክር ቤቶች ካሸነፉ፣ እያንዳንዱ አዋቂ አሜሪካዊ 5,000 ዶላር እንዲያገኝ እንደሚያደርጉ ተናገሩ። ይህ ዕቅድ ከአንድ ትሪሊዮን ዶላር በላይ የሚያስወጣ መሆኑ ተገልጿል። ትራምፕ አከራካሪ የሆነውን ይህን ቃል የገቡት በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ዘመን አማካይ ላይ የሪፐብሊካን ፓርቲ ለመጀመሪያ ጊዜ ባካሄደው ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው። ዕቅዱ እንዴት እንደሚተገበር እና ገንዘቡ ከየት እንደሚመጣ ግን ምንም ዝርዝር አልሰጡም። ሆኖም ገንዘቡ አሜሪካ ውስጥ ብቻ መዋል እንዳለበት ተናግረዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 35 |
| 14 | ሰሜን ኮሪያ አዲስ ባለ ሁለት ፎቅ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ጣቢያ መገንባቷ ተገለፀ
ሰሜን ኮሪያ ተጨማሪ ባለ ሁለት ፎቅ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ጣቢያ መገንባቷን የዓለም የኒውክሌር መሣሪያዎች ተቆጣጣሪ ተቋም አስታወቀ። ይህንን ድርጊትም "እጅግ አሳሳቢ" ሲል ገልፆታል። አዲሱ ግንባታ የዋናው ኒውክሌር ማዕከል ዮንግብዮን አካል ሲሆን፣ ዩራኒየምን ለማበልጸግ የሚጠቅሙ እስከ 28 ሴንትሪፊዩጅ የሚባሉ የማሽን ስብስቦችን ማስተናገድ እንደሚችል ተነግሯል። ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ ባለፈው ወር መጨረሻ በወጣው ሪፖርት፣ ፒዮንግያንግ በሌላ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ቦታ ላይም አዲስ ማስፋፊያ ሰርታ ወደ ሥራ አስገብታለች። እነዚህ ግኝቶች ሰሜን ኮሪያ በማዕቀብ የተገደበውን የኒውክሌር መሠረተ ልማቷን ቀስ በቀስ እያስፋፋች መሆኗን የሚያመለክቱ ናቸው። ተቆጣጣሪዎቹ ከአውሮፓውያኑ 2009 ጀምሮ ከሰሜን ኮሪያ ከተባረሩ በኋላ በሀገሪቱ ውስጥ የክትትል ሰራተኞች የሌሉት ኤጀንሲው፣ በሳተላይት ምስሎች ላይ በመመስረት ነው ግምገማዎችን የሚያደርገው።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 33 |
| 15 | ስደተኞች ከሞሮኮ ወደ ሴዩታ ከመሻገራቸው በፊት የስፔን የደኅንነት ተቋም መረጃ እንደደረሰው ተገለጸ
በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ከሞሮኮ ወደ ስፔን ግዛት ሴዩታ ከመሻገራቸው በፊት የስፔን የደኅንነት ተቋም መረጃ ደርሶት እንደነበረ አዲስ የመንግሥት ሰነድ ይፋ አደረገ። የስፔን መንግሥት በርካታ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች ከሞሮኮ መሻገራቸውን በተመለከተ ተመጣጣኝ እርምጃ አልወሰደም በሚል እየተወቀሰ ሳለ ነው ሰነዶቹን ያወጣው። በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ስደተኞች የስፔንን ድንበር እንዲሻገሩ ጥሪ የሚያደርጉ ይዘቶች መዘዋወራቸውን በተመለከተ በአውሮፓውያኑ ሐምሌ 29 የስፔን ብሔራዊ ደኅንነት ተቋም ለሞሮኮ እና ሴዩታ ባለሥልጣናት አስታውቋል። በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩት ስደተኞች ሴዩታ የገቡት ሐምሌ 30 ነበር።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 37 |
