🍂 ዲነል ኢስላም 🕌
رفتن به کانال در Telegram
♡_ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል"(አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል)ﷻ (ﷺ) « ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ ፣ በመልካም ስራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ ፣ ...» ቁርኣን[ 3:104 ] መወያያ ግሩፓችን ☞ @Dinel_islam_Group ✔ ሀሳብ አስተያየት ካሎት 👉 @DinelIslam1Bot 📩
نمایش بیشتر9 291
مشترکین
-924 ساعت
-607 روز
-22330 روز
آرشیو پست ها
9 289
🌿 የተዘነጉ ሱናዎች
ለሌላው ሰው ሰላምታን መጀመር — «السلام عليكم ورحمة الله وبركاته» ማለት።
ሰላምታን በሚያምር ሁኔታ መመለስ — ከተቻለ «وعليكم السلام ورحمة الله وبركاته» ማለት።
በቤት ሲገቡ ሰላም ማለት — ቤት ውስጥ ሰው ባይኖርም ሰላምታ ማድረግ።
ከመብላት በፊት በስም አላህ መጀመር — «بسم الله» ማለት።
በቀኝ እጅ መብላትና ከፊትህ ያለውን መብላት።
ምግብን ካጠናቀቁ በኋላ አላህን ማመስገን — «الحمد لله» ማለት።
ምግብን አለማነወር — ከወደዱት መብላት፤ ካልወደዱት ሳይነቅፉት መተው።
ከምግብ በኋላ ጣቶችን መላስ
ከመታጠብ በፊት።
ውሃን በሶስት ጊዜ መጠጣት እና ከመጠጣት በፊት ቢስሚላህ ብሎ መጀመር።
ተቀመጠን ውሃ መጠጣት እና እያረፉ መጠጣት።
ማዛጋት ሲመጣ መከላከል ከቻሉ፤ አፍንም መሸፈን።
ሲያስነጥሱ «الحمد لله» ማለት፤ የሰማውም «يرحمك الله» ማለት።
የሌሊት ሶላት (قيام الليل) — ምንም እንኳን ጥቂት ረከዓ ቢሆንም።
የዱሃ ሶላት (صلاة الضحى) — በጠዋት ከፀሐይ ከወጣች በኋላ መስገድ ሁለት ረከዓ ቢሆን።
ከእንቅልፍ ሲነሱ የተወሰነውን ዚክር ማድረግ።
መተኛት ሲፈልጉ ዉዱእ ማድረግ እና በቀኝ ጎን መተኛት።
ከመተኛት በፊት አያተል ኩርሲይን እና የመጨረሻዎቹን የሱረቱል በቀራ አንቀጾች ማንበብ።
ከመተኛት በፊት ኢኽላስ፣ ፈለቅና ናስን ማንበብ እና ሰውነትን ማበስ።
በሚወዱት ሰው ላይ ያለዎትን ፍቅር መግለጽ — «إني أحبك في الله» ማለት።
በመንገድ ላይ የሚያስቸግር ነገርን ከመንገድ ማስወገድ —
ከእነዚህ ውስጥ ያልጀመርነውን እንጀምር ሊያታግለን ይችላል ኢንሻአላህ ከልፋት ቡሃላ መዘውተርን አላህ ይወፍቀናል
9 289
በዚህ የብርሃን ወር ምንም አይነት አሉታዊ ነገሮችን ማንሳት ባልወድም 3 ነገሮችን ብቻ ልበል:
፩ኛ: የረቢዕ ወር የሚሰጠውን የሰላም አየር፣ የሚሰጠውን የደስታ ስሜት ሁሉም ባያጣጥመው «ለምን» ባልልም «እንዴት» ግን ያስብለኛል። የእርሳቸው መወለድ ከውኑን ሁሉ እንዳበራ እያወቁ በሳቸው የዊላዳ ቀን ጨለማነቱ ነው የሚታየን ማለት እጅጉኑ የሚረብሽ ነገር ነውና እንዴት ያስብለኛል። ነገር ግን በግድ ካልተደሰታችሁ ብሎ የሚያስገድድ የለም። የተደሰተውን ግን ለምን ብስራት ሆነላችሁ ይመስል በቀኑ እለት ለማፌዝ ሲሞክሩ፣ ሁሌም በተመሳሳይ የሚያስቁ ፒክቸሮች ለዘመናት የቆየውን አከባበርና ትውፊት ዝቅ ለማድረግ ሲሞክሩ ማየት ያስቃል።
ሌላው ማንም እኛ ብቻ ነን የምንወዳቸው የሚል ነገር ሳይናገር ከውስጣቸው የሚሰማቸውን የሚጮሁ ሰዎች: The term የነቢ ወዳጅ ነን እያላችሁ: ድቤ ደብድባችሁ bla bla እያሉ old fashioned trend መለፈፍ የinferiority complex ባህሪ ነውና ይቅርባችሁ ፕሊስ 😊
፪ኛ: መውሊድ የማያከብሩ: በዝምታ እያየን ነው ብለው እራሳቸውን እንደ CCTV Monitoring system የሚመለከቱ፣ ወሩን ዝም ብለን እንደተራ ወር ባናከብረውም በአንድ ቀን መድረክ ፕሮግራም አስበን እንዋል የሚሉ(which is alright) ግን ደግሞ የመውሊዱ ድባብ እነሱ በሚፈልጉት መንገድ ስለማይሄድ ቅር የሚሰኙ፣ ሞቅ ያለውን ድባብ attention ወደራሳቸው grab ለማድረግ የቀዘቀዘውን የጭቅጭቅ ድባብ እንኳን በማንሳት የሽማግሌ role ለመጫወት የሚሞክሩ፣ አቋማቸውን define ማድረግ የማይችሉ ሰዎች ያስገርሙኛል። And to clear something ዘንድሮም አምናም የነበረው የንትርክ መድረክ almost ጠፍቷል ማለት ይቻላል የፌስቡክ መንደርም ኑር በኑር ሆኖ ከርሟል። ነገር ግን the ሽማግሌ ካልሆንን cult አክባሪውም፣ የሚነቅፈውም ቀኑን የመሰዳደቢያ እያደረጋችሁት ነው አይነት ንግግር ሲያደርጉ እየተመለከትን ነው። ሐቅ ለመናገር ዘንድሮም አምናም ከተወሰኑ ሰዎች በቀር እና የጠ.ሚው ኮሜንት ስር «ቢድያ» አይነት መሰል ሸውራራ ኮሜንቶች ከሚኮምቱ አስቂኝ ሰዎች በስተቀር የረቢዕ ድባቡ እጅግ ተውቦ እንደቆየ ብሎም ምንም እንዳልተረበሸ ልናሳውቅ እንወዳለን ስለሆነም ለሚቀጥለው ሌላ ምክንያት ፈልጉ።🌚
፫ኛ: አንድ ቀን ጠብቄ አይደለም እሳቸውን የማወድሰው የምትሉ ኸልቆች ማን አንድ ቀን ብቻ ሲዘክራቸው አይታችሁ ነው እንደዛ የምትሉት?... እሳቸው ላይ ሰለዋት ማውረድን እንደ ዊርድ የያዘው ሰው'ን?... አመቱን ሙሉ ስለ እርሳቸው እና ስለባልደረቦቻቸው የሚያስታውሰንን? ከወር እስከ ወር በየሐሪማው፣ በየገጠሩ እርሳቸውን እያወደሰ የሚኖረውን?... እሱን ተውትና በየ አመቱ መውሊድ በደረሰ ቁጥር ይህንን ከምትሉን ስለ ሰለዋት፣ ስለ እርሳቸው ሸማዒል መፃፍ ገርቶላችሁ ስትፅፉና ስታስታውሱን አሳዪንማ! አመት ጠብቆ «ቢድያ» ማለት ጥቅም የለውም 😊
N.B: ሌላው ረቢዑ አላለቀምና መንደሩን በሰለዋት ከማድመቅ አትስነፉ 😊
9 289
የማይቀር ቀጠሮ !!🌸
የሴቶች በሴቶች የተዘጋጀ ልዩ የመውሊድ ድግስ እሁድ ዻጉሜ 01 ከ 3:30 ጀምሮ ካራ ቆሬ ራህማ መስጂድ በረከቱል ሀበሺያ የሴቶች ጀምዐ አዘጋጅቶ ይጠብቃቹሀል።
ሁሉም ሴት ተጋብዟል🥰
9 289
አንድ ቀን.....
