OFFICIAL DBUECSF CHANNEL
前往频道在 Telegram
This is Debre-Birhan University Evangelical Christian Students Fellowship Channel Instagram account = https://www.instagram.com/dbuecsf_7?igsh=eHlhMTR4MjQ1emY3 Felo Acc.No. 1000627958998 Mihret kiros & Helen Tigestu
显示更多987
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-330 天
帖子存档
✨Week 3
ወንጌልን መስበክ ለምን አስፈለገ?
❝በጌታ ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል። ነገር ግን ያላመኑበትን እንዴት ይጠራሉ? ያልሰሙትንስ እንዴት ያምናሉ? የሚሰብክላቸውም ከሌለ እንዴት ይሰማሉ?❞ ሮሜ 10፥13-15📌በጌታ የተወደዳቹ ወንድሞች እና እህቶች ዛሬ ዓለም በብዙ ችግሮች ተሞልታለች። ሰዎች ሰላምን፣ ተስፋን እና የሕይወትን ትርጉም እየፈለጉ ነው። እኛ ግን መልሱን እናውቃለን፤ መልሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ስለዚህ ይህን የሕይወት ወንጌል ማካፈል ኃላፊነታችን ነው። 1⃣. ወንጌልን መስበክ ትእዛዝ ነው። 📖ማቴዎስ 28፥19-20 ኢየሱስ "ሂዱ" ብሎ አዞናል። ይህ ምክር ሳይሆን ትእዛዝ ነው። ስለዚህ እያንዳንዱ አማኝ የወንጌል አገልጋይ ነው። 2⃣. አንድ ነፍስ ታላቅ ዋጋ አላት። 📖ሉቃስ 15 ላይ ኢየሱስ 99 በጎችን ትቶ አንዲቷን የጠፋችውን እንደፈለገ ይናገራል ይህ እግዚአብሔር ለአንድ ሰው ያለውን ፍቅር ያሳያል። 3⃣. ፍርሃትን እናሸንፍ 📖2 ጢሞቴዎስ 1፥7
እግዚአብሔር የፍርሃት መንፈስ አልሰጠንም" ብዙዎቻችን "ምን ይሉኛል?" ብለን እንፈራለን፣እንሸማቀቃለን። ነገር ግን የምንናገረው አማራጭ መንገድ ሳይሆን፣እ/ር ለሰው ዘር ሁሉ ያዘጋጀው ብቸኛው መንገድ ነው፣ለሌሎች ምናካፍለው። 👉ስለዚህ የምንመሰክረው"ወንጌል" የማያሳፍር፣የማያሸማቅቅ እውነት ነው።በምንናገርበትም ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ድፍረትን ይሰጠናል። 4⃣. ውጤቱ የእግዚአብሔር ነው 📖1 ቆሮንቶስ 3
፥6 ❝እኔ ተከልሁ፣ አጵሎስ አጠጣ፤ እግዚአብሔር ግን አሳደገ❞ ይህ ማለት እኛ ታማኝ ሆነን እንመሰክራለን፤ ልብን የሚለውጠው ግን እግዚአብሔር ነው። 5⃣. ዛሬ እንጀምር ለምን ነገን እንጠብቃለን? ዛሬ ለአንድ ጓደኛ፣ ለቤተሰብ አባል ወይም ለሥራ ባልደረባ ስለ ኢየሱስ ልንነግር እንችላለን። ቀላል ምስክርነታችን የአንድን ሰው ሕይወት ሊለውጥ ይችላል። ዛሬ እግዚአብሔር "ማን ይሄዳል?" ብሎ ይጠይቃል። እኛም እንደ ኢሳይያስ፦ "እነሆ እኔ ነኝ፤ ላከኝ!" ብለን እንመልስ😊 የመጨረሻ ጥያቄዎች ሁላችንም እራሳችንን ለማየት ይሁኑ🙂 1,በዚህ ሳምንት ለማን ወንጌልን እናካፍላለን? 2,ለማን እንጸልያለን? 3, ለማን "ኢየሱስ ይወድሃል" እንላለን? 🙏እግዚአብሔር ለመንግሥቱ የሚጠቀምብን ትዉልዶች ያድርገን 🙌 #Dbuecsf #1min
✨Week 3
📖1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9:16 (AMH)
••••••••••
¹⁶ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ!!
#Dbuecsf
#1min
2. ስለ አዳኛችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳውቀናል!
ኢየሱስ ራሱ እንዲህ ብሏል፦
"እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤" (ዮሐንስ 5፥39)
✨ በየቀኑ ስናነብ ኢየሱስን እንድናውቅ ይረዳናል፦
ሀ.የድነት ካርታ 🗺️፦ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኢየሱስ ታሪክና የድነት ሥራ ይናገራል። በየቀኑ ስናነብ፣ ኢየሱስ እንዴት የሕይወታችን ማዕከል እንደሆነ እንረዳለን።
> "ሙሴ በሕግ ነቢያትም ስለ እርሱ የጻፉትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል አለው።" (የዮሐንስ ወንጌል 1፥45)
ለ.ሕያው ግንኙነት 🗣️፦ ቃሉን ስናነብ፣ ከኢየሱስ ጋር እንገናኛለን። የእርሱን ልብ እናውቃለን፣ መንገዱንም እንማራለን።
> "ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው ፤ ሥጋ ምንም አይጠቅምም። እኔ የነገርኋችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወትም ነው።" (የዮሐንስ ወንጌል 6፥63)
ሐ.የነፍስ እረፍት 💖፦ በየቀኑ ኢየሱስን በቃሉ ስናውቀው፣ በጭንቀታችንና በውጥረታችን ውስጥ እውነተኛ ሰላምና እረፍት እናገኛለን።
"ቃልህ ሕያው ያደርገኛልና፣ ይህች በመከራዬ መጽናኛዬ ናት።"(መዝሙረ ዳዊት 119፥50)
🙌 ውድ ቤተሰቦች
በየቀኑ የእግዚአብሔርን ቃል በማንበብ አዳኛችን ኢየሱስን ይበልጥ እንወቅ! 🙏
✨week 3
#ReadyourBIBLE
#Seeking_GOD
#Dbuecsf
@Amh_bible_bot
#gototheCHURCH
👉እግሮች ሁሉ 🚶♀➡️🚶➡️ ወደ እግዚአብሔር ቤት ⛪
✨ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ ጸጋን እንከፋፈል!!
#Dbuecsf
#CHALLENGE
#gototheCHURCH
የህይወት ሁሉ ምንጭ የሆንክ ፣ ከህይወትህ ደግሞ በልጅህ ያካፈልከን ጌታ አምላካችን እግዚአብሔር ዛሬም በዝህ ምሽት የህይወት ቃልህን ስላካፈልከን እንባርክሃን🙌 ህይወት እንዳትደክመን ህያው የሆነ ተስፋ ሰጥተሄናል፣ ይህንም ተስፋ እንድናስብ ደግሞ ዛሬ አስታውሰህ አፅናንተሄናልና እንባርክሃን🙌 ሳምንታችን በዝህ እውነት የምንበረታበት እንድሆን እለምንሃለሁ ፣ የሰሙት ሁሉ ባርካቸው🙌 በክርስቶስ ኢየሱስ ስም አሜን🙏
✨️ጌታ ስሙ ይባረክ የረዳን ጌታ የተባረከ በዝህ የተገኛችሁ ሁሉ የጌታ ፀጋ ይብዛላችሁ 🙌 ነገ እሁድ ነውና ሁላችን በህብረት ከወንድሞች ጋር አብረን እናመልክ ዘንድ እግሮቻችን ወደ ጌታ ቤት እናቀናለን እጅግ ትወደዳላችሁ 🛐✨️
ከእኛ ጋር ደግሞ አጠቃለን ፀልየን እንጨርሳለን 🤲
✅ Answers ✅
1. ለ
2. ሠ
3. ለ
4. “እነሆ፥ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበተ ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥51-52
5. መ
✅ Short Answers ✅
1.“ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ፦ ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥54
2.ክቡር ተስፋ
1ኛ ቆሮንቶስ ምዕ 15:58
❓Questions ❓
1. “የሞት መውጊያ ህግ ነው የህግም ኃይል ሃጢአት ነው፤”
ሀ)እውነት
ለ)ሀሰት
2. “ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና ሀ) የምትደላደሉ
ለ) የማትነቃነቁም
ሐ) የጌታም ፀጋ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።
መ) ሁሉም መልስ ነው
ሠ) ሀ እና ለ
3. ሙታን ትንሳኤ የለም ብለው በማስተማር የሚታወቁት ሰዎች ማን ተብለው ይጠራሉ?
ሀ) ሐዋሪያት
ለ) ሰዱቃውያን
ሐ) ፈሪሳውያን
መ) መልሱ የለም
4. ሐዋሪያው በ1ኛ ቆሮ 15 የሚነግራቸው አንድ ምሥጢር ምንድን ነው?
5. “ሞት ...... በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን....... በኩል ሆኖአልና።”
ሀ) በአዳም.......በክርስቶስ
ለ) በሃጢአት......በፀጋ
ሐ) በሰው.......በኢየሱስ
መ) በሰው......በሰው
❓Short Answer Questions❓
1. ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል የሚፈፀመው መቼ ነው?
2. የዛሬውን የስብከት ርዕስ እና የመፅሃፉን ስም እና ምዕራፍ ጻፍ/ጻፊ?
🙌 እኛ ተስፋ እንደለላቸው አይደለንም ፣ ክቡር ተስፋ አለን፣ የምመጣ አለ ፤ ክብርን ከምድር አንጠብቅም ፣ ከሰማይ እንጅ ፣ 👉ስለዝህ እናርፋለን እንጅ አንሸበርም ፣ እንፀናለን እንጅ አንወላውልም፤ እንተጋለን እንጅ እንታክትም 🙌
እጅግ የምንወድሽ እህታችን በብዙ ተባረክልን ፣ ከዝህ በበለጠ ፀጋ ጌታ ይባርክሽ✋
“ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥58
