1 743
Подписчики
+224 часа
+37 дней
-130 день
Архив постов
በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን አረንጓዴና ጽዱ የማድረግ የአንድ ወር ዘመቻ ተጀመረ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
"Clean and Green TVET" በሚል መሪ ቃል ለአንድ ወር የሚቆየው እና ዛሬ የኮሌጁን የተለያዩ አካባቢዎችን በማፅዳት በተጀመረው ዘመቻ ላይ የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ አሰልጣኝ መምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም ሰልጣኝ ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
በመሆኑም ለአንድ ወር በሚቆየው ዘመቻ ላይ ኮሌጁን ውብ፣ ፅዱና በአረንጓዴ ልምላሜ የተላበሰ በማድረግ ለትምህርትና ስልጠና ሂደቱ ምቹ አካባቢ የመፍጠር ዓላማ ያለው መሆኑን የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አስታውቀዋል፡፡
ኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን
ጥር 06/2014 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ለክርስትና እምነት ተከታይ ሰራተኞቹ እንዲሁም ለመላው የእምነቱ ተከታዮች እንኳን ለ2014ዓ.ም የገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል።
#መልካም_በዓል
" TVET DIGITALIZATION & INTERNATIONALIZATION "
======================
▶ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተያዘው የበጀት አመት የተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ጥራትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ለውጥ አምጪ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፤
▶ ከነዚህም ተግባራት አዲስ በጸደቀውና ትኩረት በተሰጠው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ የተቀመጠው TVET DIGITALIZATION & INTERNATIONALIZATION እሳቤ መሠረት ኮሌጁን በአስተዳደሩ አልፎም በሀገሪቱ ካሉ ኮሌጆች ሞዴል ለማድረግ የሚያስችል የመጀመሪያ ምዕራፍ ስራዎች ማጠናቀቅ ተችሏል፤
▶ በዚህም መሰረት ይሄ ስራ ውጤታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ላስቻሉ በኮሌጁ ትምህርትና ስልጠና እየተከታተሉ የሚገኙ የአይ.ሲ.ቲ ዲፓርትመንት ሰልጣኝ ተማሪዎችና አሰልጣኝ መምህራን እንዲሁም በሁሉም ረገድ ለኮሌጁ ድጋፍ ያደረገው የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በተለይም በአይ.ሲ.ቲ ፑል ስር ለሚገኙ ባለሙያዎች የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም ተዘጋጅቷል፤
▶ በዚህ የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም ላይ የድሬዳዋ ቴ/ሙ/ት/ስ ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሳሊም የተገኙ ሲሆን የተሰራውን ስራ ባድነቅና የሰሩትንም አካላት በማመስገን በቀጣይ ይሄን ስራ በማስፋት በአስተዳደሩ የሚገኙ ኮሌጆችን በማስተሳሰር ብክነትን በመቀነስ ቀልጣፋ አሰራርን ሊያመጣ የሚችል ስራ ሊሰራ አንደሚገባ አመላክተዋል፤
▶ በመጨረሻም በሁለተኛው ምዕራፍ የሚከናወኑ ተግባራት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፤ የፕሮግራሙንም ማጠቃለያ የተሰሩትን ስራዎች በመጎብኘት ማድረግ ተችሏል።
የኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 28/2014 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ድህረ ጦርነት ስትራቴጂ" በሚል ርዕስ የተካሄደ ውይይት
=====================================
✍️ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ጨምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር የሰራ ክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች በወቅታዊው የሀገራችን በተለይም ድህረ ጦርነት ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ፤
