cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ዘመድኩን በቀለ

የዘመድኩን በቀለ ጦሟሩን እንደወረደ የሚለቀቅበት ስለሆነ ሁላችሁም ዘመዴን አድናቂዎች ተቀላቀሉት ጆይን አድርጉት ሸሩን ትታችሁ ሼር አድርጉት

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
4 099
المشتركون
-924 ساعات
-267 أيام
-5730 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

Photo unavailableShow in Telegram
መልካም… "…ርዕሰ አንቀጹ መነበቡን እያየሁ ነው። ዛሬም እስከአሁን ድረስ በርዕሰ አንቀጹ ላይ በኢሞጂም ቢሆን 😡 የተናደደ፣ የበገነም ሰው አላየሁም። ቀጥሎ ደግሞ የ100 ያህል አንባቢዎችን ሓሳብ እንቀበልና ከዚያ ወደ ሌሎች መረጃዎች እናልፋለን። "…ዐማራ ቢሸነፍለት አቢይ ቀጥሎ ከአፋር እና ከደቡብ በፊት ሱማሌን ነበር ለጥብስ ያዘጋጃት። ከሱማሌ በፊት ግን የሸዋ ኦሮሞ መመታት እንዳለበት በድንገቴ መወሰኑ ነው የሚሰማው። "…ሸዋዎች መሬትም፣ ሰውም ሽጠው፣ ዘርፈው በኢኮኖሚ ፈርጥመዋል። አቢይ አሁን በቀላሉ ሽመልስን ከሥልጣን ለማውረድ አይቻለውም። አዳነችንም እንደዚያው። ሊያደርግ የሚችለው አንድ ነገር ብቻ ነው። በወለጋ ጴንጤና፣ በኦሮሞ ወሃቢይ እስላም መቀጥቀጥ፣ ከዚያ ቀዳዳ ካገኘ በሙስና አዋክቦ ማስወገድ። ከቻለ ነው እሱንም። "…አቢይ የወሃቢያ እስላምንም አሁን ይጠቀምበት እንጂ ኋላላይ እነሱንም መብላቱ አይቀርም የሚሉ አሉ። ኤምሬትስ ወሀቢይን እየጠረገች ስለሆነ ከሀገሯ፣ ሳዑዲም ወሀቢይን ከሀገሯ አባርራ ወደ አፍሪካ ነው የገፋቻቸው። እዚህ እንዲረብሹ ማለት ነው። አቢይ ወሀቢይ አሁን ከፈረጠመ በኋላ ላይ ልቆጣጠረው ቢል ይከብደዋልም ነው የሚሉት ታዛቢዎቹ። "…ዐማራና የዐማራ ፋኖ ወግሞ ያዘ እንጂ አቢይ ሁሉንም በሻሻ አድርጎ ህልሙን ለመኖር ቋምጦ ነበር። ጃልመሮን ሲደራደር፣ ሸዋ የእኛስ ጃልሰኚ? ከጃል ሰኚ ጋርስ ማነው የሚደራደረው? ብለው ነበር። 😀 ሁሉም የራሱ ሸኔ ስላለው ማለት ነው። "…የፖለቲካው ቅማንት ከፋኖ ጋር መዋሃድ መጀመሩ ያሳበዳቸው ብልፅፄና ሂዊ አገው ሸንጎ ላይ መሥራት ጀምረዋል። ፋኖ ከአገው ማበሩ፣ ከጉምዝም ጋር መታረቁን ሲያዩም የቤንሻንጉል ነፃ አውጪ ነው የተባለውን በእርቅ ሰበብ አምጥተውታል። በጅማ ዐማራን ትጥቅ ለማስፈታት እየሞከሩ ነው። • ፋኖዬ ወጥር 💪💪🏿✊
إظهار الكل...
