1 065
مشترکین
-124 ساعت
-47 روز
+530 روز
آرشیو پست ها
በአስተዳደሩ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ እየተደረጉ ነው - ኢዜአ አማርኛ https://www.ena.et/web/amh/w/amh_8616480
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን አደረገ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራን የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀም በመገምገም ላይ ሲሆን በዛሬ የከሰዓት ቆይታም በመጀመሪያው ዙር (Wave 1) የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን ከሚተገብሩ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮን አፈፃፀም ገምግሟል።
በግምገማው በቢሮው በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች አፈፃፀም ለሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን አፈፃፀሙን በተመለከተም ከቢሮው የሪፎርም አስፈፃሚ ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት ጋር ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን አደረገ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራን የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀም በመገምገም ላይ ሲሆን በዛሬ የከሰዓት ቆይታም በመጀመሪያው ዙር (Wave 1) የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን ከሚተገብሩ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮን አፈፃፀም ገምግሟል።
በግምገማው በቢሮው በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች አፈፃፀም ለሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን አፈፃፀሙን በተመለከተም ከቢሮው የሪፎርም አስፈፃሚ ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት ጋር ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምርት ማእከል
የፋሲካ በዓል ኤግዚቢሽንና ባዛር በድሬዳዋ ተከፈተ
የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛር በድምቀት መካሄድ ጀምሯል።
የአስተዳደሩ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን ዝግጅቱን በይፋ ሲከፍቱ እንደገለጹት፤ እንዲህ ያሉ መድረኮች ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ ብለዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፣ ባዛሩ ለሞዴል ኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር ከመፍጠሩ ባለፈ፣ በበዓል ወቅት የሚታየውን የሸቀጦች ዋጋ ንረት ለማረጋጋት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።
የኤስ.ኦ.ኤስ (SOS) ችልድረን ቪሌጅ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሚካኤል ስንታየሁ፣ ድርጅታቸው የወጣቶችን የሥራ ዕድል ለመደገፍ ከአስተዳደሩ ጋር በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ50 በላይ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች የተሳተፉ ሲሆን የተለያዩ የምግብ ሸቀጦች፣ አልባሳትና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለገበያ ቀርበዋል።
ይህ ኤግዚቢሽንና ባዛር እስከ ፋሲካ ዋዜማ ድረስ ለህዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
©️ DireTvአማርኛ | መጋቢት 29፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
የፋሲካ በዓል ኤግዚቢሽንና ባዛር በድሬዳዋ ተከፈተ
የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛር በድምቀት መካሄድ ጀምሯል።
