ru
Feedback
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

Открыть в Telegram

« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

Канал 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀 (@https_asselefya1) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 14 290 подписчиков, занимая 6 170 место в категории Религия и духовность и 2 361 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 14 290 подписчиков.

Согласно последним данным от 19 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -68, а за последние 24 часа — 5, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 16.84%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 8.14% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 2 407 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 164 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 0.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 20 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

14 290
Подписчики
+524 часа
+347 дней
-6830 день
Архив постов
ማታ ቤይሩት ላይ የተሰማዉ የማስፈራሪያ ድምፀ በድንጋጤ እንድህም የለበሰ ነበረ....! አይ ኢስራኢል አላህ የሚገባሺን ይስጥሽ!
ማታ ቤይሩት ላይ የተሰማዉ የማስፈራሪያ ድምፀ በድንጋጤ እንድህም የለበሰ ነበረ....! አይ ኢስራኢል አላህ የሚገባሺን ይስጥሽ!

• አንዳንዴ ሂወት መልመድ የከበደንን ነገር የግድ እንድንለምድ ታስገድደናለች! =

ፋጢማ ቢንት ሙሐመድ፣ አባቷን መሳይ፣ የሴት አይነታ ~ 1. አባቷ የፍጡር ቆንጮ የሆኑት ነብያችን ﷺ ናቸው። 2. እናቷ የነብያችን የመጀመሪያ ሚስት፣ በፈተናቸው ጊዜ ከጎናቸው የቆመች፣ ወደ ኢስላም በመግባት ቀዳሚ የሆነችዋ ኸዲጃ ቢንት ኹወይሊድ ናት። 3. ባሏ አራተኛው ኸሊፋ አንበሳው ዐሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ ናቸው። 4. ልጆቿ የጀነት ወጣቶች አይነታዎች የሆኑት ሐሰንና ሑሰይን ናቸው። 5. እሷ ራሷ ደረጃዋ ከፍ ያለ ታላቅ የታላቅ ልጅ ናት። ፋጢማ * ከነብያችን ﷺ ልጆች መጨረሻ የሞተች ናት። * በ24 አመቷ ከነብዩ ﷺ ሞት ከሰባት ወር በኋላ ዱንያን ተሰናብታለች። * የነብያችን ﷺ ዘር የቀጠለው በሷ በኩል ነው፣ በሐሰን እና በሑሰይን በኩል። እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ብላለች፦ أقبَلَت فاطِمةُ تمشي كأنَّ مِشْيَتَها مَشْيُ النَّبِيِّ ﷺ، فقال النَّبِيُّ ﷺ: ((مَرْحبًا يا ابنتي))، ثُمَّ أجلَسَها عن يمينِه -أو عن شِمالِه- ثُمَّ أسَرَّ إليها حديثًا، فبَكَت، فقُلتُ لها: لمَ تَبكِينَ؟ ثُمَّ أسَرَّ إليها حديثًا فضَحِكَت، فقُلتُ: ما رأيتُ كاليومِ فَرَحًا أقرَبَ مِن حُزنٍ! فسألْتُها عمَّا قال، فقالت: ما كُنتُ لأُفشيَ سِرَّ رَسولِ اللهِ ﷺ، حتى قُبِضَ النَّبِيُّ ﷺ فسألتها، فقالت: أسرَّ إليَّ ((أنَّ جِبريلَ كان يعارِضُني القرآنَ كُلَّ سَنَةٍ مَرَّةً، وإنَّه عارَضَني العَام مرَّتينِ، ولا أراه إلَّا حَضَر أَجَلي، وإنَّكِ أوَّلُ أهلِ بَيتي لَحاقًا بي))، فبَكَيتُ، فقال: ((أمَا تَرضَينَ أن تكوني سَيِّدةَ نِساءِ أهلِ الجنَّةِ -أو نِساءِ المُؤمِنين- فضَحِكْتُ لذلك )) ​"ፋጢማ እየተራመደች መጣች፤ አረማመዷ ልክ እንደ ነቢዩ (ﷺ) አረማመድ ነበር። ነቢዩም (ﷺ) 'እንኳን ደህና መጣሽ ልጄ' አሏት። ከዚያም በቀኛቸው ወይም በግራቸው በኩል አስቀመጧት። ከዚያም በጆሮዋ ምስጢር ነገሯት፣ አለቀሰች። እኔም 'ለምንድነው የምታለቅሽው?' አልኳት። ከዚያም ደግመው ሌላ ምስጢር ነገሯት፣ ሳቀች። እኔም 'እንደ ዛሬው ለሀዘን ቅርብ የሆነ ደስታ አይቼ አላውቅም!' አልኩ። ምን እንዳሉ ጠየቅኳት። 'የአላህ መልክተኛን (ﷺ) ምስጢር አላወጣም' አለች። ​ነቢዩ (ﷺ) ከዚህ ዓለም እስካለፉ ድረስ ምስጢሩን አልተናገረችም ነበር። ከዛ በኋላ ጠየቅኳትና እንዲህ አለች፦ 'መጀመሪያ የነገሩኝ ምስጢር፦ 'ጅብሪል በየዓመቱ ቁርአንን አንድ ጊዜ ያቀርብልኝ ነበር፤ ዘንድሮ ግን ሁለት ጊዜ ነው ያቀርብልኝ። ይህ የሚያሳየው መሞቻዬ መቃረቡን ነው። አንቺም ከቤተሰቦቼ ውስጥ ቀድመሽ እኔን የምትከተይ ነሽ' የሚል ነበር፤ በዚህም ምክንያት አለቀስኩ። ​ከዚያም ደግመው፦ 'የጀነት ሴቶች አለቃ (ወይም የምእመናን ሴቶች ዋና) በመሆንሽ ደስ አይልሽም?' አሉኝ፤ በዚህ ጊዜ ደግሞ ሳቅኩ።'" [ቡኻሪይ፡ 3623፣ 3624] [ሙስሊም፡ 2450] እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ እን ዳለችው ፋጢመህ አቋቋሟም፣ አቀማመጧም፣ ሁሉ ነገሯ አባቷን መሳይ ነበረች። ትቀጥላለች ዓኢሻህ وكانت إذا دخَلَت على النبيِّ ﷺ قام إليها فقَبَّلَها وأجلَسَها في مجلِسِه، وكان النبيُّ ﷺ إذا دخل عليها قامت من مجلِسِها فقَبَّلَتْه وأجلَسَتْه في مجلِسِها ​"እሷ (ፋጢማ) ወደ ነቢዩ (ﷺ) ዘንድ በገባች ጊዜ እሳቸው ተነስተው ይቀበሏታል፤ ይስሟትም ነበር፤ ከዚያም እሳቸው በተቀመጡበት ቦታ ያስቀምጧታል። እንዲሁም ነቢዩ (ﷺ) ወደ እሷ (ቤት) በገቡ ጊዜ እሷ ከመቀመጫዋ ተነስታ ትቀበላቸዋለች፤ ትስማቸውም ነበር፤ ከዚያም እሷ በተቀመጠችበት ቦታ ታስቀምጣቸዋለች።" [አቡ ዳውድ፡ 5217] [ቲርሚዚይ፡ 3872] (ኢብኑ ሙነወር፣ ሸዋል 9/1447) = የቴሌግራም ቻናል :- https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

