ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 548 подписчиков, занимая 8 340 место в категории Технологии и приложения и 2 158 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 548 подписчиков.

Согласно последним данным от 26 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 27, а за последние 24 часа — -7, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 26.05%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.01% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 053 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 491 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 27 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 548
Подписчики
-724 часа
+147 дней
+2730 день
Архив постов
ቁልፍ የሀገር መሠረተ-ልማቶችን ደኅንነትና የህዝብን ጥቅም ለመስጠበቅ እየሠራ መሆኑን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ ........///........ ቁልፍ የሀገር መሠረተ-ልማቶችን ደኅንነት ለማስጠበቅ እና የህዝብን ጥቅም ለማረጋገጥ በትኩረት እየሠራ መሆኑን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ በቁልፍ መሠረተ-ልማቶች በተለይም በኤሌክትሪክ መሠረተልማቶች ላይ የሚደረጉ ዝርፊያዎች፣ ውድመቶችንና አሻጥሮችን በተመለከተ የሠራው ጥናት የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ቀርቦ ውይይት ተደርጓል። በቀረበው ጥናት ፀረ-ሰላም ኃይሎችና በአሸባሪነት የተፈረጀው ሸኔ በመከላከያ ሠራዊቱና በክልል የፀጥታ ኃይሎች የሚደርስባቸውን ምት መቋቋም ሲሳናቸውና ሥልጣንን በኃይል ለመቆጣጠር የነበራቸው ቅዠት ከንቱ መሆኑን ሲያረጋግጡ የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማቶችን በማውደም በህዝብና በመንግስት መካከል መቃቃር እንዲኖር አበክረው እየሠሩ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡  አንዳንድ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞችና ስግብግብ ነጋዴዎችም በመሠረተ-ልማቶቹ ዝርፊያ ላይ እጃቸው እንዳለበት የጠቆመው ጥናቱ፤ በደረሱ ውድመቶችና ስርቆቶች ከ732 ሚሊዮን ብር በላይ የሀገር ሀብት ለኪሳራ መዳረጉ አመልክቷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በመድረኩ ላይ በሰጡት አስተያየት፤ የችግሩን አሳሳቢነት በውል በመገንዘብ የውስጥና የውጭ ጠላቶች የሚጠነስሱትን ሴራ ለማምከን ተናቦና ተቀናጅቶ መንቀሳቀስ ይገባል ብለዋል፡፡ ሀገርን የማፍረስ እኩይ ዓላማ አንግበው በቁልፍ መሠረተልማቶች ላይ ውድመትና ስርቆት በሚፈጽሙ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ መውሰድ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ በሀገር ሀብቶች ላይ የሚደርሱ ውድመቶችንና የሚጎነጎኑ አሻጥሮችን በወቅቱ በመገምገም ተመጣጣኝ እርምጃዎችን ለመውሰድ የሚያስችል ብሔራዊ ግብረ ኃይል ሊቋቋም እንደሚገባም አምባሳደር ሬድዋን አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ በበኩላቸው፤ አገልግሎት መስሪያ ቤቱ በቁልፍ ተቋማትና መሠረተ-ልማቶች ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮች ጉልህ የብሔራዊ ደኅንነት አንድምታ ስላላቸው እንደ ተቋም ከፍተኛ ትኩረት የምንሰጠው ስምሪት ነው ብለዋል፡፡ በዚህም በሀገር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ትርጉም ያላቸው ተቋማትና መሠረተ-ልማቶች በሚያበረክቱት አስተዋፅኦ እና በሚሰጡት አገልግሎት ተመዝነው ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግላቸው ቢሆንም፤ በአሸባሪዎችና ጽንፈኛ ኃይሎች ወሳኝ ዒላማ ተደርገው በመወሰዳቸው ተግዳሮቶች ማጋጠማቸው አንዳልቀረም አስገንዝበዋል፡፡ በመሠረተ ልማቶች ላይ የተደቀኑ ስጋቶችን ለመቀልበስ የሚያስችል የተቀናጀ የመረጃ ስምሪት በማድረግ ስጋትን መለየት፣ ማጥናት እና መረጃዎችን አደራጅቶ በወቅቱ ጥቅም ላይ እንዲውሉ በማድረግ ረገድ የሚከናወነው የተልዕኮ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ሲሳይ አመልክተዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፤ በቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ውድመቶችንና ስርቆቶችን ለመከላከል ክልሎች ኃላፊነት ወስደውና ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር ተቀናጅተው መሥራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በበኩላቸው፤ የኃይል መቆራረጥ በክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ህዝቡን ተጠቃሚ ሊያደርጉ የሚችሉ ፕሮጀክቶችን በትኩረት መሥራትና ህዝቡ መሠረተ- ልማቶችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቅ በማድረግ በኩል በስፋት ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በመድረኩ ላይ እንዳብራሩት፤ በኤሌክትሪክ መሠረተ- ልማቶች ላይ ወንጀሎች እየተፈፀሙና ተግዳሮቶችም እያጋጠሙ በዘርፉ ከፍተኛ ጉዳት ተመዝግቧል፡፡ ችግሮች የተከሰቱባቸው አካባቢዎች የሚገኙ መሠረተ-ልማቶችን በአስቸኳይ ጠግኖ ወደ ስራ ለማስገባት ከፍተኛ  ርብርብ ይደረጋል፡፡ በውይይቱ ላይ የተሳተፉ ሌሎች የፌደራልና የክልል ከፍተኛ ኃላፊዎች እንደገለፁት፤ ቁልፍ መሠረተ-ልማቶችን ለመጠበቅ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የባለድርሻ አካላት ንቁ ተሳትፎ ሊረጋገጥ ይገባል፡፡ መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን ወደታች በማውረድ ውይይት ሊደረግባቸውና እንደየአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ የመፍትሔ አቅጣጫዎች ተቀምጠው ወደ ሥራ ሊገባ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ በወረዳና በቀበሌ ደረጃ የሚገኙ አካላት ቁልፍ መሠረተ-ልማቶችን ለመጠበቅ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ኃላፊነት ወስደው እንዲንቀሳቀሱና ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን እንዲከላከልና ጥቆማ እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በመሠረተ-ልማቶቹ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ከኅብረተሰቡ ጋር በቅርበት ለመስራት ቃል ገብተዋል፡፡ ቁልፍ ተቋማት እና መሠረተ- ልማት ላይ ጉዳት በሚያደርሱ አካላት ላይ ተጠያቂነትን የሚያሰፍን ጠንካራ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት እንዲሁም በእያንዳንዱ ክልል የሚተላለፈውን የኃይል ተሸካሚ አስተማማኝ ጥበቃ የማድረግ ኃላፊነትን በአግባቡ ያልተወጡ የአስተዳደር አካል እና የማህብረሰብ ክፍል ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር መዘርጋት በጥናቱ ከተጠቆሙ መፍትሄዎች መካከል እንደሚገኙበት የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የላከው መረጃ ያመለክታል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 23 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት የስልጤን ሕዝብ የዘመናት ጥያቄ የመለሰ ነው .......//...... የወራቤ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የስልጤ ሕዝብን የዘመናት የኃይል አቅርቦት ጥያቄ የመለሰ መሆኑን የወራቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ገለጹ። ከንቲባው አቶ ያሲን ከሊል እንደገለጹት የስልጤ ሕዝብ ራሱን በራሱ ማስተዳደር ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ባለው የመልማት አቅም ልክ ለመልማት አስተማማኝ የመብራት አቅርቦት እንዲኖረው ሲጠይቅ ቆይቷል። የወራቤ ከተማና አካባቢው እስከ 1999 ዓ.ም ድረስ ከጀነሬተር እንዲሁም ከ1999 ዓ.ም በኋላ ደግሞ ከቡታጅራ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ሲያገኝ መቆየቱን ገልጸዋል። ሆኖም ከከተማው ዕድገትና ከሕዝቡ የመልማት ፍላጎት አንጻር የነበረው የኃይል አቅርቦት በቂ አልነበረም የሚሉት ከንቲባው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይሄን ፍላጎት ከግምት በማስገባት የወራቤ ማከፋፈያ ጣቢያን መገንባቱን ተናግረዋል። ለማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ከተማ አስተዳደሩ ከወሰን ማስከበር ጀምሮ በባለቤትነት ስሜት አስፈላጊውን ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል። እንደ አቶ ያሲን ገለጻ ቀደም ሲል በኃይል አቅርቦት ችግር ምክንያት ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ቦታ ተረክበው ወደ ሥራ ያለመግባትና አካባቢውም በጸጋው ልክ ያለመልማት ችግር ነበር። ከማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ጋር ተያይዞ ግን የኢንቨስትመንት ፍሰቱ መጨመሩንና የንግድና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እያደጉ መምጣታቸውን