የአስተዳደሩ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን ዝግጅቱን በይፋ ሲከፍቱ እንደገለጹት፤ እንዲህ ያሉ መድረኮች ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ ብለዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፣ ባዛሩ ለሞዴል ኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር ከመፍጠሩ ባለፈ፣ በበዓል ወቅት የሚታየውን የሸቀጦች ዋጋ ንረት ለማረጋጋት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።
የኤስ.ኦ.ኤስ (SOS) ችልድረን ቪሌጅ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሚካኤል ስንታየሁ፣ ድርጅታቸው የወጣቶችን የሥራ ዕድል ለመደገፍ ከአስተዳደሩ ጋር በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ50 በላይ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች የተሳተፉ ሲሆን የተለያዩ የምግብ ሸቀጦች፣ አልባሳትና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለገበያ ቀርበዋል።
ይህ ኤግዚቢሽንና ባዛር እስከ ፋሲካ ዋዜማ ድረስ ለህዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
©️ DireTvአማርኛ | መጋቢት 29፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ጋር በመተባበር የዘርፉን የኢንዱስትሪ ትስስር(TVET-Industry linkage) ለማጠናከር የሚያስችል የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ዙር የኩባንያ ውስጥ ስልጠና በአስተዳደሩ ከሚገኙ ለትብብር ስልጠና መስጫነት በተመረጡ ሰባት ኩባንያዎች በ4 የሙያ ዘርፎች፤በማኑፋክቸሪንግ፤ ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ፤ በሆቴልና ቱሪዝም እንዲሁም በአውቶሞቲቭ ሙያዎች ከሁለት የመንግስት ኮሌጆች በተውጣጡ አሰልጣኞች የኩባንያዎቹን ሰራተኞች ያለባቸውን የክህሎት ክፍተት በመለየት ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
የስልጠናው ዋና አላማ የኩባንያ ሰራተኞችን በማብቃት፤ የቴክኖሎጂ ክፈተቶችን በመሙላት ምርትና ምረታማነትን ማሳደግ ሲሆን በተጨማሪም የአሰልጣኝ መምህራንን አቅም በማሳደግ በትብብር ስልጠና ሂደት ሊያጋጥሙ የሚችሉ የጥራት ችግሮችን ከወዲሁ ለመፍታት ማስቻል ነው ሲሉ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ ጀማል አደን ገልጸዋል ፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 28/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከSOS CHILDREN'S VILLAGE እና GEEDBIG PLC ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር ከመጋቢት 28/2018 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 3/2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት የሚገኘው ቦታ ላይ ይካሄዳል።
በዚህም ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን ይዘው የሚቀርቡ ሲሆን ወቅቱም የበዓል ሰሞን እንደመሆኑ በቦታው በመገኘት የአስተዳደሩ ነዋሪ ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን በማበረታታት ተጠቃሚ እንዲሆን ይጋብዛል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ
ለሴት አሰልጣኝ መምህራንና ባለሙያዎች እንዲሁም ለዲፓርትመንት ተጠሪዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፤
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ለሴት የኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራንና ባለሙያዎች እንዲሁም ለዲፓርትመንት ተጠሪዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የኮሌጆችን አቅም በመጠቀም መስጠት ተቸሏል፡፡
በዚህም ስልጠናው በኮሌጆች የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራንና ባለሙያዎች የዓለም አቀፍ የአመራር ለውጥ እና የ21ኛው ክፍለ ዘመን እይታዎች እና የሴቶች ሚና እንዲሁም የሴቶች አመራር ጥበብ፤ ለቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ማሻሻያ ለምን አስፈለገ? በተጨማሪም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 እና የቴክኒክና ሙያ ሚና AI እና የዲጂታል አማራጮችን ለቢዝነስ ስኬት መጠቀም በሚሉ ርዕሶች ላይ አተኩሮ ተሰጥቷል፡፡
