1 076
Подписчики
+224 часа
+37 дней
+230 день
Архив постов
ለመላ የክርስትና እምነት ተከታዮች
እንኳን ለስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
መልካም በዓል!
****
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ
"መጋቢት 24 የድሬዳዋን ልዕልና አረጋግጧል!"
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት የሚዘክር ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በድሬዳዋ አስተዳደር ተካሂዷል።
የሰልፉ ተሳታፊ የሆኑ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች እንዳሉት መጋቢት 24 የሃገራችን ተምሳሌታዊ ጉዞ እና የተመዘገቡ ስኬቶች መነሻ ነዉ፤ በለውጡ መንግሥት እየተከናወኑ ያሉ የልማት ተግባራትን በመደገፍ፣ በቀጣይም የተሻለ ስራ እንዲሰራ ከመንግሥት ጋር በትብብር እንደሚሰሩ የሚያረጋግጡ መልዕክቶችነም አስተላልፈዋል።
ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሃገር!
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 1/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የሥራ ማዕከላት ሶስተኛ ሩብ አመት የሥራ አፈጻጸም እና የሶስተኛ ዙር ብቃት ቅጥርን በተመለከተ ከወረዳ ሥራ ማዕከላት አመራሮች እና ባለሙያዎች ጋር የውይይት እና የግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በውስጡ ከሚገኙ ዘርፎች የስራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አንዱ ሲሆን ለዜጎች የስራ እድልን በመፍጠር አሁን ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር ለመቀነስና የስራ ባህልን በማጎልበት የሚያስፈልጓቸውን የሙያና የክህሎት ስልጠናዎች ወስደውና ወደ ስራ እንዲሰማሩ በማመቻቸትና ራሳቸውን ከስራ አጥነት እንዲያላቅቁ በማድረግና በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡
በዚህም የሚመለከታቸው የቢሮው አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም የወረዳ ሥራ ማዕከላት አመራሮችና ባለሙያዎች በተገኙበት በ2018 በጀት አመት ሶስተኛ ሩብ አመት አጠቃላይ የስራ ዕድል ፈጠራ በተለይም በብቃት ፕሮግራም የተሰሩ ስራዎች አፈጻጸም ላይ ሁሉም የወረዳ ሥራ ማዕከላት አፈጻጸማቸው ቀርቦ ሰፊ ውይይት በማድረግ በቀጣይ በአጭር እና በረጅም መሰራት በሚገባቸው ስራዎች ላይ መወያየትና መግባባት መፍጠር ተችሏል፡፡
በመድረኩም ላይ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በቢሮ እና በሥራ ማእከላቱ መናበብ የተሰሩ መልካም ስራዎችን አበረታተው በቀጣይ በተለይ የአካባቢ ፀጋዎችንና ዕድሎችን በየሴክተሩ የመለየት ሥራ በአስተዳደሩ ውስጥ በሶስቱ ዋና ዋና የስራ እድል የመፍጠሪያ የስራ ዘርፎች ማለትም በግብርና በኢንዱስትሪ እና በአገልግሎት ዘርፍ ስራ ፈላጊዎችን ከማሰማራት አንጻር የአካባቢ ጸጋ ናቸው ተብለው የታመነባቸውን የጸጋ አይነቶች እና የመስሪያ ቦታዎችን የመለየት ስራን አጠናክሮ በመስራት ተጨባጭ ስራዎችን በይበልጥ ማስፋትና መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 30/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
+6
ለኢንተርፕራይዞች ስኬትና ዘላቂነት፦ የጀማሪ ኢንተርፕራይዞችን አቅም በመገንባት ውጤታማና ተወዳዳሪ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና እንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በአስተዳደሩ ከተለያዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ::
ለኢንተርፕራዝ አንቀሳቃሾች የአቅም ግንባታ ስልጠናውን የሰጡት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ሀላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ የስልጠናው ዋና አላማ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ውጤታማ፣ ተወዳዳሪና ዘላቂነት እንዲኖራቸው ለማስቻል የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከትንሽ ተነስተው ትልቅ ቦታ ለመድረስ ያላቸውን ራዕይ አጠናክረው በቁርጠኝነት ሊተጉ እንደሚገባም ተናግረዋል::
በእለቱ ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናው በዋናነት.....
- የንግድ ስነ-ምግባር..
- የገበያ ጥናት..
- የፋይናንስ አያያዝ..
- የቴክኖሎጂ ሽግግርና ካይዘን..
- የስራ ፈጠራና የንግድ ኢንኩቤሽን እና..
- የደንበኞች አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና በሰፊው ግንዛቤ የተሰጠበት መድረክም ነበር::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
መጋቢት 30/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የኮሌጁን የቀጣይ 15 አመታት እቅድ ወደ ተግባር ለመቀየር የኢንዱስትሪውና የባለድርሻ አካላት ትልቁን ሚና ሊወስዱ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት አዘጋጅነት ከመጋቢት 23 - 25 ቀን 2026 የሚቆየው በEASTRIP ፕሮጀክት የሚደገፋ የ6 ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የቀጣይ 15 አመት እቅድ የደረሰበትን ግምገማ እና መሪ እቅድ ልማት አውደ ጥናት መርሀ ግብር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት መከናወኑ የሚታወስ ነው፡፡
በዚህ መሰረትም በአውደ ጥናቱ ላይ የተገኙ ግብአቶችን በመጠቀም ከኢንዱስትሪውና ከተለያዩ ባላድርሻ አካላት በሰነዱ ላይ ሃሳብ እና ግብዓት ለማሳባሰብ የሚረዳ መርሃ ግብር በዛሬው እለት ተከናወነ፡፡
በዛሬው እለት ለባድርሻ አካላት የቀረበው ሰነድ ተግባራዊ ሲደረግ በባቡር ኢንዱስትሪ ዘርፍ ኮሌጁን የልህቀት ማእከል የሚያደርግ ስለሆነ ይህንንም አላማ ለማሳካት ኢንዱስትሪውና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ከኮሌጁ ጋር በቅርበት ሊሰሩ እንደሚገባ የሚታመን ነው፡፡
የኢንዱስትሪን ትስስርን ለማሳደግ የኮሌጁ የኢንዱስትሪ አማካሪ ቦርድን ኮሚቴን 50 ፐርሰንት ከኢንዱስትሪው እንዲሆንና ኢንዱስትሪው በቴክኒክና ሙያ ላይ የባለቤትነት ስሜት እንዲፈጠርና ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ላይ አንድ እርምጃ ለማሳደግ ይረዳናል ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ
የኮሌጁ ዲን አያይዘውም ኮሌጁ የሚያሰለጥናቸው ሰልጣኞች ከማስመረቅ በዘለለ ኢንዱስትሪውን ማንቀሳቀስ የሚችሉና የፈጠራ ባለቤት እንዲሆኑ እንዲሁም ኮሌጁ በገቢ እራሱን የቻለ ተቋም እንዲሆን ከኢንዱስትሪወው ጋር ያለን ግንኙነት ማሳደግ ያስፈልጋል፡፡ይህ በዛሬው እለት የሚቀርበው እቅድም ኢንዱስትሪዎች ከኮሌጁ ጋር የሚኖረው ግንኙነት የተሸለ እና ጠንካራ እንዲሆን ያደርገናል ብለወል፡፡
በዛሬው እለት በተከናወነው አውደ ጥናት ላይ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በቀጣይ 15 አመታት ሊደርስበት ያሰበውን የልህቀት ማእከልነት ለኢንዱስትሪና ለተለያዩ ባለ ድርሻ አካላት ያቀረበ ሲሆን በመድረኩ የተገኙ ባለድርሻ አካላትም ኮሌጁ እስካሁን ሲሰራቸው የነበሩና በቀጣይ በስፋት ሊሰራቸው ያሰባቸው ስራዎች ወሳኝና ኮሌጁን በተለየ አይነት መልኩ ወደፊት ሊያራምዱ የሚችሉ ስራዎች በግብአትነት ሰጥተዋል፡፡
በመድረኩ ላይም የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እና የቢሮው ዳይሬክተሮች፣የኮሌጁ የኢንዱስትሪ አማካሪ ቦርድ አባላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 30/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ እየተደረጉ ነው - ኢዜአ አማርኛ https://www.ena.et/web/amh/w/amh_8616480
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን አደረገ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራን የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀም በመገምገም ላይ ሲሆን በዛሬ የከሰዓት ቆይታም በመጀመሪያው ዙር (Wave 1) የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን ከሚተገብሩ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮን አፈፃፀም ገምግሟል።
