Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 365 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 646,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 349 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 365 名订阅者。
根据 19 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -151,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 37.94%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.81% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 450 次浏览,首日通常累积 1 553 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 39。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 20 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 365
订阅者
-724 小时
-337 天
-15130 天
帖子存档
14 365
አፋሕድ የድርድሩን አጀንዳ ለማስቀየስ አስቦ በለቀቀው፣ ከአብን በኮረጀውና ማኒፌስቶ በሚል ሥም በለቀቀው የድርድር ሰነድ በፋኖ ደም ኢትዮጵያ ትቅደም ማለቱን፣የአማራን የሥልጣን ጥያቄ መካዱንና ከአማራ ብሔርተኝነት በተቃራኒ መሰለፉን ተረድቻለሁ።
14 365
ለወትሮው ከሚዲያ የማይጠፉ የፋኖ መሪዎች በሥማቸው ድርድር ሲካሄድባቸው ምነው ድምጻቸው ጠፋ? የአማራ የብሔርተኝነት ትግል በሐሳዊ ኢትዮጵያኒስት ሲጠለፍ ምነው ደብዛቸው ጠፋ?
14 365
እኅታችን ቀለብ ስዩም ትክክለኛውን የትግል መስመር ይዛ ትግል ጠላፊዎችን እየታገለቻቸው ነው። እና Subscribe በማድረግ አበረታቷት። 👇
https://youtu.be/hTu2lzMrqEk?si=pw6pUyv0rbnNce26
14 365
https://youtu.be/LUUj746Gv_M
ልዩ ቃለመጠይቅ
➻ አርበኛ መሳፍንት ተስፉ
➻ አርበኛ እሸቴ ባዬ
➻ አርበኛ ሀብቴ ወልዴ
➻ አርበኛ ባዬ ቀናው
14 365
"አሳዬ" የተባልኩት እኮ ያለምክንያት አይደለም ብዬ ልጎርር እንዴ? 🤣ለማንኛውም ግን እንደ አንድ አማራ በዋናነት ታርጌት የተደረገውን የጎጃም አማራ ያመላከተኝና ከእነሱ ጎን አሰልፎ "የዘመነ ተላላኪ" ያስባለኝ አምላክ ይክበርልኝ፡፡
14 365
በወቅታዊ ጉዳይ ከማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ መግለጫ
ትግላችንን ለዳግም ባርነት ለሚያመቻቹን የብልጽግና እሳቤ አራማጆች አሳልፈን አንሰጥም!!!
ቀን፦ ጥር 18/2017 ዓ.ም
ትግላችን የኅልውና፣ የፍትሕ፣ የነጻነት፣ የሰብዓዊ ክብር ሆኖ እያለ ከፋፋይነት፣ ብልጣብልጥነት፣ አወናባጅነት፣ ከምንም በላይ በሕዝባችን ላይ የፖለቲካ ቁማርተኝነት እሳቤዎችን ከጀርባቸው አንግበው የአማራን ሕዝብ ለዳግም ባርነት ለመዳረግ በሞቱ የሚደራደሩ የአይሁድ ሸንጎ ማኅበርተኞችን ትናንት በአደባባይ ሕዝባችንም ሠራዊታችንም የተመለከተው የአደባባይ ሐቅ ነው።
