1 064
Подписчики
-124 часа
-47 дней
+530 день
Архив постов
ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለሶስተኛ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠና ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የምርቃት እና የማጠቃለያ መድረክ ተካሄደ
" ብቃት ፣ ክህሎት ፣ ስኬት " በሚል መሪ ሀሳብ ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሶስተኛ ዙር ማጠቃለያ መርሀ ግብር በዛሬው እለት ተካሂዷል።
በዚሁ መርሀ-ግብር ላይም በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታቸው ፕሮጀክቱ በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን መቀጠል ያልቻሉ ወጣቶችን ለ 12 ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና በመስጠት በአስተዳደሩ ባሉ ድርጅቶች ላይ ለስድስት ወራት የስራ ላይ ልምምድ አድርገው በቋሚነት ተቀጣሪ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል ።
አቶ ሮቤል አክለውም ወጣቶች በተለያዩ ፋብሪካዎች ውስጥ ተቀጥረው ስራቸውን በትጋት እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቀው የስራ ባህላቸውን የቀየረ ኢንዱስትሪዎችም በዳበረ ተወዳዳሪ የሰው ኃይል እንዲመሩ ማድረግ ያስቻለ ፕሮጀክት መሆኑን ነው አቶ ሮቤል በእለቱ ያስታወቁት ።
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ እንዳሉት በብቃት ፕሮጀክት ፕሮግራም እንደ ሀገር 60 ሺህ 399 ወጣቶች ተመዝግበው ከ 54ሺ በላይ እንዳጠናቀቁና ለ 52 ሺህ ወጣቶች ደግሞ ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን ገልፀው በድሬዳዋ አስተዳደርም በሶስት ዓመታት 2 ሺህ 846 ወጣቶች ታቅፈው ከ 2 ሺህ 700 በላይ የሚሆኑት እንደተመረቁና ከነዚም መካከል 60 በመቶ ወጣት ሴቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል ።
©️ DGC የካቲት 7/2018
"ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ለሶስተኛ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠና ላጠናቀቁ 946 ሰልጣኞች የምርቃት እና የማጠቃለያ መድረክ አካሄደ።
በመርኃ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ እንዳሉት በብቃት ፕሮጀክት ፕሮግራም እንደ ሀገር 60ሺ 399 ወጣቶች ተመዝግበው ከ54ሺ በላይ የሚሆኑት ያጠናቀቁ እንዲሁም ለ52ሺ ወጣቶች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን ገልፀዋል።
በድሬዳዋ አስተዳደርም በሶስት ዓመታት 2ሺ 846 ታቅፈው ከ2ሺ 700 በላይ የሚሆኑት የተመረቁ እንደሆነ አመላክተዋል። ከእነዚም መካከል 60 በመቶ ወጣት ሴቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ሚንስትር ዴኤታው አያይዘው ዛሬ የተመረቁት 946 ወጣቶች ብቁ ሆነው መውጣታቸው ትልቅ ተስፋ ነው ያሉ ሲሆን ስኬት የሚገኘው በትምህርት ቤት ብቻ ሳይሆን በስራ ቦታ ትጋት ነው ብለዋል።
የግሉ ዘርፍም ወጣቶችን ተቀብሎ እውቀት በማጋራት የስራ እድል በመፍጠር ሀብታቸውን ሳይሰስቱ በራቸውን ከፍተው ስለከፈቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዳሉት ፕሮጀክቱ በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን መቀጠል ያልቻሉ ወጣቶችን ለ12 ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና በመስጠት በአስተዳደሩ ባሉ ድርጅቶች ላይ ለስድስት ወራት የስራ ላይ ልምምድ አድርገው በቋሚነት ተቀጣሪ ማድረግ እንደሆነ አስረድተዋል።
ወጣቶች በተለያዩ ፋብሪካዎች ውስጥ ተቀጥረው ስራቸውን በትጋት እያከናወኑ የሚገኙ እንደሆነ ገልፀው የስራ ባህላቸውን የቀየረ ኢንዱስትሪዎችም በዳበረ ተወዳዳሪ የሰው ኃይል እንዲመሩ ማድረግ ያስቻለ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።