✍️ በውይይት መድረኩ ላይ የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የተገኙ ሲሆን ጦርነቱን ቀልብሰን ከጣለብን ጠባሳ ባሻገር ያሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ በዋናነት አንድነታችንን በመጠበቅ ሰላምና መረጋጋትን በማስፈን ብልጽግናን የማረጋገጥ መንገዳችንን ለማሳለጥ የሚያስችሉ ሀሳቦች ላይ በማተኮር ተጨባጭ የሆኑ ተግባራትን ማከናወን አስፈላጊ በመሆኑ ይህም መድረክ አስፈላጊነቱ ከዚሁ የሚመነጭ ነው ብለዋል።
✍️ በሌላ በኩል በመድረኩ ተሳታፊ የነበሩ የቢሮውና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞችም አስተያየትና ሀሳባቸውን፤ ጥያቄ የፈጠሩባቸውን እና ስጋት ሊሆኑ ይችላሉ ብለው ያሰቡትን ሁሉ በፍጹም ነጻነት መድረኩን ለሚመሩ አካላት ያቀረቡ ሲሆን ከመድረኩም ምላሽ ለሚያስፈልጋቸው ሀሳቦች ምላሽ በመስጠትና እና ከመረጃ ጉድለት የተነሱ ሀሳቦችን በቂ መረጃ እን ዲያገኙ በማድረግ የተሰጡ ገንቢ አስተያያቶችን መቀበላቸውን የገለጹ ሲሆን፤
✍️ በመጨረሻም የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የመድረኩ ተሳታፊ ሰራተኛች በዋናነት አንድነትችንን ሊከፋፍሉ ከሚችሉ እኩይ እና ጊዜ የሚጠብቁ ጉዳዮችን በጥንቃቄ እንዲመለከትና መተማመንን በመፍጠር ከድል ሽሚያ ወጥተን በጦርነት ያስመዘገብነውን ድል በልማቱ መድገም እንደሚገባ በማሳሰብ መድረኩን አጠቃለዋል።
የኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 25/2014 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ድህረ ጦርነት ስትራቴጂ" በሚል ርዕስ የተካሄደ ውይይት
=====================================
✍️ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ጨምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር የሰራ ክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች በወቅታዊው የሀገራችን በተለይም ድህረ ጦርነት ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ፤
✍️ በውይይት መድረኩ ላይ የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የተገኙ ሲሆን ጦርነቱን ቀልብሰን ከጣለብን ጠባሳ ባሻገር ያሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ በዋናነት አንድነታችንን በመጠበቅ ሰላምና መረጋጋትን በማስፈን ብልጽግናን የማረጋገጥ መንገዳችንን ለማሳለጥ የሚያስችሉ ሀሳቦች ላይ በማተኮር ተጨባጭ የሆኑ ተግባራትን ማከናወን አስፈላጊ በመሆኑ ይህም መድረክ አስፈላጊነቱ ከዚሁ የሚመነጭ ነው ብለዋል።
✍️ በሌላ በኩል በመድረኩ ተሳታፊ የነበሩ የቢሮውና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞችም አስተያየትና ሀሳባቸውን፤ ጥያቄ የፈጠሩባቸውን እና ስጋት ሊሆኑ ይችላሉ ብለው ያሰቡትን ሁሉ በፍጹም ነጻነት መድረኩን ለሚመሩ አካላት ያቀረቡ ሲሆን ከመድረኩም ምላሽ ለሚያስፈልጋቸው ሀሳቦች ምላሽ በመስጠትና እና ከመረጃ ጉድለት የተነሱ ሀሳቦችን በቂ መረጃ እን ዲያገኙ በማድረግ የተሰጡ ገንቢ አስተያያቶችን መቀበላቸውን በመግለጽ የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የመድረኩ ተሳታፊ በዋናነት አንድነትችንን ሊከፋፍሉ ከሚችሉ እኩይ እና ጊዜ የሚጠብቁ ጉዳዮችን በጥንቃቄ እንዲመለከትና መተማመንን በመፍጠር ከድል ሽሚያ ወጥተን በጦርነት ያስመዘገብነውን ድል በልማቱ መድገም እንደሚገባ በማሳሰብ መድረኩን አጠቃለዋል።
የኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 25/2014 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ድህረ ጦርነት ስትራቴጂ" በሚል ርዕስ የተካሄደ ውይይት
=====================================
✍️ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ጨምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች በወቅታዊው የሀገራችን በተለይም ድህረ ጦርነት ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ፤
✍️ በውይይት መድረኩ ላይ የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የተገኙ ሲሆን የጦርነቱን ቀልብሰን ከጣለብን ጠባሳ ባሻገር ያሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ በዋናነት አንድነታችንን በመጠበቅ ሰላምና መረጋጋትን በማስፈን ብልጽግናን የማረጋገጥ መንገዳችንን ለማሳለጥ የሚያስችሉ ሀሳቦች ላይ በማተኮር ተጨባጭ የሆኑ ተግባራትን ማከናወን አስፈላጊ በመሆኑ ይህም መድረክ አስፈላጊነቱ ከዚሁ የሚመነጭ ነው ብለዋል።
✍️ በሌላ በኩል በመድረኩ ተሳታፊ የነበሩ የቢሮውና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞችም አስተያየትና ሀሳባቸውን፤ ጥያቄ የፈጠሩባቸውን እና ስጋት ሊሆኑ ይችላሉ ብለው ያሰቡትን ሁሉ በፍጹም ነጻነት መድረኩን ለሚመሩ አካላት ያቀረቡ ሲሆን ከመድረኩም ምላሽ ለሚያስፈልጋቸው ሀሳቦች ምላሽ በመስጠትና እና ከመረጃ ጉድለት የተነሱ ሀሳቦችን በቂ መረጃ እን ዲያገኙ በማድረግ የተሰጡ ገንቢ አስተያያቶችን መቀበላቸውን በመግለጽ የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የመድረኩ ተሳታፊ በዋናነት አንድነትችንን ሊከፋፍሉ ከሚችሉ እኩይ እና ጊዜ የሚጠብቁ ጉዳዮችን በጥንቃቄ እንዲመለከትና መተማመንን በመፍጠር ከድል ሽሚያ ወጥተን በጦርነት ያስመዘገብነውን ድል በልማቱ መድገም እንደሚገባ በማሳሰብ መድረኩን አጠቃለዋል።
የኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 25/2014 ዓ.ም
ድሬዳዋ
'''''''''''''''''"""""""'''''''''''''''''''''''''""""""'''''''''''''''''"""""""''''''''''''"" በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ የስራ ሂደት ቀደም ሲል በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰ መምህራን በሳይንስ፣በቴክኖሎጂ፣በምንድህስና እና ሂሳብ(STEM) የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቶ ስልጠና መስጠቱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም በአስተዳደሩ የሚገኙት የብስራተ ገብርኤል እና ጀሩሳሌም ት/ቤቶች የተመረጡ ተማሪዎቻቸውን በተቋማችን ይዘው በገኘት አስጎብኝተዋል።
ተማሪዎቹ በጉብኝታቸው የተለያዩ ዲፓርትመንቶችና ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በዲፓርትመንት ተጠሪዎችና በተቋሙ ሀላፊዎችም ስለ ቴክኒክና ሞያ ዘርፍ ሰፋ ያለ ማብራሪ ተሰቷቸው ጉብኝታቸውን አጠናቀዋል።
🇪🇹#ተመራቂዎች_እንኳን_ደስ_አላችሁ🇪🇹🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
________________________________
በኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ካምፓስ የ2014 ዓ.ም የሳተላይት ዲግሪ ፕሮግራም ፅጩ ተመራቂ ተማሪዎችን ታህሳስ 16 2014 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል።
🎓🇪🇹በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ🇪🇹🎓
🇪🇹 Industry Technical Advisory Board 🇪🇹
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
🤝 በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና እና የቴክኖሎጂ ሽግግርና የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ለማሻሻል የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል ከነዚህም ስራዎች ዋናነት ከኢንዱስትሪው ጋር ያለውን ትስስር ማጠናከር ትኩረት ተሰጥቶታል፤
🤝 በመሆኑም ከኢንዱስትሪው ጋር የሚኖረውን ግንኙነት ለማጠናከር እና በቀጣይም ሰፊ ስራዎችን መስራት ያስችል ዘንድ የኢንዱሰትሪ ቴክኒካል አዲቫይዘሪ ቦርድ ተመስርቷል፤ ይህም ቦርድ የተለያዩ አገልግሎት ሰጪና አምራች ኢንዱስትሪዎችን በአባልነት ያቀፈ ሲሆን ከዚህ ቀደም ከኮሌጁ ጋር መልካም የስራ ግንኙነት የነበራቸው ናቸው።
🤝 በዚህም የቦርድ ምስረታ ስነስርዓት ላይ ሁሉም አባላት የተገኙ ሲሆን ስለ ኮሌጁ ተልዕኮ እና አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ በኮሌጁ ዲን እና ም/ዲኖች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፤ በቀጣይም ቦርዱ በትኩረት መስራት በሚገባው ጉዳዮች ላይ አባላት የተለያዩ ሀሳቦችን በማንሳት ውይይት ማድረግ ተችሏል።
ኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 09/2014 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
