EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 540 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 340,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 161 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 540 名订阅者。
根据 28 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 1,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 24.98%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.34% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 882 次浏览,首日通常累积 2 539 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 29 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 540
订阅者
-424 小时
-147 天
+130 天
帖子存档
15 538
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የኬንያው ፕሬዝዳንት የኬትራኮ ኮንቨርተር ጣቢያን ጎበኙ
……….///………..
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ በኬንያ ሱስዋ ናሮክ ግዛት የሚገኘውን የኬትራኮ ኮንቨርተር ጣቢያን ሽንን ጎበኙ፡፡
የኮንቨርተር ጣቢያው ከኢትዮጵያ ወላይታ ሶዶ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ተመሳሳይ የኮንቨርተር ጣቢያ ከፍተኛ ኃይል ተቀብሎ ወደ ኬንያ ግሪድ የሚያስገባ ነው፡፡
የኮንቨርተር ጣቢያው በአሁኑ ወቅት 200 ሜጋ ዋት ከኢትዮጵያ የሚቀበል ሲሆን ለድንበር አቋራጭ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሰረተ ልማት ነው፡፡
እስከ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ያለው ኮንቨርተር ጣቢያው ወደ ታንዛኒያ እስከ 400 ሜጋ ዋት ኃይል ለማስተላለፍ የሚያስችለውን ዝግጅት አጠናቋል፡፡
ኢትዮጵያ አስተማማኝና ታዳሽ ኃይል በማቅረብ ለአህጉራዊ የኃይል ትስስር መሳለጥ የበኩሏን በመወጣት ላይ ትገኛለች፡፡
በጉብኝቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፣ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሸብር ባልቻ እና ሌሎች የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ተገኝተዋል፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 21 ቀን 2016 ዓ.ም
15 538
የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቱ የጣቢያውን ሠራተኞችና የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ እያደረገ ነው
.........///..........
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተከፈተው የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት የጣቢያው ሠራተኞችንና የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ማድረጉ ተገለጸ።
የትምህርት ቤቱ የወላጅ መምህራን ኮሚቴ አባል እና የጣቢያው ቴክኒሽያን አቶ ይስሀቅ ሀብቴ እንደገለጹት በጣቢያው ከኬጂ 1 እስከ ኬጂ 2 የሚያስተምር የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ተከፍቶ ላለፉት 3 ዓመታት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
ከ3 ዓመት በፊት ከወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ጋር በመነጋገር ፍቃድ ወስደው መምህራንን በማስመደብ ሥራ መጀመራቸውን ያወሱት አቶ ይስሀቅ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በመከፈቱ የጣቢያው ሠራተኞችና የአካባቢው ማኅበረሰብ ልጆቻቸውን ያለምንም ችግር እንዲያስተምሩ በማድረግ ምቹ የሥራ ከባቢን መፍጠሩን ጠቁመዋል።
የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቱ ያለበትን የግብዓት እና የሠው ኃይል ችግር በመቅረፍ የመቀበል አቅሙን ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
የትምህርት ቤቱ መምህርት ጽዮን ዓለም ዓለም እና የሥራ አጋሮቿ የትምህርት ቤቱ መከፈት ለጣቢያው ሠራተኞችና ለአካባቢው ማኅበረሰብ ልጆች የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ተደራሽ በማድረግ በኩል ከፍተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።
የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ሠሙ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቱ መከፈት የጣቢያው ሠራተኞች ልጆቻቸውን በቅርበት እንዲያስተምሩ በማድረግ የሠራተኛ ፍልሰትን በመቀነስ በኩል የጎላ ሚና መጫወቱን አረጋግጠዋል።
የአካባቢው ማኅበረሰብም ልጆቹን በጣቢያው በተከፈተው የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በማስተማር ከጣቢያው ጋር ያለውን መስተጋብር እየጎለበተ መምጣቱን ጠቁመዋል።
በጣቢያው አቅም የሚፈቱትን ከወላጆች ጋር በመሆን፥ ከጣቢያው አቅም በላይ የሆኑትን ደግሞ ከዋና መ/ቤት ፋሲሊቲ መምሪያ ጋር በመነጋገር ለመፍታት ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።
በጣቢያው የተከፈተው ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት አሁን ላይ ከ95 በላይ ልጆችን ተቀብሎ በማስተማር ላይ ይገኛል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም
15 538
የሴቶችን የማስፈጸም አቅም ለማጎልበት የሚያግዝ ሥልጠና ተሰጠ
………///……..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴት አመራሮችን የማስፈጸም አቅም ለማሳደግ እና የአመራር ክህሎታቸውን ከፍ ለማድረግ የበለጠ ትኩረት እንዲሰጥ የተቋሙ ሴት አመራሮች ጠየቁ፡፡
ለከፍተኛ አፈፃፀም ብቁ የመምራት ብቃት በሚል ርዕስ ለአንድ ሳምንት ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቋል፡፡
የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሲ ኢደኤ እንደተናገሩት ሥልጠናው የሴቶችን የማስፈጸም አቅም ለማጎልበት እና የአመራር ክህሎታቸውንና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ይረዳል፡፡
ሥልጠናው የሴት አመራሮች ባላቸው አቅም ላይ ክህሎትንና ተነሳሽነትን በመጨመር ለራሳቸውና ለተቋሙ የአሰራር ውጤታማነት ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረውም ተናግረዋል፡፡
በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ የፐብሊኬሽንና ሚዲያ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ገበየሁ በበኩላቸው ሥልጠናው የስራ ማስተባባርንና ቅልጥፍናን በበለጠ ክህሎት ለመፈፀም የሚያግዝና አሳታፊነትን የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ሌላዋ የስልጠና ተሳታፊ በኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የሰፖርትና ክሮስከቲንግ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ አስናቁ ፊቃዱ እንደተናገሩት ሥልጠናው ራሳቸውንና በስራ ክፍላቸው ያሉ ሌሎች ሰራተኞችን ለማብቃትና ይረዳል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴት አመራሮችን የመሪነት ክህሎትና ብቃት ለማሳደግ ላይ ለአንድ ሳምንት የተጋጀውን ስልጠና ያስተባበረው የተቋሙ የሥልጠናና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ነው፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም
15 538
በፕሮጀክቱ የሥራ ላይ ደኅንነት ከማስጠበቅ አኳያ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው
………///………
