ru
Feedback
OFFICIAL DBUECSF CHANNEL

OFFICIAL DBUECSF CHANNEL

Открыть в Telegram

This is Debre-Birhan University Evangelical Christian Students Fellowship Channel Instagram account = https://www.instagram.com/dbuecsf_7?igsh=eHlhMTR4MjQ1emY3 Felo Acc.No. 1000627958998 Mihret kiros & Helen Tigestu

Больше
982
Подписчики
+224 часа
+17 дней
-530 день
Архив постов
#praymobilizers ✨Week 7 ሉቃስ 18 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥ ² እንዲህ ሲል፦ በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም
#praymobilizers ✨Week 7
ሉቃስ 18 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥ ² እንዲህ ሲል፦ በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። ³ በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች፦ ከባላጋራዬ ፍረድልኝ ትለው ነበር። ⁴ አያሌ ቀንም አልወደደም፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ፦ ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር፥ ⁵ ይህች መበለት ስለምታደክመኝ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ እፈርድላታለሁ አለ። ⁶ ጌታም አለ፦ ዓመፀኛው ዳኛ ያለውን ስሙ። ⁷ እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሣቸውም ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? ⁸ እላችኋለሁ፥ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?
🔔 የትኛውም የከበደን ለኛ ግራ ያጋባን, ጎደለን ወይም አጣነው ከምንለው ነገር በላይ እግዚአብሔር ለኛ ለራሳችን(ለሕይወታችን) ነው ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው :: 💫የሚወደን አባታችን ይሰማናል! 💥 ሳንታክት የምንፀልይበትን ፀጋ ይጨምርልን 🤲 #praywithoutceasing #praymobilizers #Dbuecsf

#Counseling ✨Week 7 ሰላምን መጠበቅ – Guard Your Peace ⚡️ የዩኒቨርሲቲ ሕይወት ትምህርት፣ ፈተና፣ ጓደኝነት፣ ግንኙነትና ስለ ወደፊት የሚመጡ ጭንቀቶችን ይዞ ይመጣል። እነዚህ
#Counseling ✨Week 7 ሰላምን መጠበቅ – Guard Your Peace ⚡️ የዩኒቨርሲቲ ሕይወት ትምህርት፣ ፈተና፣ ጓደኝነት፣ ግንኙነትና ስለ ወደፊት የሚመጡ ጭንቀቶችን ይዞ ይመጣል። እነዚህ ሁሉ ውስጣዊ ሰላማችንን እንዳይወስዱብን ልባችንን በእግዚአብሔር ላይ ማስቀመጥ እንማር።
📖 ፊልጵስዩስ 4፥6–7 ⁶ ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ። ⁷ አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።
👉 Guard Your Peace – ሰላምህን ጠብቅ 💥 አንዳንድ ጊዜ የሚያስጨንቀን ችግሩ ብቻ ሳይሆን፣ በአእምሯችን ውስጥ ደጋግመን የምናስበው ነገር ነው። "ምን ይሆናል?" "ቢያልቅስ?" "ባልችልስ?" የሚሉ ሀሳቦች ሰላማችንን ሊወስዱብን ይችላሉ። 💥 ሰላም ማለት ችግር አለመኖር አይደለም። ችግሩ ቢኖርም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንዳለ ማመን ነው። ስለዚህ ሁሉን በራሳችን ለመቆጣጠር ከመሞከር ይልቅ የማንችለውን ለእርሱ እንስጥ።
📖 ኢሳይያስ 26፥3 “በአንተ ላይ ታምናለችና በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ።”
🚨 አእምሮህን ለሚያስጨንቁህ ነገሮች ብቻ አትስጥ። በጸሎት ለእግዚአብሔር አስረክብ፣ ቃሉን አስብ፣ የምትችለውን አድርግ እና የቀረውን በእርሱ ተወው። 💙 በሁኔታ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ላይ ስታምን ሰላም ታገኛለህ!! #openEYEandEAR #Counseling #Dbuecsf