👍 2
👆ከላይኛው የቀጠለ…✍✍✍ …ከሻአቢያ ጋር ሁላ እሠራለሁ እያለ ነው። የጌታቸው ረዳን ጠባቂዎች ፌደራል መንግሥቱ ቀይሮለታል የሚባለው እዚያ አካባቢ ካለ ትርምስ የመነጨ ነው። "…አሁን የፋኖ ትግል ጠንከር ሲል የሸዋ ኦሮሞዎች ግግም ብለው አዳነች አቤቤን ጠቅላይ ሚኒስትር እናደርጋለን ብለው በውስጥ ለውስጥ መክረው ጨርሰዋል። በእነሱ ቤት የአርሲ ሰው መምረጣቸው ነው። እሷ ግን ከሸዋ ወደ አሩሲ ከሄዱ ቤተሰቦች የተገኘች ሸዋዬ ነች። በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ባለሀብቱንም ሌላውንም ይዛለች፣ በዚያ ላይ ደፋር ሴት ነች ተብሎ ነው እሷን ይዘው መንቀሳቀስ የፈለጉት። አዲስ አበባ ምሽት ምሽት ዓድዋ ሚዚየም ጋር ወለጋ፣ አሩሲ፣ ጅማና ሸዋ ፉክክር ውስጥ ገብተው ሲያቀልጡት ታያለህ። ወደ ኋላ እንመለስና ታንዛኒያ እንሂድ። ታንዛኒያ ስንሄድ ሬድዋን ሁሴንን እና ጌታቸው ጉዲናን እናገኛለን። ብልፅግና እና ኦነግ ሸኔ በታንዛኒያ ድርድር ሲያደርጉ አቢይ የላከው እነርሱን ነበር። ከታንዛኒያ መልስ የጠቅላዩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ የነበረው ሬድዋን ሁሴን በተመስገን ቦታ ተተክቷል። ሬድዋን በህወሓትም፣ በአቢይም ለመወደድ የሚሠራ ስልብ ባሪያ ነው። ጌታቸው ጉዲና ከጃል መሮ ጋር ከተደራደረ ወዲህ በየትኛውም የመከላከያ ዜና ላይ ጠፍቶ ነበር የቆየው። አቢይ ጌታቸው ጉዲናን ለድርድር የላከው ከሸዋ ኦሮሞ መጥቶብኛል የሚለውን ስጋት ለመሻገር ጌታቸው የወለጋ ሰው ስለሆነ በእሱ በኩል ነገሩን መያዝ ስለፈለገ ነው። የሸዋዎች መፈርጠም አቢይን ጌታቸው ጉዲና ላይ እንዲጣበቅ አደረገው። ለዚህ ነው የሪፐብሊካኑ አለቃ እና የመከላከያ መረጃ ደህንነቱ አለቃ የአብይ ደህንነት ስላሰጋቸው እንደገና ጥበቃውን የሚያጠናክር ሌላ ጋርድ ያስመረቁት። "…የዐማራ ፋኖ በጀመረው ይቀጥል። ሥልጠናው ተጠናክሮ ይቀጥል። የሀብት ስብሰባው ከጥገኝነት ወጥቶ ከፌደራል መንግሥት ሀብቶች መካፈል ይጀምር። መጪው ክረምት ነው። ክረምት በተፈጥሮው ጭለማ ነው። ሠራዊቱም ከቀን ይልቅ በጨለማ ለመዋጋት የሚፈልግ ይመስላል። ስለዚህ በጨለማ ለሚመጣ መከላከያ ሠራዊት መድኃኒቱ የቀን እንቅልፍ በመተኛት ሌሊቱን ቀን ማድረግ እና ሌሎች ወታደራዊ ስልቶችን መጠቀም ነው። የእንቅልፍ ሰዓቱም ተገድቦ በተቆራረጠ መልኩ በፈረቃ ማድረግ እና ለጥቃት ላለማጋለጥ ጥረት መደረግ አለበት። ይሄን ማድረግ  ሁለት ዓይነት ጥቅም አለው።