የሠራተኞችን የሥራ ላይ ደኅንነት ለማስጠበቅ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግንባታ የአካባቢና ደህንነት ባለሙያ ገለጹ።
ባለሙያው አቶ ተስፋዬ ወርቅአበበ እንደገለፁት ማንኛውም አዲስ ሠራተኛ ወደ ፕሮጀክቱ ሥራ ከመግባቱ በፊት በሚሰራው ሥራ ላይ ሊገጥሙት ሥለሚችሉ የአደጋ ስጋቶች፣ አደጋዎች እንዴት መከላከል እንደሚችል፣ ከደኅንነት (safety) ዕቃዎች አጠቃቀም ጋር በተያያዘና ከሠራተኛው ምን እንደሚጠበቅ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ይሰጠዋል።
ማንኛውም ሠራተኛ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ስለ ሥራ ላይ ደኅንነት በቂ ግንዛቤ መያዙን የማረጋገጥና በየሳምንቱ የደኅንነት ዕቃ መያዣ ሳጥኖችን (safety tools box) የማቅረብ ሥራ በኮንትራክተሩ እንደሚሰራም ገልጸዋል።
በፕሮጀክቱ የሚሰሩ ሥራዎች ጥንቃቄ ካልታከለባቸው ለአደጋ የሚያጋልጡ መሆናቸውን ያወሱት አቶ ተስፋዬ እንደ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሠራተኞች በየሳምንቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እና የዘመቻ ንቅናቄ በማዘጋጀት ሠራተኛው ደኅንነቱ ተጠብቆ እንዲሰራ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም አካባቢው ለወባ የተጋለጠ ስለሆነ እያንዳንዱ ሠራተኛ ራሱን ከትንኛ ንክሻ ለመጠበቅና ለመከላከል ምን ማድረግ እንዳለበት ሠፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ገልጸዋል።
በፕሮጀክቱ የሥራ ላይ አደጋ ቢከሰት ጉዳቱን ለመቀነስ በሳይቱ ሳምቱን ሙሉ 24 ስዓት የሚሰራ ጤና ጣቢያ መኖሩን ጠቁመዋል።
የሥራ ላይ ደኅንነት መመሪያውን የማይተገብሩ ሠራተኞች ላይ በቀጥታ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው የተናገሩት ባለሙያው ከሌሎች ፕሮጀክቶች በተለየ በኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግንባታ ሂደት እስከ አሁን ምንም ዓይነት ከባድም ሆነ አደጋ አለመግጠሙን ገልጸዋል።
በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ የግንባታ ሥራ ላይ ከ 30 ሀገራት የተውጣጡ 160 የሚሆኑ የውጭ ዜጎችና ከ 5 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን እየተሳተፉ ይገኛል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም
15 538
ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በአቋም መለኪያ ጨዋታ አሸነፈ
..........///........
በሐዋሳ ከተማ ለሚካሄደው ሁለተኛ ዙር የከፍተኛ ሊግ ውድድር ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ የሚገኘው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ዛሬ ባከናወነው የአቋም መለኪያ ጨዋታ ድል ቀንቶታል።
ጎፋ መብራት ሜዳ በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ቢሾፍቱ ከነማን 2 ለ ባዶ ማሸነፍ ችሏል።
የኢትዮ- ኤሌክትሪክን ሁለት ጎሎች የአጥቂ መስመር ተጫዋቾቹ አብነት ተስፋዬ እና አቤል ሀብታሙ ከመረብ አሳርፈዋል።
ተመጣጣኝ ፉክክር በታየበት ጨዋታ ኢትዮ- ኤሌክትሪክ ያገኛቸውን የጎል ዕድሎች በመጠቀም ረገድ ከተጋጣሚው ክለብ የተሻለ ነበር።
ሁለተኛው ዙር የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ መርሀግብር የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ ይጀመራል።
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመጀመሪያውን ዙር በ31 ነጥብ አንደኛ ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 16 ቀን 2016 ዓ.ም
15 538
በተቋሙ ሥር-ነቀል ለዉጥ የሚያመጡ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶች እየተተገበሩ ናቸው
………///…….