©️ DireTvአማርኛ | የካቲት 07 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
"ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ለሶስተኛ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠና ላጠናቀቁ 946 ሰልጣኞች የምርቃት እና የማጠቃለያ መድረክ አካሄደ።
በመርኃ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ እንዳሉት በብቃት ፕሮጀክት ፕሮግራም እንደ ሀገር 60ሺ 399 ወጣቶች ተመዝግበው ከ54ሺ በላይ የሚሆኑት ያጠናቀቁ እንዲሁም ለ52ሺ ወጣቶች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን ገልፀዋል።
በድሬዳዋ አስተዳደርም በሶስት ዓመታት 2ሺ 846 ታቅፈው ከ2ሺ 700 በላይ የሚሆኑት የተመረቁ እንደሆነ አመላክተዋል። ከእነዚም መካከል 60 በመቶ ወጣት ሴቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ሚንስትር ዴኤታው አያይዘው ዛሬ የተመረቁት 946 ወጣቶች ብቁ ሆነው መውጣታቸው ትልቅ ተስፋ ነው ያሉ ሲሆን ስኬት የሚገኘው በትምህርት ቤት ብቻ ሳይሆን በስራ ቦታ ትጋት ነው ብለዋል።
የግሉ ዘርፍም ወጣቶችን ተቀብሎ እውቀት በማጋራት የስራ እድል በመፍጠር ሀብታቸውን ሳይሰስቱ በራቸውን ከፍተው ስለከፈቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዳሉት ፕሮጀክቱ በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን መቀጠል ያልቻሉ ወጣቶችን ለ12 ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና በመስጠት በአስተዳደሩ ባሉ ድርጅቶች ላይ ለስድስት ወራት የስራ ላይ ልምምድ አድርገው በቋሚነት ተቀጣሪ ማድረግ እንደሆነ አስረድተዋል።
ወጣቶች በተለያዩ ፋብሪካዎች ውስጥ ተቀጥረው ስራቸውን በትጋት እያከናወኑ የሚገኙ እንደሆነ ገልፀው የስራ ባህላቸውን የቀየረ ኢንዱስትሪዎችም በዳበረ ተወዳዳሪ የሰው ኃይል እንዲመሩ ማድረግ ያስቻለ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።
©️ DireTvአማርኛ | የካቲት 07 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
+2
#አሁን
#Happening_Now
ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሶስተኛ ዙር ማጠቃለያ መርሃ-ግብር
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ
የካቲት 7/2018 ዓ.ም
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
#በአጭር ጊዜ የራስዎን ድርጅት መክፈት ይፈልጋሉ?
#ፈጠራ እና ውበት ያላቸውን የEPOXY ምርቶችን አምርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ገበያው ላይ ተፈላጊ መሆን ከፈለጉ አንድ አንጋፋ ኮሌጅ ልጠቁማችሁ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
#በተመጣጣኝ ዋጋ እጀ ወርቅ እናደርግዎታለን ይምጡ ይሰልጠኑ ባለሙያ ይሁኑ
#አድራሻችን ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ወደ ኤርፖርት በሚወስደው መንገድ ላይ እንገኛለን
የመራጮች ምዝገባ የካቲት 28 ይጀምራል ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
****
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጀመር አስታወቀ።