አንድ ቀን፣ አላህ የፈለግከውንና የተመኘከውን ነገር በተሻለ መልኩ ፈፅሞልህ ያገኘህ ጊዜ፤ ከሚገባው በላይ ስትጨናነቅ እንደነበር ትደርስበታለህ።
9 289
+1
እነዚህ ባንኮች ለመውሊድ እንኳን አደረሳችሁ አለማለታቸው ይገርማችሗል?
ደሃን ብሩን በጀሃነም እያስፈራሩ በነጻ ወስደው ለሀብታሞች በወለድ የሚያበድሩ ተቋማት ናቸው:: ባንኮች ለደሃ አያበድሩም:: ከድሃው ላይ ብር ወስደው ትርፋማ ንብረት እና ማስያዣ ቤት ላለው ብቻ ነው የሚያበድሩት:: አትሞኙ ስላችሁ እንዲሰማችሁ አስር ዓመት መቆየትና መደህየት ነበረባችሁ::
በደኸያችሁ ቁጥር ከባንክ ትርቃላችሁ:: ድህነቱ ጭራሽ ለልጅ ልጅ ይዋረሳል:: ለግል ጥቅም ብቻ የቆሙ ናቸው:: ስማቸውን ለጥፌ ስተች ለመጀመሪያ ጊዜ ይመስለኛል:: አሁን ብዙ ነገር ግልጽ ነው::
Via Hassen Injamo
9 289
ጁምዓን የምናከብረው:- ሰማይና ምድር የተፈጠሩበት ብቻ ሳይሆን የሚጠፉበትም ቀን በመሆኑ ነው:: አባታችን አደም የተፈጠሩበትም የሞቱበትም ቀን ነው ጁምዓ::
ረቢዕ ያለፉበት ዕለት ነው የሚለው የተለያዩ ሐሳቦች ቢኖርበትም ቅሉ:- ይሁን እንበልና
ልክ እንደዚሁ ረቢዕ 12 ነቢ ሙሐመድ صلى الله عليه وسلم የተወለዱበትም ሥራቸውን ጨርሰው የተሻገሩበት ቀን ነው:: ይህ ቀን ከነቢ ሙሐመድ صلى الله عليه ላይ የዱንያ ጭንቅ የተወገደበት ቀን ለመሆኑ ልጃቸው ፋጢማ رضي الله عنها ስታለቅስ "አታልቅሽ:: ከአባትሽ ላይ ከዛሬ ወዲህ ጭንቅ የለበትም:: አብቅቷል:: ይልቅስ በቅርቡ ትከተይኛለሽ" ሲሏት በደስታ ፈገግ አለች:: መሄዳቸው ተልዕኮአቸውን በስኬት የጨረሱበት ዕለት እንጂ እንደኛ ዱንያ እንደምናባርርና እንደሚያባርረን ዐይነት አይደለም:: መሄዳቸው ለዚያኛው ዐለም ልደት ነው:: ከመሆኑም ጋር አሁንም እየመሩ መሆናቸውን ለማወቅ የቁርኣን ትንታኔዎችን ማየት ይጠይቃል::
🕋 አላህ (መልክተኛውን) በቅርቢቱም በመጨረሻይቱም ዓለም አይረዳውም ብሎ የሚያስብ ሰው ገመድን ወደ ሰማይ ይዘርጋ፡፡ ከዚያም (ትንፋሹ እስኪቆረጥ) ይታነቅ፡፡ ተንኮሉ የሚያስቆጨውን ነገር ያስወግድለት እንደሆነም ይመልከት፡፡ ቁርኣን 22:15🕋
ቢያልፉም ተረድተው መርዳታቸውን የለም የሚል ሰው ገመድ ወደ ሰማይ ወርውሮ ሲጥ ይበል ይላል ቁርኣን::
9 289
መውሊድ ማለት አሏህ ከዋለልን ትልልቅ ጸጋዎች ሁሉ ታላቅ የሆነውን ጸጋ ማስታወሻ ነው ፤ በሰይዳችንﷺ ብርሃን ለዓለም ፈንጥቋል፣ በሰይዳችንﷺ ምክንያት ሰዎች ወደ ቅኑ መንገድ ተመሪዎች ሆነዋል፣ በሰይዳችንﷺ ልቦች በርተዋል፣ ከሰይዳችንምﷺ ወደ አላህ የሚያደርሰውን የፍቅር መንገድ ተምረዋል።