ከላይ በተዘረዘሩ ሃሳቦችና ተሞክሮዎችን የተመለከቱ ሲሆን ከዚህ ባለፈ የእርስበርስ ግንኙነትን ሊያጠናክሩና ወደ መጡበት ተቋም ሲመለሱ ስትራቴጂክ ሆነው ውጤት የሚያስገኝ ስራ መስራት የሚያስችላቸውን ግንዛቤ እዲፈጥሩ ማስቻሉን በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ ጽጌ ቦደሬ ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 25/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ዋሂል ክላስተር በSolar PV Installation & Maintenance ስልጠናዋን ተከታትላ ላጠናቀቀች ወጣት በፀሀይ ሀይል የሚሰራ ዘመናዊ ማብሰያ(Solar Cooker) ድጋፍ አደረገ::
ድጋፉ በዋናነት በBMZ ADRA, Germany አማካኝነት የተገኘ ሲሆን ይህም 1.1 KW የሚያመነጭ የSolar PV System ዝርጋታ እና በሶላር የሚሰራ ማብሰያ ምድጃ(Solar Cooker) ያካተተ እንደሆነም ተገልፇል::
በፕሮጀክቱ ድጋፍ የተደረገላት ወጣት ፎዚያ ባጋጠማት የአካል ጉዳት ሳትበገር ከምትኖርበት ከዋሂል ክላስተር ጁጁማ ወረዳ ተነስታ ኮሌጅ ድረስ ለስድስት ወራት 20 ኪሎ ሜትሮችን እየተመላለሰች ስትሰለጥን የቆየች ብርቱ ሴት ስትሆን የአድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክትም የዚህችን ወጣት ድካም በመረዳት በአካባቢዋ የራሷን ቢዝነስ ሰርታ ገቢ ምታገኝበትን የSolar PV System ዝርጋታ እንዲሁም በፀሀይ ሀይል የሚሰራ ዘመናዊ ማብሰያ(Solar Cooker) በድጋፍ መልክ አበርክቷል::
የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በSolar PV Installation Maintenance ወጣቶችን አሰልጥኖ የሙያ ባለቤት ከማድረግም ባሻገር ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ አስፈላጊ ድጋፎችን ሁሉ በማድረግ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ያስታወሱት የADRA Germany ዋና ሀላፊ አቶ ዳዊት መሀሪ ሲሆኑ በድሬዳዋ ገጠር ክላስተር ላይ ለእህታችን ፎዚያ የተደረገው ድጋፍም ፕሮጀክቱ ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ተደራሽና አካታች መሆኑን ማሳያ ከመሆኑም በተጨማሪም የፕሮጀክቱ ከላይ እስከታች የሚገኙ ሀላፊዎች ከባለድርሻ አካላት ጋር ተናቦ የመስራት ድምር ውጤት እንደሆነም ገልፀዋል::
ወጣት ፎዚያ በበኩሏ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከብዙ ድካም እንግልት እንዳሳረፋት በመግለፅ በተደረገላት ድጋፍም የተለያዩ ገቢዎችን በማመንጨት የራሷንም ሆነ የቤተሰቦቿን ህይወት እንደምታሻሽል የገለፀች ሲሆን በአጠቃላይ ይህ ድጋፍ እውን እንዲሆን ያደረጉ ለADRA ፕሮጀክት ሀላፊዎችንና አስተባባሪዎች በሙሉ ምስጋናዋን አቅርባለች::
በእለቱ በነበረው የድጋፍ ርክክብ ላይ የADRA Germany, የADRA Ethiopia ሀላፊዎች እንዲሁም የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎችና የኮሌጁ አመራሮች በቦታው ተገኝተው የተደረገውን ድጋፍ ውጤታማነት የተመለከቱ ሲሆን ወጣቷንም አበረታተዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
መጋቢት 25/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+3
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት አዘጋጅነት ከመጋቢት 23 - 25 ቀን 2026 የሚቆየው በEASTRIP ፕሮጀክት የሚደገፋ የ6 ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የቀጣይ 15 አመት እቅድ የደረሰበትን ግምገማ እና መሪ እቅድ ልማት አውደ ጥናት መርሀ ግብር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት መከናወኑ የሚታወስ ነው፡፡
በዚህ መሰረትም በአውደ ጥናቱ ላይ የተገኙ ግብአቶችን በመጠቀም በኮሌጁ ውስጥ ያሉ ባላድርሻ አካላት በሰነዱ ላይ ሃሳብ እና ግብዓት ለማሳባሰብ የሚረዳ መርሃ ግብር በዛሬው እለት ተከናወነ፡፡
በመርሃ ግብሩ ማጀመሪያ ላይ በመገኘት መድረኩን የከፈቱት የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽ ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም በEASTRIP ፕሮጀክት የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል እና ዘላቂ መሪ እቅድ በማዘጋጀት ኮሌጁ ለማህበረሰቡ ተደራሽ የሚሆኑበትን አሰራር በመቀየስ የስልጠና ተደራሽነታችንን ከጥራት ጋር ልናሰፋ ይገባል ብለዋል ያሉ ሲሆን፤
