🍂 ዲነል ኢስላም 🕌
Открыть в Telegram
♡_ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል"(አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል)ﷻ (ﷺ) « ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ ፣ በመልካም ስራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ ፣ ...» ቁርኣን[ 3:104 ] መወያያ ግሩፓችን ☞ @Dinel_islam_Group ✔ ሀሳብ አስተያየት ካሎት 👉 @DinelIslam1Bot 📩
Больше9 651
Подписчики
-824 часа
-447 дней
-19630 день
Архив постов
9 651
የአላህ መልክተኛ ﷺ የጀነትን ሰዎች ሲገልጹ እንዲህ አሉ፦
«መበጠሪያቸው ከወርቅ የተሠራ ነው፤ በዕጣን ማጨሻቸው የሚቃጠለው ውድ የዑድ እንጨት (አል‐አሉው‐ዋ) ነው፤ ላባቸውም የሚሸተው ሚስክ ነው።»
ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል።
:
🔸 የጀነት ሰዎች ፀጉራቸውን የሚበጠሩት ወይም ዕጣን የሚታጠኑት እንደ ዱንያ ሰዎች በቆሻሻ ወይም በመንጨፋረራቸው ምክንያት አይደለም፤ ለሙሉ ደስታ፣ ለቅንጦት፣ ለውበትና ለመደሰት ብቻ ነው። ላባቸው እንኳን ከሚስክ የበለጠ መዓዛ ያለው ሽታ ይኖረዋል፤ ይህ ከአላህ ለጀነት ሰዎች ያዘጋጀውን የማያልቅ ፀጋና ክብር ያሳያል።
የተባረከ ጁሙዐ ይሁንልን!
9 651
የመጨረሻዋ ጠባብ ቤት🥺
"የምትወዳቸው ሰዎች ሁሉ አፈር አልብሰውህ፣ የእግር ኮቴአቸው እየራቀ ሲሄድ... ያኔ እውነተኛው ብቸኝነት ይጀምራል።"
....ያን ጊዜ ብርሃን የሚሆንህ የከማቸኸው ሀብት ሳይሆን የሰገድከው ስግደት ነው፤ የምታገኘው መጽናኛም የህዝብ ሙገሳ ሳይሆን በድብቅ ያደረግከው መልካም ስራህ ነው።
....ያለህበት መቃብር ወይ የጀነት የአትክልት ስፍራ፣ ወይም የጀሃነም የጭንቅ ጉድጓድ የሚሆነው ዛሬ በምትተነፍሳት በእያንዳንዷ ሰከንድ ነው። ያቺ ቀን ከመምጣቷ በፊት፣ ጨለማው ቀብር ሳይውጠን አሁኑኑ ወደ አላህ እንመለስ፤ ልባችንን በዱአና በተውባ እናድስ።
( اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ النَّبِيِّ الأُمِّيِّ الْحَبِيبِ الْعَالِي الْقَدْرِ الْعَظِيمِ الْجَاهِ وَعَلَى آلِهِ وَصَحْبِهِ وَسَلِّمْ )
9 651
ንግግሩ ሁሉ ስለ እሳቸው ብቻ ቢሆን፡ አንድ ክስተት በተፈጠረ ቁጥር የአላህ መልእክተኛ ይህን ብለው ነበር፣ እንዲህ አድርገው ነበር እያለ ለዐቅል የከበደ የማስታወስ ጥበብ ቢያፈልቅ ሰዎች ተጠራጠሩት። አቡ ሁረይራ ስለ ረሱለላህ መናገር ያበዛል፡ ከሙሃጂሮችም ሆነ አንሳሮች የሱን ያህል ስለ እሳቸው አስታውሶ የሚናገር የለም አሉ፡ ትናንት የሆነ ያህል አንዲት ቃል ሳያዛንፍ ዛሬም ሆነ ነገ አልያ ከዓመታት በኋላ ያንኑ ቅደም ተከተል ይዞ ነው ንግግሩን ጀምሮ ሲያጠናቅ። የንግድም ሆነ የእርሻ ስራ ሳያስተጓጉለው እንደ አቡሁረይራ ለእውቀት የከተተ ማንም አልነበረምና፡ እናስ በዚህ ልክ የማስታወስ ችሎታ ሚስጥር ምንድነው? ቢባል ከረሱለላህ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ሙዕጂዛዎች መካከል የሚጠቀስ አንድ ታሪክ አለ
