ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy
Открыть в Telegram
የግጥም ተሰጥዖ ያላችሁ አድሚን እናደርጋችኋለን በቦቱ ተመዝገቡ ግጥም ብቻ ሳይሆን መነባንብ ሆነ ሌሎችም ተሰጥዖ ያለው መሳተፍ ይችላል For any comment👉 @e_t_l_bot Buy ads: https://telega.io/c/qdist
Больше2 843
Подписчики
-224 часа
-67 дней
-5330 день
Архив постов
🎰 Welcome Bonus 1200% — Maczo Crypto Casino
🎮 Crypto exchange · Sports · Live casino — all in one place
💳 USDT instant deposit & withdrawal
→ https://tglink.io/23c000af5a8da7
🎰 Welcome Bonus 1200% — Maczo Crypto Casino
🎮 Crypto exchange · Sports · Live casino — all in one place
💳 USDT instant deposit & withdrawal
→ https://tglink.io/91dd40b3a36c27
#ራሴን_ጠላሁት
ምን መሰለሽ ውዴ
ባለኝ አንድ ልቤ አንቺኑ አፍቅሬ
እንዳልተውሽ እንኳ አይሁኑ ታስሬ
በመውደድ ጫካ ውስጥ ባለ መርሳት ጎሬ
በናፍቆት ወህኒ ስላንቺ ታስሬ
#ራሴን_ጠላሁት
የአንደበትሽ ቃል የኮቴሽ እርምጃ
መች ሆነልኝ እና ለኔ የጠብ መንጃ
በመሄድሽ ህማም ደዌ ተመትቼ
ዛሬም ወድሻለሁ ራሴን ጠልቼ
ምን ይሉት እዳ ነው ስትሄጂ መምጣቴ
እንዴት ብወድሽ ነው ራሴን መጥላቴ
#ራሴን_ጠላሁት
አዎ አላቅፍሽም ገላሽ ቢናፍቀኝ
ደርሶም አይሞቀኝም ቁር ቢያቆረፍደኝ
አይንሽን አላየው መልሶ እንዳያየኝ
ጉንጭሽ አይዳሰስ እንዳይያዝ ሆኖኝ
ድምፅሽም አይመጣ ለጆሮ ቢያሰኘኝ
ከራሴ አብልጬ ስወድሽ ኖራለሁ
ባላገኝሽ ሆዴ ፍቅርሽን ይዣለሁ
ትዝታን ታቅፌ ትዝታን ስማለሁ
አንቺን አስመስዬ ጨረቃን አያለሁ
የጥርስሽን ፀዳል ከፀሀይ ሰርቃለው
#ስለምን መሰለሽ የጠላሁ ራሴን
መኖርሽን ሳልም የተመኘው ሞቴን
ሳቅሽ እንዲበዛ የናፈኩ ሀዘኔን
ጓዳሽ እንዲሞላ ምሆን ጎዶሎዬን
ላንቺ ሰጥቼ ነው ያለኝ አንድ ልቤን
ሌላ ልብ እስካገኝ እኔን ምወድበት
ባለኝ አንድ በሱም አንቺን አፍቅሬበት
መልሼ ላልወደው ራሴን ጠላሁት።
#share @qdis
#ብትረሺኝም_አረሳሽም
ብትረሺኝም...
ከህይወት መዝገብሽ በቀይ ብትሰርዢኝ
ከትውስታ ሀረግሽ ነጥለሽ ብትመዢኝ
እንደ ቅዠት ጭጋግ ልክ እንደ ህልም አለም
አካል እና አቋሜ ባይንሽ ባይቀለም
መልኬ እንኳን ጠፍቶብሽ ሌላ ብትጠይቂ
ስሜን እየረሳሽ ሰውን ብታስቂ
ሰው መርሳት ያለ ነው ብዙ አትደነቂ
ብረሳሽ...
ሌቱ አይንጋልኝ ቀኑ ይርዘምብኝ
አንዲቷ ደቂቃ ሺህ አመት ትሁንብኝ
በፍቅርሽ ናውዤ አንቺን በማስታወስ
በራሴው ጦርነት እኔው ልተራመስ
ከሞት ደጅ አልፎ ከሲኦል ልመለስ
እያልኩኝ በነብሴ ከቶ አላሟርትም
ግን እወድሻለው ብትሆኝም የትም
ብረሳሽ...