1ኛ፦ ራስን ከጥቃት ታድናለህ፣ ሲቀጥል ወታደሩ ባላሰበው መልኩ በማያዉቀው ቦታ ጥቃት ሲደርስበት ያለ ቁጥጥር ተበታትኖ እንዲጠፋ እና ተበትኖ እንዲቀር በማድረግ  ትጥቁን ለፋኖ አስረክቦ እንዲሸነፍ ያደርገዋል። ስለዚህ ክረምቱን የመጨረሻ አድርጎ መዘጋጀት ያስፈልጋል። "…ነጮቹም የሰሙትን እንጃ ደጋግመው ብልፅግናው ላይ ጓ ማለት አብዝተዋል። አሜሪካም፣ የተባበሩት መንግሥታትም፣ የአውሮጳ ኅብረትም፣ እንደ ካናዳ ያሉ መንግሥታት ሳይቀር በግልፅ ጓ እያሉበት ነው ያለው። ፋኖ በአንድ እጁ እያለማ፣ እያሰለጠነ፣ እያመረተም፣ በሌላኛው እጁ መዋጋቱን ይቀጥል። ድርድር፣ መፈንቅለ መንግሥት ብላ ብላም አይመለከተውም። ኦሮሞዎቹ ፕላን ቢ አድርገው የሚንቀሳቀሱት እሱኑ ነው። የፋኖን ማሸነፍ እነ ጃዋር መሀመድንም፣ እነ ስታሊንንም እኩል እያስጮኸ ነው። ምንአልባት ፋኖ እየገፋ ከመጣ አስቀድመው ሸኔንም አዲስ አበባ በማስገባት አዲስ አበባን በውድመት በማስፈራራት ፋኖን ወደ ድርድር ሊያመጡት ይሞክሩ ይሆናል። ለፋኖ ግን ያለው ምርጫ ሦስት ብቻ ነው። አንደኛው ምርጫ ያው የታወቀ ነው ማሸነፍ ነው። ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ማሸነፍ ነው። ሦስተኛው ምርጫ ግን ሌላ ምርጫ ስለሌለው ማሸነፍ ብቻ ነው። "…አጀንዳዎች እየበዙ ይመጣሉ። ሸዋና አሩሲን እረፍት ለመንሣት በዚያ የሚገኙ ዐማሮች ላይ አዲስ ስደት፣ ሞት፣ መፈናቀል፣ የመሬት መቀማት፣ የከብት፣ የንብረት ዘረፋ፣ የቤት ውድመት፣ እርድና ጭፍጨፋም ይኖራል። ብዙ ታዋቂ ሰዎችን በመግደል ጉዳዩን በፋኖ ላይ ለማላከክ ዝግጅትም ተጀምሯል። ህወሓት ለፍታበት የነበረው የፖለቲካው ቅማንት እና የዐማራ ፋኖ አንድ ላይ መሆን ዐማራውን ሲያበረታ አገዛዙን አላስደሰተም። በጎጃም አገውና ዐማራ፣ ጉምዝና ዐማራ አንድ ላይ መሆናቸውም ያበሳጨው አገዛዙ ያን ጨፍጫፊ የጉምዝ መሪ ዳግም በእርቅ ሰበብ አስገብቶታል። ዐማራና አካባቢውንም ለመበጥበጥ ኩሽ ነን የሚሉ ኃይሎች በገፍ እየታጠቁ አካባቢውን ለማወክ እንቅስቃሴ ይጀምራሉ። የህወሓት ኃይልም አርፎ አይተኛም። እናም ስለዚህ ዐማራው አንድነቱን በማጠንከር፣ ልዩነቱን በማቀራረብ፣ አንድ ሆኖ ወደፊት መሄድ ብቻ ነው። በአዲስ አበባም ሆነ በኦሮሚያ ፋኖም ሳይመጣ እርስ በራሳቸው በቅርቡ ይለይላቸዋል። ይሄ ይመዝገብ። • ድል ለዐማራ ፋኖ…! • ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…! • ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ።
إظهار الكل...
👍 7
መልካም… የሚጠበቀው አመስጋኝ ከአንድ ሺም አልፏል። እግዚአብሔር ይመስገን። ከምሥጋና ቀጥሎ የሚቀርበው ያው የተለመደው ርዕሰ አንቀጻችን ነው። "…የዛሬው ርዕሰ አንቀጻችን ከወደ ጀነራሎቹ አካባቢ በወፎቼ በኩል ትናንት የመጣ ወሬ ነው። ወሬው የሚገባው ለቦለጢቀኞቹ እና ጉዳዩን በቅርበት ለሚያውቁት ብቻ ነው። እኔ ግን ጦማሩ ለታሪክ በገፄ ላይ ይቀመጥ ዘንድ በዚህ መልክ አስፍሬዋለሁ። "…እህሳ ጉበዝ… ርዕሰ አንቀጹን ለማንበብ ዝግጁ ናችሁ…?
إظهار الكل...
