cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ዘመድኩን በቀለ

የዘመድኩን በቀለ ጦሟሩን እንደወረደ የሚለቀቅበት ስለሆነ ሁላችሁም ዘመዴን አድናቂዎች ተቀላቀሉት ጆይን አድርጉት ሸሩን ትታችሁ ሼር አድርጉት

Больше
Рекламные посты
4 123
Подписчики
-124 часа
-177 дней
-9130 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

00:43
Видео недоступноПоказать в Telegram
•የጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ዘገባ ነው። "…እጅግ ዘግናኝ ነው! ትህነግ በዐማራ ላይ ሌላ ፍጅት ፈፀመ! ህፃናትን ገድሎ አስከሬናቸውን አቃጠለ። ወርቃይኑ ተብሎ በሚጠራው የትህነግ ጀኔራል የተላኩ የትህነግ ታጣቂዎች ዐማራ ክልል ሰርገው ገብተው አንድ መንደር ሙሉ በሙሉ አውድመው፣ በሺህ የሚቆጠሩ  ንፁሃንን አፈናቅለው በርካቶችን ገድለዋል። ከእነዚህ መካከል ህፃናትን ገድለው በእሳት አቃጥለዋል። "…ትህነግ ሰሞኑን በፌስቡክ "ሰኔ 30" የሚል ዘመቻ የከፈተ ሲሆን ወደ ወልቃይት እንገባለን ብለው ያሰቡበትን ቀንን ነው የዘመቻው አካል ያደረጉት። ዘመቻውን ግን በፌስቡክ ብቻ አይደለም። በተግባርም ወደ ወልቃይት ቢገቡ ሊያደርጉ የሚችሉትን አዳርቃይ ላይ ፈፅመውታል። "…ትህነግ ወደ ዐማራ ግዛቶች ቢገባ ሊፈፅመው የሚችለውን ትናንት ሌሊት በፈፀመው ጭፍጨፋ ጠቁሞናል። •የእኔ ምልከታ ይቀጥላል። "…ሰሞኑን በርዕሰ አንቀፄ እንደጠቆምኳችሁ የትግራይ ነፃ አውጪዋ ወያኔ ያለ ጦርነት መኖር አትችልም። ሚካኤል ስሁል የሚባል አረመኔ ከትግሬ ተነሥቶ ጎንደር ቤተ መንግሥት ተጠግቶ የፈጸመውን ብታነቡ ይሰቀጥጣችኋል። ዐፄ ዮሐንስ ዓለም በቃኝ ብለው ገዳም የገቡትን ንጉሥ ተክለ ጊዮርጊስን ከገዳም አውጥተው ዓይናቸውን በጋለ ብረት አውጥተው እንዴት የሳዲስትነት ተግባር እንደፈጸሙም አይተናል። "…በትግል ወቅት ወያኔ እንዴት የተንቤን ባላባቶችን ፊውዳል ናቸው ብላ መሬት ውስጥ አበስብሳ አትልታ እንደገደለች፣ አንድ የወያኔ መሪ ሁለት እህትማማቾችን ተኝቶ አድሮ ጠዋት ግንባራቸው ነድሎ እንዴት እንደረሸናቸው፣ ፀለምት ላይ በደርግ ተከበው የሚበሉት ቢያጡ ታጋዮቹ ዕጣ ተጣጥለው ዕጣው የወጣበትን የራሳቸውን ሰው አርደው በልተው ያን ክፉ የሚሉትን ዘመን እንዴት እንዳለፉት የነገሩንም ራሳቸው ናቸው። • ክረምቱ እየመጣም አይደል?
Показать все...
26.84 MB
👍 4 2
ጋዜጠኛ በለጠ ካሣ ይሄን ዘግቧል። "…ከትግራይ ደብረ ዓባይ ተከዜን የተሻገሩ የህወሓት ታጣቂዎች በሰሜን ጎንደር አዳርቃይ ወረዳ አሌ በተባለ ቦታ አሰቃቂ የንፁሃን ጭፍጨፋ ፈጽመዋል። "…ከአርሚ 11 በጀኔራል ወርቃይኑ የተላኩት ታጣቂዎች አራት ሕፃናትን እሳት ውስጥ በመጨመር አቃጥለዋል። 11 ሰዎችን በጥይት ደብድበው ገድለዋል። 17 ሰዎችን አፍነው ወስደዋል። 27 መኖሪያ ቤቶችን አቃጥለዋል። 534 የቁም ከብቶችን ዘርፈዋል። 1478 ሰዎች እንዲፈናቀሉ አድርገዋል። ከ40 በላይ ሰዎች የደረሱበት አይታወቅም። "…የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የፀጥታ አካላት ወደ ቦታው ደርሰው ያጣሩት መረጃ ነው። ታጣቂዎች ተጨማሪ ኃይል ከትግራይ ወደ ዋልድባ በኩል ተከዜን እያሻገሩ ነው። ግንቦት 27/2016 ዓም በማለት በቪድዮ የተደገፈ መረጃ አቅርቧል። "…በመቀሌ የዘፈን አይዶል ውድድር የሚያደርገው ትግሬ የሱዳን ዘፈን አድንቆ ከራያ የመጣ ተወዳዳሪ በአማርኛ ስለዘፈነ ለምን ብለው ዳኞቹ ጓ ያሉበትን ስታይ ምን ያህል በዐማራ ላይ ጥላቻ እንዳላቸው ነው የሚያሳየው። ሙዚቃ የዓለም ቋንቋ ነው። የህወሓት ሰዎች ጋር ሲደርስ ግን ሙዚቃ ራሱ ጠቦ ጠቦ ትግሬ ብቻ ይሁን ብለው ግግም ይላሉ። እና የዐማርኛ ሙዚቃ ተወዳዳሪ አንሰማም ያሉ ሰዎች በወልቃይት አማርኛ ዘፈን የከፈተ፣ በአማርኛ የሚነጋገር ሰው ይገድሉ ያስሩ የነበሩ ሰዎች አሁንማ ዐማራውን እንዲህ ጨፍጭፈው ቢጨርሱት ደስታቸው ነው። "…የትግሬ ነፃ አውጪ ሆይ ብታርፊ አይሻልሽም። ይሄን አይተው ቢያጨበጭቡልሽ የኦሮሞ ነፃ አውጪ አክቲቪስቶች ብቻ ናቸው። መከራ በራሳችሁ ላይ ባትጠሩስ? አሁን ይከብዳችኋል። አትሞክሩት። በእጥፍ የሚመልስ ትውልድ ነው የተፈጠረው። • ዐማራን ማረድ በጎንደር በኩል ወያኔ ጀመረችው ማለት ን ። እንግዲህ ሥራሽ ያውጣሽ።
Показать все...
