ru
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Assaye Derbie

Канал Assaye Derbie (@asayede) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 14 365 подписчиков, занимая 2 646 место в категории Блоги и 2 349 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 14 365 подписчиков.

Согласно последним данным от 19 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -151, а за последние 24 часа — -7, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 37.94%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 10.81% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 450 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 553 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 39.

📝 Описание и контентная политика

Описание канала не предоставлено.

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 20 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Блоги.

14 365
Подписчики
-724 часа
-337 дней
-15130 день
Архив постов
AFPO's Draft Manifesto Jan33 (1).pdf1.14 MB

photo content
+4

አፋሕድ የድርድሩን አጀንዳ ለማስቀየስ አስቦ በለቀቀው፣ ከአብን በኮረጀውና ማኒፌስቶ በሚል ሥም በለቀቀው የድርድር ሰነድ በፋኖ ደም ኢትዮጵያ ትቅደም ማለቱን፣የአማራን የሥልጣን ጥያቄ መካዱንና ከአማራ ብሔርተኝነት በተቃራኒ መሰለፉን ተረድቻለሁ።

ክሷ ምን ቢሆን ጥሩ ነው? "የጥበብ ሥራዎችሽ ውስጥ የአማራ ባሕልና ወግ ይበዛበታል"😁
ክሷ ምን ቢሆን ጥሩ ነው? "የጥበብ ሥራዎችሽ ውስጥ የአማራ ባሕልና ወግ ይበዛበታል"😁

ለወትሮው ከሚዲያ የማይጠፉ የፋኖ መሪዎች በሥማቸው ድርድር ሲካሄድባቸው ምነው ድምጻቸው ጠፋ? የአማራ የብሔርተኝነት ትግል በሐሳዊ ኢትዮጵያኒስት ሲጠለፍ ምነው ደብዛቸው ጠፋ?

እኅታችን ቀለብ ስዩም ትክክለኛውን የትግል መስመር ይዛ ትግል ጠላፊዎችን እየታገለቻቸው ነው። እና Subscribe በማድረግ አበረታቷት። 👇 https://youtu.be/hTu2lzMrqEk?si=pw6pUyv0rbnNce26

"የሽምቅ ውጊያው እንደ "ድል ለዲሞክራሲው" አልቀለለውም። ለዚያ ነው የተደራደረው።" ጄኔራል ተፈራ

https://youtu.be/LUUj746Gv_M ልዩ ቃለመጠይቅ ➻ አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ➻ አርበኛ እሸቴ ባዬ ➻ አርበኛ ሀብቴ ወልዴ ➻ አርበኛ ባዬ ቀናው

"አሳዬ" የተባልኩት እኮ ያለምክንያት አይደለም ብዬ ልጎርር እንዴ? 🤣ለማንኛውም ግን እንደ አንድ አማራ በዋናነት ታርጌት የተደረገውን የጎጃም አማራ ያመላከተኝና ከእነሱ ጎን አሰልፎ "የዘመነ ተላላ
"አሳዬ" የተባልኩት እኮ ያለምክንያት አይደለም ብዬ ልጎርር እንዴ? 🤣ለማንኛውም ግን እንደ አንድ አማራ በዋናነት ታርጌት የተደረገውን የጎጃም አማራ ያመላከተኝና ከእነሱ ጎን አሰልፎ "የዘመነ ተላላኪ" ያስባለኝ አምላክ ይክበርልኝ፡፡