የብልጽግና ሥርዓት በቅብብሎሽ የተረከበውን አማራ ጠልነት አተልቆ፣ አደርጅቶ፣ አጎምርቶ በሰው ልጆች ታሪክ ታይቶ ተሰምቶ የማያውቅ እልቂት በአማራ ሕዝብና በአማራዊ ማንነት ላይ ውርጅብኝ በሆነበት በዚህ ሰዓት ላይ የአርበኝነት፣ የሐቅና የፍትሕ ትግላችንን በድርድር ሰበብ ለማይጠረቃ የፖለቲካ ፍትወታቸው መወጣጫ መሰላል ለማድረግ የሚሞክሩ አካላትን ለሠራዊታችንና ለሕዝባችን መግለጥ እንወዳለን።
ከፋፋይነት፣ ይሉኝታ የለሽ ነጣቂነት፣ ልጓም አልባ የሥልጣን ፍትወት ላይ የሚናውዙ አካላት ትግላችንን ትናንት በሕዝባዊ ግንባር፣ ሕዝባዊ ሠራዊት፣ ፋሕፍዴን ዛሬ ላይ ደግሞ በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ጭንብል ተሸፍነው ትግላችንን ለማቃለል፣ ለማሳነስ የሄዱበት ርቀት እጅጉን አሳዝኖናል።
በደቡብ ወሎ ዞን፣ ዳውንት ወረዳ ልዩ ቦታው ኩርባክ በተባለ ቦታ የጎንደር፣ የጎጃም፣ የሸዋና የወሎ የፋኖ ተወካዮች በሚል ከአፍሪካ ኅብረት፣ ከኢጋድ፣ ከአብይ አሕመዱ ሃገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተወካዮች ጋር ንግግሮች መደረጋቸውን ከሂደቱ ጀምሮ በየተቋሞቻችን የመረጃና ደኅንነት ዘርፎቻችን በኩል ስንከታተለው የቆየነው ጉዳይ መሆኑን ሳንገልጽ አናልፍም።
እሚገርመው ደግሞ እነዚህ አካላት ድርድሩን ሚዲያ ላይ ወጥተው በመሪያቸው በአቶ እስክንድር ነጋ እና በፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊው በረ/ኘ/ር ጌታ አስራደ በኩል ገልጸውልናል።
በዚህ መሠረት ከራሳቸው የሚዲያ ማብራሪያ ብቻ ተነስተን ተጠይቆችን በማቅረብ ሕዝባችንም ሆነ ሠራዊታችን ከዚህ እኩይ እሳቤ ራሱን እንዲጠብቅ እንፈልጋለን።
የመጀመሪያው ተጠየቅ፦ አቶ እስክንድር ነጋ፣ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፣ ረ/ፕ/ር ጌታ አስራደ፣ ኮሎኔል ፋንታሁን ሙሃቤ እና ከሸዋ ማንነቱን በውል ያላወቅነው ግለሰብ በድርድር ሰበብ የኅልውና ትግሉን የማይመጥን፣ የአማራን ሕዝብ ጥያቄዎች በተወሰኑ ቡድኖች ፍላጎት ላይ ብቻ አንጠልጥሎ የጥድፊያው አንድምታ ምንድነው?፤ ያለሕዝብና ያለፋኖ ውክልና አማራውን ቀራንዮ አደባባይ ያቆመው ሥርዓት በተገኘበት መድረክ ላይ ለመገኘት ለምን ደፈራችሁ?
ሁለተኛው ተጠየቅ፦ የአማራ ፋኖ በጎጃም ሙሉ በሙሉ፣ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ) ከሁለት ክፍለ ጦር ውጭ ሙሉ ለሙሉ፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር ከሦስት ክፍለ ጦር ውጭ ሙሉ ለሙሉ፣ የሸዋ ፋኖም አንድነት ለመፍጠር የንግግር ሂደት ላይ መሆኑ እየታወቀ ድርጅት የምትሉት ተቋም በምንታገልበት የአማራ ሰማይ ሥር የት ነው ያለው?