👍 2
ርዕሰ አንቀጽ" "…ታስታውሱ እንደሆን ከዛሬ ስድስት ወር በፊት በወርሀ ህዳር ሪፐብሊካን ጋርድ የሚባሉትና የቤተ መንግሥት ዙሪያውን ጥበቃ የሚካሂዱት ወታደሮች አንድም ሳይቀሩ ወደ ደብረዘይት ተወስደው በሥልጠና ሰበብ ግምገማ አካሂደው ነበር። ሥልጠናው የተካሄደው በቢሾፍቱ አየር ኃይል ግቢ ሲሆን ስለ ሥልጠናው ሁኔታ ሪፖርት ያቀረቡት የሥልጠናው አስተባባሪ ኮሎኔል ወንዴ ወልዱ እንደነበሩ ነበር በወቅቱ የተገለፀው። ኮሎኔሉ ሙያዊ የክብር ሰልፍ ዓይነቶች፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ወታደራዊ ስልት በተያዘው ዕቅድ መሰረት እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል ሲል መረጃውን ልኮ በመከላከያ ገጽ ላይ የዘገበው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ቡድን እንደነበር ይታወሳል። "…የሪፐብሊካን ጋርዱን በስብሰባ፣ በውይይት እና በሥልጠና ሰበብ ደብረ ዘይት ከወሰዱት በኋላ በስፍራው ተካሂዶ የነበረው ሥልጠና ሳይሆን ግምገማ ነበር ነው የሚሉት ሁኔታውን በንቃት የሚከታተሉ ኃይላት። እንዲያውም ከብልፅግና ግምገማ በፊት የተደረገው ግምገማ ይሄ ነበር ነው የሚባለው። "ይመቱኛል" ብሎ አብይ በመፍራቱ ነው በወቅቱ ወታደሮቹ እርስ በራሳቸው ተገማግመው ይጥሩ ተብሎ ወደ ደብረዘይት የተወሰዱት። በእጅ ስልኩ ላይ በሚያዳምጠው ዘፈን፣ በስልኩ ላይ ሴቭ ባደረጋቸው ቪድዮዎችና ምስሎች፣ በግሩፕ ውይይት፣ በተናጥል ውይይት ወቅትም ወታደሮቹ ያላቸው አመለካከት ተጠንቶ፣ ተገምግሞ፣ ለተጨማሪ ተሃድሶ የሚፈለጉት ለሌላ ሥልጠና ሲወሰዱ አደገኛ ናቸው ተብለው በግምገማው ወቅት የተጠረጠሩት ደግሞ ከስብሰባው በኋላ ገሚሱ ለግዳጅ ተብሎ ወደ እሳቱ የዐማራ ጦርነት ውስጥ ተማግዶ ሲወገድ ቁጥራቸው ያልተገለፁትን ደግሞ የት እንዳደረሷቸው አይታወቅም። "…ይህን ሁሉ ስጋት የፈጠረው መፈንቅለ መንግሥት ነው። አቢይ መፈንቅለ መንግሥት ይገጥመኛል ብሎ ፈርቷል። በአፍሪካ ምድር እየተደጋገመ የመጣው ዕጣ ለእሱም እንዳይወድቅበት፣ ህወሓትም እግር እየተከለች ስለሆነ ትበላኛለች ብሎም ሰግቷል። ደግሞም ይቀርለት አይመስልም። እንዲያውም ዶር ዳኛቸው "ያቆሰለህን ግደለው፣ አትማረው" እያለ የሚወተውተው የሚመጣው ነገር ስላሰጋው ነው። የወያኔ ሚዲያዎች በሙሉም ዳኛቸው እንዲህ በማለቱ ከዘር ማጥፋት ጋር አያይዘው እየወረዱበት ይገኛሉ። አሁንም ከስድስት ወር በኋላ በትናንትናው ዕለት በወጣው የመከላከያ ዜና ላይ ደግሞ "የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት እያከናወነ ያለውን የዘመናዊ ሠራዊት ግንባታ ሂደት አጠናክሮ ቀጥሎበታል። በዛሬው ዕለትም የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይል ሁሉን አቀፍ ውሰብስብ ግዳጆችን በአንድ ጊዜ መወጣት የሚችሉ የልዩ ኃይል አባላትን አሰመርቋል የሚል ዜና ይዞ ወጥቷል። "…ይሄ ዜና የሚያሳየው የመፈንቅለ መንግሥቱ ሁኔታ አሁንም እንዳለ የሚጠቁም ነው። በትናንቱ ምረቃ ሥነ ሥርዓት በተባለው ዝግጅት ላይ የተገኘቱት ደግሞ የመከላከያ መረጃ በእጁ ላይ ያለው ጄነራል ጌታቸው ጉዲና እና የአቢይ አሕመድ ዘመድ እንደሆነ የሚነገርለት የጅማ ተወላጁ የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል ዋና አዛዥ ሜጄር ጄኔራል አብዱሮ ከድር ናቸው። የትናንቱ ዜና ሲሠራ ምረቃው በአብይ የጥበቃ ኃላፊ እና በመከላከያ ደህንነት ኃላፊ የተደረገ ሲሆን "ልዩ ተልዕኮ" ተብሎ የተገለፀ ነው። ልዩ ተልእኮው ምንድነው? ሌላውን ዝብዘባ ትተን እዚህ ላይ ነው ማስመር። ልዩ ተልዕኮ። አቶ ተመስገን ጥሩነህ ወደ ጠቅላዩ ቢሮ ከመሄዱ በፊት ነው ጌታቸው ጉዲና የደህንነት መሥሪያ ቤቱን ከነ ቢሮዎቹ የወረሰው። ተመስገን ስላልታመነ ነው እንደዚያ የተደረገው። አሁን አዲስ አበባ የምትመራው በመከላከያ ደህንነት ነው። "…መጀመሪያ የቤተ መንግሥቱ ልዩ ጥበቃ የነበረው ጄነራል ብርሃኑ በቀለ ነበር። ብርሃኑ በቀለ ሸዋ ነው። አቢይ ደግሞ ሸዋዎቹን እንደ ስጋት ዓይቶ ጅማና ወለጋን ይዞ መንቀሳቀስ ጀምሯል። ስለዚህ ብርሃኑ በቀለን ከሪፐብሊካን ጋርድ ኃላፊነት አነስቶ በሀገሩ ልጅ ያውም በዘመዱ ተካው። ብርሃኑን ጎንደር ላከው። ከሞትክም፣ ከኖርክም ሥራህ ያውጣህ ብሎ ነው የላከው። ብርሃኑም ከሽመልስ አብዲሳ ጋር ሆኖ የሲሚንቶ ንግዱን ያጣድፋል። የዐማራን ልጃገረዶችን ያለ ምህረት ይገለሙታል። በነገራችን ላይ አብይ የጅማና የወለጋን ኤሊት እያቀናጀ ነው። ወደ ራሱ የሚያቀርበው ጅማን ሲሆን የወለጋውን ደግሞ ሸዋ ነው የመታህ እያለ ቦታ እየሰጠ እርስ በእርስ በጥርጣሬ እንዲተያዩ እያደረገ ነው። አዲስ አበባ ከቀበሌ እስከ ክልል ድረስ በጅማ እና በወለጋ መሙላት ከጀመረ ሰነባበተ። እንዲያውም አሩሲ አላሠራ አለን፣ ጅማ እንዲህ አደረገ፣ ወለጋ ሀገሩን ሞላው ተባብለው መነቻቸፍም ጀምረዋል። "…ከስድስት ወር በፊት የቤተ መንግሥት ጥበቃዎች ደብረዘይት ላይ ሲገመገሙ ገምጋሚ የነበረው የአብይ ጥበቃ ኃላፊ የጅማ ልጅ አብድሮ ከድር አሁንም ከጌታቸው ጉዲና ጋር መኖሩ የጥበቃዎቹ ተልዕኮ ሰፊ እንዳልሆነ ያሳያል። ሰፊ ካልሆነ ሥልጠናው የአቢይን መንግሥት ከመፈንቅለ መንግሥት እንዴት እንጠብቀው ነው የሚመስለው። በነገራችን ላይ ከተወሰኑ ወራት በፊት ብርሃኑ ጁላ የተወሰኑ ጀኔራሎችን ሰብስቦ "የአገር ጉዳይ ከእኛ ከመከላከያ ትክሻ ላይ ወድቋል" ማለቱን እነ አቢይ እንደ መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ነው የወሰዱበት። አሁን አቢይ የመጨረሻ ተስፋ ያለው በጅማዎች እና በወለጋዎች ላይ እንደሆነ ነው ነገሮች የሚጠቁሙት። "…ሌላው በመፈንቅለ መንግሥቱ ህወሓትም ሌላ ስጋት ናት። ወደ ፌደራል መንግሥት ዳግም ተስባ ለመምጣት ያላት ቀሪ አማራጭ መፈንቅለ መንግሥት ነው። መፈንቅለ መንግሥቱ ከተካሄደ ደግሞ መፈንቅለ መንግሥቱን ሊያካሂዱ የሚችሉት ሁለት አካላት ናቸው። ብርሃኑ ጁላና ጌታቸው ጉዲና። የህወሓቱ ጄነራል ታደሰ ወረደ እና ብርሃኑ ጁላ በጣም የቅርብ ወዳጆች ናቸው። ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ ዳግም ስምምነት የተደረገው የኬንያ ናይሮቢ ነበር። በዚያ ውይይት ላይ ብርሃኑና ታደሰ በጦርነት ሚልዮኖችን እንዳስፈጀ ሳይሆን እንደተነፋፈቀ ሰው ነበር ሲተቃቀፉ የነበሩት። እናም  ሁለቱ ለጌታቸው ረዳና ለአብይ አሕመድ እንደ ስጋት ነው የሚታዩት። ታደሰ ወረደ የጊዜያዊ አስተዳደር አካል ሆኖም ከዓድዋው ህወሓት ጋር ነው አሰላለፉ። የብልፅግና አክቲቪስቶች ሁልጊዜ እየኮነኑ ይጽፉበታል። ብርሃኑ ደግሞ ከታደሰ ጋር ወዳጅ ነው። ህወሓት መሰል ነገር ከፈለገ ሊጠቀም የሚችለው የእነ ብርሃኑ ጁላን ጀኔራሎች ነው። "…ሌላው አቢይ በቶሎ እርምጃ የወሰደበት አብርሃ በላይን ነው። አብርሃ በላይ ህወሓት ወደ መሃል መምጣቷ አይቀርም እናም ያኔ ትበቀለኛለች አትለቀኝም የሚል እምነት ነበረው። ስለዚህ በትግሬ ላይ ለደረሰው ውድመት፣ ፍጅት የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቶት ህወሓትን ለመካስ ከእነ ብሬ ጁላ ታደሰ ወረደም ጋር መዋል ማደርም ጀምሮ ነበር። በወልቃይት እና በራያ ላይም እያሳየ የነበረው እልህ ይሄንኑ ለንስሀ መግቢያና ዐማራን እጅ መንሻ አድርጎ በማቅረብ ከትግሬ ወገኑም ጋር ለመቀራረብ ይፈልግ ነበር። ሁኔታው ስላላማረው አቢይ በቶሎ አንስቶ የቆላ ዝንብ ጠባቂ ሚንስትር አድርጎ ከመከላከያ አንሥቶ ወረወረው። በዚህ ላይ ልብ ብለን የእነ ታዬ ደንድአን፣ የእነ ጃዋርን ጉዳይና አጠቃላይ የሸዋውን ኦሮሞ እንቅስቃሴ ካየን አብይ የመፈንቅለ መንግሥት ስጋት ገጥሞታል ማለት ይቻላል። በትግራይ ያለው ሁለት መንግሥት ነው። በብልፅግና የሚደገፈው ጌታቸው ረዳና የእነ ሞንጆሪኖ መንግሥት። በሁለቱ መካከል የአንድነት መስመር የለም። አንደኛው የወያኔ ቡድን እንዲያውም 👇ከታች ይቀጥላል…✍✍✍
إظهار الكل...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
"…ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ" ማር16፥19 • ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ~በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን • አሰሮ ለሰይጣን ~ አግአዞ ለአዳም • ሰላም ~ እምይእዜሰ • ኮነ ~ ፍሥሐ ወሰላም።
إظهار الكل...