ፀፀት እና ፍቅር በውስጤ ይጣሉ
ሲሻኮቱ አድረው ሲናቆሩ ይዋሉ
ተኝቼ አልነሳ ተከፍቶ እይይ አይኔ
ጆሮዬም አይስማ ይዘጋ ልሳኔ
መጠጥ ባይኔ አይዙር እህልም አልቅመስ
ቁርበት አንጠልጥዬ ነጠላም አልልበስ
እያልኩ በስጋዬ ከቶ አላሟርትም
ግን እወድሻለው የትም ብትሆኝም
የትም
ብረሳሽ...
ብረሳሽ ሞት ይርሳኝ
ህይወት ተጠይፋ
እስትንፋሷን ትንሳኝ
ሰማይ እና ምድር
በእንዝርት ይጠቅለሉ
ወይ እንደ ወረቀት
ተጨራምተው ይጣሉ
ከዋክብት እረግፈው
ጥቁር ፅልመት ይንገስ
ተፈጥሮ ተዛብታ
ወንዙ ሽቅብ ይፍሰስ
ፍጥረት ሁሉ ይጥፉ
ተአምር ይፈጠር
ሁሉም ተነው ይለቁ
ከኔ ፍቅር በቀር
እያልኩ በፍቅርሽ ስም
ክፉን አልመኝም
"እኔ ከሞትኩ ሰርዶ..."
ሚል አቋም የለኝም
ጥለሽኝ ስትሄጂ
የኔ ሁኚ አልልም
ተስፋዬን ነጥቀሽኝ
ስታደርጊያት እልም
አረሳሽም እያልኩ
በስምሽ አልምልም
ለኔ ህግ የለኝም
ያንቺ በኔ ይሰራል
እንደዘነጋኝ እረሳሽ ይሆናል
እናም
እንዴት ረሳኝ ብለሽ እንዳትደነቂ
ሰው መርሳት ያለ ነው ይሄንን እወቂ
ግን ይሄ ላንች ነው ለኔ ልብ አይደለም
ሰው መርሳት ያለ ነው ብሎ ነገርንም እኔ ዓላቅበትም
ዘላለም አለሜን አንችን አረሳሽም
#share @qdist
#ብትረሺኝም_አረሳሽም
ብትረሺኝም...
ከህይወት መዝገብሽ በቀይ ብትሰርዢኝ
ከትውስታ ሀረግሽ ነጥለሽ ብትመዢኝ
እንደ ቅዠት ጭጋግ ልክ እንደ ህልም አለም
አካል እና አቋሜ ባይንሽ ባይቀለም
መልኬ እንኳን ጠፍቶብሽ ሌላ ብትጠይቂ
ስሜን እየረሳሽ ሰውን ብታስቂ
ሰው መርሳት ያለ ነው ብዙ አትደነቂ
ብረሳሽ...
ሌቱ አይንጋልኝ ቀኑ ይርዘምብኝ
አንዲቷ ደቂቃ ሺህ አመት ትሁንብኝ
በፍቅርሽ ናውዤ አንቺን በማስታወስ
በራሴው ጦርነት እኔው ልተራመስ
ከሞት ደጅ አልፎ ከሲኦል ልመለስ
እያልኩኝ በነብሴ ከቶ አላሟርትም
ግን እወድሻለው ብትሆኝም የትም
ብረሳሽ...
ፀፀት እና ፍቅር በውስጤ ይጣሉ
ሲሻኮቱ አድረው ሲናቆሩ ይዋሉ
ተኝቼ አልነሳ ተከፍቶ እይይ አይኔ
ጆሮዬም አይስማ ይዘጋ ልሳኔ
መጠጥ ባይኔ አይዙር እህልም አልቅመስ
ቁርበት አንጠልጥዬ ነጠላም አልልበስ
እያልኩ በስጋዬ ከቶ አላሟርትም
ግን እወድሻለው የትም ብትሆኝም
የትም
ብረሳሽ...