ሕዝባዊ ድርጅት በሚል በዲጂታል ሚዲያው የሚለፈፈው ከሐቅ የራቀ፣ ሙሉ ለሙሉ ከፋፋይ፣ መሪዎቹም ከተወሰኑት ወታደራዊ መሪዎች በስተቀር በግብር የተገለጠ ጸረ አማራ አቋም ያላቸው ስለመሆናቸው ማብራሪያና መግለጫችው ኅያው ምስክር ነው።
ታዲያ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ዘጠና በመቶ የሚሆነውን የፋኖ ኃይል የያዘ ተቋም ነው የሚለው የእስክንድር ነጋ ንግግር የአማራን ሕዝብ የኅልውና ትግል ለማይጠረቃ ግለሰባዊ የሥልጣን ፍትወቱ መጠቀሚያነት እንጅ በእውነት ለአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል የወጣ ታጋይ አለመሆኑን ዳግም አረጋግጦልናል። ምክንያቱም የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መሬት ላይ የሌለ የትግላችን መከፋፈያነት መጠቀሚያ ካርድ ለመሆኑ በየቀጠናው የሚገኙ ፋኖዎችን ጫፍና ጫፍ አቁሞ እስከማታኮስ የዘለቀ ርካሽ የፖለቲካ መቆመሪያ ድርጅት ስለመሆኑ የትናንት ገሐዳዊ ሁነቶች ያረጋግጣሉ።
ድርድርም ውይይትም በመርኅ ላይ የተመሠረተ፣ ሐቀኛ የፖለቲካ ውክልናን የያዘ፣ የትግሉ መሠረተ ሃሳቦች ላይ የቆመ፣ የትግል ፍኖተ ካርታን በግልጽ በማስቀመጥ እነዚህን ሳይነጣጠሉ ሃሳብን የማቅረቢያ አመከንዮዎችን፣ ገሐዳዊ ሐቆችን ያለአንዳች የፖለቲካ ውስልትና በማቅረብ የሕዝብ ጥያቄ ማሸነፍ የሚችልባቸውን መደላድሎች መፍጠር ነው። ቅሉ አቶ እስክንድር ነጋ፣ ረ/ፕ/ር ጌታ አስራደ፣ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፣ ኮሎኔል ፋንታሁን ሙሃቤ እና ከሸዋ አንድ ግለሰብ በጋራ የተገኙበት ሸንጎ በመርኅ ደረጃ የድርድርን መሠረተ ሃሳቦችን ያላሟላ መሆኑን ማረጋገጥ እንወዳለን።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በዚህ የንግግር ሂደት ላይ የተገኙ ዓለምአቀፍ ተቋማት መሬት ላይ ከሌለ ስብስብ ጋር መቀመጣቸው ሥርዓታዊ የዘር ማጥፋት ድርጊት እየተፈጸመበት ያለውን የአማራን ሕዝብ ያላከበረና የማይመጥን አካሄድ በመሆኑ በቀጣይ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ሐቀኛ እንዲሁም አካታች ውክልና ከሚሰጣቸው ልሂቃን ጋር ብቻ እንዲሆን መግለጥ እንወዳለን።
በጥቅሉ ዳውንት ላይ የተካሄደው ድርድርም ይሉት ውይይት ሠራዊታችን የማያውቀው ምናልባትም የሚያወግዘው፤ ሕዝባችንን ያሳዘነ የፖለቲካ ቁማር ነው። ይህንን በድፍረት ለማለት የሚያስገድደን ጉዳይም ከእውነት የራቁ ድርጅታዊ ተረኮች (90% የፋኖ ኃይል የድርጅታችን አካል ነው፣ የወከልነውም ይህንን ግዙፍ ኃይል ያለው ፋኖ ነው) የሚሉ፣ የመርኅ፣ የፖለቲካ ውክልና፣ የተዓማኒነት እንዲሁም የአካታችነት የሚሉት ጥያቄዎችና መሰል ጉዳዮች ሲነሱ ውሃ የሚያነሳ ምላሽ የለም።
መላው የአማራ ሕዝብ፣ መላው ሠራዊታችን፣ የሚዲያ አካላት ይህ ጉዳይ በቀላል የሚታይ ባለመሆኑ የአማራ ፋኖ በሸዋ፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር፣ የአማራ ፋኖ በጎጃም፣ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ) እና የአማራ ፋኖ ቢዛሞ እዝ ሕዝባችንን ለዳግም ባርነት አሳልፎ የሚሰጥ አደረጃጀትንም ሆነ አስተሳሰብ አጥብቀን ከማውገዝ ባሻገር የምንታገለው ጉዳይ ነው።
የአማራ ፋኖ በጎጃም
የአማራ ፋኖ በሸዋ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ)
የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር እና
የወለጋ ክፍለ ሃገር ፋኖ እዝ (ቢዛሞ)
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