ጠቁመዋል። ከንቲባው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስልጤ ሕዝብን የዘመናት የኃይል ጥያቄ የመለሰ የማከፋፈያ ጣቢያ በመገንባቱ እና ከቦታው የተነሱ አርሶ አደሮችን በቋሚነት ለማቋቋም ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል። የወራቤ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅና ምክትል ከንቲባ አቶ ሻፊ ሙሲ በበኩላቸው አሁን ላይ ከ215 በላይ ባለሀብቶች ኢንቨስት ለማድረግ ጥያቄ ማቅረባቸውን ተናግረዋል። የከተማ አስተዳደሩ የወራቤ ማከፋፈያ ጣቢያ በመገንባቱ እያደገ የመጣውን የኢንቨስትመንት ጥያቄ ለማስተናገድ ሶጃት የተባለ ከ720 ሄክታር በላይ የኢንዱስትሪ መንደር ከልሎ ለ147 ባለሀብቶች መስጠቱንና እነርሱም በግንባታ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከእነዚህ ውስጥ 30 የሚሆኑት ግንባታቸውን አጠናቀው ወደ ምርት ለመግባት የኃይል አቅርቦት እየተጠባበቁ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የሶጃት መንደርን በክልሉ ዋነኛው የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግና ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ለመሳብ የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት ድርሻው የጎላ መሆኑን አብራርተዋል። የወራቤ ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬተር ወ/ሪት ማህሌት ጌታቸው እንደገለጹት ጣቢያው ስድስት ወጭ መስመሮች ያሉት ሲሆን አሁን ላይ አገልግሎት እየሰጡ ያሉት በሁለት መስመሮች ብቻ ነው። ቀሪ አራት መስመሮች በአካባቢው በመገንባት ላይ ለሚገኙ ፋብሪካዎችም ሆነ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ ናቸው ብለዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

photo content

ለዳታ ማይኒንግ ከቀረበ ኃይል ከ25 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል ……..///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2016 በጀት ዓመት በዳታ ማይኒንግ ሥራ ለተሰማሩ ድርጅቶች ካቀረበው የኤሌክትሪክ ኃይል ከ25 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን በተቋሙ የገበያና ቢዝነስ ልማት መምሪያ ገለፀ። በመምሪያው የሽያጭና ደንበኞች አስተዳደር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ምኒልክ ጌታሁን እንደገለፁት የተቋሙን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳደግ ለሀገር ውስጥ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ኃይል በዶላር መሸጥ ተጀምሯል። ቀደም ሲል ለሀገር ውስጥ ደንበኞች ኤሌክትሪክ በብር ሲሸጥ እንደነበር አስታውሰው ከታህሳስ 2016 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት በዳታ ማይኒንግ ሥራ ላይ የተሰማሩ ዘጠኝ ድርጅቶች የኃይል ሽያጭ ክፍያውን በዶላር እየፈፀሙ እንደሚነኙ አቶ ምኒልክ ተናግረዋል፡፡ ድርጅቶቹ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ መሰማራታቸውንም ጠቁመዋል። በበጀት ዓመቱ በዳታ ማይኒንግ ሥራ ላይ ለተሰማሩ ድርጅቶቹ 882 ነጥብ 48 ሚሊዮን ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማቅረብ 27 ነጥብ 71 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ እንደነበር ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ 796 ነጥብ 28 ሚሊዮን ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ከ25 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ምኒልክ ገለፃ ለድርጅቶቹ የቀረበው የኤሌክትሪክ ኃይል እና የተገኘው ገቢ ከዕቅዱ አንፃር ከ90 በመቶ በላይ ማሳካተረ ተችሏል። ድርጅቶቹ በጠየቁት የኃይል ፍላጎት መሠረት በቂ ኃይል ማቅረብ ባለመቻሉ በዕቅዱና በአፈፃፀሙ መካከል ክፍተት መስተዋሉንም ነው ሥራ አስኪያጁ የገለፁት። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

