ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 540 подписчиков, занимая 8 340 место в категории Технологии и приложения и 2 161 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 540 подписчиков.

Согласно последним данным от 28 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 1, а за последние 24 часа — -4, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 24.98%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.34% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 882 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 539 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 29 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 540
Подписчики
-424 часа
-147 дней
+130 день
Архив постов
photo content
+9

photo content
+8

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የኬንያው ፕሬዝዳንት የኬትራኮ ኮንቨርተር ጣቢያን ጎበኙ ……….///……….. የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ በኬንያ ሱስዋ ናሮክ ግዛት የሚገኘውን የኬትራኮ ኮንቨርተር ጣቢያን ሽንን ጎበኙ፡፡ የኮንቨርተር ጣቢያው ከኢትዮጵያ ወላይታ ሶዶ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ተመሳሳይ የኮንቨርተር ጣቢያ ከፍተኛ ኃይል ተቀብሎ ወደ ኬንያ ግሪድ የሚያስገባ ነው፡፡ የኮንቨርተር ጣቢያው በአሁኑ ወቅት 200 ሜጋ ዋት ከኢትዮጵያ የሚቀበል ሲሆን ለድንበር አቋራጭ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሰረተ ልማት ነው፡፡ እስከ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ያለው ኮንቨርተር ጣቢያው ወደ ታንዛኒያ እስከ 400 ሜጋ ዋት ኃይል ለማስተላለፍ የሚያስችለውን ዝግጅት አጠናቋል፡፡ ኢትዮጵያ አስተማማኝና ታዳሽ ኃይል በማቅረብ ለአህጉራዊ የኃይል ትስስር መሳለጥ የበኩሏን በመወጣት ላይ ትገኛለች፡፡ በጉብኝቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፣ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሸብር ባልቻ እና ሌሎች የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ተገኝተዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

የፈተና ውጤት ማስታወቂያ

photo content
+9

photo content

የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቱ የጣቢያውን ሠራተኞችና የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ እያደረገ ነው .........///.......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተከፈተው የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት የጣቢያው ሠራተኞችንና የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ማድረጉ ተገለጸ። የትምህርት ቤቱ የወላጅ መምህራን ኮሚቴ አባል እና የጣቢያው ቴክኒሽያን አቶ ይስሀቅ ሀብቴ እንደገለጹት በጣቢያው ከኬጂ 1 እስከ ኬጂ 2 የሚያስተምር የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ተከፍቶ ላለፉት 3 ዓመታት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ከ3 ዓመት በፊት ከወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ጋር በመነጋገር ፍቃድ ወስደው መምህራንን በማስመደብ ሥራ መጀመራቸውን ያወሱት አቶ ይስሀቅ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በመከፈቱ የጣቢያው ሠራተኞችና የአካባቢው ማኅበረሰብ ልጆቻቸውን ያለምንም ችግር እንዲያስተምሩ በማድረግ ምቹ የሥራ ከባቢን መፍጠሩን ጠቁመዋል። የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቱ ያለበትን የግብዓት እና የሠው ኃይል ችግር በመቅረፍ የመቀበል አቅሙን ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። የትምህርት ቤቱ መምህርት ጽዮን ዓለም ዓለም እና የሥራ አጋሮቿ የትምህርት ቤቱ መከፈት ለጣቢያው ሠራተኞችና ለአካባቢው ማኅበረሰብ ልጆች የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ተደራሽ በማድረግ በኩል ከፍተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ሠሙ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቱ መከፈት የጣቢያው ሠራተኞች ልጆቻቸውን በቅርበት እንዲያስተምሩ በማድረግ የሠራተኛ ፍልሰትን በመቀነስ በኩል የጎላ ሚና መጫወቱን አረጋግጠዋል። የአካባቢው ማኅበረሰብም ልጆቹን በጣቢያው በተከፈተው የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በማስተማር ከጣቢያው ጋር ያለውን መስተጋብር እየጎለበተ መምጣቱን ጠቁመዋል። በጣቢያው አቅም የሚፈቱትን ከወላጆች ጋር በመሆን፥ ከጣቢያው አቅም በላይ የሆኑትን ደግሞ ከዋና መ/ቤት ፋሲሊቲ መምሪያ ጋር በመነጋገር ለመፍታት ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። በጣቢያው የተከፈተው ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት አሁን ላይ ከ95 በላይ ልጆችን ተቀብሎ በማስተማር ላይ ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም

የሴቶችን የማስፈጸም አቅም ለማጎልበት የሚያግዝ ሥልጠና ተሰጠ ………///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴት አመራሮችን የማስፈጸም አቅም ለማሳደግ እና የአመራር ክህሎታቸውን ከፍ ለማድረግ የበለጠ ትኩረት እንዲሰጥ የተቋሙ ሴት አመራሮች ጠየቁ፡፡ ለከፍተኛ አፈፃፀም ብቁ የመምራት ብቃት በሚል ርዕስ ለአንድ ሳምንት ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሲ ኢደኤ እንደተናገሩት ሥልጠናው የሴቶችን የማስፈጸም አቅም ለማጎልበት እና የአመራር ክህሎታቸውንና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ይረዳል፡፡ ሥልጠናው የሴት አመራሮች ባላቸው አቅም ላይ ክህሎትንና ተነሳሽነትን በመጨመር ለራሳቸውና ለተቋሙ የአሰራር ውጤታማነት ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረውም ተናግረዋል፡፡ በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ የፐብሊኬሽንና ሚዲያ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ገበየሁ በበኩላቸው ሥልጠናው የስራ ማስተባባርንና ቅልጥፍናን በበለጠ ክህሎት ለመፈፀም የሚያግዝና አሳታፊነትን የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌላዋ የስልጠና ተሳታፊ በኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የሰፖርትና ክሮስከቲንግ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ አስናቁ ፊቃዱ እንደተናገሩት ሥልጠናው ራሳቸውንና በስራ ክፍላቸው ያሉ ሌሎች ሰራተኞችን ለማብቃትና ይረዳል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴት አመራሮችን የመሪነት ክህሎትና ብቃት ለማሳደግ ላይ ለአንድ ሳምንት የተጋጀውን ስልጠና ያስተባበረው የተቋሙ የሥልጠናና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ነው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

በፕሮጀክቱ የሥራ ላይ ደኅንነት ከማስጠበቅ አኳያ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው ………///……… የሠራተኞችን የሥራ ላይ ደኅንነት ለማስጠበቅ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግንባታ የአካባቢና ደህንነት ባለሙያ ገለጹ። ባለሙያው አቶ ተስፋዬ ወርቅአበበ እንደገለፁት ማንኛውም አዲስ ሠራተኛ ወደ ፕሮጀክቱ ሥራ ከመግባቱ በፊት በሚሰራው ሥራ ላይ ሊገጥሙት ሥለሚችሉ የአደጋ ስጋቶች፣ አደጋዎች እንዴት መከላከል እንደሚችል፣ ከደኅንነት (safety) ዕቃዎች አጠቃቀም ጋር በተያያዘና ከሠራተኛው ምን እንደሚጠበቅ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ይሰጠዋል። ማንኛውም ሠራተኛ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ስለ ሥራ ላይ ደኅንነት በቂ ግንዛቤ መያዙን የማረጋገጥና በየሳምንቱ የደኅንነት ዕቃ መያዣ ሳጥኖችን (safety tools box) የማቅረብ ሥራ በኮንትራክተሩ እንደሚሰራም ገልጸዋል። በፕሮጀክቱ የሚሰሩ ሥራዎች ጥንቃቄ ካልታከለባቸው ለአደጋ የሚያጋልጡ መሆናቸውን ያወሱት አቶ ተስፋዬ እንደ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሠራተኞች በየሳምንቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እና የዘመቻ ንቅናቄ በማዘጋጀት ሠራተኛው ደኅንነቱ ተጠብቆ እንዲሰራ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም አካባቢው ለወባ የተጋለጠ ስለሆነ እያንዳንዱ ሠራተኛ ራሱን ከትንኛ ንክሻ ለመጠበቅና ለመከላከል ምን ማድረግ እንዳለበት ሠፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ገልጸዋል። በፕሮጀክቱ የሥራ ላይ አደጋ ቢከሰት ጉዳቱን ለመቀነስ በሳይቱ ሳምቱን ሙሉ 24 ስዓት የሚሰራ ጤና ጣቢያ መኖሩን ጠቁመዋል። የሥራ ላይ ደኅንነት መመሪያውን የማይተገብሩ ሠራተኞች ላይ በቀጥታ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው የተናገሩት ባለሙያው ከሌሎች ፕሮጀክቶች በተለየ በኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግንባታ ሂደት እስከ አሁን ምንም ዓይነት ከባድም ሆነ አደጋ አለመግጠሙን ገልጸዋል። በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ የግንባታ ሥራ ላይ ከ 30 ሀገራት የተውጣጡ 160 የሚሆኑ የውጭ ዜጎችና ከ 5 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን እየተሳተፉ ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በአቋም መለኪያ ጨዋታ አሸነፈ ..........///........ በሐዋሳ ከተማ ለሚካሄደው ሁለተኛ ዙር የከፍተኛ ሊግ ውድድር ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ የሚገኘው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ዛሬ ባከናወነው የአቋም መለኪያ ጨዋታ ድል ቀንቶታል። ጎፋ መብራት ሜዳ በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ቢሾፍቱ ከነማን 2 ለ ባዶ ማሸነፍ ችሏል። የኢትዮ- ኤሌክትሪክን ሁለት ጎሎች የአጥቂ መስመር ተጫዋቾቹ አብነት ተስፋዬ እና አቤል ሀብታሙ ከመረብ አሳርፈዋል። ተመጣጣኝ ፉክክር በታየበት ጨዋታ ኢትዮ- ኤሌክትሪክ ያገኛቸውን የጎል ዕድሎች በመጠቀም ረገድ ከተጋጣሚው ክለብ የተሻለ ነበር። ሁለተኛው ዙር የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ መርሀግብር የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ ይጀመራል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመጀመሪያውን ዙር በ31 ነጥብ አንደኛ ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