ብረሳሽ ሞት ይርሳኝ
ህይወት ተጠይፋ
እስትንፋሷን ትንሳኝ
ሰማይ እና ምድር
በእንዝርት ይጠቅለሉ
ወይ እንደ ወረቀት
ተጨራምተው ይጣሉ
ከዋክብት እረግፈው
ጥቁር ፅልመት ይንገስ
ተፈጥሮ ተዛብታ
ወንዙ ሽቅብ ይፍሰስ
ፍጥረት ሁሉ ይጥፉ
ተአምር ይፈጠር
ሁሉም ተነው ይለቁ
ከኔ ፍቅር በቀር
እያልኩ በፍቅርሽ ስም
ክፉን አልመኝም
"እኔ ከሞትኩ ሰርዶ..."
ሚል አቋም የለኝም
ጥለሽኝ ስትሄጂ
የኔ ሁኚ አልልም
ተስፋዬን ነጥቀሽኝ
ስታደርጊያት እልም
አረሳሽም እያልኩ
በስምሽ አልምልም
ለኔ ህግ የለኝም
ያንቺ በኔ ይሰራል
እንደዘነጋኝ እረሳሽ ይሆናል
እናም
እንዴት ረሳኝ ብለሽ እንዳትደነቂ
ሰው መርሳት ያለ ነው ይሄንን እወቂ
ግን ይሄ ላንች ነው ለኔ ልብ አይደለም
ሰው መርሳት ያለ ነው ብሎ ነገርንም እኔ ዓላቅበትም
ዘላለም አለሜን አንችን አረሳሽም
#share @qdist
+3
any mobile phone buyer dm
iphone 13 pro max
256gb battery health above 89 95,000birr
128 same batery health 85,000birr
13 pro max 512 98,000birr
iphone 12 pro max
256 72,000k
128 68,000birr
iphone 12pro 128 59k
11 pro max
256gGB 50,000birr
iphone 13 58,000birr
iphone 12 47,000birr
and if u want any laptop dm
we have free delivery
if u want dm @esttif2
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሰቻሁ የአመት ሰው ይበለን ሐሳባችን ሁሉ እሷ ትሙላልን ሌሎች የሀይማኖት ተከታዮችም እመብርሀን ሀሳባችሁን ትሙላላችሁ🥰🥰🥰
#share @qdist
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሰቻሁ የአመት ሰው ይበለን ሐሳባችን ሁሉ እሷ ትሙላልን ሌሎች የሀይማኖት ተከታዮችም እመብርሀን ሀሳባችሁን ትሙላላችሁ🥰🥰🥰
#አየህልኝ_ጉዴን
ያልታሰረው ቀልቤን
ያላመነው ልቤን
አየህልኝ ጉዴን
በልቤ ላሊዝህ በአፌ መጥራቴን
አምላኬ አምላኬ እያልኩ መወትወቴን
#አየህልኝ_ጉዴን
የጎደፈ ማንነቴን
ያልተገራ ልጅነቴን
ያልሰለቸኝ ምህረት እጅህ
ያልጨከነ ሩህ ሩህ ልብህ
ለመጠበቅ ያልሰለቸህ
የማተወኝ ደባቂ
አንተኮነህ ቸር አምላኬ
ወጣትነት እሳት ሁኖ
ትእቢት ልኬት አሳጥቶኝ
ትእግስትህን ስፈታተን
#አየህልኝ_ጉዴን
እኔም አለሁ እላለሁኝ
አቅሌን ስቼ አየኖርኩ
መዘመኔ መራቀቄ ምን ሊበጀኝ ካንተ ወዲያ
ምን አትርፌ ምን ሊኖረኝ ድንቄም እቴ መዘመኔ
ሲወጋ ነበረ ሲዘከር ነበረ ስልጣኔ ስይጣኔ
መራቀቄ መላቀቄ ከአይምሮ ከሀሳቤ
#አየህልኝ_ጉዴን
አንተን ትቼ ልገነባው የነበረ የአሸዋ ግግር ቤቴን
አየህልኝ ጉዴን