አንድ ወቅት ላይ የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወኣሊሂ ወሰለም "ከዚህ ምርኮ ጓደኞችህ እንደሚጠይቁት አንተ የማትጠይቀው? አሉት፡ አቡ ሁረይራ ይልቁንስ "አላህ ካሳወቀህ እውቀት ታስተምረኝ ዘንድ ነው ምጠይቅህ" ብሎ መለሰላቸው፡ እሳቸውም ጀርባው ላይ ደርቦ የለበሰውን ከበግ ጸጉር የተሰራ ኩታ አንስተው በእሳቸውና በእሱ መካከል ዘረጉት፡
አቡ ሁረይራ የሆነውን ሲያስታውስ እንዲህ ይላል፡ "...ንግግራቸውን ሙሉ ለሙሉ እስከምገነዘብ ድረስ ነገሩኝ፡ ከዚያም (ኩታህን) ሰብስበህ ወዳንተ አስጠጋ አሉኝ፡ (ያሉኝን ካደረግኩ በኋላ) ከንግግራቸው አንዲትም ፊደል የማልጥል(የማልረሳ) ሆንኩኝ"።
ከረሱለላህ ዱዓና በረካ እንደ አቡሁረይራ የታደለስ ማን አለ! አንድ ቀን ረሃብ ከቤቱ አስወጥቶት ሜዳ ላይ ሲኳትን የሱ ብጤዎችም የሚቀመስ ፍለጋ ሲዟዟሩ ተገናኙ። ወደ ሐቢቡላህ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ገቡና ችግራቸውን ነገሯቸው፡ ለእያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ተምርና የሚጠጣ ውሃ ሰጧቸው አቡሁረይራ አንዷን ተምር በልቶ አንዷን በእጁ ይዞ ሲቆይ ለምን እንደደበቃት ጠየቁት "ለእናቴ ልወስድላት ነው" አላቸው፡ የአላህ መልእክተኛም ለእሷ ሌላ ሁለት እንሰጥሃለን ያንተን ብላ" አሉት። እናቱ በዚህ ጊዜ እስልምናን አልተቀበለችም ነበር፡ ለእናቱ ያለውን ውዴታና እንክብካቤ ሌላው ቢቀር ከዚህ ክስተት መረዳት እንችላለን፡ ረሱለላህም እምነታቸውን ካለመከተል አልፋ ስለ እሳቸው መጥፎ የምትናገርን ሴት እንደ ስራዋ ሳይሆን እንደ እሳቸው ባሕሪ ነበር የሚኗኗሩት። እናም ልጇ አቡሁረይራ ወደ እስልምና ጥሪ ቢያደርግላትም ለበርካታ ጊዜያት አሻፈረኝ ብላለች፡ ይባሱን ብላ አንድ ቀን ስለ ሐቢቡላህ መጥፎ ቃላት ሰነዘረች፡ አቡሁረይራ አዝኖና ልቡ ተሰብሮ ወደ ረሱለላህ ሄደ፡ የተፈጠረውንም በእንባ እየታጠበ ነግሯቸው ዱዓ እንዲያደርጉላት ጠየቃቸው፡ የአላህ መልእክተኛ የቅናቻውን መንገድ እንዲመራት ዱዓ አደረጉ፡ አቡሁረይራም የምስራቹን ለእናቱ ሊነግር በደስታ ሲገሰግስ ለሸሃዳ እየታጠበች አገኛት፡ ከዚያም ወጣችና
أشهد أن لا إله إلا الله، وأن محمدا عبده ورسوله
ብላ የእስልምና መግቢያ ምስክርነቷን ሰጠች
እንደገና ጉዞ ወደ ረሱለላህ፡ በድሎትም በክፋት የሚያስቡት ከሁሉ የሚወዱትን አይደል! አሁን ግን የደስታ እንባ እያጎረፈ ነበር፡ እናቱ መስለሟን ነገራቸው እናም አማኞች እሱንና እናቱን እንዲወዱ ዱዓ ያደርጉለት ዘንድም ጠየቃቸው
اللهم حبب عبدك هذا وأمه إلى عبادك المؤمنين وحببهم إليهما
ብለው ዱዓ አደረጉለት
ታድያስ እንደ አቡሁረይራ እድለኛ ማን አለ!
