1 085
Подписчики
+924 часа
+207 дней
+1530 день
Архив постов
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 35ተኛ መደበኛ ስብሰባው በኢትዮጵያና በኩዌት መካከል በሥራ ስምሪት ዘርፍ የተፈረመውን የመግባቢያ ሰነድ ለማጽደቅ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አጸደቀ፡፡
የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) በኢትዮጵያና በኩዌት መካከል በሥራ ስምሪት ዘርፍ የተፈረመውን የመግባቢያ ሰነድ ለማጽደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በዚህም በኢትዮጵና በኩዌት መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲጠናከር፣ በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በሌሎችም መስኮች ጠንካራ ትስስር ተፈጥሮ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በሁለቱ ሀገራት የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
የመግባቢያ ሰነዱ ዓላማ በሁለቱ ሀገራት መካከል በሥራ ስምሪት መስክ ያለውን ትብብር ለማጠናከርና ህጋዊ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት እንዲሁም በኩዌት የሚገኙ ዜጎችን መብትና ጥቅም ለማስከበር መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ረቂቅ አዋጁ ወደ ሁለተኛ ንባብ ተሸጋግሮ አዋጅ ቁጥር 1337/2016 ሆኖ በሙሉ ድምጽ መጽደቁን ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ሰኔ 26/2016 ዓ.ም
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት https://lmis.gov.et
ለኮሌጅና ዩኒቨርስቲ ምሩቃን በሙሉ
****
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚቢሽን(Job Fair)" የፊታችን አርብ ሰኔ 28/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ በድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ሁለገብ ሜዳ የሚካሄድ ይሆናል።
በዚህም ስራ ፈላጊ ምሩቃን የተለያዩ ድርጅቶች በቅጥር ሥራ የምታገኙበትን ሁኔታ ሊያመቻቹ እናንተን ስለሚጠብቁ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን በመያዝና በአካል በመገኘት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
የድሬዳዋ አስተዳደር
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+6
“እራስን ለመቻል እና ከጠባቂነት ለመላቀቅ እዲቻል ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት ይኖርብናል፡፡”
አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ
የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች "ከተረጂነት አስተሳሰብ ለመላቀቅና በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት አደረጉ።
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱትና ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆን በንግግራቸውም እንደ አገርም እንደ ተቋም የተጀመሩ የልማት ስራዎች ወደፊት እንዲቀጥል ለማድረግ በተቋም ደረጃ በርካታ ማሽነሪዎች እንዲሁም በእውቀት እና በክህሎት የዳበረ የሰው ሃይል ያለበት ኮሌጅ ውስጥ እንደመሆናችን መጠን የአቅማችንን ሰርተን በላባችንና በደማችን አገራችን በልማት ወደፊት እንድትሄድ በጋራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ከሌላው ሳንጠብቀወ በተገቢው መንገድ እየሰራን አገራችን በልማት እና በብልጽግና ወደፊት እንድትሄድ ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
በውይይት መድረኩ ላይ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች የተገኙ ሲሆን በእለቱ የቀረበውን የውይይት ሃሳብ እንደ ኮሌጅ እንዲሁም እንደ ከተማችን ተጨባጭ ሁኔታ በማስተሳሰር ሊተገበር እንደሚገባ ከተሳታፊዎች አስተያየት ተሰጥቷል፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሰኔ 25/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
"ከተረጂነት አስተሳሰብ ለመላቀቅና በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች ውይይት አደረጉ።
በዚህም ከተረጂነት ለመላቀቅና በምግብ እራስን ለመቻል አገራዊ መግባባትን መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑና በተረጂነት ተጨባጭ ለውጥ ባለመመዝገቡ ዜጎች አመለካከት በመቀየር አቅምን በማቀናጀትና በመደጋገፍ በተለይም የዘርፉን ተጨባጭ ሁኔታ በመረዳት ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ማጠናከር እንደሚገባ የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል።
በመድረኩ ተሳታፊ ለሆኑ አመራሮችና ሠራተኞች በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን አገራዊ ዕሳቤውና አቅጣጫውን እንደ አስተዳደሩ ተጨባጭ ሁኔታ በማዘጋጀት ወደ ስራ ለመግባት ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት እንዲሰጠው አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን አክለውም ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ከተረጂነት አስተሳሰብ ለመላቀቅና በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች ውይይት አደረጉ።
