ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 548 подписчиков, занимая 8 340 место в категории Технологии и приложения и 2 158 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 548 подписчиков.

Согласно последним данным от 26 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 27, а за последние 24 часа — -7, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 26.05%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.01% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 053 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 491 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 27 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 548
Подписчики
-724 часа
+147 дней
+2730 день
Архив постов
photo content
+5

የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በአንድ ጀምበር 6 መቶ ሚሊየን ችግኞች ተከላ ላይ ተሳተፉ …..….///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት በአንድ ጀምበር 6 መቶ ሚሊየን ችግኞች ተከላ ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተሳትፈዋል:: በመርሃ ግብሩ ላይ የተለያየ ዝርያ ያላቸው ከ1 ሺህ 700 በላይ ችግኞች መተከላቸውን በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ ተናግረዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ በተቋሙ የተካሔደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እንደ ሀገር በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተጀመረው ንቅናቄ አካል ነው፡፡ ከተተከሉት ችግኞች መካከል ከ70 በመቶ በላይ የሚሆኑት ለምግብነት የሚውሉ መሆናቸውንም ነው አቶ ሙላት የገለፁት፡፡ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ የተቋሙ ሥራ አመራር ከፍተኛ ትኩረት የሰጠው መሆኑን የጠቆሙት የጽ/ቤት ኃላፊው ከ700 በላይ የዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞች የተሳተፉበት እንደሆነም አብራርተዋል፡፡ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በመጠቀም አረንጓዴ እና ጽዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር በሁሉም የኃይል ማመንጫዎች፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና በሪጅን ቢሮዎች የችግኝ ተከላ እየተከናወነ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል፡፡ አረንጓዴ አሻራን ማኖር ለቀጣይ ትውልድ ትልቅ ትሩፋት መሆኑን የገለፁት አቶ ሙላት የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ንቅናቄው ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ችግኞችን በመትከል አሻራቸውን በማኖራቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በተመሳሳይ ዜና የሠመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሠራተኞችና የሪጅኑ የሥራ መሪዎች በማከፋፈያ ጣቢያው ጊቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ አከናውነዋል፡፡ በችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ ላይ የተሳተፉት የሰሜን ምስራቅ ሪጅን 2 ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀሰን መሀመድ እንደተናገሩት ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ባለው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ላይ በስፋት እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራሙ በሪጅኑ በሚገኙት በድቼቶና አፍዴራ ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካሄዱንም ነው የተናገሩት፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጅ ገለፃ አካባቢዉ በረሀማ በመሆኑ የሚተከሉት ችግኞች በማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ሙቀት ለመካለከል ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የተሳተፉት የሠመራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አህመድ በበኩላቸው ችግኞቹን መትከል ብቻ ሳይሆን ለፍሬ እስኪበቁ ድረስ መንከባከብም እንደሚገባ አሳስበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

photo content
+9

photo content
+9

photo content

የፕሮጀክቱ ሠራተኞች በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በድንገተኛ የናዳ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ ……..///………. የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በድንገተኛ የናዳ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች ግማሽ ሚሊየን የሚጠጋ ብር ድጋፍ አድርገዋል። የፕሮጀክቱ የሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ ተስፋዬ ጥላሁን ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት በደረሰው ድንገተኛ የተፈጥሮ አደጋ በፕሮጅቱና በሠራተኞች ሥም ማዘናቸውን ገልፀዋል፡፡ ፕሮጀክቱ አደጋው በተከሰተ ማግስት ለነፍስ አድን ሥራ የሚያግዝ ከ5 መቶ ሺህ ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን አስታውሰዋል፡፡ አደጋ የደረሰባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች መልሶ ለማቋቋም የተጀመረውን ጥረት ለማገዝም የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ገንዘብ በማሰብሰብ የ 457 ሺህ 960 ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ድጋፉን የተረከቡት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ሥራውን ከጀመረ ጊዜ አንስቶ ለአከባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ በዞኑ አደጋው ከተከሰተ ጀምሮ ለነፍስ አድን ሥራ የመንገድ ጥገና ከማድረግ ጀምሮ ላደረገው በገንዘብ የማይተመን ድጋፍ በዞኑ ህዝብ ሥም ምስጋና አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ ውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራቱ ተሾመ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ከዚህ ቀደም የህዝብ ተሳትፎ በሚፈልጉ የተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ተሳታፊ እንደነበሩ አስታውሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በፕሮጀክቱ አቅራቢያ በሚገኘው ገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰው የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ሠራተኞቹ ያደረጉት ድጋፍ ከማህበረሰቡ ጋር በቅርበት መሆናቸውን ያሳያል ብለዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