👍 3🙏 1🕊 1
Photo unavailableShow in Telegram
"…ድንቄም ጠቅላይ ሚንስትሪት…😂 "…ኧረ ጉድ ነው። …ሸዋ፣ ጅማ፣ ወለጋ…?🤜👊🤛 …አሁንም ከወፎቼ ማብራሪያ እየጠበቅኩ ነው። ለዛሬ ከደረሰ ደረሰ፣ ካልደረሰ ነገ ጠዋት ያገናኘን። "…ምርኮኞች ለቤተሰቦቻቸው መልእክት እያስተላለፉ ነው። ደቡብ እና ኦሮሞዎች በጎንደር እና በጎጃም በሸዋም ምድር ላይ እንደ ቅጠል ረገፉ። • ምንም ማድረግ አይቻልም።
إظهار الكل...
👍 2🤔 1
ወፌ ደግሞ መጣይ…! "…ወፌ ወፊቱ ርግቢቱ ዛረም የጄነራሎቹን መልእክት ነው ይዛ የመጣችው። ቆይ በደንብ ላጣራው፣ በዚያም ላይ ነገርየው ከበድ ስለሚል ማብራሪያም ልጠይቅ። ወይም ደግሞ የበዛውን መልእክት አጠር አድርገው ይስደዱልኝ፣ አልያም እኔው አሳጥሬ ልጻፍ። • ወለጋ የሊጠ ቢፍቱ ዸጋን ጊቤ ኮንኮላቴ… አለ አዝማሪ ማን አብተው… ኢጆሌ ጂማ፣ ኢጆሌ ሸዋ፣ ሸዋ ሊጣ… 😂 • ራሳቸው ካፈጣጠኑት እሰየው። እኔ ግን ማብራሪያ ስለምፈልግ ማብራሪያውን እስካገኝ ድረስ ጄኔራሎችዬ ትንፍሽ ሳልላት ወደ ሌላ ወግ እሸጋገራለሁ። ኦኦ… • መጣሁ…
إظهار الكل...
👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
ዘመዴ ጉድ ስማ ይለኛል… "…አንዱ ወዳጄ እኮ ነው ዘመዴ ጉድ ስማ፣ ያየህ ሰው ሽመልስ አንድ እንግልጣራዊ ጋዜጠኛ አቢይ አሕመድ አሁን በስሙ የሚጠራባቸው አቶ አህመድ አሊ ወላጅ አባቱ አይደለም ብሎ መጽሐፍ ጻፈ፣ አንተ ወሎዬ ነው ስትል እንግሊዛዊው ደግሞ ጉራጌ ነው ብሏልም ይለኛል። 😂 "…እርግጥ ነው አቢይን ድሮ የኢትዮጵያ ኦዲዮቪዥዋል ዋና ጸሐፊ በነበርኩ ጊዜ፣ እሱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚንስትር ሆኖ ሳውቀው የጉራጌ ተክለ ሰውነት ያለው ስለሚመስል እኔም ጉራጌ ይመስለኝ ነበር። ኋላ ነው በሻሻ ድረስ ሰው ልኬ የአቢይ እናቱም፣ አባቱም ወሎዬ እንደሆኑ ተረድቼ በቀደመው ፌስቡኬም፣ በቴሌግራምና በዩቲዩብ፣ እንዲሁም በመረጃ ተለቭዥን ያጋለጥኩት። "…እነያየህ ሰው ሽመልስ የአቢይን የትምህርት ደረጃ፣ ዲግሪውን እንዴት እንዳገኘ፣ ግብጻዊው ፕሮፌሰር፣ የምክክር ኮሚሽኑ ዶር ዮናስ አዳዬ፣ የህወሓት ሰዎች በስም በፎቶ የምጠቅሳቸው እንዴት እንዳ ዶከሩት ይፋ ስላላወጣሁ እሱን የማወጣበትን ቀን እየጠበቁ ነው። እኔ ደግሞ ጊዜ እየጠበቅኩለት ነው። "…በተረፈ የአቢይ አባት ወሎዬ ነው። እናቱም የላስታ ጠዳ ሴት ናቸው። የአቢይ እናትና አሳዳጊ አባቱ አቶ አሕመድ አሊ ተጣልተው፣ ወሮ ትዝታ ወልዴ እዚያው በሻሻ ጠጅ ቤት ከፍተው ሳለ፣ በግድግዳ የሚጎራበቷቸው ወሎዬው አቶ መሀመድ አቶ አህመድ አሊንና ወሮ ትዝታን ለማስታረቅ ብዙ ደክመው ስላልተሳካላቸው፣ ኋላ ላይ ለንብረት ለማካፈል ወደ ጠጅ ቤቷ ይመላለሱ የነበሩት አቶ መሀመድ ዋሴ ከወሮ ትዝታ ወልዴ ጋር በፍቅር ይወድቃሉ። አቶ አህመድ አሊና ወሮ ትዝታ ወልዴ ከተፋቱ በኋላ በ1968 ዓም አቢይ ተወለደ። ለዚህ ነው አቶ አህመድ አሊ አቢይን እንደ ልጆቼ ነው ያሳደግኩት ብለው ቃላቸውን በሰጡ በወሩ የሞቱት። የአቢይ የአባት ልጆች ተደብቀው ነው ያሉት። • መጣሁ…!
