ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 063
Подписчики
Нет данных24 часа
-77 дней
+230 день
Архив постов
የማንሠራራት ቀን ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሠራራት ኢትዮጵያ ተነሥታለች፡፡ ከእንግዲህ ወደኋላ አትመለስም፡፡ ይሄ የማንሠራራት ጉዞዋ በዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የታገዘ መሆን አለበት፡፡ በተለይም በማዕ
የማንሠራራት ቀን ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሠራራት ኢትዮጵያ ተነሥታለች፡፡ ከእንግዲህ ወደኋላ አትመለስም፡፡ ይሄ የማንሠራራት ጉዞዋ በዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የታገዘ መሆን አለበት፡፡ በተለይም በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በግብርና፣ በአምራችነት እና በአይሲቲ ዘርፎች የላቁ ውጤቶችን እያስመዘገብን መቀጠል አለብን፡፡ ለዕድገታችን አጋዥ የሚሆን ሀብት መፍጠር እና ገቢ መሰብሰብ ይገባናል፡፡ ዕድገታችን የሚያመነጨውን ገቢና ሀብትም በሚገባ ሰብስበንና ቆጥበን ለብልጽግና ግባችን መጠቀም አለብን፡፡ የጀመርነውን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በማሣለጥና በማሳካት የኢትዮጵያ ማንሠራራት ወደ ዘላቂ የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲለወጥ እናደርጋለን፡፡

🎉📢 የታላቁ ሕዳሴ ግድባችንን መጠናቀቅ የድል ብስራት፣ በቀጥታ ስርጭት በነጻ ይከታተሉ!! የዓመታት ሕልማችን በይፋ ዕውን የሚሆንበት ታላቅ ታሪካዊ የድል ብስራት ነገ ዻጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም
🎉📢 የታላቁ ሕዳሴ ግድባችንን መጠናቀቅ የድል ብስራት፣ በቀጥታ ስርጭት በነጻ ይከታተሉ!! የዓመታት ሕልማችን በይፋ ዕውን የሚሆንበት ታላቅ ታሪካዊ የድል ብስራት ነገ ዻጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ከኢንተርኔት ክፍያ ነጻ በቀጥታ ስርጭት ይከታተሉ። ⏰ በኢቢሲ እና ፋና ዩቲዩብና ፌስቡክ ገጾች ከጠዋቱ 12:00 እስከ 4:00 🔴 EBC: https://www.youtube.com/@EBCworld 🔴 FANA: https://youtube.com/@fanamediacorporation?si=Mpj6YVepBdUYURNs #GreatEthiopianRenaissanceDam #Ethiopia #Ethiotelecom

የሀገር ፍቅር ዕንባ 🇪🇹

የእመርታ ቀን እመርታ ለዘላቂ ከፍታ የወረስነው ዕዳ ብዙ፤ የምንጓዝበት መንገድ ረዥም፤ ሕዝባችንም ፍላጎት ሰፊ ነው፡፡ ቀስ በቀስ በሚደረግ የተለምዶ ጉዞ ወደምንፈልገው የብልጽግና ምእራፍ አንደርስም፡
የእመርታ ቀን እመርታ ለዘላቂ ከፍታ የወረስነው ዕዳ ብዙ፤ የምንጓዝበት መንገድ ረዥም፤ ሕዝባችንም ፍላጎት ሰፊ ነው፡፡ ቀስ በቀስ በሚደረግ የተለምዶ ጉዞ ወደምንፈልገው የብልጽግና ምእራፍ አንደርስም፡፡ ያለን አማራጭ አንዳንድ እርከኖችን መዝለል ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ፈጠራና ፍጥነት ወሳኞች ናቸው፡፡ ከተለመደው መንገድ ወጣ ማለት፣ ከተለመደው ጊዜ በላይ መሥራት፣ ከተለመደው ዋጋ በላይ መክፈል ያስፈልገናል፡፡ ዓላማችን ከአንድ ምዕራፍ ወደ ሌላ ምዕራፍ መሻገር አይደለም፡፡ ከትናንት ዘለን ወደ ነገ መድረስ ነው፡፡ Guyyaa Tarkaanfannaa Tarkaanfannaan Olka'insa Waaraaf Idaan dhaalle baay'ee, daandiin irra imallu dheeraa, fedhiin uummata keenyaas bal'aadha. Imala suutaa barame sanaan boqonnaa badhaadhinaa barbaadnu bira hin geenyu. Filannoon qabnu gulantaawwan tokko tokko utaaluudha. Kanaaf ammoo kalaqniifi saffisni murteessitootadha. Daandii baramerraa bahuu, yeroo baramee ol hojjechuu, gatii baramee ol kanfaluu nubarbaachisa. Kaayyoon keenya boqonnaa tokkorraa gara boqonnaa kanbiraatti cehuu miti. Kaleessarraa utaallee gara borii gahuudha.