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሉ ዘርፎችን ሥራ ማዘመን የሚያስችሉት ፕሮጀክቶች ተቀርፀው እየተተገበሩ መሆኑን በተቋሙ የሞደርናይዜሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ገነቱ ደሳለኝ እንደገለጹት የተቋሙን የሥራ ሂደቶች በማዘመን ከማኑዋል አሠራር ወደ ወረቀት አልባ አሠራር በመቀየር የመረጃ ልዉዉጡና አገልግሎት አሰጣጡን ፈጣን፣ ወጪ ቆጣቢና ቀልጣፋ ለማድረግ እየተሰራ ነዉ፡፡
በተለያዩ ምዕራፎች ተከፍሎ እየተተገበረ ባለው አሰራሮችን የማዘመን ሂደት እስከአሁን በፋይናንስ፣ በሰው ኃይል አስተዳደር፣ በግዥ፣ በዕቃ ግምጃ ቤት፣ በማርኬቲንግ፣ በፕሮጀክት አስተዳደር እና ኢንቨስትመንት ተግባራዊ መደረጉን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡
የተቋሙን የሰው ሀብት ሥራ አመራር ሥርዓት ወጥና በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ እንዲሁም የተቋሙን የግዥ ሥርዓት ለማዘመን ሰክሰስ ፋክተር እና አሪባ የተሰኙ ሞጁሎች ተዘጋጅተው ተተግብረዋል፡፡
በተጨማሪም ከሳይበር ሴኪዩሪቲ፣ ከውስጥ ኦዲትና ከሪስክ ማኔጅመንት ጋር ተያይዞ ያሉትን የሥራ ሂደቶች ወጥነት ባለው መልኩ እንዲከናወኑ ለማስቻል ጂ.አር.ሲ በሚል የተገዙ ሞጁሎች ግዢ መፈፀሙን ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ ገነቱ ገለጻ የትራንስፖርት ሥምሪቱን ለማሳለጥ የሚያስችል በጂ ፒ ኤስ የታገዘ የፍሊት ማኔጅመንት ሲስተም ለ600 ተሽከርካሪዎች ተገጥሟል፡፡
በተቋሙ እየተተገበሩ ያሉ አሰራሮችን የማዘመን ሥራዎች በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ቅልጥፍናን በመጨመር፣ የተቋሙን ወጪ ከብክነት በማዳን እና የመረጃ ሽፋንና ተደራሽነትን በመጨመር በኩል ከፍተኛ ሚና መጫወታቸውን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡
በመምሪያዉ እየተተገበሩ ያሉ አሰራርን የማዘመን ሥራዎች በጅምር ደረጃ ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ያወሱት አቶ ገነቱ ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቁ በተቋሙ አሰራር ላይ ሥር ነቀል ለዉጥ የሚያመጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ተቋሙ የወረቀት ሥራዎችን ዲጂታል ለማድረግ በተለያዩ ምዕራፎች የተከፋፈለ የሳፕ ሲስተም ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም
15 538
በተቋሙ የተጀመሩት የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች ለስትራቴጂክ ዕቅዱ ስኬት የጎላ ሚና አላቸው
..........///.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሰራሩን ለማቀላጠፍ እየተገበራቸው የሚገኙ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች የስትራቴጂክ ዕቅዱን ለማሳካት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው በተቋሙ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ገለፀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ብዙአየሁ አክሊሉ እንደገለጹት አሰራሮችን ዲጂታላይዝ ማድረግ ከተቋሙ የስትራቴጂክ ዕቅድ የትኩረት መስኮች መካከል አንዱ ነው፡፡
በመሆኑም የተቋሙን አሰራሮች የሚያቀላጥፉ የተለያዩ ሲስተሞችን እና ቴክኖሎጂዎችን የማልማት፣ የመተግበርና የማስፋፋት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡
በተቋሙ የወረቀት አልባ አሰራርን ተግባራዊ ለማድረግ የተለያዩ ዘመናዊ የአሰራር ስርዓቶች በመዘርጋት ላይ እንደሚገኙ ዳይሬክተሩ አንስተዋል።
እንደ አቶ ብዙአየሁ ገለፃ በአሁኑ ወቅት የአይ ሲ ቲ ድጋፍ አሰጣጥ፣ የመረጃ ልውውጥንና የኃይል መቋረጥ ሥራዎችን የሚያቀላጥፉ፣ የሥልጠና ማኑዋሎችና ጥያቄዎች በኦንላይን የሚገኙበት እንዲሁም ፈተናዎች በኦንላይን የሚሰጡበት ስርዓት ተዘርግቷል።
ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ለተለያዩ ጉዳዮች ኃይል ለማቋረጥ ሲባል በሥራ ክፍሎች የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ወረቀት አልባ በሆነ ሲስተም እየተከናወነ መሆኑንም አመልክተዋል።