إظهار الكل...
👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
"…በሥራ ላይ ሆኜ የጻፍኩትን ርዕሰ አንቀጼን እንዳነበባችሁልኝ ቴሌግራም እየነገረኝ ነው። ይህን ከተናገርኩ በኋላ ካልገጠሙኝ በቀር እስከአሁን ዛሬም እንደትናንቱ በኢሞጂ እንኳ የተናደደ ሰው ፊት አላየሁም። "…ቀጥሎ ደግሞ የእናንተ የአድማጭ፣ የአድፋጭ፣ ተመልካቾቻችን ሓሳብ የሚሰማበት ሰዓት ነው። ተራው የእናንተ ነው። የአንድ የመቶ ያህል ሰዎችን ሓሳብ ከተቀበልን በኋላ ወደ ሌሎች መረጃዎች፣ እና ውይይቶች እናልፋለን። "…አባቴ ቴሌግራምን እንደኔ የተጠቀመባት ማን አለ? ማንአለ አልኩህ? ማኅበራዊ ሚዲያን በጨዋ ደንብ ከተጠቀሙ አይቀር እንደ ዘመዴ አላለም አንዱ ወንድሜ ጓዴ…!😂 ስንቱን ሙጢ፣ ተናጋሪ፣ ለፍላፊ አደረግኩት እኮ። እኔ መሃይም ብሆንም ስንቱን ሊቅ ዘጭ አድርጌ ሥነ ሥርዓትም፣ መረጃም አስያዝኩት አስጨበጥኩት እኮ። አፌን እከፍታለሁ የሚል ሲኖር አጠናግሬ እየለቀቅኩ ልክ አስገባሁት እኮ። በነፃነት… በጨዋም ደንብ ተንፒሱ። ተወያዩ፣ ተመካከሩ፣ ተከራከሩ። • በሉ ተንፒሱ… 1…2…3 ጀምሩ…
إظهار الكل...
🙏 6
Photo unavailableShow in Telegram
"…ዛሬ ሚጢጢዬ የግል ጉዳይ ነበረኝ። እናም በዚያ ምክንያት በጠዋት መነሣት ስለነበረብኝ ማታም በጊዜ ነው የተኛሁት። ዛሬ 9 ቀን እየቀረን የዘመነ ትንሣኤውን ሰላምታ እንኳ ዘንግቼ በዘወትር ሰላምታችን ነው የተከሰትኩት። እሱ ነገ ይስተካከላል። "…ሌላው ርዕሰ አንቀጻችን ነው። ማታ ጀምሬው ሳልፈጽመው ነበር የተኛሁት። የምስጋና ሰላምታችን ይቆያል ብዬ አስቤ የነበረ ቢሆንም ዛሬ በመፍጠኑ ተረጋግቼ እጽፈዋለሁ ብዬ አስቤ የነበረው ሳላስበው ፈጥኖብኝ ወደ እናንተ ለማድረስ ዘገየሁ። የሆነው ሆኖ በውጥረት ውስጥ ሆኜ ሥራዬን፣ ጉዳዬንም ስለፈጸምኩ አሁን የተለመደውን ቃሪያ በሚጥሚጣ የሆነውን ርዕሰ አንቀጼን ልለቅባችሁ ነኝ። • እናንተስ ለማንበብ፣ አንብባችሁም ሓሳባችሁን ለማካፈል ዝግጁ ናችሁ…?
إظهار الكل...
👍 4🕊 1