ቦርዱ እስካሁን ያከናወናቸውን የቅድመ ምርጫ ሥራዎችና ተያያዥ ውሳኔዎችን አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ በመግለጫቸው እንዳስታወቁት፣ ቀደም ሲል የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 7 እስከ መጋቢት 7 ቀን ለማከናወን ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ ቀሪ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ለማጠናቀቅ ሲባል የምዝገባው መጀመሪያ ቀን ወደ የካቲት 28 እንዲራዘም ተደርጓል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የእጩዎች ምዝገባ ማብቂያ ጊዜም ወደ የካቲት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ተራዝሟል።
109 ቀናት የቀሩት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ገለልተኛ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ቦርዱ ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዋ አስታውቀዋል።
©️Ethiopian Broadcasting Corporation
+5
በድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ፈጣሪና ስራ ፈላጊ የሆኑ ወጣቶችን ለማበረታታት በቀጣይ በትኩረት እንደሚሰራ ተገለፀ
በተባበሩት መንግስታት የኢኮኖሚክ ኮሚሽን ፎር አፍሪካ ልዑካን ቡድን በዛሬው እለት በድሬዳዋ አስተዳደር ስላለው የኢኮኖሚ እና የወጣቶች የስራ አጥነት ሁኔታ እንዲሁም ከፍልሰት ጋር ተያይዞ የተለያዩ ጥናቶች በማካሄድ በቀጣይ ለችግሮቹ መፍትሄ የሚሆኑ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ ውይይት አካሂደዋል ።
በእለቱም የስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዲሱ እሳቤ ምን እንደሚመስል ፣ የስራ እድል ፈጠራ ስራዎች ከዚህ ቀደም የነበረውና አሁን ላይ በአዲስ መልክ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ፣ የኢንደስትሪ ሰላም ግንኙነት አዳዲስ እይታዎች እንዲሁም ደግሞ የተሻሻለው የወጣቶች ፖሊሲ ይዟቸው የመጣው አዳዲስ ሀሳቦች ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት መደረጉን የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል ።
በድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ፈጣሪ የሆኑ እና ስራ ፈላጊ ወጣቶችን እንዲሁም ደግሞ በከተማዋ ያሉትን ፋብሪካዎች መመልከታቸውን በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የሶሻል ዲቪዥን አማካሪ የሆኑት አቶ ጀላል አብዱለጢፍ ተናግረው በቀጣይም በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራዎች ላይ በርካታ ስራዎችን ለመስራት እቅድ እንዳላቸውም አስታውቀዋል።
©️ DGC የካቲት 4/2018
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+3
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ SIFA ፕሮጀክት እንዲሁም በኮሌጁ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን የScience, Technology and Innovation Week 2026 ኤግዝቪሽን ላይ እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡
የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ከFeb 11-15/2026 በአዲስ አበባ እየተካሄደ ሲሆን በዚህ የመሪዎቸ ስብሰባ ጎን ለጎን
የScience, Technology and Innovation Week 2026, Exhibition ከFeb 10 - 11, 2026 በSkylight Hotel በይፋ የተከፈተ ሲሆን በዚህ ኤግዚቪሽን ላይም የኮሌጁ ልኡክ ቡድን ከተለያዩ አለማት ስብሰባውን ለመሳተፍ አዲስ አበባ ለሚገኙ እንግዶች በኮሌጁ እንዲሁም በ SIFA ፕሮጀክት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን የማስተዋወቅ ስራዎች እየሰራ ይገኛል።
በትናንትናው እለት የተጀመረው መርሃ ግብር "Shaping African's Future through AI, Science, Technology and Innovation" በሚል መሪ ቃል የተጀመረ ሲሆን በዚህም ረገድ ኮሌጁ ያለውን ልምድና ተሞክሮ ኤግዚቪሽኑን ለመታደም ለመጡ እንግዶች አቅርቧል።