በበጀት ዓመቱ ኃይል ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኃይል ለማቅረብ የሚያስችሉ ሥራዎች ተከናውነዋል ………///…….. በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የተከናወኑት የፍተሻና ጥገና ስራዎች ያልተቆራረጠ፣ ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ማድረጋቸውን በዘርፉ የዕቅድ አፈፃፀም ክትትልና ትንተና ቢሮ አሰታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ታገል ደገፋ እንዳስታወቁት ዘርፉ የ2016 በጀት ዓመት የኃይል አቅርቦቱ አስተማማኝ እንዲሆን ለማድረግ ተደራሽነቱን ለማስፋፋት በ31 ሺህ 669 ኪሎ ሜትር ርዝመት ባለው የማስተላለፊያ መስመር ላይ ፍተሻ በማከናወን 25 ሺህ 338 ነጥብ 36 ኪሎ ሜትር መስመር ተጠግኗል፡፡ ከዚህም በተጓዳኝ በማከፋፈያ ጣቢያዎች በ9 ሺህ 281 ቤዮች ላይ የፍተሻ ሥራ በማከናወን 8 ሺህ 5 ነጥብ 88 ቤዮችን መጠገናቸውን ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡ ስማርት ሜትር ባልተተከለባቸው የማከፋፈያ ጣቢያዎች የስማርት ሜትር ተከላ መገጠሙንና የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊር ተከላ በራስ አቅም የቅየራ ሥራ መከናወኑን ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ የአቅም ማሻሻያ ሥራዎችን በራስ አቅም ማከናወን መጀመሩና በአነስተኛ ወጭ ማከናወን መቻሉ፣ ቀድሞ በዉጪ ኮንትራክተሮች ይከናወን የነበረዉን የስማርት ሜትር ተከላ ሥራ በራስ ኃይል መከናወኑ የበጀት ዓመቱ ጠናካራ ጎኖች መሆናቸዉን ጠቅሰዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በተያዘው የበጀት ዓመት ከኃይል ሽያጭ 263 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዷል ----///--- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት በዶላር ከሚከናወን የኃይል ሽያጭ 263 ሚሊዮን ዶላር
በተያዘው የበጀት ዓመት ከኃይል ሽያጭ 263 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዷል ----///--- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት በዶላር ከሚከናወን የኃይል ሽያጭ 263 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን በተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ ደመረ አሰፋ እንዳስታወቁት ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ለጎረቤት ሀገራት እና በዳታ ማይኒንግ ለተሰማሩ ኩባንያዎች ከሚያቀርበው የኃይል ሽያጭ 263 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለማግኘት አቅዷል፡፡ በበጀት ዓመቱ ከውጭ ምንዛሪ ለማግኘት የታቀደው በ2016 በጀት ዓመት የተገኘውን ገቢ በእጥፍ አካባቢ ከፍ ያለ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ በሀገሪቱ ወደ ሙሉ ትግበራ የገባው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ የተቋሙን ገቢ ከፍ እንደሚያደርገው ጠቁመው ይህም የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኃይል እየቀረበላቸው ካሉ የውጭ ሀገራት በተጨማሪ በተያዘው በጀት ዓመት ለታንዛኒያ ኃይል ለማቅረብ ዕቅድ መያዙ ሀገሪቱ ለምታገኘው የውጭ ምንዛሪ ዕድገት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተገልጿል፡፡   "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ለሀገር ውስጥ ደንበኞች ቅድሚያ እየተሰጠ ነው .........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2016 በጀት ዓመት ካመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ 84 በመቶ የሚሆነውን ለሀገር ውስጥ ደንበኞች እንዳቀረበ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገለጹ:: ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጅነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት በበጀት ዓመት ጥቅም ላይ ከዋለው የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ 84 በመቶ የሚሆነው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ፣ 9 በመቶ ለውጭ ኤክስፖርት እንዲሁም  ቀሪ 7 መቶው ለተቋሙ የውስጥ አገልግሎት ውሏል። የ2016 በጀት ዓመት የኃይል አጠቃቀም ከ2015 ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ16 በመቶ ዕድገት እንደነበረው ተናግረዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የሀገር ውስጥ ፍጆታ በ17 በመቶ እንዲሁም የውጭ ኤክስፖርት በ6 በመቶ እድገት እንደነበረው ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል። በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላትም ተቋሙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ ፍላጎቱን ለማስተናገድ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በአፋጣኝ ማጠናቀቅ እና ተጨማሪ ፕሮጀክቶችን መጀምር እንደሚጠይቅ አስረድተው ለዚህም የግል አልሚዎችን ያሳተፈ ሥራ ማከናወን እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል፡፡ እንደ ኢንጅነር አሸብር ገለፃ እያደገ የመጣውን የሀገር ውስጥ ደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል። ለጎረቤት ሀገራት ኤክስፖርት እየተደረገ ያለውም ከሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚተርፈውን ኃይል እንደሆነም ጠቅሰዋል፡፡ በቀጣይም ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ኢንዱስትሪዎችንና በሀገሪቱ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ታሳቢ በማድረግ የደንበኞቹን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ በራስ አቅም ባከናወነው የስዊችጊር ቅየራ ከ2 ሚሊዮን ዶላር በላይ ማዳን ችሏል ………///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ15 እና በ 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊር ቅየራ በራስ አቅም በማከናወኑ ከ2 ሚሊዮን ዶላር በላይ ማዳኑን በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የዕቅድ አፈፃፀም ክትትልና ትንተና ቢሮ አሰታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ታገል ደገፉ እንዳስታወቁት ዘርፉ በ2016 በጀት ዓመት በ22 ማከፋፈያ ጣቢያዎች የ15 እና የ33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊር ቅየራ በራስ አቅም አከናውኗል፡፡ በጣቢያዎቹ የስዊችጊር ቅየራ ለማከናወን 2 ሚሊዮን 463 ሺህ ዶላር ግምታዊ ሥራ ለመሥራት የታቀደ ቢሆንም በዘርፉ በራስ አቅም በ12 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር መስራት በመቻሉ 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ወጪ ማዳን መቻሉን አስረድተዋል፡፡ በ2016 በጀት ዓመት ከተጠናቀቁት የስዊችጊር ቅየራዎች በተጨማሪ የ11 ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሥዊች ጊር ቅየራ ሥራ በስራ ሂደት መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ …..//….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ26 ነጥብ 46 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ በተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት ገቢው የተሰበሰበው ከኃይል ሽያጭ፣ ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ እና ከባለፈው ዓመት ከዞረ የኃይል ሽያጭ እንዲሁም ከልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች ነው፡፡ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ 27 ነጥብ 46 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ ከ26 ነጥብ 43 ቢሊዮን ብር በላይ በመሰብሰብ የዕቅዱን 96 በመቶ ማሳካት ችሏል፡፡ ገቢው የተገኘው ለሀገር ውስጥ ከቀረበ የኃይል ሽያጭና ከኦፕቲካል ፋይበር ኪራይ 19 ነጥብ 59 ቢሊዮን ብር፣ ለውጭ ሀገር ከቀረበ የኃይል ሽያጭ 5 ነጥብ 88 ቢሊዮን ብር፣ ለዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ከቀረበ ኃይል 945 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር እና ቀሪው ከተለያዩ የገቢ ምንጮች መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት የሰበሰበው ገቢ ካለፈው ተመሳሳይ በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ 19 ነጥብ 8 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን በማጠናከር፣ ወቅቱን የጠበቀ ክትትል በማድረግ እና የኃይል ሽያጩን ከሚያከናውነው የማርኬቲንግ ክፍል እንዲሁም ከደንበኞች ጋር ተቀናጅቶና ተናቦ በመሰራቱ በገቢ አሰባሰብ የተሻለ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል፡፡ ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመደበኛ ወጪዎች እንኳ ከራሱ ገቢ ሰብስቦ መሸፈን አይችልም ነበር ያሉት አቶ ደመረ አሁን ላይ ግን የገቢ አሰባሰቡን በማዘመንና በማጠናከር መደበኛ ወጪውን ሸፍኖ በራሱ ገቢ የካፒታል ፕሮጀክቶቹን ለመሸፈን ጥረት እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ በቀጣይ የተቋሙን የገቢ አማራጮችን በማስፋትና ወጪ በመቀነስ ብሎም ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጎልበት የገቢ አሰባሰቡን ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ አቶ ደመረ አብራርተዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋማችን ዛሬ በመላው ሀገሪቱ የሲስተም ማሻሻያ ሥራ ሲያከናውን በአንዳንድ አካባቢዎች ለተወሰኑ ደቂቃዎች የኃይል መቋረጥ አጋጥሞ ነበር። የማሻሻያ ሥራው ነገ እሁድ የማይከናወን መሆኑን ከወዲሁ እየገለፅን ሥራው በሚሰራባቸው ዕለታት አስቀድመን የምናሳውቃችሁ ይሆናል። የማሻሻያ ሥራው እስኪጠናቀቅ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን ጥሪያችንን እናቀርባለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 18 ቀን 2016 ዓ.