2.60 MB
3.26 MB
👍 4 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
መልካም… "…ርዕሰ አንቀፄ በሚገባ መነበቡን የቴሌግራም ግድግዳዬ ምስክር ነው። የሚስቅ እንጂ የሚናደድ ሰው አለማዬትም ደስስ ብሎኛል። ቀጥሎ ደግሞ በቀጥታ የምንሄደው ወደ እናንተ ወደ ጎዶኞቼ አስተያየት የመቀበል ሂደት ነው። ካነሰ ጨምሩበት፣ ከጎደለ ሞሉበት፣ ከጠመመ አቅኑት፣ ተቃውሞም ካለ በጨዋ ደንብ ተቃውሞአችሁን ማቅረብ መብታችሁ ነው። • 1…2…3… ጀምሩ…!
Показать все...
👍 6
👆ከላይኛው የቀጠለ…✍✍✍ …እንዴት ፓርላማ ይገባል ብትል እሱ ለምን ያኔ ለህወሓት ግዜ አልተከራከርክም ለኦሮሞ ሲሆን ነው እንዴ ዐማራን ገድሎ ፓርላማ መግባት የማይቻለው ይልሃል። በዚህ መሃል ዐማራው በላይና በታች እንደ ብረት ተቀጥቅጦ በሁለት ወገን ስለት ያለው ሰይፎ ሆኖ ሸረካክቶህ ይመጣል። "…ዐማራም እንደምንም ብሎ ውለታ አይረሳም እና ገርፎ፣ ገፍፎ እንዲነሣ፣ እንዲነቃ ያደረጉትን ወሎዬዎችን እነ አቢይ፣ ዳኒ፣ ደመቀ፣ ገዱ፣ ጌቾ፣ ጻድቃንና ወዘተረፈን ከአፈር በመቀላቀል ምስጋናውን ያቀርብላቸዋል። እንዲህ አምናለሁ። አሁንም በርቱ። ዳኒዬ፣ አቢቹ አሁንም በከተማ ተዘፍዝፈው የተቀመጡ፣ እስከ አሁን ፋኖን ያልተቀላቀሉ፣ ፋኖንም የማይደግፉ ሆዳም ዐማሮች አሉና ዥለጣው ይቀጥል። ንፁህ ነው ምናምን የለም እሰር ዝም ብለህ። አማርረው። አርፎ የተቀመጠውን ሁላ አጎሳቅለው። ያን ጊዜ ሳይወድ በግዱ የዐማራነትን ክብር ለማስመለስ የነፃነቱን መንገድ ምርጫው ያደርጋል። • ድል ለዐማራ ፋኖ…! • ድል ለተገፋው ለዐማራ ፋኖ…! • ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ…!
Показать все...
👍 2
👆ከላይኛው የቀጠለ… ✍✍✍ …ኮሎኔል ፋንታሁንና ምሬ ወዳጆም አልሠሩለት። ጀግኖቹ የዐማራ ልጆች እነ ምሬ ወዳጆ እኮ በዚህ ጭንቅ ዘመን የተወለዱት በወለዬዎቹ በእነ አቢይ አሕመድ ጥጋብና እብሪት ምክንያት ነው። አቢይ አሕመድ መሃይም መሆኑ ለዐማራ የጠቀመውን ያህል ለማንም አልጠቀመም። አስባችሁታል? አቢይ አሕመድ እንደ መለስ ዜናዊ ትንሽ ቀለም ገብ ምሁር ቢሆን ኖሮ? በእውነቱ ከባድ ነበር። "…የጃዋር መሀመድ እናት የሰሜን ሸዋ ዐማራ ናት። ኦሮሞ ሞኝ ነው ብለው ከግራ ተጫወቱበት። ከብሔር ብሔረሰብ አናከሱት። እንደ መስኖ ቦይ ነዱት። ዛሬም እኔ ሳያውቁ ነው የሚመስለኝ እግዚአብሔር ባወቀ ግን እነዚህ ወሎዬዎች ሳያስቡት ዐማራን ወደ ነፃነት እያንደረደሩት ነው። ወሎዬው ዳንኤል ክብረት ቤተ መንግሥት ገብቶ ዐማራን እንደዚያ ሙልጭ አድርጎ አንዴ ጃዊሳ፣ አንደ ጃርት፣ አንዴ አሞሌ ጨው፣ አንዴ የሆነ ነገር እያለ ባይሳደበው ኖሮ ዐማራ አሁን በእልህ ይነሣ ነበርን? ወሎዬው አቢይ አሕመድ ፋኖን ሌባ፣ ዘራፊ ብሎ ባይሳደብ ኖሮ ዐማራ በዚህ መጠን ጓ ብሎ ይነሣ ነበርን? ወሎዬው አቢይ አሕመድ የዐማራን ተማሪዎች በጉራጌው ብራኑ ነጋ በኩል ባይረፈርፍ ኖሮ ዛሬ የዐማራ ፋኖ የተማረ የሰው ኃይል ያገኝ ነበርን? በወሎዬው አቢይ አሕመድና በወሎዬው ደመቀ መኮንን፣ በወሎዬው ዳንኤል ክብረት ምክር ዐማራን ጨፍጭፈው እልህ አስይዘው ባይበሰጩት ኖሮ ዐማራም ጓ ብሎ በንዴት፣ በእልህ፣ በቁጭት ደሙን ለመመለስ ባይንቀሳቀስ ኖሮ አሁን የምናየው ሁኔታ በዐማራ ምድር ይፈጠር ነበር ወይ? እኔ በፍጹም አይፈጠርም ባይ ነኝ። አስባችሁታል ያ ከይሲ መለስ ዜናዊ በህይወት ቢኖር ኖሮ? አስባችሁታል ወይ? አታስቡማ… እህእ በምላሱ አደንዝዞ ዐማራ እንደ ዋልያና የምኒሊክ ድኩላ፣ እንደ ቀይ ቀበሮም ቁጥሩ ሳይታወቅ ጠፋ ተብሎ በሰበር ዜና ይነገረን ነበር። "…እነ አቡነ ሳዊሮስ እና አይዋ አሰፋ አቡነ ዜና