በተቋሙ ሥር-ነቀል ለዉጥ የሚያመጡ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶች እየተተገበሩ ናቸው ………///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሉ ዘርፎችን ሥራ ማዘመን የሚያስችሉት ፕሮጀክቶች ተቀርፀው እየተተገበሩ መሆኑን በተቋሙ የሞደርናይዜሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ገነቱ ደሳለኝ እንደገለጹት የተቋሙን የሥራ ሂደቶች በማዘመን ከማኑዋል አሠራር ወደ ወረቀት አልባ አሠራር በመቀየር የመረጃ ልዉዉጡና አገልግሎት አሰጣጡን ፈጣን፣ ወጪ ቆጣቢና ቀልጣፋ ለማድረግ እየተሰራ ነዉ፡፡ በተለያዩ ምዕራፎች ተከፍሎ እየተተገበረ ባለው አሰራሮችን የማዘመን ሂደት እስከአሁን በፋይናንስ፣ በሰው ኃይል አስተዳደር፣ በግዥ፣ በዕቃ ግምጃ ቤት፣ በማርኬቲንግ፣ በፕሮጀክት አስተዳደር እና ኢንቨስትመንት ተግባራዊ መደረጉን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ የተቋሙን የሰው ሀብት ሥራ አመራር ሥርዓት ወጥና በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ እንዲሁም የተቋሙን የግዥ ሥርዓት ለማዘመን ሰክሰስ ፋክተር እና አሪባ የተሰኙ ሞጁሎች ተዘጋጅተው ተተግብረዋል፡፡ በተጨማሪም ከሳይበር ሴኪዩሪቲ፣ ከውስጥ ኦዲትና ከሪስክ ማኔጅመንት ጋር ተያይዞ ያሉትን የሥራ ሂደቶች ወጥነት ባለው መልኩ እንዲከናወኑ ለማስቻል ጂ.አር.ሲ በሚል የተገዙ ሞጁሎች ግዢ መፈፀሙን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ገነቱ ገለጻ የትራንስፖርት ሥምሪቱን ለማሳለጥ የሚያስችል በጂ ፒ ኤስ የታገዘ የፍሊት ማኔጅመንት ሲስተም ለ600 ተሽከርካሪዎች ተገጥሟል፡፡ በተቋሙ እየተተገበሩ ያሉ አሰራሮችን የማዘመን ሥራዎች በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ቅልጥፍናን በመጨመር፣ የተቋሙን ወጪ ከብክነት በማዳን እና የመረጃ ሽፋንና ተደራሽነትን በመጨመር በኩል ከፍተኛ ሚና መጫወታቸውን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡ በመምሪያዉ እየተተገበሩ ያሉ አሰራርን የማዘመን ሥራዎች በጅምር ደረጃ ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ያወሱት አቶ ገነቱ ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቁ በተቋሙ አሰራር ላይ ሥር ነቀል ለዉጥ የሚያመጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ የወረቀት ሥራዎችን ዲጂታል ለማድረግ በተለያዩ ምዕራፎች የተከፋፈለ የሳፕ ሲስተም ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በተቋሙ የተጀመሩት የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች ለስትራቴጂክ ዕቅዱ ስኬት የጎላ ሚና አላቸው ..........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሰራሩን ለማቀላጠፍ እየተገበራቸው የሚገኙ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች የስትራቴጂክ ዕቅዱን ለማሳካት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው በተቋሙ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ገለፀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ብዙአየሁ አክሊሉ እንደገለጹት አሰራሮችን ዲጂታላይዝ ማድረግ ከተቋሙ የስትራቴጂክ ዕቅድ የትኩረት መስኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ በመሆኑም የተቋሙን አሰራሮች የሚያቀላጥፉ የተለያዩ ሲስተሞችን እና ቴክኖሎጂዎችን የማልማት፣ የመተግበርና የማስፋፋት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ በተቋሙ የወረቀት አልባ አሰራርን ተግባራዊ ለማድረግ የተለያዩ ዘመናዊ የአሰራር ስርዓቶች በመዘርጋት ላይ እንደሚገኙ ዳይሬክተሩ አንስተዋል። እንደ አቶ ብዙአየሁ ገለፃ በአሁኑ ወቅት የአይ ሲ ቲ ድጋፍ አሰጣጥ፣ የመረጃ ልውውጥንና የኃይል መቋረጥ ሥራዎችን የሚያቀላጥፉ፣ የሥልጠና ማኑዋሎችና ጥያቄዎች በኦንላይን የሚገኙበት እንዲሁም ፈተናዎች በኦንላይን የሚሰጡበት ስርዓት ተዘርግቷል። ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ለተለያዩ ጉዳዮች ኃይል ለማቋረጥ ሲባል በሥራ ክፍሎች የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ወረቀት አልባ በሆነ ሲስተም እየተከናወነ መሆኑንም አመልክተዋል። ሲስተሞቹ በአንዳንድ የሥራ ዘርፎች በሙከራ ደረጃ ተተግብረው ውጤታማ እንደሆኑና በቀጣይ በሁሉም የሥራ ክፍሎች ለመተግበር ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በየሰዓቱ የመነጨውን እና ወደማከፋፈያ የተጓጓዘውን የኃይል ንባብ ወረቀት አልባ በሆነ አሰራር እንዲመዘገብ የሚያደርግ ሲስተም ለማልማት እየተሰራ ነው፡፡ የተጀመሩት የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች ትክክለኛ መረጃዎችን ለመያዝና ለመረጃ ፈላጊዎች በወቅቱ ተደራሽ ለማድረግ፣ የተቋሙን ምርታማነት ለመጨመር፣ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት፣ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ለመታደግ እና የሠራተኛውን እንግልትና የሥራ ጫና ለማቃለል እንደሚያግዙ አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም ተቋማዊ የአሰራር ቅልጥፍናንና ውጤታማነትን በማሳደግ የተቋሙን ስትራቴጂክ ዕቅድ ለማሳካት ፋይዳቸው የጎላ ነው ፋይዳ እንዳላቸው ጠቅሰዋል፡፡ ሁሉም የተቋሙ ሠራተኛና የሥራ መሪ በየጊዜው የሚመጡ አዳዲስ አሰራሮችንና መመሪያዎችን በአግባቡ በመተግበር ተቋሙን ዲጂታላይዝ ለማድረግ በሚሰራው ሥራ ላይ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበበዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ ታሳቢ ያደረጉ የግሪድ ማዘመን ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ………///…….... በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና በብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ መጠቀም የሚያስችሉ የግሪድ ማዘመን ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የዲጂታላይዜሽንና አቅም ማሳደግ መምሪያ ተወካይ አቶ በኃይሉ ወ/ጊዮርጊስ እንዳስታወቁት በሁሉም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ለመረጃ ልውውጥ የሚያገለግሉ የኦፕቲካል ኮሙኒኬሽን ኔትዎርክ ዕቃዎች ተከላ እየተከናወነ ነው፡፡ ከማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መረጃዎችን በተመሳሳይ ሰዓት በማሰባሰብ ለኦፕሬሽን አገልግሎት ለማዋል የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም ችግሮች እንዳይከሰቱ የሚጠቁሙ ሶፍትዌሮች ይተገበራሉ ብለዋል። የሚተገበሩት የግሪድ ማዘመን ሥራዎች በማከፋፈያ ጣቢያዎች እና በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ያለውን የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት በማቀላጠፍ ለኦፕሬሽን ውሳኔዎች ግብዓት የሚሰጥና የማይዋዥቅ ኃይል ለማቅረብ እንደሚረዳ ተወካዩ ገልፀዋል፡፡ እንደ ተወካዩ ገለፃ የሚተገበሩት ቴክኖሎጂዎች በሰዎች እንዲሰሩ የሚጠበቁትን ውሳኔዎችን በራሳቸው የማስተካከያ እርምጃዎችን በመውሰድ ችግሮች በፍጥነት እንዳይከሰቱ ያደርጋሉ፡፡ ባለፉት 6 ወራት የሲስተም መቆጣጠሪያ ዕድሳት እና ለግሪድ ማዘመን የሚያገለግሉ ስርዓቶች ንድፍ ተዘጋጅቶ ለትግብራ የሚያገለግሉ ዕቃዎችና ሶፍትዌሮች በፍብረካ እና በመበልጸግ ላይ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡ የግሪድ ማዘመን ሥራውን ሲኖሀይድሮ ኮርፖሬሽን፣ኤክስ ዲ ግሩፕ እና ሲዋይጂ ሱንሪ የተባሉ የቻይና ኩባንያዎች እንዲሁም ጀነራል ኤሌክትሪክ ግሪድ ሶልሽን የተሰኘ የፈረንሳይ ድርጅት እያከናወኑት ሲሆን አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ሥራ ከ180 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ወጪ እንደሚጠይቅ አቶ በኃይሉ ጠቁመዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content