| 16 | በአሜሪካ ከፍተኛ የተባለውን ከ230 ሚሊዮን ዶላር በላይ ክሪፕቶከረንሲ የሰረቀው ሴንጋፖራዊ ወጣት
የሲንጋፖር ዜጋ የሆነ ወጣት በአሜሪካ ካጋጠመ ከፍተኛ ከሆኑት የክሪፕቶከረንሲ ስርቆቶች መካከል አንዱን በመምራት የቀረበበትን ክስ ተቀብሎ ለፍርድ ቤት ጥፋተኛ መሆኑን አመነ። የ22 ዓመቱ ማሎን ላም ከጓደኞቹ ጋር በመተባበር 245 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ቢትኮይን በመስረቅ እና የተሰረቀውን በሕጋዊ መንገድ እንደተገኘ ለማስመሰል መሞከሩን አምኗል። የአሜሪካ ፍትሕ ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ላም እና ተባባሪዎቹ የተሰረቀውን ገንዘብ በመጠቀም በአንድ ምሽት እስከ 500 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በምሽት መዝናኛ ክለቦች ወጪ ያደርጉ ነበር። በተጨማሪም ዋጋቸው ከ100 ሺህ እስከ 3.8 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ውድ የቅንጦት መኪኖችንም ገዝተው ነበር። ላም ጥፋተኝነቱን ማመኑን ተከትሎ እስከ 20 ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት ሊፈረድበት ይችላል። ጉዳዩን የተመለከቱት ዳኛ ኮሊን ኮላር-ኮቴሊ የቅጣት ውሳኔ ለማሳለፍ ቀን አልቆረጡም።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 31 |
| 17 | የአሜሪካ እና የኢራን ጦርነት እንዴት ሊቆም ይችላል የሦስት ተንታኞች ዕይታ
የአሜሪካ እና የኢራንን ጦርነት ለማስቆም ተጨባጭ የሆነ ስምምነት ላይ ይደረሳል የሚለው ተስፋ ደብዝዞ ይታያል፤ ሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች ጥቃቶችን በመፈጸም እና የማይለሳለሱ አቋሞችን በማንጸባረቅ ላይ ናቸው። እነዚህ ጥቃቶች የተከሰቱት አሜሪካ ወደ አዲስ ምዕራፍ እየገባች መሆኗን ከገለጸች ከቀናት በኋላ ነው፤ በኢራን እና ከኢራን ጋር የንግድ ግንኙነት ያላቸው አገራት ላይ ያነጣጠረ ሰፊ የኢኮኖሚ ማዕቀብ ይፋ አድርጋለች። የአሜሪካ ዓላማ ኢራንን ወደ ድርድር ማምጣት እና በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የምትፈጽማቸውን ጥቃቶች እንድታቆም ማስገደድ ነበር። ይህ ለዓለም ንግድ በጣም ወሳኝ የሆነው የመርከብ መተላለፊያ መስመር፣ አሜሪካ እና እስራኤል ግጭቱን ባለፈው የካቲት ወር ከጀመሩ ወዲህ በተግባር ተዘግቶ ቆይቷል። ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር የፈረሙት እና በ60 ቀናት ውስጥ ወደ ቋሚ የተኩስ አቁም እና የሰላም ስምምነት ሊያመራ የነበረው የመግባቢያ ሰነድ ጊዜው አልፏል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 29 |
| 18 | ኤርትራ ግለሰቦች እና ተቋማት በሚይዙት የጥሬ ገንዘብ መጠን ላይ ገደብ ጣለች