(ሲየር አዕላመኑበላእ ቅፅ 2)
اللهم صل على سيدنا محمد عبدك ورسولك النبي الأمى
9 651
( اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ النَّبِيِّ الأُمِّيِّ الْحَبِيبِ الْعَالِي الْقَدْرِ الْعَظِيمِ الْجَاهِ وَعَلَى آلِهِ وَصَحْبِهِ وَسَلِّمْ )
9 651
የሃይማኖት ተቋማት እና 'አስተማሪዎቹ' ሥራቸውን ትተው ቢዝነስ ውስጥ ገቡ።
ሁሉም የግል ትምህርት ተቋማት (ራስ-ገዝ ሊሆኑ የተቃረቡት የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ) ቅድሚያ ለቢዝነስ እንደሚሰጡ አይጠየቅም።
የመንግሥት ተቋማት ከሕዝብ አገልግሎት በላይ ገቢ/income የሚያሳስባቸው እየሆኑ እንደመጡ የሚታወቅ ሐቅ ነው።
የነገሮች መገለባበጥ ሲታይ ወደፊት እንደ ወንጀል ተቆጥሮበት ለፍርድ የሚቀርበው፦
- አስታራቂ ሽማግሌ ሆኖ በቅንነት የሚያገለግል ሰው
- ወንጀለኞችን የሚያጋልጥ ሰው
- ትምህርቱን በአግባቡ ተከታትሎ የተመረቀ ሰው
- ለቅሶ የተቀመጡ ሐዘንተኞችን የሚያጽናና ሰው
- የወደቀ ገንዘብ አግኝቶ ለፖሊስ የሚያስረክብ ሰው
- 'ጉቦ አልቀበልም፣ አሻፈረኝ' የሚል ሰው
- አዋቂዎችን ሲያይ በትህትና ወንበሩን ለቆ የሚያስቀምጥ ሰው
ይመስለኛል።
ቻይና በቅርቡ ጥብቅ ሕግ አወጣች። ከ 6-15 ዓመት ድረስ ያሉ ልጆች የሚማሩባቸው (እስከ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ) ት/ቤቶች ለትርፍ መቋቋም አይችሉም አለች። አንዳንድ ነገሮች እንደ ሸቀጥ መቅረብ የለባቸውም። የሃይማኖት፣ የትምህርት፣ የመንግሥት አገልግሎቶች፤ የመጀመሪያ ደረጃ ሕክምና .... ወዘተ.
Via Hawlet Ahmed
9 651
ሰው ማለት የሚገርም ፍጥረት ነው፤ ጤናውን አጥቶ ገንዘብ ያጠራቅማል፤ ከዚያም ያጠራቀመውን ገንዘብ ጨርሶ ጤናውን ለመግዛት ይሞክራል።
9 651
‹ኒቃባችሁን እንዳታወልቁ እኛ አለንላችሁ ትማራላቹ› ሚሏችሁን አትስሟቸው።
...ለስልጣናቸው ሲሉ መስጂድ ያስፈረሱ ሰዎች የናንተ መማር ምናቸውም አይደለም!