ም

የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲው የግል ባለሀብቱ በኃይል ልማት ዘርፉ እንዲሳተፍ በር ይከፍታል .......///......... በኢትዮጵያ በቅርቡ ወደ ሙሉ ትግበራ የገባው  የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ የግል አልሚዎች በኃይል ልማት ዘርፍ እንዲሳተፉ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ሥራ አስፈፃሚው አቶ ውድነህ የማነ እንዳስታወቁት በሀገሪቱ የነበሩ የህግ ማዕቀፎች፣ የውጭ ምንዛሪ  ችግሮች እና ሌሎች አሰራሮች የግል አልሚዎች በዘርፉ እንዳይሳተፉ ማነቆ ሆኖ ቆይቷል። ባለፉት አምስት ዓመታት የግል ባለሃብቱ በኃይል ልማት እንዲሳተፍ የሚጋብዝ የህግ ማዕቀፍ ቢዘጋጅም አልሚዎችን የሚያበረታታ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ባለመኖሩ ወደተግባር ሳይገባ እንደቆየ አቶ ውድነህ አስረድተዋል። አሁን በሀገሪቱ ተግባራዊ የተደረገው  የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች በዘርፉ ላይ እንዲሳተፉ የሚያበረታታ እንደሆነ አቶ ውድነህ አመልክተዋል። የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲው በሀገሪቱ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት የሀገር ውስጥ የኃይል አቅርቦት ጥያቄን ለመመለስ እና የኃይል  ኤክስፖርት ተደራሽነትን ለማስፋት ከፍተኛ ድርሻ እንደሚኖረው  አስገንዝበዋል፡፡ ኃይል ማመንጨት ብቻውን ግብ አለመሆኑን የጠቆሙት አቶ ውድነህ ስኬታማ ሊሆን የሚችለው የልማት ሥራዎችን መደገፍ ሲችልና በሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ እና የኢንዱስትሪ ልማቶችን ሲያሳድግ ነው ብለዋል። በግሉ ዘርፍ ሊለሙ የሚችሉ የኃይል መሠረተ ልማቶች ተለይተው የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የጠቆሙት ሥራ አስፈፃሚው በቅርቡ በግል አልሚ እንዲለማ የተፈረመው የአይሻ አንድ የነፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በማሳያነት አንስተዋል። በቀጣይም የግል ባለሃብቶች መሠረተ ልማቱን ሊደግፉ የሚችሉባቸው ዘርፎች እየተለዩ ተግባራዊ እንደሚደረጉ አመልክተዋል። የግል ባለሃብቱም የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በኃይል መሠረተ ልማቱ ላይ ኢንቨስት በማድረግ የሀገር ኢኮኖሚን መደገፍ እንደሚጠበቅበት አቶ ውድነህ ጥሪ አቅርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 18 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሳይት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተከናወነ .........///...... የኮይሻ ውሃ ሀይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሳይት የሚገኙ ሠራተኞች በአንድ ጀምበር 6 መቶ ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ሀገራዊ መርሃ ግብር መሰረት ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አሳርፈዋል። ፕሮጀክቱ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች ላይ በርካታ ችግኞችን በመትከል እና በመንከባከብ ተሳትፎ አድርጓል። በዛሬው ዕለትም  የተለያዩ ሀገር በቀል እና ለምብነት የሚውሉ ፍራፍሬ ዛፎች ተተክለዋል። የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር አባይነት ጌትነት እንደገለፁት በዛሬው ዕለት  ችግኝ የተተከለበት ቦታ ለፕሮጀከቱ ግንባታ በግብዓትነት የሚውል ድንጋይ ለማግኘት የተቆፈረ ቦታ እንደነበር በማመላከት  ዛሬ የተተከሉት ችግኞች ቦታው መልሶ እንዲያገግም እና ቀደም ሲል ወደ ነበረበት ተፈጥሯዊ ይዞታ እንዲመለስ የሚያስችል ነው ብለዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞችን ጨምሮ የሥራ ተቋራጩ እና አማካሪ ድርጅቱ ሠራተኞች ተሳትፈዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 17 ቀን 2016 ዓ.ም