በሳቸው ﷺ ትውስታ ልባችን ሕይወት ይዘራል:: በፍቅር፣ መንገዳቸውን በመከተልና በጥሩ ሥነ ምግባር ከሳቸውﷺ ጋር ያለንን ቃል ኪዳን እምናድስበት ወሳኝ ክስተት ነው።
እንኳን አደረሰን☺️
ተደስተንባቸው እሳቸውም በኛ የሚደሰቱብን ውድ የሰይዳችንﷺ ወዳጆች አሏህ ያድርገን
#ረቢዑልቁሉብ
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
9 289
ስዑድ ዐረቢያ መውሊድ እንዳይከበርና ልጆች ወደ መውሊድ እንዳይሄዱ ሳምንቱን ሙሉ ታላላቅ የሙዚቃ ኮንሰርት አዘጋጅተዋል:: ምክንያቱም ወጣቱ የነቢዩን صلى الله عليه وسلم ፍቅር ካዳበረ ነገሥታቱ ለሥልጣናቸው ስጋት ነው:: ሞትን ካስታወሱ ወደ ኃይማኖት ስለሚመጡ ቀብርን ከመዘየር ይልቅ ሀሎዊንን እንዲያከብሩ ያደርጉዋቸዋል:: ሚሊዮን ዶላሮችን በመመደብ መውሊድን የሚያጥላሉ ሰዎችን በየዓለማቱ በትነዋል:: ለምንድነው መውሊዱን የሚያጥላሉት? የሚል አይጠፋም:: እራሳቸው በምድር ገጽ በነበሩ ዘመን ሲያሳድዷቸው እንደነበር ከሀበሻ በላይ የሚያውቅ አይኖርም:: ሀበሻ ለመውሊዳቸው የመንግሥት ሥራ ዘግታ, መድፍ ተኩሳ, ሚዲያዎቿን በመውሊድ አሸብርቃ ውላለች::
መውሊዱን ስትቃወሙ የከረማችሁ የኮንሰርት ቲኬት ሊያልቅ ስለሆነ ሂዱና ፍቱን:: ጎግልን የዛሬ ማታ ኮንሰርት ስጠይቀው የተለያዩ አማራጮችን አምጥቶልኛል::
አላሁ ሙስተዐን 💔
9 289
Repost from አል–ዒምራን (CMC) የቁርኣንና ኢስላማዊ ት/ት ተቋም
+8
✨ የመውሊድ በዓል ድምቀቶች ✨
በዛሬው የመውሊድ ፕሮግራም ድምቀት ከነበሩት መርሀ ግብሮች መካከል፣ በአህባቡል ሐቢብ የመድህና ነሺዳ ጀመዓ የቀረበው በአይነቱ ልዩ የሆነ አዲስ ነሺዳ አንዱ ነበር። 🎙️✨
በተጨማሪም ከኢማም አል-ቡሰይሪ የቡርዳ ቀሲዳ የተመረጡ የነብያችን ﷺ ውዳሴዎችን በድምፁ በማቅረብ የታዳሚውን ልብ ያለሰለሰው ተማሪ አቀራረብም ከዕለቱ የማይረሱ ትዕይንቶች አንዱ ነበር። 🤍🌙
በመቀጠልም የዙሁር ሶላተል ጀመዓ ከተሰገደ በኋላ፣ የምሳ ግብዣና የመውሊድ ሰደቃ በመካሄድ የዕለቱ አንኳር መርሀ ግብር ሆኖ በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል። 🍽️🤲
🌹 በውልደቱ ተደስታችሁ ያገለገላችሁ፣ ፕሮግራሞችን ያሰናዳችሁ፣ ለመድረኩ ውበትና ስኬት የተጋችሁ ሁሉ፤ አላህ ሥራችሁን ይቀበላችሁ፣ ይውደድላችሁ፣ በኸይርም ይክፈላችሁ። 🤲❤️
اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا محمد ﷺ
#መውሊድ #ሐቢቡል_ሐቢብ #ቡርዳ #ነሺዳ #መድህ #ሰደቃ #ረሱለላህﷺ
9 289
Repost from አል–ዒምራን (CMC) የቁርኣንና ኢስላማዊ ት/ት ተቋም
+4
🌙✨ በታላቁ ነብይ ﷺ ውልደት እንኳን ደስ አላችሁ! ✨🌙
﴿وَمَا أَرْسَلْنَاكَ إِلَّا رَحْمَةً لِّلْعَالَمِينَ﴾
«አንተንም ለዓለማት ሁሉ እዝነት እንጂ ሌላ አድርገን አልላክንህም።»
📖 ሱረቱል አንቢያእ 21፥107
ለሰው ልጆች መመሪያ፣ መዳንና እዝነት የተላኩትን የአላህ መልእክተኛ ሙሐመድ ﷺ ውድ የሆነውን የልደት መታሰቢያ አስመልክቶ፣ በአል ዒምራን የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምህርት ተቋም የተለያዩ መንፈሳዊና ኢስላማዊ መድረኮችን በማካተት በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል። 🌿
🤲 አላህ ሆይ! ለሰው ልጆች እዝነት አድርገህ የላክከውን የእዝነት ነብይ ሙሐመድን ﷺ ፍቅርና ሱናቸውን በልባችን አጽና።
ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«مَنْ صَلَّى عَلَيَّ وَاحِدَةً صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ بِهَا عَشْرًا»
“በእኔ ላይ አንድ ጊዜ ሰላት ያወረደ ሰው ላይ አላህ አስር ጊዜ ሰላት ያወርድበታል።”
📚 ሙስሊም
🌹 መድረኩም በቲላወቱል ቁርአን እና በሸይኽ ሸሪፍ ራምሳ መንዙማ ተከፍቶ፣ በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ ግጥሞች፣ የመልእክተኛውን ﷺ ታሪክና ታላቅ ሕይወት የሚዳስሱ መልእክቶች፣ ነሺዳዎችና ሌሎች መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እየቀረቡ ይገኛሉ። 🎙️📖
🌙 የእዝነት ነብይን ﷺ ውልደት በማስታወስ፣ ሱናቸውን በመከተል እና በእሳቸው ላይ ሰላትና ሰላም በማውረድ የሚያምር ሕይወት እንገንባ።
اللهم صل وسلم وبارك على نبينا محمد ﷺ
💚 እንኳን አደረሰን፤ አደረሳችሁ!
🌹 መልካም የመውሊድ በዓል!
#አል_ዒምራን
#የነብዩ_ሙሐመድ_ውልደት
#መውሊድ
#ነብዩ_ሙሐመድ ﷺ
#Quran
#AlImran