ሲስተሞቹ በአንዳንድ የሥራ ዘርፎች በሙከራ ደረጃ ተተግብረው ውጤታማ እንደሆኑና በቀጣይ በሁሉም የሥራ ክፍሎች ለመተግበር ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡
ዳይሬክተሩ እንዳሉት በየሰዓቱ የመነጨውን እና ወደማከፋፈያ የተጓጓዘውን የኃይል ንባብ ወረቀት አልባ በሆነ አሰራር እንዲመዘገብ የሚያደርግ ሲስተም ለማልማት እየተሰራ ነው፡፡
የተጀመሩት የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች ትክክለኛ መረጃዎችን ለመያዝና ለመረጃ ፈላጊዎች በወቅቱ ተደራሽ ለማድረግ፣ የተቋሙን ምርታማነት ለመጨመር፣ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት፣ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ለመታደግ እና የሠራተኛውን እንግልትና የሥራ ጫና ለማቃለል እንደሚያግዙ አስረድተዋል፡፡
በተጨማሪም ተቋማዊ የአሰራር ቅልጥፍናንና ውጤታማነትን በማሳደግ የተቋሙን ስትራቴጂክ ዕቅድ ለማሳካት ፋይዳቸው የጎላ ነው ፋይዳ እንዳላቸው ጠቅሰዋል፡፡
ሁሉም የተቋሙ ሠራተኛና የሥራ መሪ በየጊዜው የሚመጡ አዳዲስ አሰራሮችንና መመሪያዎችን በአግባቡ በመተግበር ተቋሙን ዲጂታላይዝ ለማድረግ በሚሰራው ሥራ ላይ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበበዋል፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም
15 538
ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ ታሳቢ ያደረጉ የግሪድ ማዘመን ሥራዎች እየተከናወኑ ነው
………///……....
በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና በብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ መጠቀም የሚያስችሉ የግሪድ ማዘመን ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡
በዘርፉ የዲጂታላይዜሽንና አቅም ማሳደግ መምሪያ ተወካይ አቶ በኃይሉ ወ/ጊዮርጊስ እንዳስታወቁት በሁሉም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ለመረጃ ልውውጥ የሚያገለግሉ የኦፕቲካል ኮሙኒኬሽን ኔትዎርክ ዕቃዎች ተከላ እየተከናወነ ነው፡፡
ከማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መረጃዎችን በተመሳሳይ ሰዓት በማሰባሰብ ለኦፕሬሽን አገልግሎት ለማዋል የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም ችግሮች እንዳይከሰቱ የሚጠቁሙ ሶፍትዌሮች ይተገበራሉ ብለዋል።
የሚተገበሩት የግሪድ ማዘመን ሥራዎች በማከፋፈያ ጣቢያዎች እና በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ያለውን የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት በማቀላጠፍ ለኦፕሬሽን ውሳኔዎች ግብዓት የሚሰጥና የማይዋዥቅ ኃይል ለማቅረብ እንደሚረዳ ተወካዩ ገልፀዋል፡፡
እንደ ተወካዩ ገለፃ የሚተገበሩት ቴክኖሎጂዎች በሰዎች እንዲሰሩ የሚጠበቁትን ውሳኔዎችን በራሳቸው የማስተካከያ እርምጃዎችን በመውሰድ ችግሮች በፍጥነት እንዳይከሰቱ ያደርጋሉ፡፡
ባለፉት 6 ወራት የሲስተም መቆጣጠሪያ ዕድሳት እና ለግሪድ ማዘመን የሚያገለግሉ ስርዓቶች ንድፍ ተዘጋጅቶ ለትግብራ የሚያገለግሉ ዕቃዎችና ሶፍትዌሮች በፍብረካ እና በመበልጸግ ላይ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡
የግሪድ ማዘመን ሥራውን ሲኖሀይድሮ ኮርፖሬሽን፣ኤክስ ዲ ግሩፕ እና ሲዋይጂ ሱንሪ የተባሉ የቻይና ኩባንያዎች እንዲሁም ጀነራል ኤሌክትሪክ ግሪድ ሶልሽን የተሰኘ የፈረንሳይ ድርጅት እያከናወኑት ሲሆን አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ሥራ ከ180 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ወጪ እንደሚጠይቅ አቶ በኃይሉ ጠቁመዋል፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 14 ቀን 2016 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
