ru
Feedback
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

Открыть в Telegram

« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

Канал 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀 (@https_asselefya1) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 14 271 подписчиков, занимая 6 112 место в категории Религия и духовность и 2 369 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 14 271 подписчиков.

Согласно последним данным от 05 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -16, а за последние 24 часа — -1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 16.47%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 8.83% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 2 351 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 261 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 0.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 06 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

14 271
Подписчики
-124 часа
+147 дней
-1630 день
Архив постов
በገዛ እጃቸዉ ያጡን ሰዎች የኛ ማንነት የሚያቁት ርቀን ሄደን እኛ ስንረሳቸዉ እና የኛ ቦታ የሚተካ ሰዉ ሲያጡ ነዉ። ምንም ማድረግ አይቻል። ማጣት የማትፈልጉትን ሰዉ ከማጣታችሁ በፊት ጥንቃቄ አድርጉ በንግግራችሁ በተግባራችሁ......! ከሄደ በኋላ ተመልሶ አይመጣም.....! 🌸💎🌸

نورٌ للقلب || الشيخ: عبدالرزاق البدر

ሁን ለናትህ<=====>መከታ እውቀትን<=====>ፈላጊ በትንሽ<=====>ተብቃቂ ለጓደኛህ<=====>ታማኝ ለዲንህ<=====>ተቆርቋሪ በችግር ግዜ<=====>ታጋሽ በትግል ግዜ<=====>ብርቱ ለሱኒዎች<=====>ምቹ ለሙብተዲዎች<=====>እሬት ለድሆች<=====>አሳቢ ለተቸገረ<=====>ረጅ ግዴታህን<=====>ተወጭ መብትህን<=====>ተጠቃሚ ወላጆችህን<=====>ታዛዥ ትልቅህን<=======>አክባሪ ለትንሽህ<=======>አዛኝ ጌታህን<=====>አመስጋኝ ሁን ✍ኢብኑ ሙሀመድዘይን

እንድህ አይነት ፍቅር ይስጣችሁ! | ~የቀይስና የሉብና ፍቅር ግን ዐጂብ ነው። ከስንት ትግልና መስዋትነት በኋላ ቀይስ ሉብናን አግብቶ ፍቅሩን እያጣጣመ በደስታ ይኖር ነበር። መውለድ ባለመቻሏ ምክንያት የኋላ ኋላ ሀብታሞቹ የቀይስ ቤተሰቦች ከፍተኛ ተፅእኖ አደረጉበት። ከሉብና ጋር ላለመለያየት ብዙ ታገለ። ግን እናትም አባትም በፈጠሩበት ወደር አልባ ጫና የሚያፈቅራትንና የምታፈቅረውን የልቡን ንግስት ፈታት። የቀይስ የህይወቱ ብልሽት ከዚሁ ሀ ብሎ ጀመረ።ሉብና ሳትወድም ቢሆን ሌላ አገባች። ቀይስ ግን አግብታም ልቡ ሉብና ጋር እንደተጣመረ ነው። ከሉብና ውጭ ሴት የምትባል አትታየውም።ኋላ ላይ ሉብና ከዚህኛው ባሏም ጋር ተፋታች።ቀይስና የቀይስን ከሰውነት ውጭ መሆን የተመለከቱት ወላጆቹ የሉብናን ዒዳ መጠናቀቅ ይጠብቁ ጀመር። ዳግም ለማጋባት። ሉብና ግን ዒዳዋን ሳታጠናቅቅ ሞተች። ይህን ከባድ ዜና የሰማው ቀይስ…እኔና ሉብና ከመፈጠራችን በፊት ሩሃችንም፣ በዱንያ አካላችንም የተጣመሩ ናቸው። ሉብና ከሞተች እኔም ሞቼ አብሪያት ልኑር እያለ እየገጣጠመ እሷ በሞተች በሶስተኛው ቀን እሱም ሞተ። ماتَت لُبَينى فَمَوتُها مَوتي هَل تَنفَعَن حَسرَةٌ عَلى الفَوتِ وَسَوفَ أَبكي بُكاءَ مُكتَإِبٍ قَضى حَياةً وَجداً عَلى مَيتِ =t.me/AbuSufiyan_Albenan

«ትዳርሽን ከፈለግሽው አታድርጊው‼️ ➥ባለትዳር ሴቶች ከሌሎች ወንዶች ጋር ማድረግ የማይገባቸው ጥብቅ ጉዳዮች 1. ሌላ ወንድ ገንዘብ መጠየቅ 2. ከሌላ ወንድ ጋር ለብቻ ጊዜ ማሳለፍ 3. ከወንዶች ጋር ያለማቋረጥ መወያየት 4. ለሌሎች ወንዶች ትኩረት መስጠት 5. ከባልሽ ይልቅ ሌላ ወንድ ማክበር 6. ሌሎች ወንዶችን ውዴ ፤ማሬ ፣ የኔውድ ፣ ወዘተ ብለሽ መጥራት 7. ከሌሎች ወንዶች ጋር መቅበጥ ፤ መሽኮርመም 8. የትዳር ጓደኛን ከሌላ ወንድ ጋር ማወዳደር 9. ስለ ሌሎች ወንዶች በልብ ማሰብ 10. ሌሎች ወንዶችን መንካት 11. ሌሎች ወንዶችን ማቀፍ 12. ከባልሽ ይልቅ ለሌላ ወንድ ቅድሚያ በሚሰጡ ተግባራት መሳተፍ 13. ሌሎችን ሰዎች የቅርብ ጓደኛ ማድረግ 14. ከባልሽ ጋር ያለሽን የጠበቀ ግንኙነት ለሌሎች ሰዎች መንገር 15. ማህበራዊ ሚዲያን አላግባብ መጠቀም 16. ከቀድሞ የፍቅር አጋር ጋር መገናኘት 17. በትዳራችሁ ውስጥ የሚያጋጥሟችሁን ፈተናዎች ለሌሎች ወንዶች መንገር። በተቃራኒው ላገቡ ወንዶችም ተፈጻሚ ይሆናሉ ስንቶቻችን እንተገብራቸዋለን⁉️ http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi

በጊዜ ተንፍስ ~ አንዳንድ ወንድሞች በሆነ የዒልም ዘርፍ ከእኩዮቻቸው ሲበልጡ ወይም የበለጡ ሲመስላቸው ትእቢት ሲፈትናቸው ይታያሉ። አንዱን መናቅ፣ ያኛውን ማጣጣል፣ ሌሎችን በመገምገም ራስን ከፍ ከፍ ማድረግ ላይ ይጠመዳሉ። የሸሪዐ እውቀት አላህን መፍሪያ መሳሪያ መሆኑ ሁሌም ሊዘነጋ አይገባም። ማወቅህ ትእቢት ካወረሰህ፣ በማወቅህ ለሌሎች ንቀትን ካዳበርክ ወላሂ ማወቅህ ጎድቶሃል። ጅህልና ላንተ የተሻለ ነበር። ሰው ቴኳንዶ ሰልጥኖ ቀድሞ ያልነበረውን አደብ ሲላበስ በምናይበት ጊዜ የሆነን ዒልም ሲማር እብሪትና ንቀትን የሚያዳብር ማየት አሳፋሪ ነው። ወንድሜ ሆይ! መከበር ከፈለግክ ሰዎችን አክብር። ሌሎችን መናቅ ምናልባት ጥቂት ጊዜ ቢያስከብር ነው። ወይ ሰዎች እስከሚነቁ፣ ወይ ደግሞ ማንነትህ እስከሚገለጥ ድረስ ቢዘልቅ ነው። ከዚያስ? ከዚያማ መናቅህ መንናቅን ነው የሚያስከትልብህ። መተንፈስህ ላይቀር አፀፋ ሳያስተነፍስህ በፊት አላህን ፈርተህ ተንፍስ። በጊዜ ተንፍስ። አዎ መተንፈስ ይሻልሃል። = የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor

ምን አይነት ሰው ነህ.mp31.00 MB

በሰው ትዳር እየገባችሁ የሰው ትዳር ለምታፈርሱ ለምትበጠብጡ ሰዎች ትንሽ ምክር በእስልምና በሌሎች ትዳር ጉዳይ ያለ አግባብ መግባት በጥብቅ የተወገዘ ተግባር ነው። በትዳር መካከል ችግር መፍጠር፣ ጥላቻን መዝራት እና የትዳርን ደስታ ማደፍረስ ትልቅ ወንጀል ነው። እስልምና የሰዎችን ግላዊነት ማክበርን፣ መልካምን ነገር መመኘትን እና ከማንኛውም ዓይነት ጉዳት መራቅን ያስተምራል።) •  ኡለሞች በሌሎች ትዳር ውስጥ ያለ አግባብ ጣልቃ መግባት ትልቅ ኃጢአት እንደሆነ ይናገራሉ። ነብዩ ሙሐመድ ﷺ) "ሰዎችን በማሳሳት ሚስትን ከባሏ ወይም ባልን ከሚስቱ የሚያለያይ ከእኛ አይደለም" ብለዋል። ይህም በሰው ትዳር መካከል እየገቡ አለመግባባትን የሚፈጥር ወይም ትዳርን የሚፈታተን ማንኛውም ተግባር መፈፀም የተወገዘ መሆኑን ያሳያል። •  በተጨማሪም ኡለሞች እንዲህ ዓይነቱ ጣልቃ ገብነት በቤተሰብ ውስጥ አለመረጋጋትን እንደሚያመጣ፣ የዝምድናን ትስስር እንደሚጎዳ እና ጥላቻን እንደሚያሰፍን ያስጠነቅቃሉ። በሰው ትዳር ውስጥ መካሪዎች መስለን ከመግባታችን በፊት እነዚህን ነገሮች ማሰብ ይኖርብናል 1. ራስን መግዛት እና ወሰንን ማወቅ (ضبط النفس ومعرفة الحدود):   •  የትዳር ምክር ካልተጠየቅክ በስተቀር ዝም በል።   •  ምክር ብትሰጥም እንኳ ገንቢ እና ችግር ፈቺ መሆን አለበት።   •  በምንም ዓይነት ሁኔታ የትዳርን ሚስጥር አታውጣ። 2. በጎ ሀሳብ (حسن النية):   •  ሁልጊዜ መልካም ነገር አስብ።   •  የሰዎችን መልካም ጎን ለማየት ሞክር።   •  በሰዎች መካከል ችግር ከመፍጠር ይልቅ መፍትሔ ለመፈለግ ተነሳሳ። 3. ጥንቃቄ (الحذر):   •  የትዳር ችግር ውስጥ በቀላሉ አትግባ።   •  ለችግሩ መንስኤ የሆንክ እንዳትሆን ተጠንቀቅ።   •  ጣልቃ የምትገባበትን ሁኔታ በጥንቃቄ መርምር። 4. ምክር መስጠት ካለብህ:   •  በቁርኣን እና በሐዲስ ላይ የተመሰረተ ምክር ስጥ።   •  ሁለቱንም የትዳር አጋሮች ለመስማት ዝግጁ ሁን።   •  በፍቅር እና በርህራሄ ተናገር።   •  ችግሩን ለማባባስ ሳይሆን ለመፍታት ሞክር። 5. ዱዓ (ጸሎት):   •  ለተጋቢዎች መልካም እንዲሆን አላህን ለምነው።   •  ትዳራቸውን እንዲባርክና እንዲጠብቅ ዱዓ አድርግ። በሌሎች ትዳር ውስጥ ጣልቃ መግባት በእስልምና የተወገዘ ተግባር ነው። ከዚህ ተግባር በመራቅ፣ ራስን በመግዛት፣ በጎ ሀሳብን በማሰብ እና ጥንቃቄ በማድረግ ለሰዎች ደስታ እና ለቤተሰብ ሰላም አስተዋጽኦ ማድረግ እንችላለን። አላህ ሁላችንንም በትክክለኛው መንገድ ይምራን! ወንድማችሁ አቡ ሂበቲላህ... https://t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

ወጣ እንበል ከኩሽና እሁድ አይደል ሰላም ዋሉ🫂 =

لذة ترك المعصية || الشيخ : عبدالرزاق البدر .

የያዝነዉን ነገር ስኬት ለማድረስ ጥርስን ንክስ አድርጎ ጠበቅ አድርጎ መያዝ አንዱ የስኬት ቁልፍ ነዉ። ያዝ ለቀቅ ከሆነ ስኬቱ አያረካም። ነገር ግን አጥብቀን ይዘን ከለፍን ስኬቱ ሲያስደሳ ከልክ በላይ ነዉ። በነገራቶች ላይ አላህ ፀናት ይስጠን!!