የገባሁት ማጥ ጭቃዬን ባታተርፈኝ መሞቻዬን
#share @qdist
#አየህልኝ_ጉዴን
ያልታሰረው ቀልቤን
ያላመነው ልቤን
አየህልኝ ጉዴን
በልቤ ላሊዝህ በአፌ መጥራቴን
አምላኬ አምላኬ እያልኩ መወትወቴን
አየህልኝ ጉዴን
የጎደፈ ማንነቴን
ያልተገራ ልጅነቴን
ያልሰለቸኝ ምህረት እጅህ
ያልጨከነ ሩህ ሩህ ልብህ
ለመጠበቅ ያልሰለቸህ
የማተወኝ ደባቂ
አንተኮነህ ቸር አምላኬ
ወጣትነት እሳት ሁኖ
ትእቢት ልኬት አሳጥቶኝ
ትእግስትህን ስፈታተን
#አየህልኝ_ጉዴን
እኔም አለሁ እላለሁኝ
አቅሌን ስቼ አየኖርኩ
መዘመኔ መራቀቄ ምን ሊበጀኝ ካንተ ወዲያ
ምን አትርፌ ምን ሊኖረኝ ድንቄም እቴ መዘመኔ
ሲወጋ ነበረ ሲዘከር ነበረ ስልጣኔ ስይጣኔ
መራቀቄ መላቀቄ ከአይምሮ ከሀሳቤ
አየህልኝ ጉዴን
አንተን ትቼ ልገነባው የነበረ የአሸዋ ግግር ቤቴን
አየህልኝ ጉዴን
የገባሁት ማጥ ጭቃዬን ባታተርፈኝ መሞቻዬን
#share @qdist
እኔ እምፈልገው
እውነት ለመናገር እኔ ምፈልገው
ካንቺ ጋር መጋባት
ይህን ሀምሌ ፊቴን ደጋግሞ ማራባት
ከወፎች ጋር መንቃት በጊዜ ቤት መግባት::
"ምንም ደሃ ቢሆን ባይኖረውም ሀብት
ከደጃፍ ሲቀመጥ ደስ ይላል አባት"
ለሚል መናኛ ጥቅስ ኑሮየ ማይመጥን
ሲሻኝ በየባንኩ: ስፈልግ በሳጥን
የተረፈኝ ገንዘብ
ደጃፍ ላይ ቁጭ ብየ ድሀ የምታዘብ
ተምሳሌትነቴ የሚዳረስ ባለም
ሞዴል አባወራ ተብየ ምሸለም
አገሬን ማስከበር
ህዝቤን ማስተባበር
የልጅ ልጅ አፍርቼ
በመቶ አመት ሙቼ
ስላሴ መቀበር
ምኞቴ ይህ ነበር::
እውነት ለመናገር እኔ እምፈልገው
ወንደላጤ ኑሮ
በሴቶች መታጀብ ልክ እንዳውራ ዶሮ
ጊዜ ጥሎኝ ቢሄድ ቀን ቢገሰግስም
መላው ጭንቅላቴ ገብስማ ቢለብስም
ላቅማዳም ነው እንጂ ለትዳር አልደርስም:
ደሞ
ዘር መዝራት እርሜ ነው ደጋግሜ ባርስም
ባለመኖር ላሉት ስቃይ አላወርስም
ቢፈልግ ሌላው ህዝብ
ይፈልፍል እንደዝንብ
ይባዛ እንደንጉዳይ
አገር ስራው ያውጣው! ሰው የራሱ ጉዳይ!!
የራሴ ፈጣሪ- ነኝ የራሴ ገዳይ!!
እኔ እምፈልገው...
እኔ እምፈልገው..
እኔ እምፈልገው
ገንዘብ ቢመዘበር በገንዘብ ይተካል
እድሜ ለጉልበትሽ በላቡ ለሚያድር
በውርስ በስጦታ ግፋ ቢል በብድር:
በቆጠብነው ቁጥር
ጊዜ ነው የሚያጥር
እድሜ ነው የሚያልቀው
የምንፈልገውን በቅጡ ሳናውቀው::
✍️ በእውቀቱ ስዩም
@qdist
ሰው:- ልጅነቴን ህልሜን ቀምቶኛል
የሰው ክፋት እንጂ ፍቅር አይቼ አላደኩም
ህይወትን ገና በ11 አመቴ ነው የብቸኝነትን የመከራን ጣዕም እያጠጣምኩ እንድኖር የፈረደችብኝ
ስራብ ስጠማ እናቴ እንኳን ልጄ አላለችኝም
ሳፈቅር ስከዳ ሳምን ስሰበር ነው የኖርኩኝ
ከሚስቱ የተጣላ ሰውዬ ንዴተን እኔን በመደብደብ ይወጣ ነበር
ሰው የተባለ ዘመድ ከጥቅሙ ያለፈ አለው ያለኝ ማንም የለም አልነበረምም
እኔን ዝቅ ከማድረግ ውጭ ፍቅርን የላየው ልጅ ነኝ
...