በግምገማው በቢሮው በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች አፈፃፀም ለሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን አፈፃፀሙን በተመለከተም ከቢሮው የሪፎርም አስፈፃሚ ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት ጋር ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን አደረገ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራን የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀም በመገምገም ላይ ሲሆን በዛሬ የከሰዓት ቆይታም በመጀመሪያው ዙር (Wave 1) የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን ከሚተገብሩ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮን አፈፃፀም ገምግሟል።
በግምገማው በቢሮው በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች አፈፃፀም ለሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን አፈፃፀሙን በተመለከተም ከቢሮው የሪፎርም አስፈፃሚ ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት ጋር ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።
የፋሲካ በዓል ኤግዚቢሽንና ባዛር በድሬዳዋ ተከፈተ
የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛር በድምቀት መካሄድ ጀምሯል።
የአስተዳደሩ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን ዝግጅቱን በይፋ ሲከፍቱ እንደገለጹት፤ እንዲህ ያሉ መድረኮች ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ ብለዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፣ ባዛሩ ለሞዴል ኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር ከመፍጠሩ ባለፈ፣ በበዓል ወቅት የሚታየውን የሸቀጦች ዋጋ ንረት ለማረጋጋት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።
የኤስ.ኦ.ኤስ (SOS) ችልድረን ቪሌጅ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሚካኤል ስንታየሁ፣ ድርጅታቸው የወጣቶችን የሥራ ዕድል ለመደገፍ ከአስተዳደሩ ጋር በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ50 በላይ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች የተሳተፉ ሲሆን የተለያዩ የምግብ ሸቀጦች፣ አልባሳትና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለገበያ ቀርበዋል።
ይህ ኤግዚቢሽንና ባዛር እስከ ፋሲካ ዋዜማ ድረስ ለህዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
©️ DireTvአማርኛ | መጋቢት 29፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
የፋሲካ በዓል ኤግዚቢሽንና ባዛር በድሬዳዋ ተከፈተ
የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛር በድምቀት መካሄድ ጀምሯል።
የአስተዳደሩ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን ዝግጅቱን በይፋ ሲከፍቱ እንደገለጹት፤ እንዲህ ያሉ መድረኮች ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ ብለዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፣ ባዛሩ ለሞዴል ኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር ከመፍጠሩ ባለፈ፣ በበዓል ወቅት የሚታየውን የሸቀጦች ዋጋ ንረት ለማረጋጋት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።
የኤስ.ኦ.ኤስ (SOS) ችልድረን ቪሌጅ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሚካኤል ስንታየሁ፣ ድርጅታቸው የወጣቶችን የሥራ ዕድል ለመደገፍ ከአስተዳደሩ ጋር በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ50 በላይ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች የተሳተፉ ሲሆን የተለያዩ የምግብ ሸቀጦች፣ አልባሳትና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለገበያ ቀርበዋል።
ይህ ኤግዚቢሽንና ባዛር እስከ ፋሲካ ዋዜማ ድረስ ለህዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
©️ DireTvአማርኛ | መጋቢት 29፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