ወንድማችን ሙሐመድ አህመድ... 📢በቴሌግራም ላይ ካሉና ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ ኡማውን በታላቅ አገልግሎት እየጠቀሙ ካሉ ቻናሎች መካከል ቀዳሚውና ተጠቃሹ፦ https://t.me/MOhamedAljawi https://t.me/MOhamedAljawi ነው። በሺዎች የሚቆጠሩ የኢልም ፈላጊዎችን መንገድ እያቀለለ ይገኛል።  የዚህ ቻናል ባለቤት ወንድማችን ሙሐመድ አህመድ አል-ጃዊ ይባላል። በተለያዩ የሱና ኡስታዞች የሚሰጡ ደርሶችን ከተበታተኑ ቻናሎች ይሰበስባል፤ ድምፁን ጥራት ባለው መልኩ ያቀናጃል (አላስፈላጊ ድምፆችን ያስወግዳል)፤ የፋይሉን መጠን (MB) ይቀንሳል፤ ከዚያም በላይ ደርሱን የሚከታተሉ ተማሪዎች እንዳይቸገሩ ምርጥ የሚባሉ የኪታብ ኑስኻዎችን (PDF) ከሪከርዱ ጋር አያይዞ ያቀርባል። የእሱ ስራ ከቴሌግራም ቻናል አልፎ «ዒልም ፈላጊ» የተሰኘውን በሺዎች የሚቆጠር የድምፅ ፋይሎችን የያዘውን እጅግ ሰፊና ዘመናዊ አፕሊኬሽን የሚያስተዳድረው ይሄው ወንድማችን ነው። ይህንን ሁሉ ግዙፍ ስራ፣ ይህን ሁሉ ዳታቤዝ እና ይህን ሰፊ አፕሊኬሽን ሙሐመድ የሚያስተዳድረው ክፍለ ሀገር ሆኖ በአንዲት ስልክ ብቻ ነው! ⚠️ስለዚህ...ይህ ወንድማችን ስራውን ይበልጥ እንዲያቀላጥፍ፣ የዳዕዋውን ጥራት እንዲጨምርና ኡማውን በተሻለ ደረጃ እንዲያገለግል አንድ ዘመናዊ ላፕቶፕ ልንገዛለት አቅደናል። ይህ ተግባር ታላቅ «ሰደቃ ጃሪያ» ነው። እሱ በሚያዘጋጃቸው ደርሶች አንድ ሰው እውቀት ባገኘ ቁጥር፣ በእርስዎ ድጋፍ በተገዛው ላፕቶፕ ስራው በሰፋ ቁጥር የእርስዎም የነገ የአኼራ ስንቅ አብሮ ይከማቻል። ⌨️ስለዚህ…እኔ ጋር ያለ ተጨማሪ ላፕቶፕ አለኝ የምትሉ ካላችሁ በቀጥታ ከእሱ ጋር እናገናኛችኋለን። 🎁ወይም በገንዘብ ድጋፍ አድርጌ በጋራ እንግዛ የምትሉ ኸይር ፈላጊዎች በሙሉ.. —ይህ የ ወንድማችን አካውንት ነው። አካውንት፦1000343460377 ስም፦ ሙሐመድ አህመድ ከዛ ደረሰኙን በውስጥ ላኩልኝ'ማ ወርቆቼ! @AbuSufyan65 @AbuSufyan65

✓ ሕይወት አስተማረችኝ • የሰው ልጅ ለተባለ ሁሉ መልካምን ነገር እመኛለሁ። • ሌሎችን ለማስደሠት መጣሬ ከደስታዬ ምንም ነገር አይቀንስብኝም። • የሌሎች ሀብታም መሆን ከሲሳዬ አንድም ነገር አያጎድልም። ~ የሌሎች ጤና መሆን የኔን ጤና አይወስድብኝም። ~ አላህ ሁላችንም ደስተኞች ያርገን። = t.me/https_Asselefya1