አያይዘውም ኮሌጁ የቀጣይ 15 አመት መሪ እቅድ ለመገምገምና ገንቢ ሃሶቦችን ለመስጠት መድረኩ እንደመዘጋጀቱ መጠን እቅዱን ለመተግበር ግንባር ቀደም እንደመሆናችን መጠን ተገቢውን ግብአት በመስጠት ገንቢ ሚናችሁን እንደትወጡ ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
አውደ ጥናት ላይ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከዚህ በፊት ሲሰራቸው የነበረውን ስራ እንዲሁም በቀጣይ 15 አመታት ሊደርስበት ያሰበውን የልህቀት ማእከልነት ለኮሌጁ ባለ ድርሻ አካላት ያቀረበ ሲሆን በመድረኩ የተገኙ ባለድርሻ አካላትም ኮሌጁ እስካሁን ሲሰራቸው የነበሩና በቀጣይ በስፋት ሊሰራቸው ያሰባቸው ስራዎች ወሳኝና ኮሌጁን በተለየ አይነት መልኩ ወደፊት ሊያራምዱ የሚችሉ ስራዎች በግብአትነት ሰጥተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 24/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
#ዜና| በፀሐይ ሀይል እየተገኘ ያለው ለውጥ እና ስኬት ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለፀ
#DireTvአማርኛ | መጋቢት 25 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአድራ (ADRA) ኢትዮጵያ ጋር በመሆን በሶላር (በፀሐይ ሀይል )የሚሰሩ የተለያዩ የምርት ውጤቶችን የሚያስገኙ መሳሪያዎችን በመስራት በይፋ አስመርቆ ሥራ አስጀምሯል።
በወቅቱም ከጀርመን እና ከኢትዮጵያ አድራ የመጡ የፕሮጀክቱ ኃላፊዎች ፤ የኮሌጁ አመራሮች እና ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ የመጡ ኃላፊዎች የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የሆኑት በማህበር የተደራጁ ሰራተኞችም ተገኝተዋል።
በምርቃት መርኃግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ወደ ኮሌጁ ከመጣ በኋላ መጀመሪያ ላይ በፀሐይ ኃይል ( በሶላር ) የሚሰራ ወፍጮ በመስራት ይፋ ማድረጉን አስታውሰው አሁን ደግሞ ለኮሌጁ እና ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሚጠቅም በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የውሃ መሳቢያ ፓንፕ ፣ የዘይት መጭመቂያ መሳሪያ እና የተለያየ አካል ጉዳት ያለባቸው በማኅበር ተደራጅተው የሚጠቀሙበት የመኪና ማጠቢያ (ላቪያጆ ) በመስራት ርክክብ እንዳደረጉ ገለፀዋል።
ዲኑ አያይዘውም በተለይ በኮሌጁ ቅጥር ግቢ ውስጥ በፀሐይ ኃይል የወጣው ውሃ ኮሌጁ የነበረበትን ከፍተኛ የሆነ የውሃ እጥረት ችግር ቀርፏል ነው ያሉት። ውሃውም ከኮሌጁ አልፎ ለአካባቢው ማኅበረሰብ ብሎም በግቢው ውስጥ በመኪና አጠባ ሥራ ለተደራጁት ማኅበራት የስራ እድል መፍጠር የተቻለበት አቅም ፈጥሯልም ብለዋል።
ዲኑ አድራ ኢትዮጵያም ድጋፉን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የአድራ ኢትዮጵያ ዳሬክተር ዶ/ር ዘሪሁን አዋኖ በወቅቱ እንደገለፁት የድሬዳዋ ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በፀሐይ ኃይል አጠቃቀም በኩል በገጠርም በኮሌጁም እየደረገ ያለው ስራ እጅግ በጣም የሚበረታታ ነው ብለዋል።
ዳይሬክተሩ አያይዘውም የፀሐይ ኃይል ማመንጫውን በዘላቂነት ለመጠቀም ኮሌጁ በአጫጭር ስልጠና ያስተማራቸውን የሶላር ጥገናና ተከላ ባለሞያዎችንም በማፍራት በማህበር በማደራጀት ወደስራ ማስገባቱ የሚደነቅና ስራው ቀጣይነት እንዲኖረው የሚያደርግ ነው ብለዋል።
ይህም በፀሐይ ሓይል የሚሰራ ስራ መቀጠል አለበት በማለት ጨምረው ገልፀዋል።
የጀርመኑ አድራ ዳሬክተር አቶ ዳዊት መሐሪ በድሬዳዋ ኢትዮጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያየነው ተጨባጭ ተግባር ተደስተናል። በቀጣይም በሌላ ፕሮጀክት አብሮነታችን ይቀጥላል ብለ፥ ይህ ስራም ኮሌጁ ከራሱ አልፎ አሁንም ለሌሎች መትረፍ አለበት በማለት አሳስበዋል።
በመርኃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይም በፀሐይ ኃይል የሚሰሩት መሳሪዎች ርክክብና ስራ ማስጀመሪያ ፊርማ የተከናወነ ሲሆን እንዲሁም በመኪና አጠባ ለተደራጁት አካል ጉዳተኞች የስራ ማስጀመሪያ የሚሆን አጫጭር ስልጠና ስልጥነው ያጠናቀቁበት የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