9 651
እንባ አንቋችሁ ያውቃል? እልህ ተናንቋችሁስ? ከንዴት ከብስጭት ብዛት ጣቶቻችሁ ተንቀጥቅጠውባችሁ ያውቃል? ያ' ነው የተሰማኝ
እርርር አልኩ ግን ምንም ማድረግ አልቻልኩም💔
እኔ ሒጃቤን ጠብቄ አላደረግኩ ይሆናል
አዎ ሊፒስቲክ ተቀብቼ በየ ሚዲያው ፎቶዬን ለቅቄ ይሆናል
አዎ ሸርዒይ አይደለሁም ይሆናል
ግን .... የእነዚህ እህቶቼ ህመም የማይሰማኝ የዲኔ መደፈር የማያምመኝ ደዩስ አይደለሁም!
ይሄን ስልም ምንም እንደማላመጣ ምንም እንደማይፈጠርም አውቃለሁ። ምክንያቱም ይሄንን የሚያስፈፅም መብትን የሚያስከብር የሙስሊሙ ወኪል የሆነ ግለሰብም ተቋምም የሌለን ብኩኖች መሆናችንን ስለማውቅ።
ነገን እፈራዋለሁ
ሒጃቡን አውልቁ የምንባልበት ጊዜም እየመጣ ይመስለኛል።
መፍትሄው መማር አሁንም መማር አሁንም መማር !
መማርና ቦታውን መረከብ!
አላህ ደዩስነታችንን ይንጠቀን!
9 651
+2
ለኒቃብ ለባሽ ተማሪ እህቶቻችን ምስቅልቅል ቁጥር አንድ ተጠያቂው መጅሊስ ነው።
እንዲህ እያደፈጠ ጩኸት ሲበረታበት ብቻ አብሽሩ መፍትሄ እንፈልጋለን እያለ እየቀለደ እሰሰከመቼ በቁማሩ እንደሚቀጥል እንጃ!
ሁሌ ትምህርት እና ፈተና በመጣ ቁጥር እንዲህ ያለ ለረጅም አመት የዘለቀ አጀንዳ እንደሚቀጥል አላህ ይወቅ!
ምንድነው ከማወዛገቡ የሚገኘው?
እንደት መጅሊሱ አቋም መውሰድ ያቅተዋል?
እዚያ ተቀምጠው ደመወዝ እየተከፈላቸው የሚንፈላሰሱት እንዲህ አይነት ሁኔታዎችን ካልፈቱ እስከመቼ ነው የሚቀጥሉት?
አሁን ላይ እህቶቻችን አስቸኳይ መፍትሄ ብቻ ሳይሆን ዘላቂ መፍትሄ ይሻሉ!!
9 651
እነዚህ ለመግባት የተከለከሉት ተማሪዎች አንድ ፈተና ቢያልፋቸውም ማስክ አድርገው ወደፈተና እንዲገቡ ተፈቅዶ እህቶች ገብተዋል!
ሁሌ እዬዬዬዬ ብቻ😭
9 651
ጥያቄ ብቻ
ይቅርታ አድርጉልኝና ይሄ ጉዳይ ለምን ነገሮች ጫፍ ላይ ሲደርሱ እየተጠበቀ እንደሚቀጣጠል አልገባኝም ....