ለታንዛኒያ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል ሥራ ተጠናቋል ........///......... ኢትዮጵያ  በመጪው መስከረም ወደ ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት ማድረግ የሚያስችል ቴክኒካዊ ሥራዎች መጠናቀቃቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አስታወቁ፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የተቋሙን ገቢ ለማሳደግ በሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ እየተከናወኑ ካሉ ሥራዎች በተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ተቋሙ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት የመሆን ራዕይ በመያዝ ኃይል እያቀረበላቸው ካሉ ሀገራት በተጨማሪ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ትስስር ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ከታንዛኒያ ጋር ትስስር ለመፍጠር በተቋማቱ ደረጃ የሚከናወኑ ቴክኒካል ሥራዎች እንደተጠናቀቁ ጠቅሰው  ከኬኒያ - ታንዛኒያ  ያለው የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ፍተሻ በዓመቱ መጨረሻ ሊከናወን እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል። በኢትዮጵያ በኩልም ሽያጩ ከዚህ በፊት በተገነባው የኢትዮ -ኬንያ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እንደሚከናወን ኢንጂነር አሸብር ገልፀዋል፡፡                                                           ለታንዛኒያ በቀጣዩ መስከረም ወር አጋማሽ የኃይል ሽያጭ ሙከራ ሊጀመር እንደሚችል ጠቁመዋል። በቀጣይ ከደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊ ላንድና ሱማሊያ ጋር  ትስስር ለመፍጠር መታቀዱንና ሀገራቱም  የኃይል ግዢ ፍላጎት ማሳየታቸውን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ተቋሙ ለሱዳን ያቀርብ የነበረውን 200 ሜጋ ዋት መቀነሱን ኢንጂነር አሸብር ገልፀዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የሱዳን ሲስተም በሙሉ አቅሙ የሚቀርብለትን ኃይል መቀበል ስለማይችል የኃይል አቅርቦቱ ተቀንሶ ከ20 እስከ 30 ሜጋ ዋት ብቻ እየቀረበ ይገኛል። ኢትዮጵያ ለሱዳን ስታቀርብ የነበረውን የኃይል መጠን በመቀነሷ በተቋሙ ገቢ ላይ ምንም ዓይነት ስጋት እንደማይፈጥርና የሚመነጨውን ኃይል ለመጠቀም አዳዲስ የገቢ ምንጮች ታሳቢ እየተደረጉ እንደሚገኙ ኢንጅነር አሸብር አንስተዋል፡፡ የዳታ ማይኒንግ የኃይል አቅርቦት፣ ከታንዛንያ ጋር ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ ያለውን ሥራ እና ከኬንያ ጋር የተደረገው ተጨማሪ የኃይል ትስስርንም በምሳሌነት ጠቅሰዋል፡፡ እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለፃ በሱዳን ያለው ችግር እስኪፈታ ድረስ በአሁኑ ወቅት እየቀረበ ባለው አግባብ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ታዳሽ ኃይል በማቅረብ በቀጠናው የአረንጓዴ ትስስርን ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራች ስለመሆኗ ኢንጂነር አሸብር ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

ከሃገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ጋር የተጣጣመ የኃይል አቅርቦት ሪፎርም እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ .........///........ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን የ2016 አፈፃፀም እና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ገምግሟል። የተቋሙን የ2016 በጀት ዓመት አፈፃፀም ያቀረቡት አቶ አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ከ7ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የማመንጨት አቅም ያላቸው የአምስት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው። ተቋሙ በበጀት ዓመቱ 20 ሺህ 522 ጊጋ ዋት ሰዓት ማመንጨት የቻለ ሲሆን የዕቅዱን 97 ነጥብ 8 በመቶ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል። ከሰው ኃይል አቅም ግንባታ አንፃር ከ2 ሺህ ለሚልቁ የተቋሙ ሠራተኞች ሙያዊ እና የአመራር ክህሎት ስልጠና መሰጠቱንም ነው ያስታወቁት። በበጀት ዓመቱ ከሀገር ውስጥ እና ከኃይል ኤክስፖርት ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ በማግኘት የዕቅዱን 97 በመቶ ማሳካት ተችሏል ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው የተቋሙ የ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ አፈፃፀም 90 ነጥብ 23 በመቶ መሆኑን ተናግረዋል። በግምገማው ላይ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስትር ዲኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው ሀገሪቱ ከምትፈልገው የኃይል ፍላጎት ጋር የተጣጣመ የኃይል ዘርፍ ሪፎርም ማከናወን ይገባል ብለዋል። ተቋሙ ከኃይል ሽያጭ፣ ገቢን ከማሳደግ እና ከጎረቤት ሀገራት ጋር የኃይል ትስስር ከመፍጠር አንፃር አበረታች ሥራዎች ያከናወነ መሆኑን ሚኒስትር ዲኤታዋ ገልፀዋል:: ተቋሙ ሊያጋጥሙት የሚችሉ ስጋቶችን ቀድሞ በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫ ማስቀመጥ እንደሚገባው የተናገሩት ደግሞ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃ/ሚካኤል ናቸው፡፡ የኃይል መሠረተ ልማት ስርቆትን ከመሰረቱ እልባት ለመስጠት ከክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ጋር ዘላቂ ግንኙነት በመፍጠር በቅንጅት መስራት እንደሚገባም ነው አቶ ሀብታሙ ያስታወቁት፡፡ ከተጠናቀቀው የበጀት ዓመት አፈፃፀም በተጨማሪ የተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት የፊስካል እና የበጀት ዕቅድ ቀርቦ አስተያየት እና ግብአት ተሰጥቶበታል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመትከል 1 ቀን ብቻ ቀረው። ነሀሴ 17❗️ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች
በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመትከል 1 ቀን ብቻ ቀረው። ነሀሴ 17❗️ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በተፈፀመ ስርቆት ተቋሙ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ ደርሶበታል ስርቆትን ለመከላከል ሚዲያዎች ግንዛቤ ፈጠራ ላይ በትኩረት እንዲሰሩም ጥሪ ቀርቧል --------///----- በ2016 የበጀት ዓመት በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ  ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ስርቆት ተቋሙ 817 ሚሊዮን ብር ኪሳራ እንደደረሰበት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጅነር አሸብር ባልቻ የ2016 በጀት ዓመት አፈፃፀምን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት በሁሉም ክልሎች በሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ስርቆት በከፍተኛ ሁኔታ እየተፈፀመ ይገኛል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለያዩ ምክንያቶች ከወደቁ 74 የመስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች 57ቱ በስርቆት ምክንያት እንደወደቁ ጠቁመው እነዚህን መልሶ ለመጠገን ተቋሙ 114 ሚሊዮን ብር ወጭ እንዳደረገም አስረድተዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ስርቆት ተቋሙ በአጠቃላይ የ817 ሚሊዮን ብር ኪሳራ ደርሶበታል። በታወሮች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ተቋሙ በጥገና ሥራ ላይ እንዲጠመድ እያደረገው መምጣቱን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጠቅሰዋል። ይህም የኃይል  ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተከናወነ ባለው ሥራ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ  ኢንጂነር አሸብር ተናግረዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው  እንዳሉት በመሠረተ ልማቱ ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶች ተቋሙን ለኪሳራ ከመዳረጋቸውም ባለፈ የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማስተጓጎል ለህብረተሰቡ አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል እንዳይቀርብ እያደረገ ይገኛል። ከዚህም ሌላ በግንባታ ላይ ባሉ መስመሮች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው መርሃ ግብር ተጠናቀው ወደ አገልግሎት እንዳይገቡ እያደረጋቸው ስለመሆኑም ገልፀዋል። ስርቆትን ለመከላከል የተለያዩ ሥራዎች ቢከናወኑም መስመሮቹ የሚያልፉበት መልከዓ ምድር አስቸጋሪ በመሆኑ ውጤት ማምጣት አልተቻለም ብለዋል። ስርቆትን ለመከላከል መስመሮቹ በሚያልፉበት አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ሚና ከፍተኛ እንደሆነ እና ይህን በመገንዘብ እያንዳንዱ ቀበሌ በአካባቢው ያሉ መሠረተ ልማቶችን በኃላፊነት እንዲጠብቅ የሚያደርግ አሰራር ለመዘርጋት ዝግጅት እየተደረገ ስለመሆኑም ኢንጂነር አሸብር አመልክተዋል ። ፕሮጀክቶቹ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩና ተጨማሪ ፕሮጀክቶችን በመገንባት የኤሌክትሪክ ኃይልን በመላ ሀገሪቱ ለማዳረስ ሁሉም ህብረተሰብ በአካባቢው ለሚገኙ የኃይል መሠረተ ልማቶች ጥበቃ ማድረግ እንዳለበት ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል። መገናኛ ብዙኃንም መሰረተ ልማቱ ለሀገር ስለሚኖረው ፋይዳ እና ስርቆቱ በሀገር ኢኮኖሚና በህብረተሰቡ ላይ እያሳደረ ስላለው ተፅዕኖ ግንዛቤ በመፍጠር ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቀርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