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ በተዋቀረው አዲስ የኢንተርፕራይዝ አደረጃጀት እና የኮሌጁ የምርት ሂደት አተገባበር ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ:: ተቋሙ በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ መሰረት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ከትምህርትና ስልጠናው ጎን ለጎን ምርትና ምርታማነት ላይ በሰፊው እንዲሰሩ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የራሱን ውስጠ ገቢ የሚያሳድግበትን አሰራር ዘርግቶ ወደ ትግበራ ለመግባት በሂደት ላይ ሲሆን በዛሬው እለትም በኮሌጁ ለሚገኙ የፑል አመራር አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ተችሏል:: ኮሌጁ ከተለመደው የአሰራር ሂደት የተለየና በነፃነት ቢዝነሱ ላይ ትኩረት አድርጎ መንቀሳቀስ የሚችል አዲስ የኢተርፕራይዝ አደረጃጀት ማዋቀሩን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም ኢንተርፕራይዙ ከህግ አንፃር ማሙላት የሚገባውን ነገር በሙሉ አሟልቶ የተቋቋመ መሆኑንና በቀጣይ ኢንተርፕራይዙን ከኮሌጁ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛልም ብለዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም በቀጣይ በተቋሙ የሚኖረን የምርት ሂደት አሰራር ሁለት ጉዳዮችን ታሳቢ ያደርጋል ያሉ ሲሆን የመጀመርያው የተቋሙ ቀጣይነት ያለው ገቢ ሊያመንጭ የሚችል አቅም መፍጠር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በምርት ሂደት ውስጥ የሚሳተፉ አሰልጣኝ መምህራንን ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ ማስቻል በመሆኑ ሁለቱንም እጣጥሞ ማስኬድ ከኛ ይጠበቃልም ብለዋል:: አዲስ የተዋቀረውን የኢንተርፕራይዝ አደረጃጀት ጨምሮ የኮሌጁ የምርት ሂደት አተገባበር ላይ ያተኮረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለመድረኩ ተሳታፊዎች የሰጡት የኮሌጁ የምርት ክፍል ሀላፊ አሰልጣኝ መምህር ነዋይ ይልማ ሲሆኑ ባቀረቡት ሰነድም ከዚህ ቀደም የነበረው የምርት ሂደት ተገቢውን የህግና የአስራር ሂደት የተከተለ ባለመሆኑ በሚፈለገው አግባብ ውጤት ማምጣት እንዳልቻለ ያመላከቱ ሲሆን አሁን ላይ ተሻሽሎ በፀደቀው የውስጥ አሰራር መመሪያ መሰረት ወደ ተቋሙ የሚመጡ ምርትና አገልግሎቶች በተቀመጠው የአሰራር ሂደት ውስጥ እንዲያልፉ የሚደረግበት አግባብ መዘርጋቱንም ገልፀዋል:: በአጠቃላይ በመድረኩ በቀጣይ ኢንተርፕራይዙን ለመማጠናከርና ውጤታማ እንዲሆን ለማስቻል ምን ማድረግ አለብን በሚል በመድረኩ በርካታ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ለቀጣይ ስራዎች የጋራ መግባባት የተያዘበት መድረክም ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጷጉሜ 1/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 በጀት ዓመት የእቅድ ስምምነት ፊርማ ሥነ-ስርዓት በዛሬው እለት አካሄደ:: በእቅድ ስምምነቱ ላይ የኮሌጁ ዲን የሆኑት አቶ ታደለ አሰፋ በስራቸው ከሚገኙ ዋና ስራ ሂደቶች እና ደጋፊ ስራ ሂደቶች ጋር የ2018 በጀት አመት የእቅድ ስምምነትን ፊርማ በመፈራረም ርክክብ አድርገዋል:: በተጨማሪም በኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት ሀላፊ ም/ዲን የሆኑት አቶ ኤሊያስ አህመድ በስራቸው ከሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች፣የስልጠና አስትባባሪዎች እና የክፍል ተጠሪዎች ጋር የ2018 የስልጠና ዘመን የእቅድ ስምምነትን ፊርማ በመፈራረም ርክክብ አድርገዋል:: እንዲሁም በኮሌጁ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዋና ስራ ሂደት ሀላፊ ም/ዲን የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ በስራቸው ከሚገኙ የጥናትና ቴክኖሎጂ ሽግግር አስተባባሪ እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አስተባባሪ ጋር የ2018 በጀት ዓመት የእቅድ ስምምነትን ፊርማ በመፈራረም ርክክብ አድርገዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጷጉሜ 1/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኅብር ቀን ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ ኢትዮጵያ በብዙ ጸጋዎች የተሞላች ሀገር ናት፡፡ እነዚህ ጸጋዎቿ የተለያዩ ሳይሆኑ ልዩ ልዩ ናቸው፡፡ የባህል፣ የቋንቋ፣ የታሪክ፣ የሥልጣኔ፣ የእምነት፣ የጾታ፣ የ
የኅብር ቀን ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ ኢትዮጵያ በብዙ ጸጋዎች የተሞላች ሀገር ናት፡፡ እነዚህ ጸጋዎቿ የተለያዩ ሳይሆኑ ልዩ ልዩ ናቸው፡፡ የባህል፣ የቋንቋ፣ የታሪክ፣ የሥልጣኔ፣ የእምነት፣ የጾታ፣ የአመለካከት፣ ወዘተ. ብዝኃነት ያለንን የጸጋ ብዛት የሚያመለክት ነው፡፡ ብዝኃነት የኢትዮጵያ ታሪኳ እና መልኳ ነው፡፡ Guyyaa Daneessummaa Daneessummaa, Faaya Itoophiyaa Itoophiyaan biyya kennaawwan hedduudhaan guutamtedha. Kennaawwanshee kunneen kan gargar bahan utuu hin ta'iin adda addadha. Daneessummaan aadaa, afaanii, seenaa, qaroominaa, amantaa, saalaa,  ilaalchaa kkf. heddumina kennaa qabnu kan agarsiisanidha. Daneessummaan Itoophiyaadhaaf seenaafi bifa isheeti.

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ሶስተኛ ዙር ትግበራ አራተኛ ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ተካሄደ። በዚህም የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ወጣቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና ወስደው በስራ ላይ ልምምድ የገጠሟቸው ገጠመኞች ላይ በመወያየት እርስ በእርስ አቅም የሚገነባቡበት መድረክ ተፈጥሮላቸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጳጉሜ 1/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የጽናት ቀን ጽኑ መሠረት ብርቱ ሀገር ኢትዮጵያ ብልጽግናዋን የምታረጋግጠው መሠረቷን ለማጽናት በሚችሉ ብርቱ እጆች ነው፡፡ በሁሉም ዘርፎች በምናደርገው ተጋድሎ የኢትዮጵያን መሠረት እናጸናለን፡፡ ለማና
የጽናት ቀን ጽኑ መሠረት ብርቱ ሀገር ኢትዮጵያ ብልጽግናዋን የምታረጋግጠው መሠረቷን ለማጽናት በሚችሉ ብርቱ እጆች ነው፡፡ በሁሉም ዘርፎች በምናደርገው ተጋድሎ የኢትዮጵያን መሠረት እናጸናለን፡፡ ለማናቸውም ችግሮች የማትበገር፣ ፈተናዎችን ወደ ዕድል የምትቀይር፣ በመጪው ዘመንም ከዓለም ኃያላን ተርታ የምትሰለፍ ብርቱ ሀገር በደምና በላብ እንገነባለን፡፡ Guyyaa Ciminaa Bu'ura Cimaa Biyya Jabduu Itoophiyaan badhaadhinashee kan mirkaneessitu harkawwan jajjaboo bu'urashee cimsuu danda'aniinidha. Qabsoo gama hundumaan taasifnuun bu'ura Itoophiyaa ni cimsina. Biyya jabduu rakkoowwan kamiifuu hin sarmine, qormaatawwan carraatti jijjiirtu, baroota dhufanittis tarree biyyoota gurguddoota addunyaa hiriirtu, dafqaafi dhiigaan ni ijaarra.

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ " ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሶስተኛ ዙር ትግበራ የአራት ወራት አተገባበርን በተመለከተ ከቢሮው አስተባበሪዎች፤ ከወረዳ አንድ ማዕከል አመራሮች እና ባለሞያዎች ጋር የውይይት እና የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ አካሄደ፡፡ በዚህም የፕሮግራሙ ሶስተኛ ዙር ትግበራ የአራት ወራት የተከናወኑ ተግባራትን የሚመለከታቸው የቢሮው አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም የወረዳ ሥራ ክህሎት ማስተባበሪያዎች በተገኙበት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎባቸዋል በተለይም የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ወጣቶች በኢንደስትሪዎች ላይ ባለፉት አራት ወራት የነበረውን የሥራ ላይ ልምምድ የተሰሩ ሥራዎች አፈጻጸም ላይ ሁሉም የወረዳ አንድ ማዕከላት አፈጻጸማቸው ቀርቦ ሰፊ ውይይት በማድረግ በቀጣይ መሠራት በሚገባቸው ሥራዎች ላይ መወያየት ተችሏል፡፡ በመድረኩም ላይ በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተገኝተው በቢሮ እና በአንድ ማዕከላቱ መናበብ ለተሰሩ አበረታች ሥራዎች ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይ ወራት የሚከናወነውን ውጤታማ ሥራ ወጥነት ባለው የዕቅድና ሪፖርት መናበብ አጠንክሮ በማስቀጠል ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በመስራት ውጤት ለማምጣት ሁሉም ተረባርቦ ሊሰራ እንደሚገባው አሳስበዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ነሀሴ 30/2017 ዓ.ም

photo content
+8

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ለ120 ተማሪዎች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፤ ነሐሴ 30 ቀን 2017 ዓ.ም – የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ መጪውን የ2018 የትምህርት ዘመን ምክንያት በማድረግ 120 ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የትምህርት መርጃ ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ። ቢሮው በርክክቡ ወቅት ደብተር፣ እስክሪብቶ፣ እርሳስና ሌሎች ቁሳቁሶችን ያካተተ 87,434 ብር የሚያወጣ ድጋፍ ለአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እና በቢሮው የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አሚን አብዱላሂ አስረክበዋል ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት

photo content
+2