ማርቆስ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ዐማራ ባይሆኑ ኖሮ፣ ያውም የሰሜን ሸዋ ዐማራ በዚህ መጠን ኦርቶዶክሱ ነቅቶ የጠላትን ሴራ ያፈራርስ ነበርን? አይመስለኝም። ኦሮሞን መናጆ አድርገው እረድ እያሉት እያሳረዱት፣ አውድም፣ አቃጥል እያሉ እንዲያቃጥል እያደረጉት ለሽ ብሎ፣ ተኝቶ የነበረውን ዐማራ ጀት አድርገው እንደ አራስ ነብር፣ እንደ አቦሸማኔ ተምዘግዝጎ እንዲነሣ አደረጉት። አሁን ዐማራ በሀገሪቱ ላይ ወሳኝ ወደ ሆነ ምዕራፍ ወደሚያደርሰውን መንገድ ተያይዞታል። እኔ ይሄን ስናገር አንዳንዶች ድኩማን ቦለጢቃ ያልገባቸው ዐማራ ቅብ ዐማራ መሳይ ዐሞሮች አቢይን ወሎዬ አትበለው፣ ዳንኤልንም፣ ደመቀንም ወሎዬ አትበል ይሉኛል። በደም፣ በአጥንት፣ በጉልጥምት በምትመራ ሀገር እንዴት ነው እኔ እንደዛ የማልለው? እላለሁ እንጂ። ፈጥሬ አላወራሁ። "…እስቲ ተመልከቱ የገዳይነት ሥልጣን ከተሰጣቸው የአባ ገዳ ልጆች ምርኮኛ ጀነራሎች ውጪ የማነው? የውጭ ጉዳይ ሚንስትርነቱ የማነው? የዐማራ ያውም የሰሜን ሸዋ እና የወልቃይት ዐማራ ተወላጁ የአቶ አጽቀሥላሴ ልጅ አቶ ታዬ አጽቀጽሳሌሴ ነዋ የያዘው። ወያኔን በኒውዮር በተባበሩት መንግሥታት ጉባኤ ላይ ድራሽ አባቷን ያጠፋት ጎንደረፀና ሸዋዬው ታዬ ነው። አያችሁልኝ። ኦሮሞ እኮ አያርፍም። ፍርፋሪ ጥለውለት ነጭ ቡሉኮ አልብሰው ለኢሬቻ ካስጨፈሩት በቃ። አያችሁ ወሎዬዎቹ ተጠቃቅሰው የውጭ ጉዳይ ሚንስትርነቱ እንኳ ከዐማራ ያውም ከሸዋና ከጎንደር እንዲወጣ አላደረጉም። ይሞታሉ እንዴ? ፌዴሬሽን ምክርቤቱ በማነው የሚመራው በጎንደሬው አገኘሁ ተሻገር አይደለምን? ኦሮሞ የሽመልስ አብዲሳን ቀደዳ፣ የአዳነች አቤቤን ዲስኩር ከሰማ መች አነሰው? ኦሮሞ ኢሬቻ ወጥቶ ኢሬቻውን በልቶ ወደ ቤቱ ከገባ መች አናሰው? ኦሮሞ በቋንቋው እንዲጨፍር ካሜራ ፊት ካቀረቡት መች አነሠው? ከምር ዐማራ ይችላል። "…የብሔራዊ ባንክ ብሬዘዳንቱ ማነው? ጎጃሜው የጎጃም ዐማራው አቶ ማሞ እስመለዓለም ምህረቱ አይደለምን? ጎጃም ያደገው ወሎዬው ደመቀ መኮንን ምክትል ጠቅላይ ሚንስትርነቱን ለማነው የለቀቀው? ለጎጃሜው ተመስገን ጥሩነህ አይደለምን? የማዕድን ሚንስቴሩ ማነው የአገው ዐማራው ኢንጅነር ሀብታሙ አይደለምን? ቴሌ በማን ስር ነው በፍርዬ ሥር አይደለምን? ሌላው ቀርቶ ያለ ፍርድ ቤት ትእዛዝ እስከ አሁን በኦሮሚያ እስር ቤት ታጉረው የሚገኙት የኦነግ አባላት የታሠሩት በማነው በእነ አቢይ አሕመድ አይደለምን? የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነሩ ሳዲስቱ አቶ ደመላሽ ገብረ ሚካኤል ማን እንደሆነ የመረመረ ኦሮሞ እስከዛሬ አለ? አለወይ ንገሩኝ? የለም። ሰሜን ሸዋ መሳሪያ አስይዞ የፌደራል ፖሊስ አባላትን የሚልከው ማነው? መከላከያው የሚመራው በእውነት በብራኑ ጁላ ብቻ ነውን? የድሮን አስተኳሽ ዋነኛ ወሳኙ ሰው የየት ተወላጅ ነው? ኦሮሞ ይሄን የሚመረምርበት ጊዜም የለው። አንድ ሰው ኦሮሚኛ ካወራ፣ ስሙ የኦሮሞ ከመሰለው አበቃ። "…እናም ርዕሰ አንቀጼን ሳጠናቅ ዐማራ እንኳንም መልስ በኪሱ፣ በአደንዛዡ፣ በመለስ ዜናዊ ሥር እስከዛሬ አልኖረ። ዐማራ እንኳን በወላይታው ፓስተር በኃይለማርያም ደሳለኝ አስተዳደር ስር አልኖረ። ዐማራ እንኳንም ከተዘፈዘፈበት ገድለውት፣ ገርፈውት፣ ገፍፈውት፣ ጀት አድርገው፣ ለዐማራነቱ ዐማራው ቆርጦ በዘዴ እንዲታገል ባደረጉት በወሎዬዎች በእነ ደመቀ መኮንን እና በእነ አቢይ አመድ ዘመን ተቆስቁሶ ተነሣ። ጎንደሬው አገኘሁ ተሻገር ለአንድ ቀንም ቢሆን "ዐማራ ሆይ ሊወርህ የመጣውን የትግሬ ወራሪ ባገኘኸው ነገር ገድለህ መሣሪያውን ገፍፈህ ውሰድ፣ ውረስም ባይለው ኖሮ አስባችሁታል ግን? ብቻ በብዙ ነገር ዐማራ በዚህ በአቢይ አመድ ዘመን የሆነ ነገሩን አጥቶ፣ የበዛ ነገር አግኝቷል። እስሩ፣ ግድያው፣ መሰደቡ ሁሉ ለዐማራ ኢነርጂው፣ ወኔ፣ ጉልበትም ነው የፈጠረለት። ልክ ትግሬዎቹ በደርግ ጊዜ በሀውዜን ከተማ ላይ የራሳቸውን ሰው አስጨፍጭፈው ትግሬውን በሙሉ ታጋይ እንዳደረጉት ነው እነ አቢይ ዐማራውን ዠልጠው ገርፈው ይኸው አራስ ነብር እንዳደረጉት ነው የምቆጥረው። አዎ እንደዚያ ነው የምቆጥረው። "…ተመልከት አሁን ዐማራ ክልል ገብቶ እንደ ቄጤማ እየታጨደ ያለው ማነው? እነ አቢይ አፍሰውም፣ ፎግረውም አስገድደውም፣ ሰብከውም ወደ ዐማራ ክልል እየላኩት ያለው ማንን ነው? ኦሮሞውን አይደለምን? የደቡቡን ጴንጤውን አይደለምን? እና አቢይ አሕመድ በወለጋ የታረዱትን የወሎ ዐማሮችን፣ የጎጃም የጎንደር ዐማሮችን፣ በአሩሲ፣ በባሌ፣ በምዕራብ ሸዋ የታረዱትን ዐማሮችን፣ በኦሮሚያ ቄሮዎች፣ ሸኔዎች የታረዱትን ዐማሮች አራጆቹን ቀዬአቸው ድረስ ወስዶ አላስረፈረፋቸውም። አላሳጨዳቸውምን? ብድር በምድር አላስከፈላቸውምን? ጎንደር ሚስቱ ዝናሽ ሀገር የተላከው የኦሮሞ ወታደር ለዘር ተርፏልን? ንገሩኝ ወሎ የገባው የኦሮሞ ወታደር በደፈጣ፣ በቆረጣ እምሽቅ እያለ ያለው በማን ጥበብ ይመስልሃል? ኦሮሞ ይሄን ቢባንን ችግር ስለሚፈጥር ይሄን ነገር ብዙ ማጮህ አስፈላጊ አይደለም፣ እነ ጉማ ሰቀታ፣ እነ ዳንኤል ዳባ። ዳንኤል ዳባ በነገራችን ላይ የመርካቶ ጉራጌ ነው በእናቱ ወገን። መኪና ሽጠው ነው በሜክሲኮ በኩል አማሪካ ቦስተን ያስገቡት። አዎ ከነቁ ደግሞ እነ ሕዝቅኤል፣ እነ ፀጋዬ አራርሳ ጓ ይሉና ነገር ያበላሻሉ። ጎንደሬውን መላኩ አለበልን ከፈረንካው አካባቢ ቢያርቁት የሚፈጠረውን አስባችሁታል? አቶ ደመቀ መኮንን፣ አቶ ላቀ አያሌው ከሥልጣን ወረዱ ተባለ አይደል? እሺ ይውረዱ አሁን የት ናቸው? የሚያውቅ ሰው አለ? የለም። 👇ከታች ይቀጥላል…✍✍✍
Показать все...
👍 4
"ርዕሰ አንቀጽ" "…አስባችሁታልን…? የዐማራ ሕዝብ አስቀድሞ በጥቂት ልባም ልጆቹ በኩል ባይነቃ ኖሮ አሁን ላይ ምን ሊውጠው? ምንስ ሊገጥመው እንደሚችል? ደግሞስ ፈጣሪ እንደ አቢይ አሕመድ ዓይነቱን "ሀ" ገደሉ ንክ የአእምሮ በሽተኛውን ጠሽ መሪ ባይጥልለት ኖሮ አስባችሁ ታውቃላችሁ እንዴት ሟምቶ ይጠፋ እንደነበር? እንደ አፅሜ መለስ ዜናዊ ዓይነት አሳስቆ እያጃጃለ እያሟሟም ገዳይ በሕይወት ቆይቶ በላዩም ላይ ነግሦ ቢቀጥል ኖሮ አስባችሁታል ወይ በአሁን ሰዓት ዐማራ ላይ ምን ሊፈጠር እንደሚችል? እኔ ሳስበው ይዘገንነኝ እና እሳቀቃለሁ። ቃል አክባሪው ዐማራ፣ መሪ ሁሉ መሪ የሚመስለው ዐማራ፣ ሁሉን አማኙ ዐማራ መለስ ዜናዊ ከነተንኮሉ እስከአሁን ኖሮ ቢቀጥል ኖሮ አልቆለት ነበር። መቼም እግዚአብሔር ሳይደግስ አይጣላም አምጥቶ አቢይ አሕመድን የመሰለ ጠሽ ጣለለት። አቢይ አሕመድ ለዐማራ ከሰማይ የወረደ የነጻነቱ ቀንዲል፣ የጣለውን ነፍጥ ያነሳበት ገፊ ምክንያቱ ነው። አስረዳለሁ… "…በመለስ ዜናዊ ሰበካ እና አደንዛዥ ምላስ ተወስውሶ በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሰበብ ትግሬና ትግሬ በተጣላ ባድመ፣ ፆረና፣ ቡሬ፣ ዛላንበሳ ወዘተረፈ ሄዶ ያለቀውን የዐማራ ልጅ አስቡ። መለስ ዜናው ዐማራውን ትግሬ ምድር አስገብቶ ከላይ በሻአቢያ ከኋላ በትግሬ አዛዦች እንደ ጉድ ነው የጨፈጨፉት። ሻአቢያና ወያኔ ለሁለት ነው ፍጭት ያደረጉት። ዐማራው ታዲያ ሞቶም በዘፈን ይሸነግሉት ነበር። ቀላል ይዘፍንለታል? ዘሩን በጦርነት ሰበብ እየቀነሱት ለመንቃት አልቻለም ነበር። ኢትዮጵያን ከልቡ ስለሚወዳት በኢትዮጵያ የመጣን ሁለቴ አያስብም። ገበሬው ሞፈሩን ጥሎ፣ ነጋዴው ንግዱን፣ ወዛደር ሸክሙን፣ መምህሩ ጠመኔውን፣ ተማሪው ደብተሩን ጥሎ ነው እየፎከረ፣ እየሸለለ፣ ደስስ እያለው የሚዘምተው፣ ደስስ እንዳለው ለሀገሩ የሚሞተው። ግን ውለታ ከፋይ፣ አመስጋኝ የለውም። እሱ ሀገሩን በሞቱ ሲገነባ የትግሬና የኦሮሞ ነፃ አውጪዎች ነን ባዮች ስሙን ሲያጠለሹ፣ ለሞቱ መርዝ ሲቀምሙ ነው የሚገኙት። ከአናሳ አእምሮ ከዚህ በላይ ሊመነጭ፣ ሊፈልቅ አይችልም። "…ዶር ቴዎድሮስ አድኃኖም የተባለ አስመራ ኤርትራ የተወለደ የደርግ ልጅ የወያኔ ባለ ሥልጣን በነበረ ጊዜም ዐማራ በወባ በሽታ እንደ ቅጠል ረግፏል። በኤድስ በሽታ ማስፋፋት ረግፏል። ኪኒን እያስዋጠ፣ በመርፌ እየወጋ መካን አድርጎ ያለዘር እንዳስቀረውም ባለሙያዎች መስክረዋል። ይህን ሁሉ እያየ ዐማራ ሊቃወም አልተቻለውም ነበር። ዝም ብሎ ነበር የሚሞተው። በፓርላማ ብቻ የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ አካሂደን ከሦስት ሚልዮን በላይ ዐማራ የት እንደገባ አናውቅም ብለው እንደ ጠፋ ዕቃ ሪፖርት ሲያቀርቡ ለምን ብሎ ጓ የሚል ዐማራ አልነበረም። ዐማራውን እንኳን ሊሟገቱለት ይቅርና እንደ ዓለምነህ መኮንን ዓይነቱ ጭራሽ የተሾመበትን ሕዝብ ዐማራውን ለሀጫም፣ ንፍጣም እያሉ ነበር ሲሰድቡት የነበር። ይሄን የሚበቀል ዐማራም አልነበረም። ዐማራው ከደቡብ፣ ከቤኒሻንጉል ተጨፍጭፎ ሲፈናቀል፣ መለስ ዜናዊ የተጨፈጨፉት፣ የተፈናቀሉት ዛፍ ቆርጠው፣ ደን ጨፍጭፈው ነው በማለት በፓርላማ ሲሳለቅበት መልስ የሚሰጥ ዐማራ አልነበረም። የጎጃም ዐማራ ወንዱ እንደ ሴት ማኅጸን ዘሩን ሲያስቋጥር፣ በመርፌ የዐማራ ሴት እንዳትወልድ ሲደረግ ለምን የሚል ዐማራ አልነበረም። በወልቃይት የአማርኛ ሙዚቃ ሰማችሁ ተብለው፣ አማርኛ አወራችሁ ተብለው ዐማሮች ሲገደሉ ምላሽ የሚሰጥ ዐማራ አልነበረም። ትግሬው መለስ ዜናዊ ዐማራን አፉን ለጉሞ ረግጦ የሚገዛበት የሆነ ጥበብ ነበረው። "…አሁን በመጨረሻ መጣልሃ ወሎዬው የወሎ ዐማራው የኦሮሞ ጠርናፊ አቢይ አሕመድ፣ መጣልሃ እብዱ ቀዌው አቢይ አመድ። መጣልህና የትግሬንም፣ የኦሮሞንም ድብቅ ገዳይነት፣ ጨፍጫፊነት፣ በጥበብ የዐማራውን ዘር አጥፊነት በአንደዜ ገለፀው፣ አደባባይም አወጥቶ አረፈው። መጣልሃ አቢይ አህመድ ዋሾ፣ ቀጣፊው፣ በሥልጣን ጥም ያበደው ፓስተርና ኡስታዙ። መጣ እየደሰኮረ፣ እያፏነነ። መጣና ዐማራ እንዲደራጅ፣ ዐማራ ትጥቅ እንዲታጠቅ፣ ዐማራ ዐማራ ነኝ ብሎ እንዲነሣ አደረገው። ይሄ የሆነው እግዚአብሔር ብቻ ባወቀው መንገድ ነው። አቢይ ባይመጣና ሀገሩን ዝብርቅርቁን ባያወጣው ኖሮ፣ አቢይ መጥቶ ትግሬዋን ህወሓት እወጋለሁ ብሎ ትግሬ ምድር ድረስ ገብቶ ነካክቷት ባይወጣ፣ ትግሬዋም ሂዊም እንደ ድሮ መስሏት አቢይን ተከትላ ዐማራ ክልል ድረስ ዘከንተፍ ዘከንተፍ እያለች ዘው ብላ ባትገባ ኖሮ ዐማራ ለዛሬው ለመነሻ የሚሆነውን ጠመንጃ ከየት ያገኝ ነበር? ምስኪን ሚልዮን ትግሬዎች ተግተልትለው ወደ ዐማራ ክልል እንጀፍ፣ እንጀፍ እያሉ ባይገቡ ኖሮና ዐማራም ያንን ሁሉ ትግሬ ከአፈር ቀላቅሎ መሳሪያውን ባይረከበው ኖሮ አስባችሁታል? "…አዎ ለዐማራ ነፃነት መፍጠን ዋነኛው ምክንያት በሻሺቱ እንግዳ የወይራ ጢስ ጥንቆላ የተወለደው የላስታ፣ መሪ፣ ጠዳ፣ ተወላጇ የወሮ ትዝታ ወልዴ ፈንታ ልጅ በወሎዬው በወሎ ዐማራው በአቢይ አሕመድ ዘመነ መንግሥት ነው። ይሄ ዘመን በዐማራ ታሪክ ውስጥ በጉልህ ተጽፎ የሚቀመጥ ዘመን ነው። ወልቃይት የታጠቀው፣ መሬቱን የተረከበው በወሎዬው አቢይ አሕመድ እና በወሎዬው አማካሪው በዳንኤል ክብረት ዘመነ መንግሥት ነው። ወሎዬው ደመቀ መኮንን፣ ወሎዬው ገዱ አንዳርጋቸውም ቀላል አበርክቶ አይደለም ያላቸው። ዛሬ ላይ ገለል ቢደረገሙ ለዛሬው ዐማራ እሳት ለብሶ፣ እሳት ጎርሶ መነሣት ጉልህ ድርሻ ነው ያላቸው። ኦሮሞ በዚህ ዘመን መናጆ ነው የሆነው። እነ ዳኒና አቢይ ኦሮሞን እንደ ዕቃ ነው እየተጠቀሙበት ያለው። ኦሮሞ ለምን ብሎ የሚጠይቅ ሰው ስለሌለው፣ አይ ኦሮሞ እያሉ እየቀለደቡት ነው እየነገዱበት የሚገኘው። ወሎዬው አቢይ አሕመድ ከጎንደሬዋ ዝናሽ ታያቸው ጋር ሆኖ ለዐማራ የዋሉለትን ውለታ ዐማራ መቼም ከሲኦል ቀላቅሎአቸውም ቢሆን ሳይከፍላቸው የሚቀር አይመስለኝም። "…አቢይ አሕመድ ኦሮሞን ከመጸየፉ የተነሣ የኦሮሞ ሴት እንኳ አላገባም። መለስ ዜናዊም እንደዚያው ትግሬ አላገባም። ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ መንግሥቱ ኃይለማርያምም ቢሆን ሁላቸውም ጎንደሬ ወይ ዐማራ ሴት ነው ያገቡት። ዘመኑ የኦሮሞ ነው ተብሎ በሚነገርበት፣ እውነትም ኦሮሞም ዘመኔ ነው ብሎ በሚፏልልበት በዚህ ዘመን ቤተ መንግሥቱ አሁንም እንኳ በጎንደር ዐማራዋ ዝናሽ ታያቸው እና በወሎ ዐማራው አቢይ አሕመድ ቁጥጥር ስር ነው ያለው። መቼም የፈጣሪ ሥራ እኮ ይገርማል። በወሎዬው አቢይ አሕመድ ዘመን ነው የወሎ ዐማሮች በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የዐማራ ጦር በወሎ ምድር የመሠረቱት። የላስታ፣ የራያ፣ የሰሜን እና ደቡብ ወሎ ፋኖ ሆኖ እስላም ክርስቲያኑ ታጥቆ ወራሪውን የኦሮሙማ ጦር አፈር ከደቼ እየቀላቀለ ያለው በወሎዬው በአቢይ አሕመድ ዘመነ መንግሥት ነው። ይሄንን መካድ አይቻልም። "…ዐቢይ ኦሮሞንም ዱቄት እያደረገው ነው። ወሎዬው አቢይ ወሎዬውን ጌታቸው ረዳን ይዞ ነው የዓድዋ ትግሬዎችን እነ ደፂን ልክ እያስገባቸው ያለው። አሁን የትግሬ ንጉሥ ወሎዬው ጌታቸው ረዳ ነው። ወሎዬው ገዱ አንዳርጋቸው እንዳይታሰር አድርጎ በቦሌ ወደ አውሮጳ የሸኘው ወሎዬው አቢይ አሕመድ ነው። ወሎዬው ደመቀ መኮንን እና ወሎዬው አቢይ አሕመድ፣ ከወሎዬው አማካሪው ከዳንኤል ክብረት ብርሃኔ እና (ዳኔ ወሎ ተወልዶ ባህርዳር ጎጃም ይደግ እንጂ የኤርትራ ትግሬ ነው) የሚሉ እንዳሉ ሆነው ከወሎዬው ገዱ አንዳርጋቸው ጋር በመሆን ለዐማራው የሠሩለትን ሥራ እነ አርበኛ ዘመነ ካሴም፣ ጋሽ መሳፍንትም፣ ጋሽ አሰግድና መከታውም… 👇ከታች ይቀጥላል…✍✍✍
Показать все...
👍 5
👆ከላይኛው የቀጠለ…✍✍✍ "…እናም ወሎዬው አቢይ አመድ ዐማራ ሀገሪቷን እንዲረከብ በግሩም ሁኔታ እየሠራ ነው። ተከፋዮቹ እነ ብሩክ አበጋዝ እንኳ ወሎዬ ናቸው። ጃጀው እና ጌትነት አልማው ጎንደሬና ጎጃሜ ናቸው። አቶ በቴ ኡርጌሳ ለኦሮሞ ትግል በጣም ጠቃሚ ሰው ነበር። ነገር ግን አቶ ምን ሆነ? ጃዋር መሀመድ አሁን የት ነው ያለው? እናውራ እንዴ? የአብኖቹ እነ ክርስቲያን ታደለ መታሰራቸቅን ብቻ አትዩ። አትመልከቱ። ወሎዬዎቹ በለጠ ሞላና የሱፍ ኢብራሂም ተሹመው እነ በቴ ኦሮሞዎቹ በጥይት ተደብድበው የሞቱት ወደው ይመስልሃል? ገና ወሎዬው የወሎ ዐማራው ጌታቸው ረዳ ሚንስትር ይሆናል። ገና የራያው ተወላጅ ጻድቃን ገብረ ተንሣይ ወዘተረፈ ወሎ የወሎ ዐማሮች ወደፊት ይመጣሉ። እኔ እንደዚያ ነው የማምነው። ይሄ የዓድዋ የእነ አቦይ ስብሃት፣ መለስ ዜናዊ መስመር፣ የኦሮሙማው መስመር ሰው ባላወቀ፣ እግዚአብሔር ባወቀ በንጉሥ ሚካኤል ልጆች በወሎዬዎቹ በእነ አቢይ አህመድ፣ በእነ ጌታቸው ረዳ፣ ጻድቃን፣ ዳንኤል ክስረት፣ ወዘተረፈ ይጸዳል። "…ትናንት በምንጃር፣ በሰሜን ሸዋ ያለቀውን የኦሮሞ መከላከያ ብዛት ያየ ኦሮሞ ተርፏል ወይ ብሎ ቢጠይቅ አይፈረደብትም። ትናንት ጎጃም ላይ ያለቀውን የኦሮሞና የደቡብ ጴንጤ ወታደር ያየ እየተሠራ ያለው ሥራ ወለል ብሎ ነው የሚገለጽለት። አይደለም የሚዋጋው ብርሸለቆ የገባው ምልምል ወታደር ለጉድ ነው። ትናንት ጎንደር በክፍለጦር ደረጃ ለጎንደር ዐማራ ፋኖ እጁን የሰጠው መከላከያን ያየ መከላከያ ውስጥ ያሉ ዐማሮችና የዐማራ ወዳጆች ባይኖሩ ኖሮ ብሎ ማሰብ ግድ ነው። አቢይ አሕመድ እስክንድር ነጋን ብአዴኖች በቁጥጥር ስር አውለውት ሳለ ታስሮ ወደ አዲስ አበባ እየመጣ ሳለ ደጀን ሲደርስ መኪናውን አስቁሞ ትንሽ ድራማ ተሠርቶ ወደ ባህርዳር መልሶ በአውሮጵላን ማምጣት ሲችል ፍቱት ብሎ መልሶ ባህርዳር ላይ የለቀቀው ምን አስቦ እንደሆነ አንድም የትግሬ ነፃ አውጪና አንድም የኦሮሞ ነፃ አውጪ ጠርጥሮ አይቼም ሰምቼም አላውቅ። ወዳጄ አርበኛ ዘመነ ካሤን በእሁድ ቀን ከእስር ቤት አውጥቶ፣ በከተማ ምን ሳያስደርገው አቆይቶ፣ አሁን ጫካ ገብቶ የኦሮሞን ወታደር እንዲያጭድ እንዲከምር፣ የዐማራን ፋኖን እንዳይበተን ያደረጉት ወሎዬዎቹ የቤተ መንገሥት አለቆች ናቸው ብለህ ብትጠራጠር መናፍቅ አያሰኝህም። "…ወሎዬዎቹ እነ አቢይ አሕመድ በቀጣይ የሚያደርጉትን እንገምት። አንድም የኦሮሞ ቄሮ ለዘር ሳያስቀሩ ወደ ዐማራ ክልል ከፋኖ ጋር ለማዋጋት ይልካሉ። በዚያም ማንም ተጠያቂ ባልሆነበት መንገድ የኦሮሞ ቄሮ በዐማራ ምድር እንዲደመሰስ ያደርጋሉ። ዐማራ በዘር ማጥፋት አይከሰስ፣ አይወቀስ አለቀ። ወሎዬዎቹ አሁንም ተመካክረው የቀረውን የትግሬ ወጣት የእሳት ራት ለማድረግ ትግሬን እስከ ወልድያ ድረስ ጎትተው ያመጣሉ። ከወልድያም አሳልፈው እስከ ደሴ ሊያመጧት ይችላሉ። ከዚያ ትግሬ ዐማራ ምድር ላይ ዘሩ ያልቃል። በላይ በጎንደርም እንዲሁ ያስደርጋሉ። ሞኙ የትግሬ ነፃ ዐውጪም እውነት መስሎት ዘው ብሎ ይገባል ነገር ግን አይወጣትም። የሚደርሰኝ የቪድዮ መረጃ የሚያሳየው ይሄንኑ ነው። "…በመሃል የነቁ የኦሮሞ ነፃ አውጪዎች እና የትግሬ ነፃ አውጪዎች ወጥረው ወትውተው ይቺን ክረምት ዐማራ ክልልን ለማድቀቅ መላላጣቸው አይቀርም። ህወሓት ራያና አላማጣን ይዛለች። ወሎ ፋኖ እንዲዋጋ ይጠበቀል። እነ ህወሓት መከላከያው ካገዛቸው ፋኖን አጣብቀው ሊወቅጠጡት ይመኛሉ። ጎንደርም ላይ ልክ እንደዚያው ማድረግ ይፈልጋሉ። ዐማራ በዚሁ ፍጥነት በቶሎ ጎንደርን ከብልፅግና ሠራዊት ነጻ ካላወጣ ወያኔ ወለቃይትን ሊወስድ ሲመጣ የጎንደር ፋኖ ሲከላከል የኃይል መሳሳት ሊፈጠር ይችልና በመሐል ቤት ከጀርባ ሊወቁ ማሰባቸው አይቀርም። የጎጃም ፋኖም በሦስት አቅጣጫ ሊፈተን ይችል ይሆናል። ሸዋንም በርከት ያለ የኦሮሞ ቄሮና የጁላ ወታደር ይፋለመዋል ተብሎም ይጠበቃል። ዕቅዳቸው ከዚህ አይዘልም። የዐማራ ፋኖም በዚያው መጠን መዘጋጀቱ አይቀርም። ጎጃም ፋኖ ጎጃም ላይ ብቻ አይወሰንም። የጎጃም ፋኖ ወደ ጎንደር የሚተመውን ቀርጥፎ ካስቀረ ጎንደር ከሱዳንና ከመቀሌ የሚነሣውን የትግሬ ወራሪ ማደባየት አያቅተውም። ወልቃይት ላይ ከሀላ እንዳይመቱ አድርገው ትግሬ ለወረራ ከመጣ ጎንደር የትግሬን ወራሪ መቀጥቀጡን ይቀጥላል ማለት ነው። ሸዋም ከኦሮሙማው ቄሮ ጋር እየተዋጋ ጎን ለጎን አድማሱን ማስፋት ይጠበቅበታል። "…ልብበሉ ወለዮዎቹ እነ አቢይ ህወሓትን በኢትዮጲያ ስም ለማድቀቅ በሻሻ ለማድረግ ሰበብ ፈልገው ጦር አዘመቱባት። ከዚያ ደግሞ በተንኮል ዐማራንና አፋርንም ጨምሮ በሴራ አስመቷቸው። አሁን ደግሞ ህወሓትን ሽባ ካደረጓት በኋላ ወደ ተፎካካሪ ፓርቲነት የመለሳት ያለ ምክንያት አይደለም። "በጦርነት ትጨፈጭፈውና በሰላሙ ትደግመዋለህ፣ በጦርነት ድል አድርገህ በሰላም ስም አባብለህ ካልያዝከው ተመልሶ ይበላሃል ብሎ ራሱ አቢይ የተናገረውን ቪድዮ ማየቱ በቂ ነው።  አቢይ እንዲህ ያለው በቴሌቭዥን በሕዝብ ተወካዮች ስብሰባ ላይ ነው። እንዳለውም ህወሓትን መጀመሪያ አደቀቃት፣ ከዚያ በሰላሙ ባለው አሁን እየካሳት ነው። አቢይ ሌላውን በሻሻ ሲያደረግ ህወሓት ተመልሳ እንዳትበላው በሰላሙ እያንበሸበሻት፣ እየካሳት ነው። •የሁሉንም ክልላዊ መንግሥት አመራሮች መቀሌ ድረስ ልኮ ለማስተዛዘኛ ሳንቲም እንዲመፀውቱላት አስደረገ። አቤት ግፉ እኮ። አዳነች አበቤን ወስዶ አላገጠባቸው። •በፕሪቶሪያ ስምምነት ሰበብ ከተገደሉት ትግሬዎቹ የህወሓት አመራሮች መካከል እንዲተርፉ የተደረጉት የተወሰኑ የህወሓት አባላት እና ወታደሩ ጭምር በራብም እየተገረፉ ስለነበር እንዲያገግሙ አደረጋቸው። ጌታቸው ረዳን ሬድዋን ሁሴን ይዞት አውሮጳ ሆላን ወስዶ ጫማ ሁላ ገዛለት። •ትግሬዎቹ ምቾት እንዲሰማቸው በሚሊኒየም አዳራሽ ትግሪኛ ጨፍሩ። ባህላችሁን ግለፁት፣ ደስም ይበላችሁ ብሎ ፈቀደላቸው። አስጨፈራቸውም። እነሱም ደስ አላቸው። ጨፈሩም። ብዙዎቹም አዲስ አበባ ገቡ። አዲሰ አበባን ለልመና ሁሉ ነው የፈቀደላቸው። •አሁን አላማጣን ሰጣቸው። ገና እስከ ሰኔ 30 ወልቃይትን ሁሉ ትወስዳላችሁ ብሏቸው የሌለ ጮቤ ረገጣ ላይ ናቸው። ደስታቸውን አስቡት። •ህውሓትን ከአሸባሪነት አውጥቶ እንደ አብን ተፎካካሪ ፓርቲ አድርጓት አረፈው። ይሄ ማለት በጦርነት ያሸነፍከውን በሰላሙ ካሰው፣ በሰላሙ ካልካስከው መልሶ ይነክስሃል በሚለው መርሁ መሰረት እየተተገበረ ያለ ነው። ህወሓት አሁን በሰላሙ ተክሳለች አቢይም፣ ወይም ኦሮሞ እንዲህ አደረገኝ አትልም። እንዲያውም የአቢይ ጠላት ጠላቴ ነው ብላ የምትፎገላው።             "…ወሎዬዎቹ እነ አቢይ ለዐማራ ፋኖም ይሄንኑ ሂደት ነው የሚያስቀምጡት። በእነሱ እሳቤ የደም ግብሩም አለ። እንደ ትግሬ 1ሚልዮን ሳይሆን አንድ 10 ወይ ደግሞ 15ሚሊየን ዐማራ ጨፍጭፈው ካበቁ በኋላ የቀረዉን በመደለያ ደልለው ቂም እንዳይዝም አድርገው ከዚያ አፋርን፣ ሶማሌን፣ ደቡብን በተመሳሳይ መንገድ በኢትዮጵያ ስም እየጨፈጨፉ፣  ለኦሮሞም ይኸው ይህን ሁሉ የምናደርገው ለአንተ ጥቅም ስንል ነው። መጨረሻ ላይ ሁሉንም ክልል ወግተን በሻሻ አድርገን ስናበቃ የነፃነት ሃውልቱን አምቦ ላይ እንተክልልሃለን። እስከዚያው ሙትልን እያሉ ይማግዱታል። ነገርየው የሚያሳየው ግን ዐማራው እየባሰበት መምጣቱን ነው። ወሎዬው አቢይ ለህወሓት የተሻሻለ የምርጫ ሕግ ያወጣል። ለሸኔም እንዲሁ ያወጣና ሸኔም ሕጋዊ ፓርቲ ትሆናለች። አንተ ተነሥተህ ሸኔ 👇ከታች ይቀጥላል…✍✍✍
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
መልካም… "…የትንሣኤውን ጌታ ያውጅ ዘንድ ዘወትር የምንጠብቀው 1ሺ ሰው ሞልቷል። እንዲያውም አልፏል። አሁን ደግሞ በመርሀ ግብራችን መሠረት በቀጥታ የምንሄደው ወደ ተለመደው ርዕሰ አንቀጻችን ነው። "…የዛሬው ርዕሰ አንቀጻችን የሚዳስሰው፣ የሚቃኘውም "ወሎዬዎቹን" የዐማራ ፋኖ ነዳጆችን ነው የሚያወሳው። ዐማራ መቼም የእነዚህን ውለታ መቼ ቆጥሮ እንደሚከፍል ባላውቅም እኔ ዛሬ ዞሬአቸዋለሁ። "…የዛሬውን ርዕሰ አንቀጼን የሚያነብ ኦሮሞም፣ ትግሬም፣ የወሎም፣ የጎጃም፣ የጎንደር ዐማራም መናደድ የለበትም። ሸዋም አመስጋኝ ነው መሆን ያለበት። 😂 "…አሁኑኑ ልለጥፈው ነኝ ዝግጁ ናችሁ…? ወይስ እስ ሰነ 30 ልጠብቅ…? ሃኣ…?
Показать все...
👍 3
Фото недоступноПоказать в Telegram
“…የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ፤ እርሱንም በእግዚአብሔር በተወሰነው አሳቡና በቀደመው እውቀቱ ተሰጥቶ በዓመፀኞች እጅ ሰቅላችሁ ገደላችሁት። እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና።” ሐዋ 2፥ 22-24 • ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ~በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን • አሰሮ ለሰይጣን ~አግአዞ ለአዳም • ሰላም ~እምይእዜሰ • ኮነ ~ፍስሐ ወሰላም።
Показать все...
🙏 5 2🕊 1
"…ኦነግ ተቀብቶ የሚዋጋው የፓስተር አራራ ዘይት ይሄ ነው። 😂 ጥይት እንዳይመታቸው የወለጋ ጴንጤ ኦነግ ይሄን ተለቅልቆ ነው ወደ ውጊያ የሚገባው። • እምነት መሆኑ ነው። •
Показать все...
👍 3😁 3