ታዲያ እኔ ሰውን ብፈራው ቢጨንቀኝ ምኑ ይገርማል ሰው እንደ እሳት ገረፈኝ ብል ምን ይገርማል አይ ወንድም እህት እናት አባት ጓደኛ ፍቅረኛ እንሁን ብሎ ያለን ሰው ዝም ብል ምኑ ክፉ ያስመስለኛል? አቃለሁ ሁሉም ሰው ክፋ አይደለም ነገር ግን ሰው ለኔ ከዚህ በሖላ ከላይ የገለፅኩት ነው ማንንም ማመን አልፈልግም አለቀ በቃ
አንዳንዴ እናንተ ባላችሁት መንገድ ስላልሄድኩ ብቻ መጥፎ ነገር ከመናገር እባካችሁ ተቆጠቡ ስለ አምታምኑት አምላክ🙏🙏 በዉስጥ እየመጣችሁ ስለምትሳደቡት ባጠቃላይ ለንግግራችሁ ገደብ አስቀምጡለት ደካማ ላይ እየመጣችሁ አፋችሁን አትክፈቱ የእናንተ አፋ በተከፈተበት ልክ የኔ አፍ መከፈት እና ምላሸ መስጠት አይችልም ብችሉ ጥሩ ነገር ባደረጋችሁ ባችሉ ግን ለምትነገሩት ነገር ተጠንቀቁ ወይም ከመጀመሪያውም ምንም አይነት Text አታድርጉ ልኑርበት ከስድብ ተቆጠቡ Plz🙏🙏🙏
#አብሮ_መጥፋት
በፍቅር ሰንሰለት እኔን ላንቺ ድሮ
ያለፈ ታሪክሽን
የኀጢአቴን ግርሻት ሊያጠፋ ቀን ቀጥሮ
ወደ ኋላ መዞር ላ'ፍታ ሳትመኙ
ወደ ፊት ተጓዙ ነጋችሁን ቃኙ
ለፍቅር ታመኑ ለፍቅር ተቀኙ!
የሚል ትእዛዝ ሰጥቶን
ትናንትናችን ላይ እቶን እሳት ቢለቅ
ወላዋይ መንፈስሽ
ልክ እንደ ሎጥ ሚስት ታየ ሲፍረከረክ፡፡
የቀድሞ ፍቅረኛሽ…
ያ ሁሉ ትዝታ
መጥፋት አብከንክኖሽ በድንገት ስትዞሪ
የጨው ሐውልት ግግር
አድርጎ ቢያስቀርሽ የፍጥረት ፈጣሪ
ሎጥን ልምሰል ብዬ…
የፍቅርሽ እርምጃ
ከኋላዬ ሲቀር ወደ ፊት አልሄድም
አይቼሽ ለማልቀስ
አይቼሽ ለመድረቅ
ያ'ምላኬን ቃል ሽሬ መዞሬ አይቀርም፡፡
✍️Unknown
#Share @qdist
ለእራሴ ሞት ላንባ
ወዳጅ አለኝ ብዙ ስቆ የሚያስቀኝ
ዘመድ አለኝ ለስም የማውቀው ማያቀኝ
ሀዘን ፊቴ የለም በሳቅ ተሸፍኖ
የውስጤን ቁስሎች በፈገግታ አክስሞ
ለሚያየኝ ሙሉ ነኝ ምንም ያልጎደለው
ከዘመድ ከሀብቱ በእጅጉን ያደለው
ድሎት አና ምቾት ዘውትር የከበበው
እውነትም ሆን እንዴ እነሱ እንዳሉት
እሱ ይህ ነው ብለው እንደተናገሩት
ብዬ የጥያቄ ሰደድ በላዬ አንግቤ
ሳወጣ ሳወርደው ዕርቄ ከቀልቤ
አይምሮየም "ውሸት" ከእውነት የራቀ
ማነው እንዲህ ያለኽ ብሎ ተሳለቀ
የአይምሮን ሹፈት ወደ ዳር አድርጌ
ልቤኑ ጠየኩት ተስፋዬን አንግቤ
እሱም እየጣረ እኔን ላለመጉዳት
አይምሮ ልክ ነው አለኝ በማፅናናት
በእውነቱ ከበደኝ ትንሽም ደነቀኝ
የይምሰል ህይወቴን እንዳየው አረገኝ
ለካስ ባዶ ነኝ ምንም የሌለኝ
ለይምሰል የምኖር ሳቄ የሸፈነኝ
ከዘመድ ዘመድ ከ ጓድ ጓደኛ
ያልታደልኩ ብቸኛ
በአንዲት ጥያቄ ቁስሌን አንግቤ
መኖሬ ለምን ነው?