قراءة_مميزة_وهادئة_سورة_الكهف_الشيخ_عبدالحليم_حسين_Sh_Abdualhalim.mp39.19 MB

•ይገርመኛል የአላህ ሥራ። የሆነ ጊዜ እጅግ ስንመኘው የነበረ ነገር ድንገት ለሱ ያለን ፍላጎት በውስጣችን ይሞታል። =

ጀርባ ቆራጭ ዝና ፍለጋ.mp31.40 MB

የሸዋል ዒድ (ትንሹ ዒድ) ~ በኢስላም አመታዊ ዒዶቻችን ሁለት ናቸው። ማስረጃውም አነስ ብኑ ማሊክ ረዲየላሁ ዐንሁ ያስተላለፉት ሐዲሥ ነው። ነብዩ ﷺ መዲና ሲመጡ ነዋሪዎቿ የሚጫወቱባቸው ሁለት ቀናት
የሸዋል ዒድ (ትንሹ ዒድ) ~ በኢስላም አመታዊ ዒዶቻችን ሁለት ናቸው። ማስረጃውም አነስ ብኑ ማሊክ ረዲየላሁ ዐንሁ ያስተላለፉት ሐዲሥ ነው። ነብዩ ﷺ መዲና ሲመጡ ነዋሪዎቿ የሚጫወቱባቸው ሁለት ቀናት ነበሯቸው። “ምንድን ናቸው እነዚህ ሁለት ቀናት?” ብለው ጠየቁ። “በጃሂሊያው ጊዜ እንጫወትባቸው ነበርን” አሉ። በዚህን ጊዜ የአላህ መልእክተኛ ﷺ “የላቀው አላህ ከነሱ በላጭ በሆኑ ሁለት ቀናት ተክቶላችኋል። እነሱም የአድሓ ቀንና የፊጥር ቀን ናቸው” አሉ። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 1039] “ተክቶላችኋል” የሚለው አነጋገር የሙስሊሞች ዒዶች የተወሰኑና፣ በሸሪዐ የሚደነገጉ እንደሆኑ ጥቆማ ይሰጣል። የሰለፎቻችን አካሄድም ይህን ግንዛቤ ይበልጥ ያጠነክራል። ኋላ ላይ እንግድ ቢድዐዎች እስከሚመጡ ድረስ ነብዩ ﷺ ከደነገጓቸው ዒዶች ውጭ ሌላ ዒድ አልተንፀባረቀም። በተለይም ደግሞ ነብዩ ﷺ “ከሰው ሁሉ በላጩ የኔ ትውልድ ነው። ከዚያም ከእነሱ ቀጥለው የሚመጡት፤ ከዚያም ከነሱ ቀጥለው የሚመጡት” ብለው ምስክርነት የሰጡት ሶስቱ ወርቃማ ዘመን ውስጥ እንዲህ አይነት ነገር አልነበረም። ኋላ ላይ ከመጡ እንግዳ በዓላት ውስጥ አንዱ ታዲያ የሸዋል ዒድ የሚባለው ቢድዐ ነው። ይሄ በአል በሸሪዐ ቦታ ቢኖረው ኖሮ በቁርአንና በሐዲሥ ውስጥ ይጠቀስ ነበር። ቁርአንና ሐዲሥ ውስጥ ከሌለ፣ ቀደምቶች ካላወቁት ቢድዐ ከመሆን ውጭ ሌላ ምርጫ የለም። ነብዩ ﷺ “ወደ ጀነት የሚያቀርባችሁና ከእሳት የሚያርቃችሁ ሆኖ በእርግጠኝነት የነገርኳችሁ ቢሆን እንጂ የተውኩት ነገር የለም” ብለዋል። [አሶሒሐ፡ 4/416] ይሄ የሸዋል ዒድ የተወገዘ ቢድዐ እንደሆነ ዑለማኦች ይናገራሉ። አንድ ሁለቱን ልጥቀስ፦ 1- ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- وأما اتخاذ موسم غير المواسم الشرعية كبعض ليالي شهر ربيع الأول التي يقال: إنها ليلة المولد, أو بعض ليالي رجب, أو ثامن عشر ذي الحجة, أو أول جمعة من رجب, أو ثامن من شوال الذي يسميه الجهَّال عيد الأبرار: فإنها من البدع التي لم يستحبها السلف , ولم يفعلوها. "ሸሪዐዊ ያልሆኑ ክብረ በዓላትን ክብረ-በዓል አድርጎ መያዝ ግን ‘የመውሊድ ሌሊት’ የሚባሉትን የተወሰኑ የረቢዐል አወል ሌሊቶችን ወይም የረጀብ ሌሊቶችን ወይም ደግሞ ዙልሒጃ አስራ ስምንትን ወይም ደግሞ የረጀብ የመጀመሪያ ጁሙዐን ወይም ደግሞ መሃይማን 'የደጋጎች ዒድ' እያሉ የሚጠሩትን #ሸዋል_ስምንትን የመሰሉ እነዚህ ሰለፎች እንደሚወደዱ ያልገለጿቸውና ያልተገበሯቸው #ቢድዐዎች ውስጥ ናቸው።” [መጅሙዑል ፈታዋ፡ 25/298] በተጨማሪም እንዲህ ብለዋል፦ وأما ثامن شوال : فليس عيداً لا للأبرار ولا للفجار , ولا يجوز لأحد أن يعتقده عيداً, ولا يحدث فيه شيئاً من شعائر الأعياد "ሸዋል ስምንትን በተመለከተ ለደጋጎችም ይሁን ለባለ -ጌዎች ዒድ አይደለም። ለማንም ቢሆን ዒድ አድርጎ ሊያምንበት አይፈቀድም። በሱ ውስጥ የትኛውም የበዓላት መገለጫዎች ሊንፀባረቁበት አይገባም።" [አልኢኽቲያራቱል ፊቅሂያህ፡ 199] 2- ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲሰላም ኸዲር አሹቀይሪይ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- ويكون الاحتفال بهذا العيد في أحد المساجد المشهور فيختلط النساء بالرجال ويتصافحون ويتلفظون عند المصافحة بالألفاظ الجاهلية, ثم يذهبون بعد ذلك إلى صنع بعض الأطعمة الخاصة بهذه المناسبة "ይሄ ዒድ የሚከበረው ከታዋቂ መስጂዶች ውስጥ በአንዱ ይሆናል። ከዚያ ሴቶች ከወንዶች ጋር ይቀላቀላሉ። በሰላምታ ይጨባበጣሉ። ሲጨባበጡም የጃሂሊያ ቃላትን ይናገራሉ። ከዚያም በኋላ ለዚህ ጊዜ የተለዩ የተወሰኑ የምግብ አይነቶችን ያዘጋጃሉ።" [አሱነኑ ወልሙብተደዓት፡ 166] በመጨረሻም በአንድ ማሳሰቢያ ልዝጋ። የጉዳዩን ብይን የሚያሳዩ የሸሪዐ መሰረቶች እና የዑለማእ ንግግር እየተጠቀሰ አይኑ እያየ ልክ እኛ ከኪሳችን የተናገርን ይመስል "ሁሉን ነገር ቢድዐ አደረጋችሁብን" አይነት የአላዋቂዎች ተቃውሞ የሚያሰማ አካል ቦታ የለውም። እለቱን ዒድ አድርጎ መያዝ አይገባም ስለተባለ ዱንያ ሁሉ ቢድዐ እንደተባለ እያስመሰሉ ማቅረብም ራስን መሸወድ ነው። ሲጀመር በአንዳንድ አካባቢዎች ካልሆነ በስተቀር ይሄ ልማድ በብዙ ቦታዎች አይታወቅም። ይልቅ ከሙስሊም የሚያምረው ለማስረጃ እጅ መስጠት ነው። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