«لَا الشَّمْسُ يَنْبَغِي لَهَا أَنْ تُدْرِكَ الْقَمَرَ وَلَا اللَّيْلُ سَابِقُ النَّهَارِ وَكُلٌّ فِي فَلَكٍ يَسْبَحُونَ » =

Repost from Ibnu Muhammedzeyn
ልብ ያለው ልብ ይበል አንድ ነገር ሀራም ከሆነ ባሌ፣ወንድሜ፣እህቴ፣እናቴ፣አክስቴ፣ዘመዴ፣ጓደኛየ እና ሌሎችም አዘውኛል ተብሎ ሀራም ነገር አይሰራም ለዚህም መረጃው ነብዩ ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም "ፈጣሪን በማመፅ ፉጡርን መታዘዝ የለም" የሚለው ወርቃማ ንግግር ነው። ✍ ኢብኑ ሙሀመድዘይን

((ኢማንን ማደስ! ቁ 1)) የሰው ልጅ በዚህ አለም ሲኖር ከሚያሳስቡት ነገር ሁሉ ሊያሳስበው የሚገባው የኢማኑ ጉዳይ መሆን አለበት! ነፍስ ከምከስበው ትልቁ ነገር ቢኖር ኢማን ነው። አንድ ባሪያ በኢማን ሰበብ በዱኒያም ይሁን በአኼራ ትልቅ ቦታን ያገኛል። እንደውም የዱኒያም ይሁን የአኼራ መልካም ነገር በኢማን የተገደበ ነው። ኢማን ይህ ከሆነ እያንዳንዳችን ኢማናችንን መከታተል ግድ ይለናል! እውን ኢማናችን እየጨመረ እና የጠነከረ ነውን? ወይንስ በተቃራኒው እየቀነሰ እና እየተዳከመ ነው? ኢማን ማንኛውንም ነገር ከማደስ የበለጠ ማደስን ይፈልጋል! ኢማንን ብዙ የሚያዳክሙት ነገሮች አሉ ለምሳሌ:- የዱኒያ ፊትና፣የሰይጣን ወስዋስ፣መጥፎ ጓደኛ፣መጥፎ ቅልቅል(አላህ የሚታመፅበትን ሰርግ ይመስል)፣በመጥፎ የምታዝ ነፍስ እና ሌሎችም ኢማንን የሚያደክሙ ከዚህም አልፈው ከመሰረቱ የሚያጠፉት ነገሮች አሉ። መልእክተኛው ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲ ይላአሉ:- "ኢማን ከናንተ በአንዳችሁ ሆድ ውስጥ ልክ ልብስ እንደሚያልቀው(እንደሚያሩገው) ያልቃል(ያሩጋል) አላህ በቀልባችሁ ውስጥ ኢማንን እንዲያድስላችሁ ለምኑት" አልባኒ ሶሂህ ብለውታል(ሲልሲለቱ ሶሂህ ቁ 1585) መልእክተኛው ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም በዚህ ሀዲስ አላህ በቀልባችን ውስጥ ኢማንን እንዲያድስልን እንድንለምነው አዘውናል! አዎ ነገሩ ጠንከር ብለን በእውነተኛ ቀልብ ችክ ብለን ዱአ ማድረግ ያስፈልገዋል! ለነገሩ የሁለት አገር የደስታ መሰረት የሆነው ኢማን ችክ ተብሎ ያልተለመነውን ምን ይለመናል? በዚህ አለም ካሉ በጣም ውድ ከሆኑ ነገሮች ሁሉ ውዱ እና የውዱች ቁንጮ የሆነው ኢማናችን ስለሆነ ኢማናችንን ከሚያዳክሞት ነገር መጠንቀቅ ያስፈልጋል ። ኢማንን ያጣ በጣም ትልቅ ነገርን አጥቷል በርግጥም ዱኒያ አኼራውን ኸስሯል። እውነተኛ ሂወትንም እየኖረ አይደለም መብላት፣መጠጣት፣መቆም እና መተኛት… ይህ የሀቂቃ ትክክለኛ ሂወት አይደለም ይህማ ሂይወት ከሆነ ከሀያው፣ከበጉ በጥቅሉ ከእንሰሳ በምን እንለያለን? እነሱም እንደኛው ይበላሉ፣የጠጣሉ ወ… ወ… ታዲያ ምንድነው ልዩነታችን? ትክክለኛ ሂወት ማለት አር-ረህማንን መታዘዝ መልእክተኛውን (ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) መከተል ነው። አላህ እንዲህ ይላል"እናንተ ያመናችሁ ሆይ (መልእክተኛው) ህያው ወደሚያደርጋችሁ (እምነት) በጠራችሁ ግዜ ለአላህ እና ለመልእክተኛው ታዘዙ" (አንፋል 24) ሰለፎች ኢማናቸውን ለማደስ ትልቅ ትግል ያደርጉ ነበር ! ኡመር ኢብኑል ኸጧብ (ረዲየላሁ አንሁ) ለባልደረቦቹ "ኑ (ተሰብሰቡ) ኢማናችንን እንጨምር" ይል ነበር (ኢብኑ አቢ ሸይባ 11/26) ከላይ ያለውን የኡመርን ንግግር ሸይኽ አብዱረዛቅ አል-በድር እንዲህ ሲሉ ያብራሩታል "ጀነትን፣እሳትን፣የአላህን ቃልኪዳን እና ዛቻውን በማውሳት ኢማናችን እስኪጨምር ድረስ እንቀመጥ" ምንጭ ( ተጅዲዱል ኢማን ገፅ 4) አብዱላህ ኢብኑ መስኡድ (ረዲየላሁ አንሁ) "አላህ ሆይ ኢማንን፣(የዲን) ግንዛቤን እና የቂንን ጨምረኝ) ይሉ ነበር።(አስ-ሱናህ 1/368) አቡ ደርዳእ (ረዲየላሁ አንሁ) "(ኢማኑ) እየጨመረ እና እየቀነሰ መሆኑን እንድሁም የሰይጣን ተንኮል በምን በኩል እንደሚመጣው (አንድ ሰው) ማወቁ ከግንዛቤ(ፊቅህ) ጭምርት ነው" ይላሉ (ኢባና 2/ 849) አንድ ሰው ኢማኑ መቀነሱን እና መጨመሩን ማወቁ በራሱ የሚወደስ ነገር ነው ብዙ ሰዎች ኢማናቸው ሳያስተውሉት ቀንሱ ቀንሱ ከነአካቲው እስከሚያልቅም አያውቁትም አላህ ይጠብቀን እና ገፍላ ማለት እሄ ነው። ((እኛ እርስ በእርሳችን ስንገናኝ ኢማናችን እንዲጨምር ልክ እንደ ሱሀቦች ተዋውሰን እናውቃለን? የኢማናችን ጉዳይ አስጨንቆን አላህ ኢማናችንን እንዲያድስለን እና እንዲጨምርልንስ ዱአ እየደረግን ነውን? እያንዳንዳችን ነፍሳችንን እንጠይቅ ነፍሳችንን እንተሳሰብ)) ኡመይር ኢብኑ ሁበይብ "ኢማን ይጨምራል ይቀንሳል" ይሉ ነበር የሚጨምረው እና የሚቀንሰው እንዴት ነው ተባላቸው? "አላህን ባወሳን፣ባመሰገን እና ባጠራን ግዜ(ይህ ኢማንን ይጨምራል) (ከአላህ)በተዘናጋን እና በረሳን ግዜ (ኢማን ይቀንሳል" በማለት መለሱ (አጥ-ጦበቃት 4/381) ኢማሙል አውዘኢይ (ረሂመሁላህ) ኢማን ይጨምራልን ተብለው ተጠየቁ እርሰዎም "አዎ ተራራ እስከሚያክል (ይጨምራል)" አሉ ኢማን ይቀንሳልን? ተብለው ሲጠየቁ "አዎ ከእርሱ ምንም እስከማይቀር ይቀንሳል" በማለት መለሱ (አስ–ሱናህ 5/959) ከሱሀቦች ከታብእዮች እነሱንም በመልካም ከተከተሉ ታላላቅ አኢማዎች በኢማን ዙሪያ የተዘገበ እጅግ በጣም ብዙ ነው። የኢስላም ታላላቅ አኢማዎችን ከድሩ እስከ ዘንድሩ ያሉትን ታሪካቸውን ብንከታተል ኢማናቸውን ለማደስ የሚያደርጉትን ጥረት እና ክትትልን ፍንትው አድርጎ ያሳየናል። ኢማንን ማደስ እንዲህ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን ታወቅን ከውስጣችን ኢማንን የሚጨምሩ እና የሚቀንሱ ነገሮች ምንድን ናቸው? የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም! በቀጣይ ፅሁፌ ኢማንን የሚጨምሩ እና የሚቀንሱ ነገሮችን ኢንሻ አላህ አቀርብላችኋለሁ ይቀጥላል… ወንድማችሁ ኢብኑ ሙሀመድዘይን (ህዳር 28/2010) ​•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈• http://t.me/IbnuMuhammedzeyn

የጥፋቶች መጀመሪያ.mp33.97 KB

ስነ ስርአት እንያዝ.mp32.07 KB