ru
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Открыть в Telegram
1 739
Подписчики
-124 часа
+17 дней
-730 день
Архив постов
Repost from N/a

photo content

photo content
+1

photo content

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2016 ዓ.ም የስልጠና ዘመን አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ ስማሰልጠን አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቆ ሰልጣኞችን በመጠባበቅ ላይ መሆኑን እየገስፀ የቴክኒክና ሙያ መግቢያ መስፈርትን የምታሟሉ ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ ኮሌጃችን ከታች በተዘረዘሩት የሙያ መስኮች እርሶን ስማሰልጠን በመጠባበቅ ላይ መሆኑን በደስታ እናበስራስን፡፡

photo content
+1

photo content

Repost from N/a
photo content
+6

Repost from N/a
የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ውጤታማነት እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ ተቋማት ቅንጅት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተገለጸ። በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ኢንተርፕራይዞች ፍትሃዊ መንግስታዊ ድጋፎች ተጠቃሚ በማድረግ የኢንተርፕራይዞች ውጤታማነት እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር አድርገዋል። ኮሌጆቹ ድጋፍ በመስጠት በአስተዳደሩ ጉልህ ስራዎችን እየሰሩ ሲሆን በተለይም በ4ቱ የድጋፍ ማእቀፎች የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችንና አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪግ ኢንደስትሪዎችን  የምርትና ምራታማነት በማሻሻልና  ብቁ የሆነ የሰዉ ሐይል በማፍራትና የሥራ እድል እንዲፈጥሩ በማስቻል ድጋፍ እየሰጡ እንደሚገኙ ይታወቃል፤ የሁለቱ ኮሌጆች የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዳይሬክቶሬቶች በጋራ በመሆን  ይህን መድረክ ያዘጋጁ ሲሆን ለባለድርሻ አካላትም የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበር ጽንሰ ሃሳብ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን ከዚህ በፊት የነበሩ ደካማ ጎኖችን በመንቀስ ለቀጣይ የመፍትሔ አማራጮች የ2016 ዓ.ም የጋራ ዕቅድ በማዘጋጀት ከተለመደው አሰራር በተለየ መልኩ ውጤት አምጪ ተግባራት ላይ ትኩረት ይደረጋል፤ የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመድረኩ ተገኝተው  የክትትልና ድጋፍን በማጠናከር፤ ከኢንተርፕራይዝ ልየታ ጀምሮ እስከ ምዘና እና ሀብት ልኬት እንዲሁም ደረጃ ሽግግር ድረስ ያሉት ተግባራት በጥብቅ ቅንጅት መከናወን እንደሚገባቸው ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 4/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋማት መካከል የሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ አቅሞችን በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል የውይይት መድረክ ከባለ ድርሻ ተቋማት ጋር እካሄደ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የጥ/ቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አገልግሎት አቅዶ ከሚሰራባቸው ግቦች መካከል በዘርፉ ላይ የሚታዩ ውስነቶችን በሚያሻሽል መልኩ የጥናትና ምርምርየፈጠራ ስራዎችየቴክኖሎጂ ሽግግር የSTEM እውቀቶች እንዲሁም የማህበረሰብ አገልሎትቶችን የማሳደግ ስራዎች የሚገኙበት ሲሆን እነዚህን ስራዎች ውጤታም ለማድረግ ከባለድርሻ ተቋማት ጋር አጋርነትና ትብብር አስፈላጊ በመሆኑ የተዘጋጅ የውይይት መድረክ ነው:: በዕለቱ በነበረው መድረክ በድሬዳዋ አስተዳደር ከሚገኙ የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተወጣጡ ርዕሰ መምህራንምክትል ርዕሰ መምህራን እንዲሁም የቴክኖሎጂ ክበብ ተጠሪዎች በውይይት መድረኩ የተካፈሉበትም ነበር:: በመድረኩ ለተካፈሉ ባለ ድርሻ ተቋማትም በቴ/ሙ/ት/ስ ስትራቴጂ ላይ ሰፊ ገለጻ በማድረግ በSTEM እና INNOVATION እንዲሁም ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ግንዛቤ በመፍጠር እና የ2016 ረቂቅ ሰነድ ላይ በመወያየት የጋራ ስምምነት ላይ መድረስም ተችሏል፡፡ በመጨረሻም ግንዛቤ ከመፍጠሩ ባሻገር በቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍ ኮሌጁ ውስጥ ያለው አቅምን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ባዩት ነገር መደነቃቸውን እና ከኮሌጁ ጋር በትብብር ለመስራት ይበልጥ ፍላጎት እንዳሳደረባቸው ጨምረው ገልፀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥቅምት 30/2016 ዓ.ም