በዚህም ከተረጂነት ለመላቀቅና በምግብ እራስን ለመቻል አገራዊ መግባባትን መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑና በተረጂነት ተጨባጭ ለውጥ ባለመመዝገቡ ዜጎች አመለካከት በመቀየር አቅምን በማቀናጀትና በመደጋገፍ በተለይም የዘርፉን ተጨባጭ ሁኔታ በመረዳት ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ማጠናከር እንደሚገባ የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል።
በመድረኩ ተሳታፊ ለሆኑ አመራሮችና ሠራተኞች በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን አገራዊ ዕሳቤውና አቅጣጫውን እንደ አስተዳደሩ ተጨባጭ ሁኔታ በማዘጋጀት ወደ ስራ ለመግባት ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት እንዲሰጠው አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን አክለውም ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የአስተዳደሩን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የስርዓተ-ስልጠና መሳሪያዎችን ስርጭት፣ አጠቃቀም፣ አተገባበር እና ተግዳሮቶች የሚዳስስ ጥናት ተደረገ፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከክልልና የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በሁሉም የትኩረት መስኮች ከደረጃ አንድ እስከ አምስት የስርዓተ ትምህርትና የስልጠና መሳሪያዎች በአዲስ መልክ በማዕከል በማዘጋጀት እና በማስተቸት አሰራጭቶ ለትምህርትና ስልጠናውም ተደራሽ በማድረግ ለኢንዱስትሪዎች የሰው ሃይል ልማቱን በእውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት የዳበረ በየጊዜው አዲስ ከሚፈጠሩ ክህሎቶች እና እውቀቶች እራሱን በማላመድ ምርታማነት ለማሳደግ በሚያስችል ለስልጠና እንዲውል መደረጉ ይታወቃል፤
ይህንን መሠረት በማድረግ በአስተዳደሩ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራንን አቅም በመጠቀም እነዚህ በፌደራል ደረጃ በማዕከል ተዘጋጅተው የተሰራጩ የውጤት ተኮር መተግበሪያ መሳሪያዎች ውስጥ አንዱ የሆነውን የስርዓተ-ስልጠና መሳሪያዎችን ሰርጭት፣ አጠቃቀም፣ አተገባበር እና ተግዳሮቶችን ምን እንደሚመስል በጥናት በማረጋገጥ Assessment of outcome-based training tools in technical vocational institute in Dire Dawa Administration በሚል ርዕስ የተጠና ጥናት ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ እንዲፀድቅና የተመላከቱ የመፍትሔ ሃሳቦችን በመውሰድ ስራ ላይ እንዲውል አቅጣጫ መቀመጡን የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ ጀማል አደም ገልጸዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 24/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from E-LMIS - ብቁ
🌏ለውጭ ሃገር የሥራ ስምሪት ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ላላችሁ ዜጎች!
የሥራና ክህሎት ሚንስቴር የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይልን ባለፉት ሁለት ዓመታት ወደ 4 የመዳረሻ ሃገራት የሁለትዮሽ ስምምነት በመፈጸም ዜጎች መብታቸው፣ ደህንነታቸው እና ክብራቸው ተጠብቆ እንዲሰማሩ ሲደረግ ቆይቷል።
አሁን ደግሞ ዜጎች ለሥራ የሚሄዱባቸውን የመዳረሻ ሃገራት በማስፋት ዜጎች በሰፊው የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ከተጨማሪ ሁለት ሃገራት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈጽሞ ወደ ስራ ተገብቷል።
በአሁኑ ሰዓት ሃገራችን ስምምነት በመፈጸም የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል የምታሰማራባቸው የመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ፣ ኳታር፣ ጆርዳን፣ ሊባኖስ እና ኩዌት ሲሆኑ በአውሮፓ እና በኢሺያ ደግሞ ከተለያዩ የሰው ሃይል ፍላጎት ካላቸው ካምፓኒዎች ጋር ስምምነት በመፈጸም በሚያቀርቡት ጥያቄ እና መስፈርት መሰረት የሰለጠነ የሰው ሃይል እያሰማራ ይገኛል።
በመሆኑም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ከቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች ተመርቃችሁ ሲስተሙ ላይ ተመዝግባችሁ ለውጭ ሃገር የስራ ስምሪት በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ ዜጎች በተለያየ ሃገር በሚገኙ ቀጣሪ ድርጅቶች ስትመዘግቡ ያስገባችሁትን የተለያዩ መረጃዎች ማየት እንዲችሉ የሲስተም አክሰስ የተሰጣቸው በመሆኑ ቀጣሪ ድርጅቶቹ መረጃዎቻችሁን በማየት ለስራ እስኪመርጧችሁ በትዕግስት እንድትጠባበቁ እንዲሁም ያልተሟላ መረጃ ያላችሁ ዜጎች መረጃዎቻችሁን እንድታሟሉ እናሳስባለን።
ለተመዘገባችሁ መልካም ዕድልን እንመኛለን። ላልተመዘገባችሁ ዜጎች በመመዝገብ ዕድላችሁን እንድትሞክሩ እናሳስባለን።
✨ብቁ ሰራተኛ • ብቁ ቀጣሪ • ብቁ ውሳኔ ሰጪ!
💼የሥራ ባለቤት እርስዎ ኖት!