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
የካቲት 4/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ለኢኮኖሚ ዕድገት ዋነኛው ሞተርና ለብቁ የሰው ኃይል ግንባታ መሠረት ነው።
በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ወጣቶች አስፈላጊ ክህሎቶችን እንዲታጠቁ በማድረግ፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለኢንዱስትሪ ሽግግሩ ስኬት ጽኑ መሠረት በመጣል ላይ ትገኛለች።
በኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና የሚሰጥባቸው ዘርፎች የሚከተሉት ናቸው፦
1. ማኑፋክቸሪንግና ኢንዱስትሪ
2. ኮንስትራክሽንና መሰረተ-ልማት
3. መረጃና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT)
4. ንግድ፣ ፋይናንስና አገልግሎት
5. ግብርናና ተፈጥሮ ሀብት
6. ጤናና ማኅበራዊ አገልግሎት
#EthiopianBroadcastingCorporation #technical #vocationaltraining
"ቤተሰባዊነትን ያስቀደመ ተቋም ተልዕኮውን ከግብ ለማድረስ የሚያደርገው ጉዞ ቀልጣፋና ውጤታማ ይሆናል"
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
በዛሬው ዕለት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የመረዳጃ ዕድር ይፋዊ ምስረታ አንደኛ አመት ምክንያት በማድረግ መርሃግብር ተካሄደ።
በዚህ መርሃግብር ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው አመራሩ እና ሠራተኛው በደስታና በሃዘን የሚገጥማቸውን የህይወት ገጠመኞች በመረዳዳትና በመደጋገፍ የሚያደርጉት መተጋገዝ በቀጥታ በመንግስታዊ ተልዕኮ መፈጸም ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ እንዳለው ገልጸው ቢሮውም ይህን ቤተሰባዊነት የሚያጠናክር ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የመረዳጃ ዕድር ኮሚቴ ተወካዮች በበኩላቸው የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ማኔጅመንታቸው ዕድሩን የሚያጠናክሩ የተለያዩ ድጋፎችን ስላደረጉ እና ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ስላበረከቱ አመሥግነዋል።
በማጠቃለያውም ባለፈው አንድ አመት የተከናወኑ ተግባራትና የፋይናንስ ሪፖርት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት የተካሄደ ሲሆን በተለያየ ምክንያት በተጓደሉ የመረዳጃ ዕድሩ ኮሚቴ አባላት ምትክ አዲስ የኮሚቴ አባላትን በመምረጥ መርሃግብሩ ተጠናቋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 1/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
🔎የሙያ ብቃት ምዘና፡ ለላቀ ክህሎትና ለተሻለ የሥራ ዕድል!
አግባብነት ያለው፣ ጥራቱን የጠበቀና ፍትሀዊ የሥልጠና ሥርዓት በመዘርጋት ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ማፍራት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዋነኛ ተልዕኮ ነው፡፡
ይህንን ተልዕኮ ለማሳካት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ሰልጣኞች የቀሰሙትን እውቀትና ክህሎት በተግባር የሚያረጋግጡበት የሙያ ብቃት ምዘና ሥርዓት ቀዳሚውን ድርሻ ይይዛል፡፡
በመሆኑም፣ ሰልጣኞች ብቃታቸውን አረጋግጠው ወደ ሥራው ዓለም በልበ ሙሉነት እንዲቀላቀሉ ለማስቻል «ሀገር አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የሙያ ብቃት ምዘና፣ እውቅናና የምስክር ወረቀት አሰጣጥ የተሻሻለ መመሪያ ቁጥር 912/2014» በሥራ ላይ ውሏል፡፡
🕹የሙያ ብቃት ምዘና ምንድን ነው❓
• ምዘና ማለት አንድ ተመዛኝ በሙያ ደረጃው የተቀመጡ መስፈርቶችን ማሟላቱን በንድፈ-ሀሳብና በተግባር በማረጋገጥ የብቃት ማረጋገጫ የሚሰጥበት ሳይንሳዊ ሂደት ነው፡፡