የኤርትራ ግለሰቦች እና የንግድ ተቋማት ከባንክ ሥርዓት ውጭ ለተወሰነ ጊዜ መያዝ የሚችሉትን የጥሬ ገንዘብ መጠን የሚገድብ አዲስ መመሪያ ማውጣቷን የአገሪቱ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ። ረቡዕ ጳጉሜ 42018 ዓ.ም. በአገሪቱ መንግሥታዊ የሕግ ጋዜጣ ላይ ታትሞ ይፋ በተደረገው መመሪያ ማንኛውም ዓይነት የኤርትራ ገንዘብ፣ ናቅፋ ዝውውር በባንኮች እና በገንዘብ ተቋማት ብቻ መሆን እንዳለበት አዝዟል። በአዲሱ መመሪያ መሠረት ግለሰቦች ከ25 ሺህ ናቅፋ በላይ የሚሆን ጥሬ ገንዘብ ከ15 ቀናት በላይ በእጃቸው ማቆየት አይችሉም። እንዲሁም በተለያዩ ሦስት ደረጃዎች የተመደቡ የንግድ ተቋማትም በ50 ሺህ፣ በ100 ሺህ እና በ150 ሺህ ናቅፋ መጠን የተገደበ ጥሬ ገንዘብ ለሁለት ሳምንታት ብቻ መያዝ እንዲችሉ ተፈቅዷል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 43 |
| 19 | ሜታ የሕጻናት ወሲባዊ ብዝበዛ ይዘት ያላቸው ማስታወቂያዎች ማስተላለፍ መቀጠሉን አዲስ ሪፖርት አጋለጠ
ሜታ ሰው ሠራሽ አስተውሎት በመጠቀም በመቶዎች የሚቆጠሩ የሕጻናት ወሲባዊ ብዝበዛ ይዘት ያላቸው ማስታወቂያዎችን ማስተላለፉን አዲስ የወጣ ሪፖርት አጋለጠ። ክፍያ የተፈጸመባቸው ማስታወቂያዎቹ ባለፉት 10 ወራት መለቀቃቸውን መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገ የመብት ተሟጋች ቡድን ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል። እነዚህ ማስታወቂያዎች በሕንድ በስፋት ወጥተዋል። ከሁለት ወራት በፊት ሜታ የሕጻናት ወሲባዊ ብዝበዛ ይዘት ያላቸውን ማስታወቂያዎች ከኢንስታግራም እንዲያጠፋ ከሕንድ መንግሥት ማሳሰቢያ ተሰጥቶት ነበር።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 40 |
| 20 | የሱዳን የጤና ሥርዓት የውድቀት አፋፍ ላይ መድረሱን አንድ የሕክምና በጎ አድራጎት ድርጅት ገለፀ
ዓለም አቀፍ ድጋፍ በመቀነሱ ምክንያት በመላው ሱዳን በርካታ የጤና ተቋማት እየተዘጉ መሆናቸውን እና ቀድሞውንም የተዳከመው የሱዳን የጤና ሥርዓት የውድቀት አፋፍ ላይ እየተጠጋ እንደሆነ ሜዲሲን ሳን ፍሮንቲየርስ (ኤንኤስኤፍ) አስጠነቀቀ። የሕክምና በጎ አድራጎት ድርጅቱ እንዳለው፣ የሱዳን ከፍተኛ እርዳታ ለጋሽ የነበረችው አሜሪካ የውጭ እርዳታ የሚያቀርበውን ኤጀንሲ ዩኤስኤአይዲን ባለፈው ዓመት ከዘጋች በኋላ፣ በርካታ ድርጅቶች ተለዋጭ የገንዘብ እርዳታ ምንጭ ማግኘት አልቻሉም። በኒው ዮርክ የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ የተሰበሰቡ የዓለም መሪዎች ፈጣን እርምጃ እንዲወስዱ ኤንኤስኤፍ ጥሪ አቅርቧል። በሱዳን ጦር እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች መካከል በሚያዝያ ወር 2015 ዓ. ም. የተጀመረው ጦርነት፣ ዓለም ላይ ካሉት እጅግ አስከፊ ሰብአዊ ቀውሶች አንዱ እንዲፈጠር አድርጓል። በአሁኑ ጊዜ በሱዳን ከ33 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የሕክምና እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።
ወቅታዊ መረጃ @BBCAMARGNA | 36 |