በወቅታዊ ጉዳይ ከማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ መግለጫ ትግላችንን ለዳግም ባርነት ለሚያመቻቹን የብልጽግና እሳቤ አራማጆች አሳልፈን አንሰጥም!!! ቀን፦ ጥር 18/2017 ዓ.ም ትግላችን የኅልውና፣ የፍትሕ፣ የነጻነት፣ የሰብዓዊ ክብር ሆኖ እያለ ከፋፋይነት፣ ብልጣብልጥነት፣ አወናባጅነት፣ ከምንም በላይ በሕዝባችን ላይ የፖለቲካ ቁማርተኝነት እሳቤዎችን ከጀርባቸው አንግበው የአማራን ሕዝብ ለዳግም ባርነት ለመዳረግ በሞቱ የሚደራደሩ የአይሁድ ሸንጎ ማኅበርተኞችን ትናንት በአደባባይ ሕዝባችንም ሠራዊታችንም የተመለከተው የአደባባይ ሐቅ ነው። የብልጽግና ሥርዓት በቅብብሎሽ የተረከበውን አማራ ጠልነት አተልቆ፣ አደርጅቶ፣ አጎምርቶ በሰው ልጆች ታሪክ ታይቶ ተሰምቶ የማያውቅ እልቂት በአማራ ሕዝብና በአማራዊ ማንነት ላይ ውርጅብኝ በሆነበት በዚህ ሰዓት ላይ የአርበኝነት፣ የሐቅና የፍትሕ ትግላችንን በድርድር ሰበብ ለማይጠረቃ የፖለቲካ ፍትወታቸው መወጣጫ መሰላል ለማድረግ የሚሞክሩ  አካላትን ለሠራዊታችንና ለሕዝባችን መግለጥ እንወዳለን። ከፋፋይነት፣ ይሉኝታ የለሽ ነጣቂነት፣ ልጓም አልባ የሥልጣን ፍትወት ላይ የሚናውዙ አካላት ትግላችንን ትናንት በሕዝባዊ ግንባር፣ ሕዝባዊ ሠራዊት፣ ፋሕፍዴን ዛሬ ላይ ደግሞ  በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ጭንብል ተሸፍነው ትግላችንን ለማቃለል፣ ለማሳነስ የሄዱበት ርቀት እጅጉን አሳዝኖናል። በደቡብ ወሎ ዞን፣ ዳውንት ወረዳ ልዩ ቦታው ኩርባክ በተባለ ቦታ የጎንደር፣ የጎጃም፣ የሸዋና የወሎ የፋኖ ተወካዮች በሚል ከአፍሪካ ኅብረት፣ ከኢጋድ፣ ከአብይ አሕመዱ ሃገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተወካዮች ጋር ንግግሮች መደረጋቸውን ከሂደቱ ጀምሮ በየተቋሞቻችን የመረጃና ደኅንነት ዘርፎቻችን በኩል ስንከታተለው የቆየነው ጉዳይ መሆኑን ሳንገልጽ አናልፍም። እሚገርመው ደግሞ እነዚህ አካላት ድርድሩን ሚዲያ ላይ ወጥተው በመሪያቸው በአቶ እስክንድር ነጋ እና በፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊው በረ/ኘ/ር ጌታ አስራደ በኩል ገልጸውልናል። በዚህ መሠረት ከራሳቸው የሚዲያ ማብራሪያ ብቻ ተነስተን ተጠይቆችን በማቅረብ ሕዝባችንም ሆነ ሠራዊታችን ከዚህ እኩይ እሳቤ ራሱን እንዲጠብቅ እንፈልጋለን። የመጀመሪያው ተጠየቅ፦ አቶ እስክንድር ነጋ፣ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፣ ረ/ፕ/ር ጌታ አስራደ፣ ኮሎኔል ፋንታሁን ሙሃቤ እና ከሸዋ ማንነቱን በውል ያላወቅነው ግለሰብ በድርድር ሰበብ የኅልውና ትግሉን የማይመጥን፣ የአማራን ሕዝብ ጥያቄዎች በተወሰኑ ቡድኖች ፍላጎት ላይ ብቻ አንጠልጥሎ የጥድፊያው አንድምታ ምንድነው?፤ ያለሕዝብና ያለፋኖ ውክልና አማራውን ቀራንዮ አደባባይ ያቆመው ሥርዓት በተገኘበት መድረክ ላይ ለመገኘት ለምን ደፈራችሁ? ሁለተኛው ተጠየቅ፦ የአማራ ፋኖ በጎጃም ሙሉ በሙሉ፣ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ) ከሁለት ክፍለ ጦር ውጭ ሙሉ ለሙሉ፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር ከሦስት ክፍለ ጦር ውጭ ሙሉ ለሙሉ፣ የሸዋ ፋኖም አንድነት ለመፍጠር የንግግር ሂደት ላይ መሆኑ እየታወቀ ድርጅት የምትሉት ተቋም በምንታገልበት የአማራ ሰማይ ሥር የት ነው ያለው? ሕዝባዊ ድርጅት በሚል በዲጂታል ሚዲያው