#1min ✨Week 7 👉ዘወትር በመጸለይ _ለሰዎች ልብ መከፈት፦ የምንመሰክርላቸው ሰዎች ልብ እውነትን እንዲቀበል መጸለይ። _ለድፍረትና ጥበብ፦ ወንጌልን በድፍረትና በጥበብ ለመናገር መንፈስ ቅዱስ
#1min ✨Week 7 👉ዘወትር በመጸለይ     _ለሰዎች ልብ መከፈት፦ የምንመሰክርላቸው ሰዎች ልብ እውነትን እንዲቀበል መጸለይ።     _ለድፍረትና ጥበብ፦ ወንጌልን በድፍረትና በጥበብ ለመናገር መንፈስ ቅዱስ እንዲረዳን መጸለይ።   👉  የእግዚአብሔር ቅድስና፦ እግዚአብሔር ፈጣሪና ቅዱስ አምላክ መሆኑን መግለጽ። 👉    የሰው ልጅ ኃጢአተኝነት፦ ሰው ሁሉ ኃጢአት አድርጎ ከእግዚአብሔር ክብር መራቁንና ፍርድ እንደሚገባው ማሳየት።
ሮሜ 3፥23፦ "ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድላቸዋል፤"
👉    የክርስቶስ ማዳን፦ ኢየሱስ የኃጢአት ክፍያ ለመክፈል በመስቀል ላይ መሞቱንና መነሣቱን መመስከር።
ሮሜ 5፥8፦ "ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያሳያል።
"ሮሜ 6፥23፦ "የኃጢአት ደሞዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ የዘላለም ሕይወት ነው።"
👉የንስሐ ጥሪ፦ ሰዎች በክርስቶስ አምነውና ንስሐ ገብተው የዘላለም ሕይወት እንዲያገኙ መጋበዝ።
ሮሜ 10፥9-10፦ "ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሳው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤"
#1min #ለአፋርህዝብእንጸልይ #Dbuecsf

“እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።” — ሮሜ 10፥17 1. እምነት የመንፈሳዊ ሕይወታችን ምግብ ነው ሥጋችን በየቀኑ የቁሳዊ ምግብ እንደሚያስፈልገው ሁሉ፣ መንፈሳዊ
“እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።”   — ሮሜ 10፥17 1. እምነት የመንፈሳዊ ሕይወታችን ምግብ ነው ሥጋችን በየቀኑ የቁሳዊ ምግብ እንደሚያስፈልገው ሁሉ፣ መንፈሳዊ ሕይወታችን እና እምነታችንም በየቀኑ መንፈሳዊ ምግብ ያስፈልገዋል። በጥቅሱ ላይ «እምነት ከመስማት ነው» እንደሚለው፣ እምነታችን አየር ላይ የሚፈጠር ሳይሆን የእግዚአብሔርን ቃል በየቀኑ በመመገብ (ማንበብና በማሰላሰል) የሚገነባና የሚያድግ ነው። 2. «መስማት» በዘመናችን ከንባብ ጋር ያለው ግንኙነት በጥንት ዘመን ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ በግል እጃቸው ላይ ስለማይገኝ በጉባኤ ተሰብስበው የጽሑፉን ቃል «ይሰሙ» ነበር። ዛሬ ግን መጽሐፍ ቅዱስ በእጃችን ወይም በስልካችን ይገኛል። በየዕለቱ መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብ፣ ስናሰላስል ወይም በድምፅ ስንሰማው፣ የእግዚአብሔርን ድምፅ ለሕይወታችን በየቀኑ እየሰማን ነው ማለት ነው። 3. የዓለምን ድምፅ በእግዚአብሔር ቃል መተካት በየቀኑ በሚዲያ፣ በሥራ ቦታ እና በኅብረተሰቡ ውስጥ የምንሰማቸው ዜናዎች፣ ፍርሃቶች፣ ጭንቀቶች እና የዓለም ፍልስፍናዎች እምነታችንን ሊያናጉት ይችላሉ። በየዕለቱ መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብ ግን አእምሮአችን በእግዚአብሔር እውነት ይቃኛል፤ የዓለም ፍርሃት ተወግዶ በእግዚአብሔር ላይ ያለው እምነት እና እፎይታ ይተካል።

#gototheCHURCH 👉እግሮች ሁሉ 🚶‍♀‍➡️🚶‍➡️ ወደ እግዚአብሔር ቤት ⛪ ✨ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ ጸጋን እንከፋፈል!! #Dbuecsf #CHALLENGE #gototheCHURCH
#gototheCHURCH 👉እግሮች ሁሉ 🚶‍♀‍➡️🚶‍➡️ ወደ እግዚአብሔር ቤት ⛪ ✨ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ ጸጋን እንከፋፈል!! #Dbuecsf #CHALLENGE #gototheCHURCH

የረዳን እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን ከመጀመርያችን ጀምሮ እስከመጨረሻው ድረስ አብሮን የነበረ መንፈስ ቅዱስ የተመሰገነ ይሁን። 🥰 ✨️እግዚአብሄር ሆይ እናመሰግንሀለን እንወድሀለን ስለረዳኀን ስላገዝከን እናመሰግንሀለን በኛ በትንንሾች በኛ በደካሞች ነገር ግን በስምህ በተሰባሰብን ልጆችህ መሀል ስለተገኘህልን እናመሰግንሀለን እውነት አንተ ባትረዳን በዚህ ስፍራ መገኘት ስምህን መጥራት አንችልም ጌታ ሆይ ሁሉ ባንተ ሆኖልናል እናመሰግንሀለን ስምህ ይባረክ ደግሞ ሁላችንን በፊትህ እንድትጠብቀን በማያልቀው ምህረትህ ይቅር እንድትለን እንለምንሀልን በዚህ ያገለገሉ የተገኙ ሁሉ እግዚአብሔር ሆይ አንተ ባርካቸው እኔንም ባሪያህን ባርከኝ ይህን ሁሉ በምትወደው በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ፀለይን አሜን!!🙌🙏✨️ የጌታ መልካም ፍቃድ ከሆነና እርሱ ካልመጣ ወይ እኛ ወደርሱ ካልሄድን ፕሮግራማችን ቀጣይ ሳምንት በሰአታችን ይደረጋል ነገ እሁድን በያለንበት አጥቢያ ቤተክርስቲያን እግዚአብሔር እያመለክን ከወንድሞች ጋር ህረት እያደረግን እናሳልፍ ዘንድ እናሳስባችሁአለን ተባረኩልን መልካም አዳር🖐

🎊አሸናፊዎች🎊 🥇Daniel 2nd year other natural science 🥈Meklit 2nd year Computing 🥉Gedion 2nd year Computing ዛሬ ሁለተኛ አመቶች አልተቻሉም ዳኒዬ መኩ ጌዲ ፀጋ ይብዛላችሁ ተባረኩ🙌 በጣም እንወዳችኋለን 🥰

✅️መልስ✅️ 1.ሀ 2.ለ 3.መ 4.? 5.ሀ #SUMMER_ONLINE_PROGRAM #Answer_For_questions #DBUECSF
✅️መልስ✅️ 1.ሀ 2.ለ 3.መ 4.? 5.ሀ #SUMMER_ONLINE_PROGRAM #Answer_For_questions #DBUECSF

⁉️✨️ጥያቄ✨️⁉️ 1.በክርስቶስ ያመንን እኛ የነብሳችን ዋጋ ምን ያህል ነው? ሀ. የክርስቶስን ደም ያህል ለ. ክርስቲያን የመሆናችን መጠን ሐ. የወረስነውን ዘላለም ያህል መ. ሁሉም 2.በእግዚአብሔ
⁉️✨️ጥያቄ✨️⁉️ 1.በክርስቶስ ያመንን እኛ የነብሳችን ዋጋ ምን ያህል ነው? ሀ. የክርስቶስን ደም ያህል ለ. ክርስቲያን የመሆናችን መጠን ሐ. የወረስነውን ዘላለም ያህል መ. ሁሉም 2.በእግዚአብሔር ከፍ ያለ ቦታ ያለን ለምንድነው ሀ. የተገዛንበት ገንዘብ መጠን ብዙ ስለሆነ ለ. የተገዛነው ከዘመናት በፊቲ ከዛም በኃላ ከእርሱ ጋር አብሮት ባለው በከበረው በልጁ ደም ስለሆነ ሐ. የእጁ ፍጥረት ስለሆንን መ. ሁሉም 3.የክርስቶስ ቤዞት በምን ነበር ሀ. ክቡር የሆነው ደሙ ለ. ነብሱን ሐ. ሀ እና ለ መ. ሁሉም 4.አሁን ላይ ነብሳችንን ለማን እያስገዛን ነው?(personal question) ሀ. ለእግዚአብሔር ለ. ለነገሮች ( ለስሜት, ለምኖርበት ህይወት ሐ. ለምወደው ነገር መ. መልስ የለም 5.ይህ ውድ የሆነው የነብሳችን ዋጋ የከፈለው እግዝአብሔር ነው ሀ. እውነት ለ. ሐሰት

በመቀጠል ደግሞ ሁላችንንም አሳታፊ የሚያደርገን ስለሆነ በጉጉት የምንጠብቀው😍 የጥያቄና መልስ ፕሮግራም ይሆናል የሚኖረን ከተማረው የእግዚአብሔር ቃል የወጡ ጥያቄዎች አሉ መልሶቻችሁን በ 15 ደቂቃ ውስጥ በዚህ @hozzy0 የቴለግራም አካወጥ ላኩልን ተባረኩ መልካም እድል 🤗