🕹የምዘናው ዋና ዓላማ
• የተመዛኞችን ብቃት የሚያረጋግጥ ሥርዓት በመዘርጋት፤ በሙያው የሚተማመን፣ በጥራትና በታማኝነት ለገበያ/ለኢንዱስትሪ የሚቀርብ ብቁ የሰው ኃይል ማፍራት ነው፡፡
♻️ተመዛኞች ሊያውቋቸው የሚገቡ መሰረታዊ መረጃዎች
1️⃣ለምዘና ለመቅረብ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፦
• ተገቢው የሥራ ልምድ ወይም የትምህርት ማስረጃ ማቅረብ፤
• የምዘና መግቢያ ካርድ መያዝ፤
• የሙያ ብቃት ምዘና ስምምነት ቅጽ መፈረም፡፡
2️⃣የምዘና ሂደትና የማለፊያ ነጥብ፦
• በምዘና ማዕከሉ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መመዝገብ፤
• እንደ ሙያው ዓይነትና ደረጃው፣ በክልል ህጋዊ አካላት የጸደቀ ክፍያ መፈጸም፤
📍የማለፊያ ነጥብ፦
➡️በንድፈ-ሀሳብ (Theory): ቢያንስ 55% እና ከዚያ በላይ ማምጣት፤
➡️በተግባር (Practical): የቀረበውን ፕሮጀክት በስታንዳርዱ መሠረት 💯%(ሙሉ በሙሉ) ማከናወን፡፡
3️⃣ዳግም ምዘና (Re-assessment)፦
• በመጀመሪያው ምዘና ስኬታማ ላልሆኑ ተመዛኞች ክፍተታቸውን በሥልጠና በመሙላት፣ ዝግጁ በሆኑበት በማንኛውም ጊዜ ዳግም ማመልከት ይችላሉ።
• ምዘናው የሚከናወነው ቀደም ሲል ባመለከቱበት ሙያና ደረጃ ላይ ብቻ ይሆናል፡፡
4️⃣የምስክር ወረቀት አሰጣጥ፦
• ምዘናውን ባጠናቀቁ በ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ይሰጣል፡፡
• የምስክር ወረቀት ቢጠፋ ወይም ቢበላሽ፣ ህጋዊ ማስረጃ በማቅረብና የአገልግሎት ክፍያ በመክፈል ምትክ ማግኘት ይቻላል፡፡
የካቲት 1/2018 ዓ.ም
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
አዋጁ ምን ይላል?
ክፍል ሁለት
"ብቁ ሠራተኛ፣ ብቁ አሠሪ እና ብቁ ውሳኔ ሰጪ"
በክፍል አንድ ላይ እንደተመለከትነው፣ አዲሱ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 1389/2017 ለዜጎች መብትና ክብር እንዲሁም ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ዋስትና የሚሰጡ አንቀፆችን አካቷል። ከእነዚህም መካከል እጅግ ወሳኝ የሆነው እና የዘርፉን አሰራር ሙሉ በሙሉ የቀየረው "የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (lmis)" ነው።
ለመሆኑ የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ምንድን ነው?
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ከ23 በላይ አገልግሎቶችን ይዞ "ብቁ ሠራተኛ፣ ብቁ አሠሪ እና ብቁ ውሳኔ ሰጪ" በሚል መሪ ሀሳብ ሙሉ በሙሉ በሀገር ልጆች በልፅጎ ሥራ ላይ የዋለ የዲጂታል ስርዓት ነው፡፡
ይህ ስርዓት፤ መረጃን ከውሳኔ፣ ውሳኔን ደግሞ ከስልጠናና ከሥራ ስምሪት ጋር በማስተሳሰር የዜጎችን ተጠቃሚነትና ሀገራዊ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ፋይዳው የማይተካ ነው።
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ፋይዳ
📊 ተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲና ስትራቴጂ ለመንደፍ
• መንግሥት የሥራ ገበያውን ፍላጎት በግምት ሳይሆን በተጨባጭ መረጃ ላይ ተመስርቶ ውጤታማ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን እንዲቀርጽ ያስችለዋል።
🎓 ስልጠናን ከሥራ ጋር ለማጣጣም
• በሥራ ገበያው ውስጥ የሚፈለጉ እውቀትና ክህሎቶችን በመለየት፣ በሠራተኛው አቅም እና በሥራ ገበያው ፍላጎት መካከል ያለውን አለመጣጣም ይቀንሳል።
⚖️ ፍትሃዊ የሥራ መረጃ ለሁሉም ለማድረስ
• ሥራ ፈላጊዎች ስለ ሥራ ዕድሎች እና ስለ ደመወዝ ደረጃ ወቅታዊ መረጃ በፍትሃዊነት እንዲያገኙ በማድረግ ሥራ የማግኘት እድላቸውን ያሰፋል።
🏫 የትምህርትና ስልጠና ስርዓትን ውጤታማነትን ለመደገፍ
• የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ይዘታቸውን ከገበያው ተጨባጭ ፍላጎት ጋር እንዲያጣጥሙ በማድረግ የተመራቂዎችን የሥራ አጥነት ምጣኔ ይቀንሳል።