የሚለፈፈው ከሐቅ የራቀ፣ ሙሉ ለሙሉ ከፋፋይ፣ መሪዎቹም ከተወሰኑት ወታደራዊ መሪዎች በስተቀር በግብር የተገለጠ ጸረ አማራ አቋም ያላቸው ስለመሆናቸው ማብራሪያና መግለጫችው ኅያው ምስክር ነው። ታዲያ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ዘጠና በመቶ የሚሆነውን የፋኖ ኃይል የያዘ ተቋም ነው የሚለው የእስክንድር ነጋ ንግግር የአማራን ሕዝብ የኅልውና ትግል ለማይጠረቃ ግለሰባዊ የሥልጣን ፍትወቱ መጠቀሚያነት እንጅ በእውነት ለአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል የወጣ ታጋይ አለመሆኑን ዳግም አረጋግጦልናል። ምክንያቱም የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መሬት ላይ የሌለ የትግላችን መከፋፈያነት መጠቀሚያ ካርድ ለመሆኑ በየቀጠናው የሚገኙ ፋኖዎችን ጫፍና ጫፍ አቁሞ እስከማታኮስ የዘለቀ ርካሽ የፖለቲካ መቆመሪያ ድርጅት ስለመሆኑ የትናንት ገሐዳዊ ሁነቶች ያረጋግጣሉ። ድርድርም ውይይትም በመርኅ ላይ የተመሠረተ፣ ሐቀኛ የፖለቲካ ውክልናን የያዘ፣ የትግሉ መሠረተ ሃሳቦች ላይ የቆመ፣ የትግል ፍኖተ ካርታን በግልጽ በማስቀመጥ እነዚህን ሳይነጣጠሉ ሃሳብን የማቅረቢያ አመከንዮዎችን፣ ገሐዳዊ ሐቆችን ያለአንዳች የፖለቲካ ውስልትና በማቅረብ የሕዝብ ጥያቄ ማሸነፍ የሚችልባቸውን መደላድሎች መፍጠር ነው። ቅሉ አቶ እስክንድር ነጋ፣ ረ/ፕ/ር ጌታ አስራደ፣ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፣ ኮሎኔል ፋንታሁን ሙሃቤ እና ከሸዋ አንድ ግለሰብ በጋራ የተገኙበት ሸንጎ በመርኅ ደረጃ የድርድርን መሠረተ ሃሳቦችን ያላሟላ መሆኑን ማረጋገጥ እንወዳለን። ከዚህ ጋር ተያይዞ በዚህ የንግግር ሂደት ላይ የተገኙ ዓለምአቀፍ ተቋማት መሬት ላይ ከሌለ ስብስብ ጋር መቀመጣቸው ሥርዓታዊ የዘር ማጥፋት ድርጊት እየተፈጸመበት ያለውን የአማራን ሕዝብ ያላከበረና የማይመጥን አካሄድ በመሆኑ በቀጣይ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ሐቀኛ እንዲሁም አካታች ውክልና ከሚሰጣቸው ልሂቃን ጋር ብቻ እንዲሆን መግለጥ እንወዳለን። በጥቅሉ ዳውንት ላይ የተካሄደው ድርድርም ይሉት ውይይት ሠራዊታችን የማያውቀው ምናልባትም የሚያወግዘው፤ ሕዝባችንን ያሳዘነ የፖለቲካ ቁማር ነው። ይህንን በድፍረት ለማለት የሚያስገድደን ጉዳይም ከእውነት የራቁ ድርጅታዊ ተረኮች (90% የፋኖ ኃይል የድርጅታችን አካል ነው፣ የወከልነውም ይህንን ግዙፍ ኃይል ያለው ፋኖ ነው) የሚሉ፣ የመርኅ፣ የፖለቲካ ውክልና፣ የተዓማኒነት እንዲሁም የአካታችነት የሚሉት ጥያቄዎችና መሰል ጉዳዮች ሲነሱ ውሃ የሚያነሳ ምላሽ የለም። መላው የአማራ ሕዝብ፣ መላው ሠራዊታችን፣ የሚዲያ አካላት ይህ ጉዳይ በቀላል የሚታይ ባለመሆኑ የአማራ ፋኖ በሸዋ፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር፣ የአማራ ፋኖ በጎጃም፣ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ) እና የአማራ ፋኖ ቢዛሞ እዝ ሕዝባችንን ለዳግም ባርነት አሳልፎ የሚሰጥ አደረጃጀትንም ሆነ አስተሳሰብ አጥብቀን ከማውገዝ ባሻገር የምንታገለው ጉዳይ ነው። የአማራ ፋኖ በጎጃም የአማራ ፋኖ በሸዋ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ) የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር እና የወለጋ ክፍለ ሃገር ፋኖ እዝ (ቢዛሞ)