እንደ ሰው ሳልኖረው ኖርኩኝ ነው ሚባለው?
ብሞት ለቀብሬ የሚመጣው ዘመድ
ተቀምጦ አልቅሶ አንብቶ ቢራመድ
ለኔ ምን ያረጋል ኖሬ ያልጎበኘኝ ዛሬ ላይ ቢያነባ
ደረት ቢደቀድቅ ቢለብስ የሀዘን ካባ
አልቅሰው አይቀሰቅሱኝ
ከሞት አይመልሱኝ
ምንድነው ማንባቱ ?
ውሀ ከፈሰሰ ይቅር የታባቱ
ነውና ተረቱ
በእኔው ቀብር ቆመው እኔን ሊቦልቱ
እኔው ለችግሬ እኔው ለሀዘኔ ደርሻለውና
ለእራሴ ሞት ዕንባ በቃለውኝና
ማስመሰሉ ይቅር ጭራሽኑ አትምጡ
በለቅሶ ጋጋታ ምንም ላታመጡ
አንዴ ሞቷል ተብሎ ተነፍቷል ጥሩንባ
ሀዘናቹ ይቅር ለእራሴ ሞት ላንባ።
#share @qdist
Repost from ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy
እብድ ነኝ አታውሩኝ
ዝም ብል ከራሴ ጋ ባወራ
ከሰው ጋ ባልግባባ
እራሴን ባይ ሰዎችን ባላይ
ከሰው ልጅ ክፋትን ከምማር
ከራሴ ጋ ብመራመር
ሰው ካልሆነ ሰው ጋ ከምኖር
ብፈልገው የራሴን እንቁ ሚስጥር
ምን አለበት ማን ከልክሎኝ
ከራሴ ጋ ብሆን ማንስ አስመርጦኝ?
በቃ ይበቃል እኔን ለኔ ተውት
እንደው እብድን ድሮስ ማን ፈልጎት
እኔ እብድ ነኝ
እራሴን ለፍቅር የገደልኩኝ
በእውነት አለም ልኑር ያልኩኝ
የዘመኑ ፋራ የጅሎች መሪ ነኝ
አዎ እኔ እብድ ነኝ አታውሩኝ።
ህይወቴን ለሰው የተውኩኝ
በደልን በበደል ያልመለስኩኝ
ያለ እድሜዬ ፍቅር የሰበኩኝ
ህልሜን የተነጠኩኝ
በውሸት ቃል ያነገሱኝ
ህልሜን አስጠፍተው በቁሜ የቀበሩኝ
ከሙታን በላይ ከሚኖሩት በታች የሚያኖሩኝ
ሰው አማኝ ነኝ ከንቱ ፍጡር የባዘንኩኝ
የእብዶች እብድ ቅዠታም የተባልኩኝ።
አዎ እኔ እብድ ነኝ
እንዳንተ አይደለሁም
ቃሎቸን አላጥፍም ልክ እንደ ይሁዳ
ለሆድ ተገዝቸ ፍቅርን የማልከዳ
ለራሴ የማልኖር ልክ እንደ ጲላጦስ
ትምህርትን የወሰድኩ ፍቅርን ከክርስቶስ
የዘመኑ ፋራ የጅሎች አባት ነኝ
በደልን በውስጤ አፍኜ የያዝኩኝ
የሞቴን ቀን የቆጠርኩኝ
የውስጤን ስቃይ ለማንም ያላካፈልኩኝ
ከሰው ሁሉ የራኩኝ
አዳማጭ ያጣሁኝ
ከዘመኑ ሃሳብ የወጣሁኝ
እኔም አብሬ እንደ ዘመኑ ሰው ያላጌጥኩኝ
የደበዘዝኩ የፈዘዝኩኝ
የከንቱወች ከንቱ ሃሰትን የጠላሁኝ
የጠፋችውን እውነት የወደድኩኝ
...