የሸዋል ዒድ ወይም ትንሹ ዒድ ተብሎ  የሚደገሰውና የሚከበረው በአል የተወገዘ ቢድዓ ነው። ኢስላም ከሁለቱ ዒዶች ውጪ የሚከበር ሌላ ዒድ የለውም። የሚያሳዝነው ይህን ዒድ የሚያከብሩ ሰዎች ከዋናው ዒዱል ፊጥር በላይ በጉጉት ጠብቀውትና ተዘጋጅተውለት መሆኑ ነው። ይህ የቢድዓ አንዱ መዘዝ ነው። ከፊሎች ደግሞ ቤተሰብ ዚያራን ሰበብ አድርገው ድብን አድርገው ያከብሩታል። በተቻለ መጠን ይህን ተግባር በብስለትና በእውቀት ልናወግዘው ይገባል። منقول

• ትንሹ ኢድ ( የሸዋል ፍች )የሚባል ነገር የለም።❌ ሁለት ዒድ ብቻ ነዉ ያለን ! ①ኢድ አልፊጥር ②ኢደል አድሀ አረፋ •ስለዚህ ይሄንን መጤ ተግባር ሁላችንም በጋራ እንከላከል!!

ሁሉንም ጥንካሬ የለው አላህ ለሙሳ እንዲህ ባለው ጊዜ ነው፦ «እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ፤ እሰማለሁ፤ አያለሁም፡፡»(ቁርኣን 20:46) ጥንካሬው በአንተ ውስጥ አይደለም፤ ነገር ግን ከጌታህ ጋር ከሆንክ ነው፦ ባሕሩን መንገድ ያደረገ፣ ብትሩን ተአምር ያደረገ፣ ፍርሃትንም ወደ ሰላም የለወጠ።” = t.me/https_Asselefya1

« لا تحسدوا النَّاسَ على راحةٍ ظاهرة، فإنَّ نصيبهم من الابتِلاءِ لم يُرى.» «ሰዎችን በሚያሳዩት ግልጽ ምቾት አትቅና፤ የመከራቸው ድርሻ አይታይምና። » = t.me/https_Asselefya1

ዓኢሻ ኢስላማዊ ኮሌጅ አሰቸኳይ ኡስታዝ ይፈልጋል 👉 መስፈርት 1) ኢስላማዊ አደብ የተላበሰ/ች 2)  ከሰወች ጋር ተግባቢነት ያለው /ላት 3)ኪታቦችን ማቅራት እሚችል/ትችል :- ፊቅህ ፣ ሐዲሥ፣ አሕካመ ተጅዊድ ፣ሉጛ ...መሰል ትምህርቶችን ማስተማር እሚችል/ትችል ከነዚህ የተወሰኑትንም ከቻለ /ች 4) እዛው አቅራቢያ ቢሆኑ ይመረጣሉ 👉 ብዛት :- 3 👉 አድራሻ = ከሚሴ 👉 ደመወዝ :- በስምምነት 👉 ቅጥር በቋሚነት 👉 የትምህርቱ ሰኣት ከጧት 3:00- 5:00 ከሰኣት 8:00- 10:00 ዐስር በዚህ ስልክ ይደውሉ +251920189240 +251912341423 https://t.me/Ibnu_siraj_Alkemissie

ዓኢሻ ኢስላማዊ ኮሌጅ አሰቸኳይ ኡስታዝ ይፈልጋል 👉 መስፈርት 1) ኢስላማዊ አደብ የተላበሰ 2)  ከሰወች ጋር ተግባቢነት ያለው 3)ኪታቦችን ማቅራት እሚችል :- ፊቅህ ፣ ሐዲሥ፣ አሕካመ ተጅዊድ ፣ሉጛ ...መሰል ትምህርቶችን ማስተማር እሚችል ከነዚህ የተወሰኑትንም ከቻለ 4) እዛው አቅራቢያ ቢሆኑ ይመረጣሉ 👉 ብዛት :- 3 👉 አድራሻ = ከሚሴ 👉 ደመወዝ :- በስምምነት 👉 ቅጥር በቋሚነት 👉 የትምህርቱ ሰኣት ከጧት 3:00- 5:00 ከሰኣት 8:00- 10:00 ዐስር በዚህ ስልክ ይደውሉ +251920189240 +251912341423 https://t.me/Ibnu_siraj_Alkemissie