ትምህርት ሚኒስትሩ በኒቃብ ላይ ያለው አቋም ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ አላሳወቀም?። የኢትዮዽያ መጅሊስም በጉዳዩ ላይ የተስማማ ይመስል እነዚህ ጉዳዮች ላይ ጫን ብሎ ከመከራከር ይልቅ በተደጋጋሚ ላሽ አላለም?። በኒቃብም ላይ ያለው ይፋዊ ፈትዋው የታወቀ አይደለም?።
መልሱ አዎ ከሆነ ለምንድነው ለነዚህ ተማሪዎች መብት በመጅሊሱ በኩል ምትከራከሩት ? እሺ እነዚህ በምስሉ ላይ የሚታዩት ሊፈተኑ የመጡት ልጆችስ በየት/ት ቤቱ ኒቃብ ለብሰው ተምረው ከሆነ አሁን እንዳይፈተኑ ለምን ይከለክላቸዋል? ህጉ ፈተና ላይ ለምን ይፀናል ወይስ በተገላቢጦሽ ያለኒቃብ ተምረው ፈተና ላይ አርገውት መጥተው ነው ?
ወደ ሌላው ጉዳይ ስንመጣ ችግሮቻችንን ቀጥታ ከዛው ቀጥታ ከgov(ከት/ት ሚኒው) በኩል አቤት ብንል አይሻልም? መጅሊሱ ችግሮች ከመፈጠራቸው በፊት አርቆ አሳቢ (Proactive) ከመሆን ይልቅ ችግሩ ተፈጥሮ ከተካረረ በኋላ መግለጫ በማውጣት ተከታይ (Reactive) መሆንን የመረጠልን አይመስላቹም ?።
ይሄ የመጅሊሱ አካሄድ የሙስሊሙ ድምፅ የሚታፈንበት የgov አካሄድ እንደሆነ ግልፅ አያደርግልንም ?።
እናንተ እኮ አተፍሩም አይደለም ብላቹ ለመጅሊሱ ጥብቅና ልትቆሙለት ነው ....😑
እስቲ የአክሱም ተማሪዎች ? ጉዳይስ ከምን ደረሰ ?
9 651
ቁርአን ትንሽ ከፍለህ ለማስተማርና ሲያኸትም ለመደገስ ሰስተህ ለኬጂ over መደገስህ ነው ያናደደኝ።ልጅህ የዲን ተርቢያ ከማን ይማር? ያለቦታው ስላባከንክም የሸይጧን ወንድም ነህ።
9 651
እውነታ!
ዝም ብሎ ይደብርሃል፣ አጣሁት የምትለው ነገር ሳይኖርም ይደብርሀል፣ እጅህ ላይ የኾኑ ጸጋዎች ኖረው ይደብርሀል፣ ያለህ እየበዛ ይደብርሀል፣ የወደፊትን እያሰብህ ይደብርሀል፣ ሶሻል ሚዲያ በበዛው የቁስ ሰበካ ድንገት ይደብርሃል፣ የሌለህን በሚድያ መልክ እየሰራህ እያሳየህ ይደብርሀል፣ መንፈሳዊ ተቋማት ሳይቀር ገበትህ ይህ ድብርት ይጫጫንሀል። ይህ ስሙ ጘፍላ (ከአላህ መዘናጋት) ይባላል። እኛ ባንዘናጋ እንኳን አንዳንዴ ጘፍላ እያሳደደ ሊያጠቃን የሚታገል ይመስለኛል። ጓፍላ የሸይ^ጣን መረብ ነውና።
ሰዎች ቀን ከሌት በሚያስፈራሩት ነገር በፍርሀት መሸበብ ራሱ ጓፍላ ነው። በሚሆን በማይሆነው ማዘን ወደ ጘፍላ ይወስደናል። አንዳንዴ ንቃትን መጠበቅ ጘፍላ እንዳይጫወትብን ይኾናል። ከጓፍላ በላይ ሐይ (ሕያው) ለመኾን ደግሞ ወደ አላህ ያለን መቃረብ መስተካከል ወሳኝ ነው። ሕያው በመኾን የሚገኘው መረጋጋት እጅግ ዘላቂና በምንም የሚቀማ አይደለም።
የለሊት አምልኮዎች መሰል ያለመረጋጋት ስሜታችንን ያቃናልናል። አላህ ይህን አይከልክለና!
አላህ ይመልሰና ♥
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