💰 መረጃን መሰረት ያደረገ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ
• ባለሀብቶች ኢንቨስት ከማድረጋቸው በፊት ስለ ሠራተኛ አቅርቦትና የክህሎት ክፍተቶች ግልጽ መረጃ እንዲያገኙ ያግዛል።
🔍 የሥራ ገበያ ግልጽነት
• ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ተደራሽ በማድረግ በሥራ ገበያው ውስጥ ግልጽነት እንዲሰፍን ያደርጋል።
📈 የሥራ ገበያ ለውጦችን መከታተል
• የሥራ አጥነት መጠንን፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እድገትን እና የዘርፍ ለውጦችን በየጊዜው ለመከታተል ያስችላል።
አዋጁ ስለ የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ምን ይላል ❓
አዲሱ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 1389/2017 ስርዓቱን በተመለከተ የሚከተለውን ደንግጓል፦
1️⃣ሚኒስቴሩ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገልግሎት ለመስጠት የተዘረጋውን የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ተግባራዊ ያደርጋል፣ አፈጻጸሙንም ይከታተላል߹ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ቋት ያደራጃል߹ እንዳስፈላጊነቱ ያሻሽላል ወይም አዲስ ስርዓት ያለማል፡፡
2️⃣ማንኛውም የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አገልግሎት በሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ውስጥ ማለፍ እና መረጃው በአግባቡ መያዝ ይኖርበታል፡፡
📢 ስለ አዋጁ ዝርዝር መረጃ ይፋዊ ገፆቻችንን ይከታተሉ፡፡
ለተጨማሪ መረጃና አስተያየት
📞 9138 ነፃ የስልክ መስመር ወይም
📧 info@mols.gov.et ይጠቀሙ።
"ዘመናዊ አሰራር ለዜጎች ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት!"
ህጋዊና ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት፤ ለሁለንተናዊ ተጠቃሚነት!
#SafeMigration #Proclamation1389/2017
የካቲት 1 /2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtT
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የብልፅግና ህብረት የ2018 በጀት አመት የሁለተኛ ሩብ አመት ኮንፈረንስ ተካሄደ።
በተካሄደው ኮንፈረንስ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዳሉት የብልጽግና ህብረቱ ባለፉት ስድስት ወራት በርካታ የፖለቲካ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀው በተለይ ደግሞ ከመንግስት ሥራ አፈፃፀም ጋር በተያያዘ የተገኘው ውጤታማ አፈጻጸም በጥምረት መቅረቡ ፖለቲካው ህብረተሰቡን የሚጠቅም ተጨባጭ ስራ ለመስራት ወሳኝ ሚና እንዲጫወት አድርጎታል ብለዋል።
የብልጽግና ህብረቱ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታቸው አክለው በአስተዳደሩ ትኩረት የተሰጠውንና የቢሮው ዋነኛና ተቀዳሚ ተልዕኮ የሆነውን ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ጉዳይ አባላት ውጤት ሊያስገኝ የሚችልን ስራ በመስራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በግንባር ቀደምነት ልንሰለፍ ይገባል ብለው አባላት በመጪው ሀገራዊ ምርጫ በንቃት እንዲሳተፉና ምርጫው ውጤታማና የተሳካ እንዲሆን የአባላት ሚና የላቀ መሆኑን አሳስበዋል።
በኮንፈረንሱ ፕሮግራም ላይ የብልጽግና ህብረቱ የስድስት ወር የዕቅድ ክንውን ሪፖርት እና የቀጣይ ስድስት ወር ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት በአባላቱ በሙሉ ድምፅ በማጽደቅ ኮንፈረንሱ ተጠናቋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 30/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