የ2016 ዓ.ም የሥራ ዕድል ፈጠራ እንዲሁም "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የስራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡
በመድረኩም የቢሮውና በአስተዳደሩ የሚገኙ አንድ ማዕከላት አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በግምገማ መድረኩም አንድ ማዕከላት አመታዊ የሥራ አፈጻጸማቸውን አቅርበው ባቀረቡት አፈጻጸም ላይ በመነሳት ሀሳብ አስተያየት ተሰጥቶ ያለባቸውን ክፍተትም ለማሟት ያግዝ ዘንድ የቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ለዜጎች የስራ እድልን በመፍጠር አሁን ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር ለመቀነስና የስራ ባህልን በማጎልበት የሚያስፈልጓቸውን የሙያና የክህሎት ስልጠናዎች ወስደውና ወደ ስራ እንዲሰማሩ በማመቻቸትና ራሳቸውን ከስራ አጥነት እንዲያላቅቁ በማድረግና በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡
በመድረኩም ላይ የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በቢሮ እና በአንድ ማዕከላቱ መናበብ የተሰሩ መልካም ስራዎችን አበረታተው በቀጣይ በተለይ ዋና ዋና የስራ እድል የመፍጠሪያ የስራ ዘርፎች ማለትም በግብርና በኢንዱስትሪ እና በአገልግሎት ዘርፍ ስራ ፈላጊዎችን በቋሚነት ወደ ሥራ ከማሰማራት አንጻር ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 23/2016 ዓ.ም
ሐረር
በዘርፉ አዲስ እሳቤ ዙሪያ "ማርሽ ቀያሪ ምዕራፍ" በሚል ርዕስ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ተሰጠ።
በስልጠና መክፈቻው ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለፁት፤ ቢሮው ለባለድርሻ አካላት አዲሱን እሳቤ ለማሰረፅና ተቀናጅቶ በመስራት ወደ ተግባር ለማውረድ የተለያዩ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛል።
በዚህም ከቴክኒክና ሙያ ስልጠና፣ ከሥራ ዕድል ፈጠራ እና ከኢንዱስትሪ ሠላም አኳያ የተቀረፁ እሳቤዎች ወደ መሬት ወርደው የልማት ፀጋዎቻችንን አልምቶ መጠቀም በሚያስችል አግባብ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሚኒስቴር ዴኤታ አማካሪ አቶ አዝመራ ከበደ የተቋሙን አዲስ እሳቤ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ የዘርፉ የአዲሱ እሳቤዎች ዓላማ ከሰው ሃይልና ቴክኖሎጂ ልማት፣ ከሥራ ዕድል ፈጠራ እና ከአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት አኳያ ያሉ ማነቆዎችን በመፍታትና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የታለመውን ሀገራዊ ልማትና ብልጽግናን እውን ማድረግ ነው፡፡
ስለሆነም ባለድርሻ አካላት የእሳቤዎቹን ዓላማና ግብ በአግባቡ ተረድተው ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ታስቦ ስልጠው መዘጋጀቱን የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል፡፡
ይህንን ተከትሎ ቢሮው የስልጠና ተሳታፊ ከሆኑት ባለድርሻ አካላት በአዲሱ እሳቤ የተመላከቱ ተግባራትን መሬት በማስነካትና ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ለማምጣትና ሰፊ ርብርብ ለማድረግ መግባባት መፍጠር ችሏል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 21/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ከደቡብ ኮርያ የመጣ የቮለንተር ቡድን በኮሌጁ ሙያዊ ልምድ ልውውጥ አካሄደ::
ቡድኑ ከWitness of christ Church ጋር በመተባበር በሚያደርገው ድጋፍ አማካኝነት በኮሌጁ ተገኝቶ ልምድ ልውውጥ ያደረ ሲሆን በዚህም ከኮሌጁ ጋር በትብብር ለመስራት በሚችሉበት አግባብ ዙሪያ ከኮሌጁ ሀላፊዎች ጋር ተወያይተዋል::
በተጨማሪም የቮለንተር ቡድኑ በWitness of christ Church አጫጭር ስልጠና ተማሪዎች አማካኝነት በኮሌጁ የተሰሩ ስራዎችን የተመለከቱ ሲሆን የኮሌጁን የት/ትና ስልጠና ወርክ ሾፖችንም ተዘዋዉረው ተመልክተዋል::
ይህ ከደቡብ ኮርያ የመጣው ቡድን በውስጡ ከተለያዩ ቴክኒካል ሞያዎች የተወጣጡ ባለሙያዎችን ያቀፈ ሲሆን በቀጣይ ከሙያዊ ድጋፍ ጀምሮ ከተቋሙ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችላቸውን ቆይታም አድርገዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ሰኔ 20/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን ቢሮን የ2016 በጀት አመት የማጠቃለያ ዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ።
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን የ2016 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጸም የገመገመ ሲሆን በመድረኩም የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢና አባላት እንዲሁም የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የማኔጅመንት አባላት ተገኝተውበታል።
የድሬደዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የ2016 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል በተለይም በክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ እሳቤ ቢሮው የሚመለከታቸውን የባለድርሻ አካላት በማስተባበር የተገኘው ውጤት በጥሩ ጎን የታየ ሲሆን በቀጣይም ለዜጎች የሥራ ዕድል የመፍጠሩ ስራ ላይ የታየው በቅንጅት መስራት ተጠናክሮ መቀጥል እንዳለበት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 18/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