የጅሎች ጅል ማለት እኔ ነኝ
እውነት እውነት እኔ እብድ ነኝ
ላትረዱኝ አትቅረቡኝ
የእብዶች እብድ የእብዶች መሪማለት እኔ ነኝ!!!
#Share @qdist
For any comment&question 👉 @e_t_l_bot #እቀፊኝ
ሰማዩ ይጠቅለል ምድር ትተጣጠፍ
የወደድኩሽ አንቺን አቅፌሽ ልንሳፈፍ
እንወድቃለን ብለሽ ከቶ አትጨነቂ
ማንም ያላወቀው መልአክ መሆንሽን ድንገት እንድታቂ
#ወደቅን ስንባል ክንፎችሽ ይዘርጉ
ለኔ የሚታየኝ ብርሀንሽን አይተው
ጨለማና ፅልመት ድንገት ይሸሸጉ
ከዚህ አለም ውሰጂኝ
ካንቺ ገነት ልኑር
ከእቅፍሽ አልውጣ
ህይወቴ እንዲሰምር
ሲኦልሽ ውሰጂኝ እኔ እንደሆን አልቀር
#አንቺ ካለሽበት ገነት ነው የኔ አለም
ካንቺ ጋራ ሆኘ እሳትም ቢበላኝም
እንጦሮጦስ ይሁን
ብወርድም ግድ የለኝ
ተራራን አክሎ መብረቅ ቢዘንብብኝ
አውሎ ንፋስ መጥቶ ወስዶ ቢያንገላታኝ
ለኔ ምንም ነው
#አንቺ ካለሽልኝ
መከራው ቢበዛ ለሰከንድ አትራቂኝ
በይ እቀፊኝ
ስታቅፊኝ
ችግር ምን እንደሆን ስለምታስረሺኝ
#እባክሽ የኔ እናትዘላለም እቀፊኝ።
#Share @qdist
ብዬማ አልዋሽሽም
እኔ እኮ ያላንቺ ምንም ነኝ ብዬ
ብዙ አልዘበዝብም
ስሚኝ አንቺ ሆዬ
ትተሽኝ ከሄድሽ
ልቤ ድንኳን ጥሎ
ደረቱን ይደቃል
ከሰው ተነጥሎም
ሀዘን ይቀመጣል
ከመኖር ተጣልቶም
ሞትን ይናፍቃል
ብዬማ አልዋሽሽም
ከተውሽኝ አልኖርም
ያላንቺ ምስቀዉ
ሳቄም ሳቅ አይሆንም
ስልማ አልዋሽሽም
ምን በወጣሽ ፍቅሬ
ባምላክ ትዕዛዝ እንጂ
ባንቺ አይደል መኖሬ ።
#share @qdist
#ልመንህ_ወይ
ላፈቅርህ ነዉ አተወኝም
ልመንህ ወይ አትከዳኝም
ገብሬልን ማርያምን በልና ማልልኝ
በልብህ ዙፋን ላይ ቃልኪዳን ግባልኝ
አልተውሽም ብለህ በላ በላኮ ማልልኝ
አምኜህ ልቀመጥ ቀልቤ ይረፍልኝ
ደግመህ እንደማተወኝ ልቤ ይወቅልኝ
በላ በል እኮ ማልልኝ
#share @qdist
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