600 ሚሊየን ችግኞች በአንድ ጀንበር! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በብር 20 ቢሊዮን እና በደላር ደግሞ140 ሚሊዮን ገቢ ተገኝቷል ..........///.......... በ2016 በጀት ዓመት ከተለያዩ የገቢ ምንጮች በብር 20 ቢሊዮን እና በዶላር ደግሞ 140 ሚሊዮን ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተቋሙን የ2016 በጀት ዓመት የፕሮጀክት፣ የኦፕሬሽን እና የገቢ አፈፃፀምን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው በመግለጫው እንዳመለከቱት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴን ግድብን ጨምሮ 7 ሺህ 242 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አምስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በግንባታ ላይ ይገኛሉ ። በግንባታ ላይ ካሉት ፕሮጀክቶች መካከል የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በተወሰኑ ዩኒቶቻቸው ኃይል ማመንጨት መጀመራቸውንም  ጠቁመዋል። ከማመንጫ ጣቢያዎች በተጨማሪ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ በበጀት ዓመቱ የኃይል ማመንጫዎች የግንባታ አፈፃፀም ከ76 በመቶ በላይ እንዲሁም የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች አፈፃፀም በአማካኝ 86 በመቶ ማከናወን ተችሏል። በ2016 በጀት ዓመት 20 ሺህ 974 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ  20 ሺህ 522 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማመንጨት የዕቅዱን 98 በመቶ ማሳካት እንደተቻለም ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥ 96 በመቶ ከውሃ፣ 3 ነጥብ 3 በመቶ ከንፋስ እንዲሁም 0 ነጥብ 2 በመቶው ደረቅ ቆሻሻ በማቃጠል የመነጨ መሆኑን ገልፀዋል። በበጀት ዓመቱ ከመነጨው ኃይል ጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የ34 በመቶ፣ ህዳሴ የ17 በመቶ  እንዲሁም በለስ የ 9 ነጥብ 6 በመቶ ድርሻ እንደነበራቸውም በመግለጫው ጠቁመዋል። የተቋሙ ኃይል የማመንጨት አቅም ባለፉት ስድስት ዓመታት በአማካኝ በስምንት በመቶ እየጨመረ ስለመሆኑም ተነስቷል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንዳሉት ተቋሙ በአሁኑ ወቅት ከሀገር ውስጥና ከውጭ የኃይል ሽያጭ፣ ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ፣ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በማስወገድ እና ለሦስተኛ ወገን የማማከርና የግንባታ ሥራዎን በማከናወን ገቢ እያገኘ ይገኛል። በዚህም በበጀት ዓመቱ ለሀገር ውስጥ በብር ከተሸጠ ኃይልና ከሌሎች አገልግሎቶች 19 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅድ 20 ቢሊዮን ብር  የተገኘ ሲሆን ለውጭ ሀገራት ኤክስፖርት ከተደረገ ኃይል እና ከዳታ ማይኒንግ የኃይል አቅርቦት ደግሞ 140 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኝቷል ብለዋል። ይሁንና ለሱዳን እና ለጅቡቲ የቀረበው ኃይል በመቀነሱ ምክንያት ከኃይል ኤክስፖርት የተገኘው ገቢ አፈፃፀም ከዕቅዱ የ23 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን ነው ያስታወቁት። ኢንጂነር አሸብር በመግለጫቸው እንዳነሱት ተቋሙ በበጀት ዓመቱ  በሀገር ውስጥ በዳታ ማይኒንግ ሥራ ላይ ለተሰማሩ ድርጅቶች ካቀረበው ኃይል 27 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ በማግኘት የዕቅዱን 97 በመቶ ማሳካት ተችሏል። ካለፉት ስድስት ዓመታት ወዲህ የተቋሙ ገቢ በአማካኝ በ34 በመቶ ዕድገት እያሳየ መሆኑን የተናገሩት ዋና ሥራ አስፈፃሚው የገቢ አሰባሰቡም በየዓመቱ እየተሻሻለ እንደሚገኝ ነው ያነሱት። በዚህም የ2016 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ ከ2015 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ17 በመቶ እድገት ያለው መሆን ዋና ሥራ አስፈፃሚው በማሳያነት አንስተዋል። በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ሥራዎችን ለማከናወን በማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆትና የፀጥታ ችግሮች ፈተና ሆነው እንደነበር ኢንጂነር አሸብር ተናግረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት ክፍት የሥራ መደቦች ሥራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂ
+1
የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት ክፍት የሥራ መደቦች ሥራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው ዋና መስሪያ ቤት እየመጣችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም