1 220
Подписчики
-124 часа
Нет данных7 дней
-1730 день
Архив постов
1 221
ከሚያዝያ 26/08/2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲሱ የነዳጅ ችርቻሮ ዋጋ
- ነጭ ናፍጣ 180.46 ብር
- ቤንዚን 167.50 ብር
- ኬሮሲን 320.66 ብር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ 170.62 ብር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 167.37 ብር
- የአውሮፕላን ነዳጅ 319.76 ብር
መሆኑ ተገለፀ።
1 221
#ነዳጅ
በነጭ ናፍጣ ብቻ በሊትር 10 የዋጋ ብር ጭማሪ ተደርጎ 139.84 ብር ገብቷል።
ቤንዚንም የ3 ብር ጭማሪ ተደርጎ በሊትር 132.18 ብር ሆኗል።
በደብዳቤው በተገለጸው መሰረት በሊትር፦
- ነጭ ናፍጣ 139.84 ብር
- ቤንዚን 132.18 ብር
- ኬሮሲን 146.14 ብር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ 137.03 ብር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 133.45 ብር
- የአውሮፕላን ነዳጅ 145.23 ብር ሆኗል
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
1 221
ስለ ፕላስቲክ ማሸጊያዎች አጠቃቀም አዲስ ማብራሪያ ተሰጠ‼️
የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በቅርቡ በወጣው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 ላይ የተካተቱ የፕላስቲክ ማሸጊያዎችን ትርጓሜና አጠቃቀም በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥቷል።
ባለስልጣኑ እንዳስታወቀው፣ በአዋጁ መሰረት "የፕላስቲክ ማሸጊያ" ማለት ማንኛውንም ምርት ከብክለት ለመከላከል ወይም ከሌሎች ነገሮች ጋር እንዳይቀላቀል ለማድረግ በአምራቾች ጥቅም ላይ የሚውል ከፕላስቲክ የሚዘጋጅ መጠቅለያ ወይም መያዣ ነው።
በአዲሱ አዋጅ መሰረት የሚከተሉትን ምርቶች ለማሸግ የሚውሉ ፕላስቲኮች የተፈቀዱ መሆናቸውን ባለስልጣኑ አረጋግጧል፦
1. የምግብ ምርቶች የተለያዩ የታሸጉ ምግቦች፤
2. የባልትና ውጤቶች በቤት ውስጥ የሚዘጋጁ የባልትና ምርቶች፤
3. የላውንደሪ አገልግሎት፦ ለፅዳትና ለልብስ እጥበት አገልግሎት የሚውሉ ማሸጊያዎች፤
4. ሌሎች የንግድ ምርቶች፦ በተለያዩ አምራቾች የሚወጡ የኢንዱስትሪ ውጤቶች።
እነዚህ የተፈቀዱ የፕላስቲክ ማሸጊያዎች ጥቅም ላይ ከዋሉ በኋላ የሚኖራቸው አወጋገድ በአዋጁ እና አዋጁን ተከትለው በሚወጡ የማስፈፀሚያ ህጎች ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግባቸው ተገልጿል።
ይህም በሀገሪቱ የሚታየውን የደረቅ ቆሻሻ ብክለት በዘላቂነት ለመቅረፍ የታለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
ባለስልጣኑ በመጨረሻም "ፅዱ ኢትዮጵያን ባህል እናድርግ!" በማለት መላው ህብረተሰብ ለህጉ ተገዥ እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።
======================
💎⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
1 221
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 2/2018 ዓ.ም ይጀምራል፡፡
ጥር 30/2018 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 2/2018 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
1 221
Ethiopian music video clip by Netsanet Werkneh
https://youtube.com/watch?v=qX30uzzvZxw&si=yWviRf5VUanFsclz
1 221
ከፍተኛ የጨው አጠቃቀማችን እየገደለን ይሆን ?
በኢትዮጵያ ከሚሞቱ ሰዎች መካከል 43 በመቶ የሚሆኑት ህይወታቸው የሚያልፈው ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች ምክንያት እንደሆነ ጥናቶች ያሳያሉ። ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ከፍተኛ የጨው አጠቃቀማችን እንደሆነም ይነሳል።
በአሁኑ ወቅት በሀገራችን 96 በመቶ የሚሆነው ህዝብ የዓለም ጤና ድርጅት ካስቀመጠው የጤና ገደብ በላይ ጨው የሚመገብ ሲሆን፣ ይህም በየዓመቱ ለሚከሰተው 32 በመቶ የልብና የደም ዝውውር በሽታ ሞት ዋነኛ መንስኤ ሆኗል።
አንድ ኢትዮጵያዊ በቀን በአማካይ 8.25 ግራም ጨው የሚመገብ ሲሆን፣ ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ መወሰድ አለበት ተብሎ ከተቀመጠው 5 ግራም እጅግ ከፍ ያለ ነው።
ይህ አደገኛ የአመጋገብ ልማድ የደም ግፊትን ከመጨመሩ ባለፈ በሀገር ደረጃ በየዓመቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ያለ ዕድሜያቸው ለህልፈት እየዳረገ ይገኛል።
የጨው አጠቃቀምን ወደ 2 ግራም ሶዲየም ዝቅ ማድረግ ቢቻል በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ 2.5 ሚሊዮን ሰዎችን ህይወት መታደግ እንደሚቻል ጥናቶች ያሳያሉ።
ይህ የጤና ቀውስ በሀገሪቱ የጤና ተቋማት ላይ እጅግ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ ይገኛል። ከደም ግፊት፣ ከልብ እና ከኩላሊት ህመም ጋር ተያይዞ ወደ ሆስፒታሎች የሚመጡ ታካሚዎች ቁጥር መጨመር የህክምና ቁሳቁስ፣ የመድኃኒት እና የባለሙያ እጥረት እንዲባባስ አድርጓል።
የታካሚዎች ቁጥር ካለው የሆስፒታል አልጋ እና የሰው ሃይል አቅም በላይ መሆኑ ተቋማቱ ለሌሎች ድንገተኛ ህመሞች የሚሰጡትን ትኩረትና ጥራት እንዲቀንስ እያደረገው ነው።
ይህንን የጤና ቀውስ ለመግታት የተዘጋጀው አዲስ ረቂቅ አዋጅ በታሸጉ ምግቦች ውስጥ ያለውን የጨው መጠን በጠበቀ ሁኔታ ለመቆጣጠር ትኩረት ሰጥቷል።
በረቂቅ አዋጁ መሰረት በአንድ የታሸገ ምግብ ውስጥ የሚገኘው የሶዲየም መጠን ከምግቡ አጠቃላይ የኃይል መጠን ጋር እኩል ወይም የሚበልጥ ከሆነ ምግቡ ከመጠን ያለፈ ጨው እንዳለው ተቆጥሮ ልዩ ቁጥጥር ይደረግበታል።
ይህንን የቁጥጥር ስርአት ተግባራዊ ማድረግ ለጤና ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለሀገር ኢኮኖሚም ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
ኢትዮጵያ በጤናማ ያልሆነ አመጋገብ ምክንያት ለሚከሰቱ በሽታዎች ህክምና እና ለምርታማነት መቀነስ በየዓመቱ ከ31 ቢሊዮን ብር በላይ የምታጣ ሲሆን ከዚህ ውስጥ፣ 26.9 ቢሊዮን ብሩ የሚጠፋው ሰዎች በህመም ምክንያት ስራ በመፍታታቸው ወይም ያለ ዕድሜያቸው በመሞታቸው ምክንያት በሚሰላ ኪሳራ እንደሆነ ተቀምጧል።
የጨው አጠቃቀምን በመቀነስ ረገድ የሚደረግ ኢንቨስትመንት እስከ 230 በመቶ የሚደርስ የኢኮኖሚ ትርፍ እንደሚያስገኝ ጥናቶች ያሳያሉ።
1 221
የታሸገ ውሃ‼️❓👇
የታሸገ ውሃ በየቀኑ መጠቀም አይመከርም፣ ለምን❓❓👇👇
በየቀኑ የታሸገ ውሃ የሚጠጡ ሰዎች ከቧንቧ ውሃ ከሚጠጡ ሰዎች ሲነፃፀር ከ90,000 በላይ ጥቃቅን ፕላስቲክ (micro plastic) እንደሚጠጡ አዲስ ጥናት አመልክቷል፣ ይህም አደጋዎቹን ለመቆጣጠር አስቸኳይ የቁጥጥር እርምጃዎችን ይጠይቃል።
ግምገማው በተጨማሪም ሰዎች የታሸገ ውሃ አብዝተው የሚጠቀሙ ሰዎች በአማካይ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ39,000 እስከ 52,000 የማይክሮፕላስቲክ ቅንጣቶችን እንደሚውጡ አስታውቋል።
እነዚህ በአንድ ላይ ሲጠራቀሙ መጠናቸው ከአንድ ሺህ ሚሊሜትር እስከ አምስት ሚሊሜትር ይደርሳል።
የፕላስቲክ ጠርሙሶች በሚመረቱበት፣ በሚከማቹበት እና በሚጓጓዙበት ወቅት ማይክሮፕላስቲክዎችን ይለቃሉ። በተለይ ለፀሐይ ብርሃን እና ለሙቀት ሲጋለጡ ከፍተኛ የሆነ ማክሮፕላስቲክ ይለቃሉ። በካናዳ የኮንኮርዲያ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች እንደገለጹት፣ እነሱን የመመገብ የጤና መዘዝ “ከባድ ሊሆን ይችላል” ሲሉ ያስጠነቅቃሉ።
“በድንገተኛ ጊዜ ከፕላስቲክ ጠርሙሶች ውሃ መጠጣት ጥሩ ነው፣ ነገር ግን በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ ጥቅም ላይ መዋል የለበትም” ብለዋል።
(አዩዘሀበሻ)
=========≠============
💎⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
1 221
+1
ቤንዚን 129.12 ብር‼️
የአለም የነዳጅ ዋጋን መነሻ በማድረግ ከታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ የአውሮፕላን፣ የቀላል ጥቁር ናፍጣ አና የከባድ ጥቁር ናፍጣ መሸጫ ዋጋ በህዳር ወር ሲሸጥበት በነበረው ዋጋ የሚቀጥል ሲሆን፣ የቤንዚን፣ የነጭ ናፍጣ እና የኬሮሲን ነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከላይ በተቀመጠው ሠንጠረዥ መሠረት ተግባራዊ እንዲሆን በመንግስት ተወስኗል።
የአዲስ አበባ ከተማ የጭርቻሮ መሸጫ ዋጋ:-
ቤንዚን፣ኬሮሲን እና ነጭ ናፍጣ በ129.12 ብር እንዲሸጡ ተወስኗል።
(አዩዘሀበሻ)
==========≠============
💎⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