አላችሁ ቅዱሳን እስኪ አለን በሉኝ⁉️

ጥቤዋ ወንድማለም ፀጋው ይብዛልህ እጅግ በጣም ትወደዳህ ደግሞም ትናፈቃለህ እግዚአብሄር ህይወትህን ዘመንህን ያንተ የሆነውን ሁሉ ይባርክልህ፤ ለዚህ ህብረት ስላለህ የቀና ልብ እግዚአብሔርን እናመሰግነዋለን፤ የልብህን መሻት ሀሳብህን ሁሉ እንደሱ ሀሳብ እና እንደ ቃሉ ፍቃድ ሁሉ አድርጎ ይፈፅምልህ ተባረክልን✨️🙌🖐

ማን ይቤዤን ማን ያድነን ነበር ግን ወገኖቼ ?? እግዚአብሔር ስለእኛ አንድ ልጁን ለነፍሳችን ቤዛ አድርጎ ባይልክልን ከሀጥያት፣ ከህግ ባይቤዤን ቀድሞ ከነበርንበት አለማዊ ህይወት፣ አዳማዊ ማንነት እግዚአብሔር ተቤዥቶ ባያወጣን ማን በራሱ አቅም ታግሎ እና አሸንፎ ይወጣ ነበር?? ብቻ እግዚአብሔር ይመስገን የእኛ የነፍስ ዋጋዋ እጅግ ታላቅ ነው እግዚአብሔርን አንድያ ልጁን አስከፍሎታል 🙏

1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1:18-19 (NASV) •••••••••• ¹⁸ ከቀድሞ አባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከንቱ ከሆነ ሕይወት የተዋጃችሁት በሚጠፋ ነገር፣ በብር ወይም በወርቅ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ፤ ¹⁹ ነገር ግን እናንተ የተዋጃችሁት ነውርና እንከን እንደሌለበት በግ ደም፣ በክርስቶስ ክቡር ደም ነው።

መዝሙረ ዳዊት 49:8-9,15 (NASV) •••••••••• ⁸ የነፍስ ቤዛ ውድ ነውና፤ በቂ ዋጋም ከቶ ሊገኝለት አይችልም፤ ⁹ በዚህም ዘላለም ይኖራል፣ መበስበስንም አያይም። ........... ¹⁵ እግዚአብሔር ግን ነፍሴን ከሲኦል እጅ ይቤዣታል፤ በርግጥም በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት አለኝ። ሴላ

📖✨️WORD OF GOD✨️📖 ጥበቡ ኢሳያስ (የቀድሞ መሪ) 2018 ተመራቂ የነፍሳችሁ ዋጋ ምን ያህል ነው? 📖የነፍስ ቤዛ ውድ ነውና፤ በቂ ዋጋም ከቶ ሊገኝለት አይችልም፤ መዝሙር 49:8📖

በመቀጠል በጣም የምንወደውን እና የከበረውን የእግዝአብሄርን ቃል የምንሰማበት ጊዜ ነው😍 ልባችንን ሁሉ መንፈስ ቅዱስ ያስተምረን ዘንድ ከፍተን ጆሮዎቻችንን ለሚያገለግለን አገልጋይ አስገዝተን በሚመች
በመቀጠል በጣም የምንወደውን እና የከበረውን የእግዝአብሄርን ቃል የምንሰማበት ጊዜ ነው😍 ልባችንን ሁሉ መንፈስ ቅዱስ ያስተምረን ዘንድ ከፍተን ጆሮዎቻችንን ለሚያገለግለን አገልጋይ አስገዝተን በሚመች ሁኔታ ውስጥ ሆነን እንካፈላለን.....🙌

#የመባ_ሰአት ✨መባ እና የፍቅር ስጦታ የምንሰጥበት ጊዜ✨ 🏦Commercial Bank of Ethiopia CBE -- 1000627958998 Mihret kiros & Helen Tigestu Telebir
#የመባ_ሰአት ✨መባ እና የፍቅር ስጦታ የምንሰጥበት ጊዜ✨ 🏦Commercial Bank of Ethiopia CBE -- 1000627958998    Mihret kiros & Helen Tigestu Telebir -- 0900802814 Hossana Anteneh እግዚአብሔር አምላክ ይባርካችሁ🙌 #የመባ_ሰአት #onlineprogram #Dbuecsf

ሁላችን በዚህ ያለን መሪዎች አገልጋዮች ሁሉ ተማሪዎች ነን ለዚህ ህብረት ለእግዚአብሔር መንግስት መስፋት ብቻችንን እናገለግል በገንዘብን እንቆም ዘንድ አንችልም እና ሁላችሁ አጥብቃችሁ ስለዚህ ህብረት እንድትፀልዩ በገንዘባችሁም እንድትቆሙ ልናሳስባችሁ እንወዳለን🥰🙏

በክርስቶስ ኢየሱስ ያመንን የፀደቅን ርስት በሰማይ ያለን ወገኖች ሁሉ አላችሁን ?!